en
Feedback
RN.05 - Channel

RN.05 - Channel

Open in Telegram

ከኢትዮጵያና አዉሮፓ የሚተላለፍ የራድዮ ፕሮግራም አዲሱን ዩቱብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ: https://www.youtube.com/c/RN05Channel ፌስቡክ ገፃችንን like ያድርጉ: https://www.facebook.com/RNZeroFive/ https://twitter.com/RNZeroFive Support Us: http://bit.ly/3c09jfJ https://RNZeroFive.com

Show more
2 342
Subscribers
+524 hours
+67 days
-730 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
June '26
June '26
+32
in 0 channels
May '26
+37
in 0 channels
Get PRO
April '26
+45
in 0 channels
Get PRO
March '26
+74
in 0 channels
Get PRO
February '26
+28
in 0 channels
Get PRO
January '26
+28
in 0 channels
Get PRO
December '25
+37
in 0 channels
Get PRO
November '25
+78
in 1 channels
Get PRO
October '25
+76
in 0 channels
Get PRO
September '25
+49
in 0 channels
Get PRO
August '25
+39
in 0 channels
Get PRO
July '25
+105
in 0 channels
Get PRO
June '25
+133
in 0 channels
Get PRO
May '25
+62
in 0 channels
Get PRO
April '25
+103
in 0 channels
Get PRO
March '25
+68
in 0 channels
Get PRO
February '25
+56
in 0 channels
Get PRO
January '25
+93
in 1 channels
Get PRO
December '24
+45
in 1 channels
Get PRO
November '24
+61
in 0 channels
Get PRO
October '24
+175
in 0 channels
Get PRO
September '24
+24
in 0 channels
Get PRO
August '24
+32
in 1 channels
Get PRO
July '24
+12
in 0 channels
Get PRO
June '24
+47
in 0 channels
Get PRO
May '24
+111
in 1 channels
Get PRO
April '24
+66
in 1 channels
Get PRO
March '24
+53
in 0 channels
Get PRO
February '24
+148
in 0 channels
Get PRO
January '24
+126
in 0 channels
Get PRO
December '23
+146
in 0 channels
Get PRO
November '23
+427
in 1 channels
Get PRO
October '23
+29
in 0 channels
Get PRO
September '23
+12
in 0 channels
Get PRO
August '23
+29
in 0 channels
Get PRO
July '23
+11
in 0 channels
Get PRO
June '23
+13
in 0 channels
Get PRO
May '23
+4
in 0 channels
Get PRO
April '23
+13
in 0 channels
Get PRO
March '23
+40
in 0 channels
Get PRO
February '23
+5
in 0 channels
Get PRO
January '23
+2
in 0 channels
Get PRO
December '22
+36
in 0 channels
Get PRO
November '22
+4
in 0 channels
Get PRO
October '22
+29
in 0 channels
Get PRO
September '22
+12
in 0 channels
Get PRO
August '22
+120
in 0 channels
Get PRO
July '22
+159
in 0 channels
Get PRO
June '22
+9
in 0 channels
Get PRO
May '22
+89
in 0 channels
Get PRO
April '22
+9
in 0 channels
Get PRO
March '22
+3
in 0 channels
Get PRO
February '22
+3
in 0 channels
Get PRO
January '22
+5
in 0 channels
Get PRO
December '21
+94
in 0 channels
Get PRO
November '21
+25
in 0 channels
Get PRO
October '21
+7
in 0 channels
Get PRO
September '21
+3
in 0 channels
Get PRO
August '21
+8
in 0 channels
Get PRO
July '21
+39
in 0 channels
Get PRO
June '21
+24
in 0 channels
Get PRO
May '21
+1 067
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
26 June0
25 June+5
24 June+1
23 June0
22 June+1
21 June+3
20 June+1
19 June+1
18 June0
17 June+1
16 June0
15 June+1
14 June+1
13 June+2
12 June+4
11 June+2
10 June+2
09 June0
08 June+1
07 June+1
06 June+1
05 June+1
04 June+2
03 June0
02 June0
01 June+1
Channel Posts
የሆርሙዝ ጦርነት፣ በእሬት የተለወሰ ማር ~~~~~~ #የቢላል_ትዝብት . ኢራንና አሜሪካ የመጀመሪያውን ዙር ድርድር ጄኔቭ ላይ አጠናቀው ተበትነዋል። ድርድሩ በትራምፕ የተለመደ ያልተገራ ንግግር ሳብያ ችግር ውስጥ ወድቆ የነበረ ቢሆንም እንደምንም እንደገና አንሰራርቶ መቀጠል ችሎ ነበር። ተደራዳሪዎቹ፣ በተለይም አሜሪካውያኑ ተደራዳሪዎች ድርድሩ ስኬታማ ነበር ሲሉ ተደምጠዋል።ሌባኖስ ላይ ተኩስ ማቆም የስምምነቱ አንድ አካል እንድያውም ግንባር ቀደም ቅድመሁኔታ እንደሆነ ያስታወቀችው ኢራን በእስራኤል አማካኝነት ሌባኖስ ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት ካልቆመ ድርድሩን እንደማትጀምር አስረግጣ በመናገሯ እስራኤል ለጊዜውም ከተኩስ ለመታቀብ ተገድዳለች። ከኢራንና ከአሜሪካ እርምጃዎች የምናነባቸው በርካታ ቀምነገሮች ያሉ ይመስለኛል። ኢራን እርግጥ ነው ከፍተኛ ድብደባ ደርሶባታል፣ በዋጋ የማይተመን የሰው ሃይልና ከፍተኛ የሆነ የንብረት መውደምን አስተናግዳለች። ያም ሆኖ ግን ይህንን ሁሉ መከራ በጽናት መቋቋም በመቻሏ የኋላ ኋላ አትራፊ ሆና ወጥታለች። በዚህ ጦርነት ኢራን በአንድ በኩል ጥንካሬዋን ያስመሰከረች ስትሆን በሌላ በኩል ደግሞ የሃያሏን አሜሪካ አቅም ውሱንነት አጋልጣለች።አሜሪካ ከእነ አላት ግዙፍ የሚሊቴሪ አቅም ኢራን የዘጋችውን የባህር በር በሃይል ማስከፈት ሳትችል ቀርታለች። በሌላ በኩል ኢራን የሆርሙዝን ባህረሠላጤ በመዝጋት ብቻ የአለምን ኤኮኖሚ ማሽመድመድ እንደምትችል አስመስክራለች። . የሆርሙዝ ቀውስ ያስተማረን ሌላ ትልቅ ቁምነገር ቢኖር በዘመናዊው ዓለም የኃይል ሚዛን መለኪያው የጦር መሣሪያ ግዝፈት ብቻ አለመሆኑን ነው። ኢራን ስልታዊ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጧንና ጂኦ-ፖለቲካዊ ተፅዕኖዋን በመጠቀም የዓለምን ኃያላን አቅጣጫ ማስቀየር ችላለች። የጄኔቩ ስምምነት የጦርነቱን ማብቂያ ያበሰረ ቢመስልም፣ የቀጠናው እውነተኛ የኃይል ሚዛን ግን ወደ አዲስ ምዕራፍ መሸጋገሩንና የአሜሪካ የብቸኝነት የበላይነት ማክተሙን ያሳየ ታሪካዊ ክስተት ሆኖ ይመዘገባል። ቀደም ባሉት ጊዜያት በመካከለኛው ምስራቅ ቀጠና ውስጥ ፍላጎቷን በጉልበት የምታስፈጽመው፣ የፈለገችውን የምትቀጣውና የምትሾመው ብቸኛዋ ኃያል ሀገር አሜሪካ ነበረች። ነገር ግን በዚህ የሆርሙዝ ቀውስ፣ ኢራን የአሜሪካን ወታደራዊ ጫና ተቋቁማ የራሷን የድርድር ቅድመ-ሁኔታ ማስከበር ችላለች። ይህም ማለት ቀጠናው በአንድ ወገን ፍላጎት ብቻ የሚነዳ መሆኑ ቀርቶ፣ ኢራንም የራሷን አጀንዳ በኃይል የምታስወሥን እኩል ተወዳዳሪ ሆና ብቅ ማለቷን ያሳያል። . ይህ የጄኔቩ ስምምነትና ኢራን በሆርሙዝ ባህረ-ሰላጤ ላይ ያሳየችው የኃይል የበላይነት፣ በቀጣይ በመካከለኛው ምስራቅ ለሚኖራት ክልላዊ ሚና እና ከአካባቢው ሀገራት ጋር ለሚኖራት ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው። ኢራን በድርድሩ ወቅት እስራኤል ሌባኖስ ላይ የምታደርገውን ጥቃት እንድታቆም እንደ ቅድመ-ሁኔታ ማስቀመጧና ይህንኑ ማስፈጸሟ፣ በአካባቢው ላይ ያላትን የተፅዕኖ አቅም በእጅጉ ያሳድገዋል። ይህ እርምጃ በሌባኖስ (ሒዝቦላህ)፣ በየመን (ሁቲዎች) እና በሶሪያ ያሉ አጋሮቿ በኢራን ላይ ያላቸውን እምነት ያጠናክረዋል። ኢራን ለራሷ ጥቅም ብቻ ሳይሆን ለአጋሮቿም መከታ መሆን የምትችል ቀጠናዊ ኃይል መሆኗን ስላስመሰከረች፣ በአረቡ ዓለም ውስጥ ያላት የፖለቲካ እና የወታደራዊ ተሰሚነት ከበፊቱ በበለጠ ይገዝፋል። . እንደ ሳውዲ አረቢያ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ያሉ የባህረ-ሰላጤው ሀገራት ይህንን ስምምነት በሁለት መንገድ ያዩታል። በአንድ ወገን ኢራን የሆርሙዝን ባህረ-ሰላጤ በመዝጋት የዓለምን ኢኮኖሚ ማሽመድመድ እንደምትችል በተግባር ማሳየቷ እነዚህን ሀገራት ያስደነግጣል። ምክንያቱም የእነሱም የነዳጅ የሚመላለሰው በዚህ የባህር መስመር ላይ በመሆኑ፣ ከኢራን ጋር በቀጥታ መጋጨት ከፍተኛ ዋጋ እንደሚያስከፍላቸው ይረዳሉ።በሌላ ወገን አሜሪካ ኢራንን በሃይል ማንበርከክ አለመቻሏን ሲረዱ፣ የገልፍ ሀገራት ደህንነታቸውን ለመጠበቅ ሲሉ ከአሜሪካ ጥገኝነት ወጥተው ከኢራን ጋር ቀጥተኛ የሰላም እና የዲፕሎማሲ ግንኙነትን ለማጠናከር ይገደዳሉ። መጋጨትን አስወግደው የጋራ ጥቅምን ወደ ማስከበር ያመራሉ። . እስራኤልን በተመለከት እስራኤል አሜሪካ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ እንድትወስድ ወይም ማዕቀቡን እንድታጠብቅ ትፈልግ ነበር። ነገር ግን አሜሪካ ወደ ስምምነት መምጣቷና እስራኤልም ለጊዜው ከተኩስ እንድትታቀብ መገደዷ ለእስራኤል ዲፕሎማሲያዊ ሽንፈት ነው። ይህ ስምምነት ኢራን በቀጠናው ያላትን ይፋዊ ተቀባይነት ስለሚጨምር፣ እስራኤል ኢራንን ብቻዋን ለመጋፈጥ የምታደርገውን ጥረት ከባድ ያደርገዋል። . የሆርሙዝ ባህረ-ሰላጤ የዓለም ነዳጅ የሚያልፍበት ዋና ማነቆ (Chokepoint) ነው። ኢራን በዚህ መስመር ላይ ያላትን ወታደራዊ የበላይነት ማረጋገጧ፣ በቀጣይ ማናቸውም ቀጠናዊ የንግድና የደህንነት ስምምነቶች ያለ ኢራን ፍቃድና ተሳትፎ ሊሳኩ እንደማይችሉ ያሳያል። ይህም ኢራን ከአካባቢው ሀገራት ጋር በሚኖራት የንግድ ልውውጥ ላይ የላይነት እንድትይዝ ያደርጋታል። ባጠቃላይ፤ ይህ ስምምነት ኢራንን በቀጠናው ላይ "ማንም ሊዘነጋት የማይችል ዋና ተዋናይ" ያደርጋታል። ከጎረቤቶቿ ጋር የሚኖራት ግንኙነት በፉክክር ላይ የተመሰረተ ቢሆንም፣ ጎረቤቶቿ ግንኙነታቸውን በሃይል ሳይሆን በዲፕሎማሲያዊ ጥንቃቄ እና መከባበር ላይ ለመመስረት የሚገደዱበትን ምህዳር ይፈጥራል። . የእናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ? የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን! ============= . ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ https://t.me/RNZeroFive

2
No text...
179
3
ይህ አካሄድ ስለ ዛሬው ጊዜያዊ ሰላም ወይም ጥቅም እንጂ፣ ስለ ነገው የረጅም ጊዜ የፖለቲካ ዋስትና ዝግጁ አለመሆኑን ያሳያል። የራሱን አማራጭ ኃይሎች (እንደ ነእፓ ያሉ) አዳክሞ ሙሉ በሙሉ በዜሮ ማሰናበት፣ ነገ ሌላ የፖለቲካ ማዕበል እና በደል ቢመጣ እንኳ መከላከያ ወይም ድምፅ የሚሆን ወኪል አልባ የመሆን ስልታዊ እውርነት ነው። ይህ የዛሬው ምርጫ ውጤት የኤሊቱን የፖለቲካ ብስለት እና አርቆ አሳቢነት ትልቅ ጥያቄ ምልክት ውስጥ የከተተ መስታወት ነው። . ትልቁ ቅድመ-ሁኔታ እና የነእፓ ዝምታ -------------- እርግጥ ነው፣ ይህ ማህበራዊ ሂስ ትርጉም የሚኖረው "የተካሄደው ምርጫ ነጻ፣ ፍትሃዊ እና የመራጩን እውነተኛ ፍላጎት ያንጸባረቀ ነበር" ብለን በቅንነት ካመንን ብቻ ነው። ነገር ግን ሂደቱ ሙሉ በሙሉ ከማጭበርበርና ከፖለቲካዊ ጫና የነጻ ነበር ብሎ ለመቀበል ይከብዳል። ውጤቱ የፖለቲካ ቁማር እና ስልታዊ ማግለል ውጤት ሊሆን የሚችልበት ዕድል ሰፊ ነው። . ነገር ግን ጉዳዩ የምርጫ ማጭበርበር ከሆነ ደግሞ፣ ሂሱ በቀጥታ የሚዞረው ወደ ራሱ ወደ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) አመራሮች ነው። ምርጫው ፍትሃዊ ካልነበረ እና ድምፅ ከተሰረቀ፣ ፓርቲው ለምን እስካሁን በይፋ ወጥቶ ሂደቱንና ውጤቱን አልሞገተም? ለህዝብ ግልጽ የሆነ መግለጫ በመስጠት የምርጫውን ተአማኒነት የመመርመር ስራ ለምን አልተሰራም? . ህዝቡ ድምፅ ሰጥቶአቸው ከሆነና ያ ድምፅ ከተሰረቀ፣ ያንን ተከላክሎ ማስከበር የፓርቲው ቀዳሚ ኃላፊነት ነበር። ፓርቲው ወጥቶ ስለ ምርጫው እውነተኛነት በግልጽ አለመናገሩ፣ ማህበረሰቡ በአመራሮቹ ላይ "የቁርጠኝነት ማጣት" ወይም "የፖለቲካ ስምምነት" ጥርጣሬ እንዲያድርበት ያደርጋል። ድምፅን ከማስከበር ይልቅ ዝምታን መምረጥ፣ የመረጣቸውን ህዝብ በፖለቲካ ተስፋ መቁረጥ ውስጥ መተው ነው። ሲጠቃለል:- -------- በመጨረሻም፣ የአዲስ አበባ እና የክልሎች ምርጫ ውጤት ለነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ትልቅ ማቆሚያ ነጥብ ነው። ምርጫው ፍትሃዊ ሆኖ ህዝቡና ኤሊቱ "በዜሮ" አሰናብቷቸው ከሆነ፣ ማህበረሰቡ ትናንት ከኢህአዴግ ያልተማረውን ዛሬ ከብልጽግና ጋር እየደገመው ያለ የታሪክ ስህተት ነው። . ያ ካልሆነ እና ምርጫው ተጭበረብሮ ከሆነ ግን፣ ነእፓ ወጥቶ እውነቱን የመናገር እና የመሞገት የሞራልም የፖለቲካም ግዴታ አለበት። ይህንን ሳያደርግ በዝምታ ማለፍ ግን ማህበረሰቡ ለነዚህ ታጋዮች የነበረውን የቆየ አመኔታና ክብር ዋጋ የሚያሳጣ፣ የታሪክ ምፀት ሆኖ ይቀጥላል። . እናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ? የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን! ============= . ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ https://t.me/RNZeroFive
346
4
የአዲስ አበባ ም/ቤት ድምፅ እና የነእፓ እጣ ፈንታ፡ ከታሪካዊ ውለታ እስከ ፖለቲካዊ 'ዜሮ' — ማህበራዊ ሂስ ~~~~ #RN05 . ሰሞኑን ይፋ የሆነው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የምርጫ ውጤት ለብዙዎች አስገራሚ፣ ለፖለቲካ ተንታኞች ደግሞ አዳዲስ ጥያቄዎችን ያረገዘ ሆኖ አልፏል። በዚህ ምርጫ ከተመዘገቡት ትልልቅ መደነቆች መካከል የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) በአዲስ አበባ መዲናችን አንድም መቀመጫ ማግኘት አለመቻሉ እና በዜሮ ማሰናበቱ ግንባር ቀደሙ ማህበራዊና ፖለቲካዊ እንቆቅልሽ ሆኗል። ይህ ውጤት እንዲሁ በተራ የምርጫ ሽንፈት የሚታለፍ ሳይሆን፣ የማህበረሰባችንን ስነ-ልቦና፣ የፓርቲውን ዝምታ እና የኤሊቱን የፖለቲካ ብስለት በጥልቀት እንድንመረምር የሚያስገድድ ማህበራዊ ሂስ (Social Critique) ነው። . ታሪካዊው ውል እና የህዝብ ውለታ --------- ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የዋዛ ስም አይደለም። በተለይም የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮችና መስራቾች፣ የዛሬ አስር አመት ገደማ በነበረው ታሪካዊው የ"ድምጻችን ይሰማ" የህዝብ ንቅናቄ ውስጥ የነበሩ፣ ስለ ማህበረሰቡ መብትና እኩልነት ድምፃቸውን ከፍ አድርገው መጮህያ ብሎም በመሞገቻ አንደበቶች የነበሩ እንዲሁም የሆኑ ናቸው። እነዚህ ግለሰቦች በሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘንድ እንደ መብት ታጋይ እና ባለውለታ የሚታዩ፣ ጥልቅ ማህበራዊ ቅቡልነት (Social Capital) የነበራቸው ናቸው። ከዝያም አልፎ ሁሉንም አካታች ቢሆኑም ለመጀመርያ ጊዜ በሙስሊሞች የተመሰረተ የፖለቲካ ፓርቲ በመሆኑ ብቻ "ሙስሊም አይታመንም!" በሚል የቆየ ብሂል መሰረት ብዙ ሲተቹና ሲብጠለጠሉ እንደነበር ሁሉም በገሃድ የሚያውቀው ነው፡፡ . ፓርቲው ወደ ፖለቲካው ሲገባም ይዞት የተነሳው የፍትህ፣ የእኩልነት እና የነጻነት መርህ ከዚሁ ታሪካዊ መነሻ ጋር የተቆራኘ ነበር። በመሆኑም በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ ውስጥ ባለው ሰፊ የሙስሊም ማህበረሰብ ዘንድ ፓርቲው ቢያንስ ጠንካራ ተፎካካሪ ሆኖ እንደሚወጣ መገመቱ ተፈጥሯዊ ነበር። . የቁጥር እና የውጤት ተቃርኖ፡ ከአዲስ አበባ እስከ ክልሎች ------------- ለመሆኑ በአዲስ አበባ ውስጥ ያለው የሙስሊም ማህበረሰብ ቁጥር እና ስርጭት ምን ያህል ነው? መልሱ ግልጽ ነው፤ በጣም ሰፊና በከተማዋ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መስተጋብር ውስጥ አንቀሳቃሽ ኃይል የሆነ ማህበረሰብ ነው። ታዲያ ይህ ሁሉ ህዝብ ባለበት መዲና፣ የራሱን መብት ለማስከበር የተጋደሉለትን መሪዎች እንዴት "በዜሮ" አሰናበታቸው? . ይህንን እንቆቅልሽ ይበልጥ አጉልቶ የሚያሳየው የሌሎች ፓርቲዎች ውጤት ነው። ለምሳሌ የወላይታ ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄን የመሰሉ፣ መነሻቸውና ዋነኛ አጀንዳቸው ከተወሰኑ የሀገሪቱ ክልሎች ጋር የተያያዘ የፖለቲካ ድርጅቶች እንኳ ሳይቀሩ፣ በአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ውስጥ ቢያንስ አንድ ወይም ከዚያ በላይ መቀመጫዎችን አሸንፈው ብቅ ማለት ችለዋል። በክልል ደረጃ የሚንቀሳቀስ ንቅናቄ በአዲስ አበባ አሸንፎ መቀመጫ ሲያገኝ፣ መላውን አገር አቀፍ አጀንዳ ይዞ የተነሳው ነእፓ ግን የከተማዋን መራጭ ልብ ሳይገዛ መቅረቱ የሚገርም ብቻ ሳይሆን የሚሞግትም ነው። , አዲስ አበባ ያሉ የወላይታ ተወላጆች ምን ያህል በፖለቲካው የነቁ ቢሆኑ ነው ያዉም አዲስ አበባ ምክር ቤት ዉስጥ ያዉም "የነጻነት ንቅናቄ" ፓርቲያቸዉን የወላይታ በመሆኑ ሊመርጡና 1 መቀመጫ እንዲያገኝ ያደረጉት የሚለው ለፖለቲካ ብዛት ብቻ ሳይሆን ንቃት ወሳኝ ስለመሆኑ ማሳያ ነው፡፡ ብዙ ወላይታዎች እኮ ብልጽግናን መርጠው ሊሆን ይችላል፣ እንቁላላቸዉን ሁሉ ግን በአንድ ቅርጫት ዉስጥ ጨርሰው አልዶሉም፡፡ "ምን የነቃና ያነቃ ኤሊት ቢኖራቸው ነው?" የሚያሰኘዉም ይሄ ነው፡፡ . የነእፓ መደነቅ በአዲስ አበባ ብቻ አይበቃም። ጉዳዩን ይበልጥ አሳሳቢና ገራሚ የሚያደርገው የፓርቲው አገራዊ የምርጫ ውድቀት ነው። ነእፓ የሙስሊሙ ማህበረሰብ በብዛት በሚኖርባቸው እንደ ኦሮሚያ፣ አፋር፣ ቤኒሻንጉል እና ሐረር ባሉ ሰፋፊ ክልሎች ውስጥ—ወይ ጨርሶ እጩ አላቀረበም፣ ካልተባለ በቀር—ከድሬዳዋ በስተቀር በአንድም ክልል አንድም ወንበር ማሸነፍ አለመቻሉ ነው። . የታሪክ ድግግሞሽ፡ የ1997ቱ ትዝታ እና የዛሬው መስታወት ይህ የዛሬው የ"ዜሮ" ውጤት እና የማህበረሰቡ ምርጫ አዲስ የመጣ ክስተት አይደለም። ወደ ኋላ ሄደን የኢትዮጵያን የፖለቲካ ታሪክ ስንፈትሽ፣ የሙስሊሙ ኤሊት (Elite) ለተመሳሳይ ስልታዊ የፖለቲካ ስህተት እራሱን አጋልጦ ሲሰጥ የኖረ መሆኑን እንረዳለን። . ለዚህ ትልቅ ማሳያ የሚሆነው ታሪካዊው የ1997 ዓ.ም ምርጫ ወቅት የነበረው ትዝታ ነው። በወቅቱ በሬዲዮ ነጋሺ የዝግጅት ክፍል በኩል በምርጫው ዙሪያ በኢህአዴግ እና በቅንጅት መካከል የነበረውን ከፍተኛ ፉክክር አስመልክቶ፣ ከሁለቱም ወገን ያሉ ሙስሊም ምሁራንን እና ኤሊቶችን በማነጋገር ልዩ ፕሮግራም ለመስራት ታቅዶ ነበር። በኢህአዴግ በኩል ያሉትን ማግኘት ቀላል የነበረ ቢሆንም፣ በቅንጅት በኩል ያሉትን ለመፈለግ ወደ አንድ ታዋቂ የሀገር ውስጥ ኡስታዝ ስልክ ተደወለ። . የኡስታዙ ምላሽ ግን አስደንጋጭና የፖለቲካ ምህዳሩን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነበር፦ "በሉ አትልፉ! የኢህአዴግ ደጋፊ ካላችሁኝ መስጂዱም፣ ሜዳውም ሙሉ ነው፤ የምትፈልጉትን አይነት ሰዎች ላገናኛችሁ። በቅንጅት በኩል ግን ከእኔ በቀር ማንንም አታገኙም፤ እኔ ደግሞ ሚዲያ ላይ ቃሌን አልሰጥም፤ ስለዚህ አትልፉ" ነበር ያለው። ያም ሆኖ ተስፋ ሳይቆረጥ በተለያዩ መንገዶች ጥረት ቢደረግም፣ ከተራ ምእመናን በስተቀር በኤሊት ደረጃ ተቃውሞን (ቅንጅትን) ደግፎ ሃሳብ የሚሰጥ አንድም ሙስሊም ምሁር ማግኘት አልተቻለም ነበር። . በወቅቱ ለምን ይህ ሆነ ተብሎ ሲከታተል የተደረሰበት እውነት የከፋ ነበር። በሀገሪቱ የምርጫ ህግ መሰረት በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ የፓርቲ ቅስቀሳ ማድረግ የተከለከለ ቢሆንም፣ ያንን ህግ ሁሉ በመጣስ በመስጂዶች ውስጥ ሳይቀር ህዝቡ ኢህአዴግን ብቻ እንዲመርጥ ሰፊ ቅስቀሳ ይደረግ ነበር። . ዛሬ ላይ ቆመው "የኢህአዴግን ስም አትጥሩብን" የሚሉ ብዙዎቹ የትናንት ኤሊቶች፣ ያኔ ግን ምንም አይነት የፖለቲካ አማራጭ ሳይተዉ ኢህአዴግን ሲሰብኩ እና ሲያስመርጡ የነበሩ ናቸው። የሚገርመው ግን፣ ማህበረሰቡ ያንን ተከትሎ የሰጠው ድምፅና ያደረገው ውለታ፣ ከዓመታት በኋላ በዚሁ በኢህአዴግ መንግስት አማካኝነት በሙስሊሙ ላይ የተፈጸመውን ታሪካዊ ግፍ፣ በደል እና ጣልቃ ገብነት ሊያስጥለው አልቻለም። ያው የኤሊቱ ስህተት ነው በኋላ ላይ ለ"ድምጻችን ይሰማ" ታላቅ የህዝብ ትግል ሰበብ የሆነው። . እንቁላሎችን በአንድ ቅርጫት ውስጥ የማከማቸት አደጋ ------------ ይህ ታሪካዊ ማስታወሻ ዛሬ ላይ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በግልጽ እንድንረዳ ያደርገናል። ሙስሊሙ ማህበረሰብ፣ በተለይም መሪ መሆን የነበረበት ኤሊቱ፣ ካለፈው የታሪክ ጥፋቱ የተማረ አይመስልም። ዛሬም ማህበረሰቡ ያለውን የፖለቲካ ካርድ እና "እንቁላል ሁሉ በአንድ ቅርጫት ውስጥ" (በገዢው ፓርቲ ብልጽግና ስር) ብቻ ማከማቸቱን መርጧል። .
326
5
እርግጥ ነው፣ ይህ ማህበራዊ ሂስ ትርጉም የሚኖረው "የተካሄደው ምርጫ ነጻ፣ ፍትሃዊ እና የመራጩን እውነተኛ ፍላጎት ያንጸባረቀ ነበር" ብለን በቅንነት ካመንን ብቻ ነው። ነገር ግን ሂደቱ ሙሉ በሙሉ ከማጭበርበርና ከፖለቲካዊ ጫና የነጻ ነበር ብሎ ለመቀበል ይከብዳል። ውጤቱ የፖለቲካ ቁማር እና ስልታዊ ማግለል ውጤት ሊሆን የሚችልበት ዕድል ሰፊ ነው። . ነገር ግን ጉዳዩ የምርጫ ማጭበርበር ከሆነ ደግሞ፣ ሂሱ በቀጥታ የሚዞረው ወደ ራሱ ወደ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) አመራሮች ነው። ምርጫው ፍትሃዊ ካልነበረ እና ድምፅ ከተሰረቀ፣ ፓርቲው ለምን እስካሁን በይፋ ወጥቶ ሂደቱንና ውጤቱን አልሞገተም? ለህዝብ ግልጽ የሆነ መግለጫ በመስጠት የምርጫውን ተአማኒነት የመመርመር ስራ ለምን አልተሰራም? . ህዝቡ ድምፅ ሰጥቶአቸው ከሆነና ያ ድምፅ ከተሰረቀ፣ ያንን ተከላክሎ ማስከበር የፓርቲው ቀዳሚ ኃላፊነት ነበር። ፓርቲው ወጥቶ ስለ ምርጫው እውነተኛነት በግልጽ አለመናገሩ፣ ማህበረሰቡ በአመራሮቹ ላይ "የቁርጠኝነት ማጣት" ወይም "የፖለቲካ ስምምነት" ጥርጣሬ እንዲያድርበት ያደርጋል። ድምፅን ከማስከበር ይልቅ ዝምታን መምረጥ፣ የመረጣቸውን ህዝብ በፖለቲካ ተስፋ መቁረጥ ውስጥ መተው ነው። ሲጠቃለል:- -------- በመጨረሻም፣ የአዲስ አበባ እና የክልሎች ምርጫ ውጤት ለነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ትልቅ ማቆሚያ ነጥብ ነው። ምርጫው ፍትሃዊ ሆኖ ህዝቡና ኤሊቱ "በዜሮ" አሰናብቷቸው ከሆነ፣ ማህበረሰቡ ትናንት ከኢህአዴግ ያልተማረውን ዛሬ ከብልጽግና ጋር እየደገመው ያለ የታሪክ ስህተት ነው። . ያ ካልሆነ እና ምርጫው ተጭበረብሮ ከሆነ ግን፣ ነእፓ ወጥቶ እውነቱን የመናገር እና የመሞገት የሞራልም የፖለቲካም ግዴታ አለበት። ይህንን ሳያደርግ በዝምታ ማለፍ ግን ማህበረሰቡ ለነዚህ ታጋዮች የነበረውን የቆየ አመኔታና ክብር ዋጋ የሚያሳጣ፣ የታሪክ ምፀት ሆኖ ይቀጥላል። . እናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ? የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን! ============= . ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ https://t.me/RNZeroFive
48
6
🚩የአዲስ አበባ ም/ቤት ድምፅ እና የነእፓ እጣ ፈንታ፡ ከታሪካዊ ውለታ እስከ ፖለቲካዊ 'ዜሮ' — ማህበራዊ ሂስ ~~~~ #RN05 . ሰሞኑን ይፋ የሆነው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የምርጫ ውጤት ለብዙዎች አስገራሚ፣ ለፖለቲካ ተንታኞች ደግሞ አዳዲስ ጥያቄዎችን ያረገዘ ሆኖ አልፏል። በዚህ ምርጫ ከተመዘገቡት ትልልቅ መደነቆች መካከል የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) በአዲስ አበባ መዲናችን አንድም መቀመጫ ማግኘት አለመቻሉ እና በዜሮ ማሰናበቱ ግንባር ቀደሙ ማህበራዊና ፖለቲካዊ እንቆቅልሽ ሆኗል። ይህ ውጤት እንዲሁ በተራ የምርጫ ሽንፈት የሚታለፍ ሳይሆን፣ የማህበረሰባችንን ስነ-ልቦና፣ የፓርቲውን ዝምታ እና የኤሊቱን የፖለቲካ ብስለት በጥልቀት እንድንመረምር የሚያስገድድ ማህበራዊ ሂስ (Social Critique) ነው። . ታሪካዊው ውል እና የህዝብ ውለታ --------- ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የዋዛ ስም አይደለም። በተለይም የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮችና መስራቾች፣ የዛሬ አስር አመት ገደማ በነበረው ታሪካዊው የ"ድምጻችን ይሰማ" የህዝብ ንቅናቄ ውስጥ የነበሩ፣ ስለ ማህበረሰቡ መብትና እኩልነት ድምፃቸውን ከፍ አድርገው መጮህያ ብሎም በመሞገቻ አንደበቶች የነበሩ እንዲሁም የሆኑ ናቸው። እነዚህ ግለሰቦች በሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘንድ እንደ መብት ታጋይ እና ባለውለታ የሚታዩ፣ ጥልቅ ማህበራዊ ቅቡልነት (Social Capital) የነበራቸው ናቸው። ከዝያም አልፎ ሁሉንም አካታች ቢሆኑም ለመጀመርያ ጊዜ በሙስሊሞች የተመሰረተ የፖለቲካ ፓርቲ በመሆኑ ብቻ "ሙስሊም አይታመንም!" በሚል የቆየ ብሂል መሰረት ብዙ ሲተቹና ሲብጠለጠሉ እንደነበር ሁሉም በገሃድ የሚያውቀው ነው፡፡ . ፓርቲው ወደ ፖለቲካው ሲገባም ይዞት የተነሳው የፍትህ፣ የእኩልነት እና የነጻነት መርህ ከዚሁ ታሪካዊ መነሻ ጋር የተቆራኘ ነበር። በመሆኑም በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ ውስጥ ባለው ሰፊ የሙስሊም ማህበረሰብ ዘንድ ፓርቲው ቢያንስ ጠንካራ ተፎካካሪ ሆኖ እንደሚወጣ መገመቱ ተፈጥሯዊ ነበር። . የቁጥር እና የውጤት ተቃርኖ፡ ከአዲስ አበባ እስከ ክልሎች ------------- ለመሆኑ በአዲስ አበባ ውስጥ ያለው የሙስሊም ማህበረሰብ ቁጥር እና ስርጭት ምን ያህል ነው? መልሱ ግልጽ ነው፤ በጣም ሰፊና በከተማዋ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መስተጋብር ውስጥ አንቀሳቃሽ ኃይል የሆነ ማህበረሰብ ነው። ታዲያ ይህ ሁሉ ህዝብ ባለበት መዲና፣ የራሱን መብት ለማስከበር የተጋደሉለትን መሪዎች እንዴት "በዜሮ" አሰናበታቸው? . ይህንን እንቆቅልሽ ይበልጥ አጉልቶ የሚያሳየው የሌሎች ፓርቲዎች ውጤት ነው። ለምሳሌ የወላይታ ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄን የመሰሉ፣ መነሻቸውና ዋነኛ አጀንዳቸው ከተወሰኑ የሀገሪቱ ክልሎች ጋር የተያያዘ የፖለቲካ ድርጅቶች እንኳ ሳይቀሩ፣ በአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ውስጥ ቢያንስ አንድ ወይም ከዚያ በላይ መቀመጫዎችን አሸንፈው ብቅ ማለት ችለዋል። በክልል ደረጃ የሚንቀሳቀስ ንቅናቄ በአዲስ አበባ አሸንፎ መቀመጫ ሲያገኝ፣ መላውን አገር አቀፍ አጀንዳ ይዞ የተነሳው ነእፓ ግን የከተማዋን መራጭ ልብ ሳይገዛ መቅረቱ የሚገርም ብቻ ሳይሆን የሚሞግትም ነው። , አዲስ አበባ ያሉ የወላይታ ተወላጆች ምን ያህል በፖለቲካው የነቁ ቢሆኑ ነው ያዉም አዲስ አበባ ምክር ቤት ዉስጥ ያዉም "የነጻነት ንቅናቄ" ፓርቲያቸዉን የወላይታ በመሆኑ ሊመርጡና 1 መቀመጫ እንዲያገኝ ያደረጉት የሚለው ለፖለቲካ ብዛት ብቻ ሳይሆን ንቃት ወሳኝ ስለመሆኑ ማሳያ ነው፡፡ . የነእፓ መደነቅ በአዲስ አበባ ብቻ አይበቃም። ጉዳዩን ይበልጥ አሳሳቢና ገራሚ የሚያደርገው የፓርቲው አገራዊ የምርጫ ውድቀት ነው። ነእፓ የሙስሊሙ ማህበረሰብ በብዛት በሚኖርባቸው እንደ ኦሮሚያ፣ አፋር፣ ቤኒሻንጉል እና ሐረር ባሉ ሰፋፊ ክልሎች ውስጥ—ወይ ጨርሶ እጩ አላቀረበም፣ ካልተባለ በቀር—ከድሬዳዋ በስተቀር በአንድም ክልል አንድም ወንበር ማሸነፍ አለመቻሉ ነው። . የታሪክ ድግግሞሽ፡ የ1997ቱ ትዝታ እና የዛሬው መስታወት ይህ የዛሬው የ"ዜሮ" ውጤት እና የማህበረሰቡ ምርጫ አዲስ የመጣ ክስተት አይደለም። ወደ ኋላ ሄደን የኢትዮጵያን የፖለቲካ ታሪክ ስንፈትሽ፣ የሙስሊሙ ኤሊት (Elite) ለተመሳሳይ ስልታዊ የፖለቲካ ስህተት እራሱን አጋልጦ ሲሰጥ የኖረ መሆኑን እንረዳለን። . ለዚህ ትልቅ ማሳያ የሚሆነው ታሪካዊው የ1997 ዓ.ም ምርጫ ወቅት የነበረው ትዝታ ነው። በወቅቱ በሬዲዮ ነጋሺ የዝግጅት ክፍል በኩል በምርጫው ዙሪያ በኢህአዴግ እና በቅንጅት መካከል የነበረውን ከፍተኛ ፉክክር አስመልክቶ፣ ከሁለቱም ወገን ያሉ ሙስሊም ምሁራንን እና ኤሊቶችን በማነጋገር ልዩ ፕሮግራም ለመስራት ታቅዶ ነበር። በኢህአዴግ በኩል ያሉትን ማግኘት ቀላል የነበረ ቢሆንም፣ በቅንጅት በኩል ያሉትን ለመፈለግ ወደ አንድ ታዋቂ የሀገር ውስጥ ኡስታዝ ስልክ ተደወለ። . የኡስታዙ ምላሽ ግን አስደንጋጭና የፖለቲካ ምህዳሩን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነበር፦ "በሉ አትልፉ! የኢህአዴግ ደጋፊ ካላችሁኝ መስጂዱም፣ ሜዳውም ሙሉ ነው፤ የምትፈልጉትን አይነት ሰዎች ላገናኛችሁ። በቅንጅት በኩል ግን ከእኔ በቀር ማንንም አታገኙም፤ እኔ ደግሞ ሚዲያ ላይ ቃሌን አልሰጥም፤ ስለዚህ አትልፉ" ነበር ያለው። ያም ሆኖ ተስፋ ሳይቆረጥ በተለያዩ መንገዶች ጥረት ቢደረግም፣ ከተራ ምእመናን በስተቀር በኤሊት ደረጃ ተቃውሞን (ቅንጅትን) ደግፎ ሃሳብ የሚሰጥ አንድም ሙስሊም ምሁር ማግኘት አልተቻለም ነበር። . በወቅቱ ለምን ይህ ሆነ ተብሎ ሲከታተል የተደረሰበት እውነት የከፋ ነበር። በሀገሪቱ የምርጫ ህግ መሰረት በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ የፓርቲ ቅስቀሳ ማድረግ የተከለከለ ቢሆንም፣ ያንን ህግ ሁሉ በመጣስ በመስጂዶች ውስጥ ሳይቀር ህዝቡ ኢህአዴግን ብቻ እንዲመርጥ ሰፊ ቅስቀሳ ይደረግ ነበር። . ዛሬ ላይ ቆመው "የኢህአዴግን ስም አትጥሩብን" የሚሉ ብዙዎቹ የትናንት ኤሊቶች፣ ያኔ ግን ምንም አይነት የፖለቲካ አማራጭ ሳይተዉ ኢህአዴግን ሲሰብኩ እና ሲያስመርጡ የነበሩ ናቸው። የሚገርመው ግን፣ ማህበረሰቡ ያንን ተከትሎ የሰጠው ድምፅና ያደረገው ውለታ፣ ከዓመታት በኋላ በዚሁ በኢህአዴግ መንግስት አማካኝነት በሙስሊሙ ላይ የተፈጸመውን ታሪካዊ ግፍ፣ በደል እና ጣልቃ ገብነት ሊያስጥለው አልቻለም። ያው የኤሊቱ ስህተት ነው በኋላ ላይ ለ"ድምጻችን ይሰማ" ታላቅ የህዝብ ትግል ሰበብ የሆነው። . እንቁላሎችን በአንድ ቅርጫት ውስጥ የማከማቸት አደጋ ------------ ይህ ታሪካዊ ማስታወሻ ዛሬ ላይ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በግልጽ እንድንረዳ ያደርገናል። ሙስሊሙ ማህበረሰብ፣ በተለይም መሪ መሆን የነበረበት ኤሊቱ፣ ካለፈው የታሪክ ጥፋቱ የተማረ አይመስልም። ዛሬም ማህበረሰቡ ያለውን የፖለቲካ ካርድ እና "እንቁላል ሁሉ በአንድ ቅርጫት ውስጥ" (በገዢው ፓርቲ ብልጽግና ስር) ብቻ ማከማቸቱን መርጧል። . ይህ አካሄድ ስለ ዛሬው ጊዜያዊ ሰላም ወይም ጥቅም እንጂ፣ ስለ ነገው የረጅም ጊዜ የፖለቲካ ዋስትና ዝግጁ አለመሆኑን ያሳያል። የራሱን አማራጭ ኃይሎች (እንደ ነእፓ ያሉ) አዳክሞ ሙሉ በሙሉ በዜሮ ማሰናበት፣ ነገ ሌላ የፖለቲካ ማዕበል እና በደል ቢመጣ እንኳ መከላከያ ወይም ድምፅ የሚሆን ወኪል አልባ የመሆን ስልታዊ እውርነት ነው። ይህ የዛሬው ምርጫ ውጤት የኤሊቱን የፖለቲካ ብስለት እና አርቆ አሳቢነት ትልቅ ጥያቄ ምልክት ውስጥ የከተተ መስታወት ነው። . ትልቁ ቅድመ-ሁኔታ እና የነእፓ ዝምታ --------------
43
7
No text...
272
8
No text...
372
9
~ አደፍራሽ እያለ ማን ንጹህ ይጠጣል? ~~~ #የቢላል_ትዝብት . አሜሪካና ኢራን የመግባቢያ ስምምነት የተፈራረሙበት ቀለም ሳይደርቅ ስምምነቱ እየፈረሰ ያለ ይመስላል። የመግባቢያ ስምምነቱ ከመነሻው ስታጣጥለው የቆየችው እስራኤል የአፍራሽነት ሚና እንደምትጫወት በሁሉም ዘንድ የታመነ ቢሆንም ያለምንም እፍረት የአፍራችነት ሚናዋን አጠናክራ ይዛለች። ትራምፕ ቢሳደብም ቢያስፈራራም ከቁብ የቆጠረችው አይመስልም. ምንም እንኳን ከሂዝቡላህ ጋር አርብ 19/06እለት የጦር ማቆም ስምምነት ፈጽማለች ቢባልም በማግስቱ የአየር ላይ ጥቃት በመፈጸም በርካቶችን ገድላለች። ኢራንና አሜሪካ ስምምነት ከደረሱባቸ ነጥቦች መካከል አንዱ የሆነው የሌባኖስ ጉዳይ እልባት አለማግኘቱን እንደምክንያት በመጥቀስ ኢራን የሆርሙዝን ባህረሠላጤ መልሳ መዝጋቷን አስታውቃለች። . የእስራኤል መንግሥትና ባለሥልጣናት የአይሁድ ወዳጅ እያሉ ሲያወድሱት የነበረውን ፕሬዚደንት ትራምፕ ክፉኛ ማብጠልጠሉን አጠናክረው ይዘውታል። አሜሪካ ፖለቲካ ላይ ባላቸው ተጽዕኖ ፈጣሪነት ላይ ከፍተኛ እምነት እንዳላቸው በተለያዩ መንገዶች እያሳዩ ነው። እስከ አሁን ድረስ ትራምፕን ክፉ ተናግረው የማያውቁት የሪፖብሊካን ሴኔተሮች ትራምፕን ማውገዝ ጀምረዋል። ስምምነቱን ከአሜሪካ ፍላጎት አንጻር ሳይሆን ከእስራኤል ፍላጎት አንጻር የሚመዝኑት እነኝህ ሴኔተሮች ስምምነቱ ከዚህ በፊት በኦባማ ከተደረገው ስምምነት የከፋ ነው በማለት ሲፈርጁት ተደምጣዋል። ይሄ ገና ጅማሬ ብቻ ነው። . ቀኑ እየገፋ ከሄደና ስምምነቱ የመተግበር አዝማሚያ ካሳየ ትራምፕ ገና ከዚህም በላይ ይጠብቀዋል።ያ ማለት ግን ትራምፕ ለእስራኤል ከማጎብደድ ውጪ ሌላ አማራጭ የለውም ማለት አይደልም። ወይንም የእስራኤል እጅ ጥምዘዛ ሙከራ ይሳካል ማለትም አይደለም። ትራምፕ ጓንቱን አውልቆ ካርዶቹን ያለማወላወል ለመጠቀም ከወሰነ እስራኤልና ወዳጆቿን ማንበርከክ የሚችልበት አቅም አለው። እንደሚታወቀው እስራኤል በአሁኑ ሰዓት በአሜሪካ ህዝብ መካከል ያላት ተቀባይነት እጅግ በጣም ወርዷል። የወግ አጥባቂው ጠንካራ ድምፆች እስራኤልን ክፉኛ ማወገዝ ከጀመሩ ውለው አድረዋል።ስምምነቱን የአውሮፓ ህብረትን ጨምሮ የጎልፍ አገራትም ደግፈውታል። ስምምነቱ ከተፈረመ በኋላ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መውረዱ በርካታ አገራትን አስደስቷል። የጎፍ አገራቱ ምርቶቻቸውን ያለመደነቃቀፍ መሸጥ በመቻላቸው ብቻ ሳይሆን ከኢራን ከፍተኛ ድብደባም የተማረሩ በመሆናቸው ስምምነቱ አንዳይደናቀፍ ያላቸን አቅም በሙሉ እንደሚጠቀሙ ይጠበቃል። በአጠቃላይ ሲታይ ስምምነቱን ከሚያወግዙት ይልቅ የሚደግፉት በብዛትም ሆነ በአቅም ከፍተኛ ብልጫ አላቸው። ከሁሉም በላይ ደግሞ እስራኤል ያለ አሜሪካ ድጋፍ የመዋጋት አቅሟ በጣም ውስን ስለሆነ ትራምፕ በስምምነቱ ለመግፋት ቁርጠኝነት ካሳይ እስራኤል ከመቀበል ውጪ አማራጭ አይኖራትም። . እናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ? የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን! ============= . ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ https://t.me/RNZeroFive
440
10
No text...
412
11
No text...
677
12
"መቸም የማይበደር የለም" ሊባል ይችል ይሆናል :: ግን ግን ችግሩ ያለው ተበድረን ስናበቃ የአበዳሪ ሳቅ መሳቃችን ይመስለኛል!! ችግሩ ያለው ብድሩ የተመቸን, ስጦታ አድርገን የቆጠርነው መምሰሉ ላይ
"መቸም የማይበደር የለም" ሊባል ይችል ይሆናል :: ግን ግን ችግሩ ያለው ተበድረን ስናበቃ የአበዳሪ ሳቅ መሳቃችን ይመስለኛል!! ችግሩ ያለው ብድሩ የተመቸን, ስጦታ አድርገን የቆጠርነው መምሰሉ ላይ ይመስለኛል:: እናንተስ? . ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ https://t.me/RNZeroFive #የአቅል_አይምሮ_ትዝብት_ለRN05
965
13
የፖለቲካ ኪሳራን በሃይማኖት ካባ የመሸፈን አደገኛ ቁማር እና የችግሩ መልከ-ብዙ ገጽታ ~~~~~~~~~ #RN05 . "አሁን ባለው የኢትዮጵያ ሁኔታ ለምሳሌ በአርሲ የተከሰተዉን ችግር ተንተርሰው የፖለቲካ ችግሮችን ወደ ሃይማኖት ለማምጣት የሚሹ አካላት ስለመኖራቸው በቂ ማስረጃ አለ፡፡ አጀቡ የቀዘቀዘባቸው እና ለችግሮቻቸው እዉነተኛዉንና ዘላቂ ብሎም ጠቃሚ መፍትሄ መፈለግ ያቃታቸው, አልያም እርስ በእርስ የማበጣበጥ እና በግርግሩም የማትረፍ አጀንዳ ያነገቡ አንድ አንድ ሰባኪያንና አክትቪስቶች የፖለቲካ ልዩነቶችንና በዚህም ሰበብ ህዝባችን ላይ የሚፈጠሩ ችግሮችን በግድ ወደ ሃይማኖት በማምጣት ግጭቶችን ለመፍጠር እየሞከሩ እንደሆነ ይስተዋላል፡፡ ያልተገነዘቡት ነገር ግን ቢሳካላቸው እንኳን በሂደት የባሰ ይከስሩ እንደሁ እንጂ በዘላቂነት የማያተርፉ መሆናቸዉን ነው !!" 1. በኢትዮጵያ ያለው የሃይማኖት ውጥረት መልከ-ብዙ ባህሪ (Multi-faceted Nature) አለው . በሀገራችን በሃይማኖት ስም የሚነሱ ግጭቶችና የሚፈጸሙ በደሎች ሁልጊዜ አንድ ዓይነት መልክ የላቸውም። ችግሩን ውስብስብ የሚያደርገውና የአክቲቪስቶችንም ሴራ በቀላሉ ለመለየት የሚያስቸግረው የችግሩ መልከ-ብዙ መሆን ነው። እውነታውን ስንመረምረው የሚከተሉትን የተለያዩ ገጽታዎች እናገኛለን፦ . ተቋማዊና መዋቅራዊ ጫናዎች (Institutional & Structural Bias)፦ በእርግጥ በሀገሪቱ ውስጥ የሃይማኖት ጭቆናዎች መኖራቸው እሙን ነው። ለምሳሌ በአክሱም ሙስሊሞች ላይ የታወጀውን ጭቆና መጥቀስ ይቻላል። ይህ ድርጊት ምንም እንኳን በቀኖና ደረጃ የክርስትና ሃይማኖት ትምህርትና ትዕዛዝ ባይሆንም፣ በሲኖዶስና በቄሶች የሚመራ፣ የአካባቢውን የፖለቲካ አስተዳደርም የሚጠቀም በመሆኑ "ክርስትናዊ" ባይባልም "ቤተክርስቲያናዊና ፖለቲካዊ" ልንለው እንችላለን። በጎንደርና በአካባቢውም በየወቅቱ በሙስሊሞች ላይ የሚፈጸመው በደል ተመሳሳይ መልክ የተላበሰ ነው። . ፖለቲካዊ ውድቀቶችና የወንጀል ማዕበሎች (Political & Criminal Acts)፦ በሌላ በኩል ደግሞ ድርጊቶቹ ሙሉ በሙሉ ከሃይማኖት ተቋማት አስተምህሮ ውጭ በፖለቲካ ኃይሎች የሚፈጸሙበት ሁኔታ አለ። ለምሳሌ በወለጋ ሙስሊሞች ላይ ላይ የተሰራው ጭፍጨፋ እንደ አክሱሙ ቤተክርስቲያናዊ ሳይሆን ንጹህ ፖለቲካዊ ነው። የጋራ ሰለባነት (Shared Victimhood)፦ በተመሳሳይ መልኩ በአርሲ በተለያዩ ወቅቶች በክርስቲያን ወገኖቻችን ላይ የደረሰው ግድያና ጥቃት መስጊድን ያማከለ አልነበረም። ወይም ደግሞ እንደ አክሱሙ ሁኔታ በሙስሊም ተሟጋቾችና መምህራን የተመራ አይደለም። ይልቁንም ወንጀል ፈጻሚው ማንም ይሁን ማን፣ የራሱን ድብቅ ፖለቲካዊ አጀንዳ ያነገበ አካል የፈጸመው ነው። ጥቃቱ በብዛት ያነጣጠረው በክርስቲያኖች ላይ ቢሆንም፣ በወቅቱ ሙስሊሞችም ጭምር አብረው መገደላቸው የተዘገበ ጉዳይ ነው። ይህ የሚያሳየው ጥቃቱ የሃይማኖት ሳይሆን ህዝብን የማተራመስ ፖለቲካዊ ግብ ያለው መሆኑን ነው። . 2. አደገኛነቱ የት ላይ ነው? (የአክቲቪስቶች ቁማር) -የችግሩ መልክ እንዲህ የተለያየና ውስብስብ መሆኑን እያወቁ፣ አንዳንድ አክቲቪስቶችና ሰባኪያን ግን ሁሉንም ነገር "አንድ ወጥ" አድርገው ማቅረብ ይፈልጋሉ። . -በአንድ በኩል ያሉ እውነተኛ ተቋማዊ በደሎችን መፍትሄ ከመፈለግ ይልቅ ጥላቻን ለመዝራት ይጠቀሙባቸዋል። በሌላ በኩል ደግሞ በወለጋና በአርሲ የሚፈጸሙትን፣ ሁለቱንም እምነቶች እኩል ሰለባ ያደረጉትን ንጹህ ፖለቲካዊ ወንጀሎች በግድ ወደ ሃይማኖት ፍልሚያ በመቀየር ህዝቡን እርስ በርስ ለማባላት ይጥራሉ። . -ይህ አጀንዳቸው የቀዘቀዘባቸው አካላት የፖለቲካ ልዩነቶችን በሃይማኖት ካባ እየሸፈኑ በግርግር ለማትረፍ የሚያደርጉት ጥረት ነው። ነገር ግን ቢሳካላቸው እንኳን በሂደት ሀገር ስትፈርስ እነሱም አብረው የባሰ ይከስሩ እንደሁ እንጂ አያተርፉም! . 3. መውጫ መንገዱ ምንድን ነው? ችግሮችን ለይቶ ማወቅ፦ የትኛው ተቋማዊ/መዋቅራዊ በደል እንደሆነ፣ የትኛው ደግሞ የፖለቲካ ኃይሎች የፈጸሙት ወንጀል እንደሆነ ለይቶ ማወቅና ማጋለጥ። በጋራ መቆም፦ በአርሲም ሆነ በሌላ ቦታ ወንጀለኞች ጥቃት ሲፈጽሙ ክርስቲያኑንም ሙስሊሙንም እኩል እንደሚያጠፉ ተገንዝቦ፣ በጋራ ወንጀለኞችን መኮነን። የጥላቻ ነጋዴዎችን አለመስማት፦ ከሩቅ ሆነው የህዝብን ደምና ስሜት ለዲጂታል ገበያቸው የሚጠቀሙ አክቲቪስቶችንና ሰባኪያንን በር መዝጋት። . ማጠቃለያ መልእክት፦ ----------- በሀገራችን ያለው የሃይማኖት ውጥረት መልከ-ብዙና ውስብስብ መሆኑ አይካድም። መዋቅራዊ በደሎችን በፍትሃዊ መንገድ መፍታት እንደሚገባው ሁሉ፣ የፖለቲካ ቁማርተኞች ወንጀላቸውን በሃይማኖት ስም እንዲነግዱበት ግን ሊፈቀድላቸው አይገባም። እናም #በጋራ_ለመቆም -ንቁ እንሁን! እንላለን! . የበለጠ መረጃዎችን ለማግኘት ገጻችንን Like እና Follow ማድረጎን አይርሱ! በጉዳዩ ላይ ያለዎትን አስተያየት በኮሜንት ያጋሩን። . ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ https://t.me/RNZeroFive . #ኢትዮጵያ #ፍትህ #አብሮነት #ንቁ #ወቅታዊ_ጉዳይ
952
14
No text...
614
15
በአልባንያ ምን እየተካሄደ ነው? በጃሬድ ኩሽነር እና በእስራኤል ባለሀብቶች የታሰበው የቢሊዮን ዶላር ታላቅ ፕሮጀክት እና የሕዝቡ ቁጣ! ~~~~~~~~ #RN05 . የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አማች እና የነጩ ቤተ መንግሥት ከፍተኛ አማካሪ እንዲሁም (የእስራኤል ጥምር አገልጋይ ነው) * የሚሰኘው ጃሬድ ኩሽነር በአልባንያ የባህር ዳርቻ ላይ ሊገነባ ያቀደው ግዙፍ የሪል እስቴት እና የቅንጦት ቱሪዝም ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ውስጥ ታላቅ የፖለቲካ እና የሕዝብ ውዝግብ አስነስቷል። . የዚህን ግዙፍ እና አወዛጋቢ ፕሮጀክት አጠቃላይ ዝርዝር በአጭሩ እንመልከተው፦ . 1. ምን ታስቦ ነበር? ------- የፕሮጀክቱ ይዘት፦ በቀዝቃዛው ጦርነት ወቅት ወታደራዊ የባህር ኃይል ማዕከል በነበረችው ሳዛን ደሴት (Sazan Island) እና የስደተኛ ወፎች (በተለይም ፍላሚንጎዎች) መናኸሪያ በሆነው በሕግ ጥበቃ በሚደረግለት ቪዮሳ-ናርታ (Vjosa-Narta) የተፈጥሮ ጥበቃ ቀጠና ላይ ግዙፍ የቅንጦት ሪዞርት ለመገንባት ታስቦ ነበር። . በጀቱ፦ ወደ 4 ቢሊዮን ዶላር ገደማ የሚጠጋ በጀት የተመደበለት ሲሆን፣ 10,000 የሆቴል ክፍሎችን፣ ዘመናዊ ቪላዎችን እና የቅንጦት መርከቦች ማቆሚያ (marina) መሥራትን ያካተተ ነበር። . 2. በስተጀርባው ያለው ማን ነው? ------- ፕሮጀክቱን የሚመራው የኩሽነር Affinity Partners የተባለ የኢንቨስትመንት ተቋም ነው። ይህ ተቋም ከሳውዲ አረቢያ የሀብት ፈንድ (PIF) እና ከእስራኤል ጋር ግንኙነት ካላቸው ታዋቂ የፋይናንስ ዘርፎችና ባለሀብቶች ጋር የጠበቀ ትስስር ያለው በመሆኑ፣ ፕሮጀክቱ በስተጀርባው የጂኦፖለቲካ እና የጥቅም ትስስር እንዳለበት በሰፊው ይነገራል። . 3. የአልባንያው መሪ ሚና ------- የአልባንያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኤዲ ራማ (Edi Rama) ለዚህ ፕሮጀክት ሙሉ ድጋፋቸውን ከመስጠታቸዉም በላይ በዚሁ ጉዳይ ከህዝባቸው ጋር ተጋጭተዋል። እንዲሁም ለኩሽነር ኩባንያ “የስትራቴጂክ ባለሀብት” የሚል ልዩ ደረጃ በመስጠት፣ ካምፓኒው ከተለያዩ ታክሶች ነፃ እንዲሆን እና የመንግሥትን መሬት በቀላሉ እንዲያገኝ ፈቅደዋል። . ይህንን ለማድረግ ሲባልም መንግሥት የተፈጥሮ ጥበቃ ቀጠናዎችን ለግንባታ ክፍት የሚያደርግ የሕግ ማሻሻያ ጭምር አድርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ኤዲ "እኔ እስካለሁ ድረስ ይህ ፕሮጀክት እዉን ይሆናል፣ እንኳን 5ሺ ሰው ቀርቶ 5 መቶ ሺ ህዝብ ሰልፍ ቢወጣ ማንም አያቆመኝም!" ሲሉ ቢዝቱም በእምቢ ባዩ ጠንካራው ህዝባቸው ስለመሸነፋቸው እየተዘገበ ይገኛል፡፡ . ጠቅላይ ሚኒስትር ኤዲ ቀደም ባሉት ግዝያት የእስራኤልን እና የዋሽንግተን መንግስታትን ሲተቹ ቢሰሙም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን እስራኤልን እና በተለይ ናትያንያሁን ከምርጥ መሪዎች አንዱ አድርገው መናገራቸው ሲያወዛግብ መቆየቱ ይታወሳል! . 4. የአልባንያ ሕዝብ እና የአካባቢ ጥበቃ ተሟጋቾች ምላሽ ------- ከፍተኛ ቁጣና ሰላማዊ ሰልፍ፦ ከዚህ ፕሮጀክት እዉን መሆን ማግስት የፍልስጤም እጣ ይደርሰናል ብለው የሰጉ የሃገሪቱ ዜጎች “ሀገሪቱ ለውጭ ባለሀብቶች እና ለኦሊጋርኮች እየተሸጠች ነው” በሚል በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በዋና ከተማዋ ቲራና እና በባህር ዳርቻው አካባቢ ሰፊ ሰላማዊ ሰልፎችን አድርገዋል። . ሃገራችን ጋዛ እንዲሆን አንፈቅድም ባዮቹ የሃገሪቱ ዜጎች “አልባንያ የአልባንያውያን ናት!” እና “ተፈጥሯችንን አታውድሙ!” በሚሉ መፈክሮች ታጅበው ያካሄዱት ይህ ተቃውሞ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋ የመጣ ሲሆን ፣ በአካባቢው አጥር ሲታጠር የተቃወሙ ሰልፈኞችን የግል ጥበቃዎች በኃይል ሲጎትቱ የሚያሳይ ቪዲዮ በመውጣቱ የሕዝቡን ቁጣ ይበልጥ አናሯል። . 5. አሁን ያለበት ደረጃ፡ ፕሮጀክቱ ከሽፏል ወይስ ቆሟል? ------- በሕግ ቁጥጥር ስር መውደቁ፦ የአልባንያው ገለልተኛና ታዋቂው የፀረ-ሙስና ልዩ አቃቤ ሕግ ተቋም (SPAK)፣ መንግሥት መሬቱን ያስተላለፈበትን መንገድ እና የተፈጥሮ ጥበቃ ሕጉን የለወጠበትን አካሄድ አስመልክቶ ይፋዊ የወንጀል ምርመራ ጀምሯል። . ምንም እንኳን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፕሮጀክቱን ለመግፋት ቢፈልጉም፣ በከፍተኛው የሕዝብ ተቃውሞ እና በጀመረው የሙስና ምርመራ ምክንያት ፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት ላይ ትልቅ ማነቆ ገጥሞታል፤ ግንባታው እንዲታገድም ዓለም አቀፍና የአገር ውስጥ ግፊቶች በከፍተኛ ደረጃ እየተደረጉበት ይገኛል። . የበለጠ መረጃዎችን ለማግኘት ገጻችንን Like እና Follow ማድረጎን አይርሱ! በጉዳዩ ላይ ያለዎትን አስተያየት በኮሜንት ያጋሩን። . ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ https://t.me/RNZeroFive . #Albania #JaredKushner #SazanIsland #VjosaNarta #Geopolitics #Environment #CorruptionInvestigation #GlobalNews #የአለምዜና #አልባንያ
767
16
No text...
522
17
No text...
703
18
No text...
832
19
ይድረስ ለ Moges Zewdu Teshome እዉነቱን ከተነጋገርን ዘመኑ እንዳልከዉ የዳግማዊ ግራኝ አህመድ ቢሆን ኖሮ #አርሲም ሆነ #አክሱም ፣ #ቤተ_ክርስትያንም ሆነ #መስጂድ ፣ #ክርስትያኑም ሆነ
ይድረስ ለ Moges Zewdu Teshome እዉነቱን ከተነጋገርን ዘመኑ እንዳልከዉ የዳግማዊ ግራኝ አህመድ ቢሆን ኖሮ #አርሲም ሆነ #አክሱም ፣ #ቤተ_ክርስትያንም ሆነ #መስጂድ ፣ #ክርስትያኑም ሆነ #ሙስሊሙ ምዕመን ደህንነታቸው በተጠበቀ ነበር፡፡ ይህንን የምንለው በስሜት ሳይሆን በመረጃ ነው፡፡ ባይሆን ዘመኑ የ #አጼዎቹ አይነት ሆኖ እንደሁ መርምር! . አብዛኞቹ የኢትዮጵያ ኤሊቶች ምንም ሞደሬት ቢመስሉም የከፋ እለት ከተለመደው የልምድ አስተሳሰብ መላቀቅና ሚዛን መጠበቅ እጅግ ያዳግታቸዋል፡፡ ለዚህም ልዩ ኮርስ መዉሰድ ሳይጠበቅባቸው አይቀርም! . #RN05 . እናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ? የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን! ============= . ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ https://t.me/RNZeroFive . ፍትህ ለ #አርሲ_ክርስትያኖች፣ ፍትህ ለ #አክሱም_ሙስሊሞች ፍትህ #ለመላው_ሃገራችን_ህዝቦች
1 145
20
የመሪዎች መራቅ እና የህዝብ እምባ፡ ከአርሲው ግፍ በስተጀርባ ያለው የፖለቲካ ትዝብት! ~~~~~~ #የአቅል_አይምሮ_ትዝብት_ለrn05 . "የአርሲን ግፍ ማንም ፈጸመው ማን እንዲጣራ አዘው በዚህ ሰአት ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ህዝባቸውን ለማጽናናት አርሲ መታየት ነበረባቸው! ግን እንኳን እሳቸው ምክትሎቻቸውም ሆኑ ሰልስቶቻቸው አልተገኙም፡፡ የመጡ ሰሞን በየቀየው ለቅሶ ሲደርሱ ያየን መስሎን! የሰለጠነ መንግስት ግለሰቦች ላይ ሳይሆን ህዝብ ተኮር አደጋ ሲደርስ ቦታው ላይ ቀድሞ ይገኛል፡፡ አደጋው ከደረሰበት ህዝብም ጋር ይወያያል፡፡" ይህ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚንሸራሸር እውነት፣ ዛሬ በሀገራችን ኢትዮጵያ ያለውን የመንግስት እና የህዝብ ግንኙነት መከፋፈል ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ትልቅ ትዝብት ነው። በአርሲ ንጹሃን ዜጎች በማንነታቸው እና በሃይማኖታቸው ምክንያት እጅግ ዘግናኝ በሆነ መልኩ ሲገደሉ፣ የመንግስት ከፍተኛ አመራሮች ዝምታን መምረጣቸው ወይም በቦታው ተገኝተው ህዝቡን አለማጽናናታቸው ትልቅ የታሪክ ጠባሳ ነው። 1. የሰለጠነ መንግስት መገለጫ፡ በጭንቅ ቀን ቀድሞ መገኘት በፖለቲካ ሳይንስ እና በመልካም አስተዳደር መርህ፣ የአንድ መንግስት ህጋዊነት (Legitimacy) የሚለካው ህዝብ አደጋ ላይ ሲወድቅ በሚያሳየው አፋጣኝ ምላሽ ነው። የሰለጠነ መንግስት መሪዎች ህዝብ ተኮር አደጋዎች፣ የተፈጥሮ አደጋም ሆነ የሽብር ጥቃት ሲደርስ ቀድመው ቦታው ላይ ይገኛሉ። ይህንን የሚያደርጉት ለፖለቲካ ፍጆታ ብቻ ሳይሆን፦ የህዝብን ስነ-ልቦናዊ ስብራት ለመጠገን፦ መሪው አብሮኝ አለቀሰ ማለት ህዝቡ የተረሳና ኦናነት እንደማይሰማው ያደርጋል። ፍትህ ለማረጋገጥ፦ በቦታው ተገኝቶ ወንጀለኞች እንደሚቀጡ ቃል መግባት ለተጎጂዎች ትልቅ መጽናኛ ነው። 2. አለምአቀፍ ፋክቶች እና ማሳያዎችን (Global Examples) በአለም ታሪክ መሪዎች ለህዝባቸው ያላቸውን አጋርነት በችግር ቀን እንዴት እንዳሳዩ ጥቂት ምሳሌዎችን እንመልከት፦ የኒውዚላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ጃሲንዳ አርደርን (እ.ኤ.አ 2019)፦ በክራይስትቸርች መስጊዶች ላይ የሽብር ጥቃት ደርሶ 51 ሙስሊሞች ሲገደሉ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሯ በሰዓታት ውስጥ ጥቁር ሂጃብ ለብሳ ከተጎጂዎች ጎን ቆማለች። እምባዋን እየጠረገች ቤተሰቦቻቸውን አቅፋ አጽናንታለች። ይህ ተግባሯ በሃገሯና በአለም አቀፍ ደረጃ የመሪነት ተምሳሌት አድርጓታል። የአሜሪካ ፕሬዝዳንቶች ተሞክሮ፦ በአሜሪካ የጅምላ ተኩስ (Mass Shootings) ወይም እንደ ካትሪና ያሉ አውሎ ነፋሶች ሲከሰቱ፣ ፕሬዝዳንቱ (ኦባማ፣ ባይደንም ሆኑ ሌሎች) ወዲያውኑ ስራቸውን አቋርጠው ወደ ስፍራው ያመራሉ። የተጎጂዎችን እጅ ይይዛሉ፣ አብረው ያለቅሳሉ። የፈረንሳዩ ኢማኑኤል ማክሮን፦ በፈረንሳይ የሽብር ጥቃት በደረሰ ቁጥር ማክሮን በቀጥታ ጥቃቱ ወደተፈጸመበት ቦታ በመሄድ ከህዝቡና ከፀጥታ አካላት ጋር በመቆም አጋርነታቸውን ሲያሳዩ በተደጋጋሚ ታይተዋል። 3. የሀገር ውስጥ ታሪካዊ ማሳያዎች (Historical Contrast) ወደ ሀገራችን ስንመጣ፣ የወቅቱ መሪዎች የመጡ ሰሞን ያሳዩት የነበረው "ህዝባዊነት" እና ዛሬ የመጡበት ደረጃ እጅግ የሚራራቅ ሆኗል፦ የመጡ ሰሞን የነበረው ለቅሶና ጉብኝት፦ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን በረገጡ ማግስት በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በሶማሌ እና በደቡብ ክልሎች እየተዘዋወሩ ከህዝብ ጋር ይመክሩ፣ ሲያዝኑ አብረው ያዝኑ ነበር። ያ አቀራረብ በህዝብ ዘንድ ትልቅ ተስፋን ጥሎ ነበር። የዛሬው እውነታ፦ ዛሬ ግን በአርሲ፣ በወለጋ፣ በፋኖ እና በመንግስት ጦርነት ምክንያት በአማራ ክልል፣ እንዲሁም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ንጹሃን በየቀኑ ሲረግፉ፣ መሪዎች በቤተመንግስት ውስጥ የአትክልት ስራና የፓርክ ምርቃትን ሲያከናውኑ ይታያሉ። ይህም "ህዝቡ እያለቀሰ መሪው ይደሰታል" የሚል አደገኛ የፖለቲካ ትረካ እንዲሰፍን አድርጓል። 4. "ግለሰብ ተኮር" እና "ህዝብ ተኮር" አደጋዎች የወቅቱ መንግስት ትኩረት "ግለሰቦች ላይ ሳይሆን ህዝብ ተኮር አደጋ ላይ" መሆን ነበረበት። በአሁኑ ወቅት የአንድ ባለስልጣን ዘመድ ወይም ታዋቂ ግለሰብ ላይ አደጋ ሲደርስ መንግስታዊ መግለጫዎች ይዥጎደጎዳሉ፣ ለቅሶ ይደረሳል። ነገር ግን በመቶዎች የሚቆጠሩ ምስኪን ገበሬዎች፣ እናቶችና ህጻናት በአርሲ ምድር በገጀራና በጥይት ሲጨፈጨፉ አፋጣኝ የሀዘን መግለጫ እንኳን አለመስጠት፣ ታሪካዊ ትዝብትና የታሪክ ተጠያቂነትን ያመጣል። ማጠቃለያ --- መሪነት በሰላም ጊዜ ሪቫን መቁረጥና ፎቶ መነሳት ብቻ አይደለም። እውነተኛ መሪነት የሚፈተነው ህዝብ በሚያለቅስበት የጭንቅ ሰዓት ነው። በአርሲ የደረሰው ግፍ የኢትዮጵያ ህዝብ የጋራ እምባ ነው። በዚህ ሰዓት ጠቅላይ ሚኒስትሩም ሆኑ ከፍተኛ ምክትሎቻቸው በቦታው ተገኝተው የህዝቡን እምባ አለማበሳቸው፣ በመንግስትና በህዝብ መካከል ያለው ማህበራዊ ውል (Social Contract) ምን ያህል እንደፈረሰ ማሳያ ነው። የሰለጠነ መንግስት ከህንጻዎችና ከፓርኮች በፊት ለሰው ልጅ ህይወትና ክብር ቅድሚያ ይሰጣል። የወገኖቻችን ደም በከንቱ አይፍሰስ፤ ለተጎጂዎች መጽናናትን፣ ለሀገራችን ሰላምን ይስጥልን! . እናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ? የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን! ============= . ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ https://t.me/RNZeroFive . #አርሲ #የንጹሃን_ጭፍጨፋ #ኢትዮጵያ #የመሪዎች_ትዝብት #ፍትህ
829