RN.05 - Channel
Ir al canal en Telegram
ከኢትዮጵያና አዉሮፓ የሚተላለፍ የራድዮ ፕሮግራም አዲሱን ዩቱብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ: https://www.youtube.com/c/RN05Channel ፌስቡክ ገፃችንን like ያድርጉ: https://www.facebook.com/RNZeroFive/ https://twitter.com/RNZeroFive Support Us: http://bit.ly/3c09jfJ https://RNZeroFive.com
Mostrar más2 331
Suscriptores
-124 horas
-67 días
+230 días
Carga de datos en curso...
Canales Similares
Nube de Etiquetas
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
septiembre '26
septiembre '26
+13
en 0 canales
agosto '26
+75
en 0 canales
Get PRO
julio '26
+37
en 0 canales
Get PRO
junio '26
+34
en 0 canales
Get PRO
mayo '26
+37
en 0 canales
Get PRO
abril '26
+45
en 0 canales
Get PRO
marzo '26
+74
en 0 canales
Get PRO
febrero '26
+28
en 0 canales
Get PRO
enero '26
+28
en 0 canales
Get PRO
diciembre '25
+37
en 0 canales
Get PRO
noviembre '25
+78
en 1 canales
Get PRO
octubre '25
+76
en 0 canales
Get PRO
septiembre '25
+49
en 0 canales
Get PRO
agosto '25
+39
en 0 canales
Get PRO
julio '25
+105
en 0 canales
Get PRO
junio '25
+133
en 0 canales
Get PRO
mayo '25
+62
en 0 canales
Get PRO
abril '25
+103
en 0 canales
Get PRO
marzo '25
+68
en 0 canales
Get PRO
febrero '25
+56
en 0 canales
Get PRO
enero '25
+93
en 1 canales
Get PRO
diciembre '24
+45
en 1 canales
Get PRO
noviembre '24
+61
en 0 canales
Get PRO
octubre '24
+175
en 0 canales
Get PRO
septiembre '24
+24
en 0 canales
Get PRO
agosto '24
+32
en 1 canales
Get PRO
julio '24
+12
en 0 canales
Get PRO
junio '24
+47
en 0 canales
Get PRO
mayo '24
+111
en 1 canales
Get PRO
abril '24
+66
en 1 canales
Get PRO
marzo '24
+53
en 0 canales
Get PRO
febrero '24
+148
en 0 canales
Get PRO
enero '24
+126
en 0 canales
Get PRO
diciembre '23
+146
en 0 canales
Get PRO
noviembre '23
+427
en 1 canales
Get PRO
octubre '23
+29
en 0 canales
Get PRO
septiembre '23
+12
en 0 canales
Get PRO
agosto '23
+29
en 0 canales
Get PRO
julio '23
+11
en 0 canales
Get PRO
junio '23
+13
en 0 canales
Get PRO
mayo '23
+4
en 0 canales
Get PRO
abril '23
+13
en 0 canales
Get PRO
marzo '23
+40
en 0 canales
Get PRO
febrero '23
+5
en 0 canales
Get PRO
enero '23
+2
en 0 canales
Get PRO
diciembre '22
+36
en 0 canales
Get PRO
noviembre '22
+4
en 0 canales
Get PRO
octubre '22
+29
en 0 canales
Get PRO
septiembre '22
+12
en 0 canales
Get PRO
agosto '22
+120
en 0 canales
Get PRO
julio '22
+159
en 0 canales
Get PRO
junio '22
+9
en 0 canales
Get PRO
mayo '22
+89
en 0 canales
Get PRO
abril '22
+9
en 0 canales
Get PRO
marzo '22
+3
en 0 canales
Get PRO
febrero '22
+3
en 0 canales
Get PRO
enero '22
+5
en 0 canales
Get PRO
diciembre '21
+94
en 0 canales
Get PRO
noviembre '21
+25
en 0 canales
Get PRO
octubre '21
+7
en 0 canales
Get PRO
septiembre '21
+3
en 0 canales
Get PRO
agosto '21
+8
en 0 canales
Get PRO
julio '21
+39
en 0 canales
Get PRO
junio '21
+24
en 0 canales
Get PRO
mayo '21
+1 067
en 0 canales
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 16 septiembre | 0 | |||
| 15 septiembre | 0 | |||
| 14 septiembre | 0 | |||
| 13 septiembre | +1 | |||
| 12 septiembre | 0 | |||
| 11 septiembre | 0 | |||
| 10 septiembre | 0 | |||
| 09 septiembre | +1 | |||
| 08 septiembre | +3 | |||
| 07 septiembre | +1 | |||
| 06 septiembre | 0 | |||
| 05 septiembre | 0 | |||
| 04 septiembre | +1 | |||
| 03 septiembre | +4 | |||
| 02 septiembre | +1 | |||
| 01 septiembre | +1 |
Publicaciones del Canal
~ ፍረጃው ቢቀር!!
~ ፖለቲካ ወይስ ኢጎ? | ሰይጣንን ማን አሳሳተው?
~~~~~~~~~~~
#የቢላል_ትዝብት
.
በአማፅያኑ መካከል እንደተፈጠረ በሚነገረው ህብረት ዙሪያ ያለው ክርክር እየተጧጧፈ እንደሆነ እየተመለከትን ነው። በእውነቱ በጉዳዩ ዙርያ ውይይቱና ክርክሩ መጧጧፉ ሰናይ ነው ባይ ነኝ። በተለይ መፈራረጁ ቢቀርና ሁሉም ሃሳቡን ያለመሸማቀቅ እንዲገልጽ እድሉ ቢመቻች ውይይቱና ክርክሩን ፍሬያማ ውጤት ላይ ያደርስ ነበር የሚል እምነት አለኝ። መፈራረጁ ግን አፍራሽና ውይይቱን ፍሬ አልባ የሚያደርግ ነው። የመፈራረጅ ነገር ሲነሳ በተለይ ጅዋር መሃመድ ላይ እየተደረገ ያለው የተለየ ነው። በመሠረቱ ጥምረቱን አስመልክቶ ጀዋር መሃመድ ያለው በርካቶች፣ ለምሳሌ ኤፍሬም ማዴቦ ካለው የተለየ አይደለም፣ ነገር ግን የ”ፋኖ” ሚዲያዎችና ፖለቲከኞች ሁለቱን ግለሠቦች የፈረጁባቸው መንገዶች ፈጽሞ ለእየቅል ናቸው። በጣም አስገራሚው ደግሞ የልደቱ አያሌው ነገር ነው። ርዕዮት ሚዲያ ላይ ቀርቦ ባደረገው ውይይት ላይ “ጀዋር ከአሁን በኋላ አብቅቶለታል፣ በተቃውሞ ፖለቲካ ውስጥ ቦታ የለውም!” በማለት ብያኔ ሲሰጥ ሳዳምጥ በጣም ነው የተገረምኩት። ልደቱ አያሌው፤ ከጥቂት አመታት በፊት “ልደቱ – ክህደቱ” እየተባለ ማንም የተቃውሞ ፖለቲከኛ ተወግዞ በማያውቅበት ደረጃ ተወግዞ የተተፋ ገጸ ባህሪይ አሁን ደርሶ የተቃውሞ ፖለቲከኝነትን ማእረግ ሰጪና ነሺ አድርጎ ራሱን ሲሾም መመልከት አጃዒብ የሚያሰኝ ነው።
ልደቱ ጎበዝና ደፋር ለአላማው በጽናት የቆመ ፖለቲከኛ ነው። ላመነበት የፖለቲካ አቋም ሽንጡን ገትሮ የሚከራከርና በዚህም ብዙ ሂሳብ የከፈለ ሰው ነው። ነገር ግን የልደቱ የፖለቲካ ስብዕና የተገነባውና የፖለቲካ ትርክቱ የተቃኘው ኢትዮጵያን ላለፉት መቶ አመታት ከአንዱ ግጭት ወደ ሌላው ግጭት እያንከባለለ አሁን ለገባንበት ውጥንቅጥ የፖለቲካ ቅርቃር ምንጭ በሆነው የአማራ የበላይነት ፖለቲካዊ እምነት ነው። አዎን ልደቱ ፊትለፊት ወጥቶ የአማራን የበላይነት አያቀነቅንም። እንዲያውም የአማራ የበላይነት አቀንቃኝ መሆኑ ከእርሱም ከራሱ የተደበቀበት ሊሆን ይችላል፤ ነገር ግን የፖለቲካ ትንታኔው ፖለቲካውን ከምን አውድ እንደሚቀርበው ያሳብቅበታል። ይህም ነው ጀዋርን “ተቃውሞ ፖለቲካ ውስጥ ቦታ የለውም!” ሲል ብያኔ እንዲሰጥ ምክንያት የሆነው።
ለልደቱና መሰሎቹ በአማራው ኤሊት የማይመራና የአማራውን ኤሊት ይሁንታ ያላገኘ የተቃውሞ እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ እውቅና የለውም።ልደቱ በተለይ በአብይ ዘመነ መንግሥት ተሰዶ የዲያስፖራውን ማህበረሰብ ከተቀላቀለ በኋላ ብልጽግናና መሪው ላይ በሚሰነዝራቸው የሰሉ ትችቶች ሳቢያ ቀድሞ “አይንህ ላፈር!” ብሎት ከነበረው ማህበረሰብ ጋር ከመታረቅ አልፎ እንደ ጠንካራ መሪ እየተገለጸ መምጣቱ አደጋ ላይ እየጣለው የመጣ ይመስለኛል። እንዲያውም ነገሩ የአዛዚልን ታሪክ ነው ያስታወሰኝ። ታሪኩ እንዲህ ነው፡ አዛዚል የሰይጣን የቀድሞ ስሙ ነው። አዛዚል በጣም ለፈጣሪው የተገዛ፣ ለፈጣሪው የቀረበ ፍጡር ነበር። አዛዚል በጣም አማኝ ብቻ ሳይሆን በጣም አዋቂም ነበር። በእውቀቱ የተነሳ መላዒካዎች(መላክቶች) ሳይቀሩ አንዳንድ ነገሮችን እንዲያብራራላቸው፣ በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ፈትዋ (ብያኔ) እንዲሰጣቸው ይጠይቁት ነበር አሉ። ታድያ አንድ ጊዜ መላዒካዎች አላህ ዘንድ ያለው መጽሃፍ ላይ “አንድ ለእኔ ቅርብ የሆነ አገልጋይ” ያምፃል የሚል ነገር ያነቡና በጣም ይደናገጣሉ። ከዚያ አዛዚል ዘንድ ሄደው “እንዲህ የሚል ነገር አነበብንና ይህ በአላህ ላይ የሚያምጽ ባሪያ ከእኛ መካከል እንዳይሆን ሰጋን” ሲሉ ያማክሩታል። አዛዚልም “እሱን ነገር እኔም አንብቤዋለሁ፣ አብሽሩ እናንተን የሚያሳስባችሁ ጉዳይ አይደለም” ይላቸዋል።መላዒካዎቹ ግን “ጉዳዩ አስጨንቆናልና ይህ አመጸኛ ፍጡር ከእኛ መካከል እንዳይሆን ዱዓ አድርግልን” ይሉታል። አዛዚልም እጁን ከፍ አድርጎ “አላህ ሆይ ይህ አመጸኛ ፍጡር ከመላዒካዎቹ መካከል እንዳይሆን ፈቃድህ ይሁን” ሲል ዱዓ ያደርግላቸዋል። አዛዚል፣ ምንም እንኳን አዋቂ መሆኑ በመላዒካዎች ሳይቀር የተመሰከረለት ፍጡር ቢሆንም ለመላዒካዎቹ ዱዓ ሲያደርግ ያ ፈጣሪው ላይ እንደሚያምጽ የተተነበየለት ፍጡር እርሱ ራሱ ሊሆን እንደሚችል ማሰብ አልቻለም ነበር። ምክንያቱም ፈጣሪውን በማምለክ፣ በኢባዳው፣ በእውቀቱ የተመሰከረለት ፍጡር ነዋ! እንዴት በዚህ ይጠረጠራል! በኋላ ላይ የሆነውን ሁላችሁም ታውቁታላችሁ፤ፈተናውን ወደቀ፣ ፈጣሪውም ላይ አመጸ።
ታዲያ ይሄንን የአዛዚልን ቂሳ (ትረካ) ሳዳምጥ አዕምሮዬ ውስጥ የመጣ አንድ ጥያቄ ነበር፤ ስዎች ብዙ ጊዜ ጥፋት ስናጠፋ ሰይጣን አሳሳተን እንላለን፣ እሺ ታድያ ሰይጣንንስ ማን አሳሳተው? ያገኘሁት መልስ ነፍስያው ወይንም በፈረንጆቹ ቋንቋ ኢጎው የሚል ነው። ኢጎ ወይንም ነፍስያ ከሰይጣን የከፋ ሃይል ነው። ሰይጣን ሲያሳስተን ከምንም በላይ ኢጎዋችንን ስለሚጠቀምበት ነው፣ ሰይጣንና ኢጎን መለየት በማንችልበት ደረጃ ተዛምደው ወደ ጥፋት እየወሰዱን ያሉት። ስለዚህ ጥንቃቄ ማድረግ ይመከራል። አንድ ሰው ፖለቲከኛ ሲሆን የፖለቲካ ትንታኔው የሚነሳው ከሚወግነው ሃይል አሰላለፍ ነው። ኢትዮጵያውያን በዜግነት አንድ ብንሆንም በብሄር በሃይማኖት የተለያየንና ለዘመናትም በመለዩዎቻችን ተቧድነን ስንቧቀስና ስነጨቋቆን ነው የኖርነው። ኢትዮጵያውያን እንደ ተጨማሪ መለዩዎቻችን አቅማችንም ለእየቅል ነው። ስለዚህም ኢትዮጵያ ውስጥ የሚከሰት ነገር በሙሉ የሚያስከትለው መዘዝ ሁሉም ላይ ተመሳሳይ ላይሆን ይችላል። አንድ ብቁ ፖለቲከኛ አላማውን ለማሳካት እይታውን ሰፋ በማድረግ በርካታ አውዶችን ከግምት ውስጥ ማስገባት ይኖርበታል። ይህንን ማድረግ ከተቻለ ትኩረቱ ከመፈራረጅ ይልቅ ሁሉንም ሊያስማማ የሚችል ቀመር ወደመፈለጉ ላይ ይሆናል። የሚበጀውም ይሄ ነው።
.
የእናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive
| 2 | Sin texto... | 296 |
| 3 | የአማጽያኑ ጥምረት ያስነሳው ማእበል!!
~~~
#የቢላል_ትዝብት
.
ህወሃት ከፋኖና ከኦላ ጋር ተጣምሮ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውጇል። ይሄንንም ተከትሎ በኢትዮጵያ ፖለቲካ መነቃቃት መታየት ጀምሯል። ጥምረቱን አንዳዶች ሲያወድሱት የብልጽግና ካድሬዎች ደግሞ እያጣጣሉት ነው። ሌሎች ደግሞ ጥምረቱ ያሉበትን ችግሮች በመጠቆም ችግሮቹ ሳይፈቱ የሚደረግ የይድረስ ይድረስ ጥምረት ኋላ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን አደጋ በመተበይ ጥምረቱ በጥንቃቄ እንዲታይ ሲያሳስቡ ይደመጣሉ። በሃገራችን ፖለቲካ በተደጋጋሚ እንደታዘብነው በጭፍን መደገፍ ወይንም በጭፍን መቃወም ካልሆነ በስተቀር ነገሮችን ከስሜት በራቀ መልኩ ተጨባጩን መተንተን በአንዱ ወይንም በሌላ ወገን አቀንቃኝነት ሲያስፈርጅም እያየን ነው።
.
ህወሃት፣ ፋኖና ኦላ በአንድ ወቅት በጠላትነት ተፈራርጀው በምላስና በነፍጥ ያለ ምህረት እርስ በርስ ሲጨፋጨፉ የነበሩ ከመሆናቸውም በላይ የአብይን የብልጽግና መንግሥት ከመገርሰ በዘለለ ምንም አይነት የጋራ የሆነ ራእይ የሌላቸው አማጽያን በመሆናቸው አሁን ደርሰው እየተጣመሩ መሆናቸውን ሲገልጹ ጥምረቱን ትኩረት ሰጥቶ መገምገም ተገቢ ብቻ ሳይሆን ግዴታም ነው ባይ ነኝ። እነኝህ አማጽያን ወገኖች እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ እርስ በርስ ሲዋጉ የነበሩ ብቻ ሳይሆን ነፍጥ ላማዘዟቸው ጉዳዮች እልባት ሳይሰጡ፣ እርዮቶቻቸውን ሳያጣጥሙና የጋራ የሆነ ራእይ ሳይኖራቸው ህብረታቸውን በአብይ መንግሥት ላይ ባላቸው ጥላቻ ላይ ብቻ መስርተው የሚፈጥሩት የጋራ ትግል ውጤታማ የመሆን እድሉ ላይ ብቻ ሳይሆን በለስ ቀንቷቸው የአብይን መንግሥት ቢገርሡ እንኳን ሃገሪቱ ሊገጥማት ስለሚችለው እድልና አደጋ መነጋገር ጨለምተኝነት ሳይሆን የሃላፊነት ስሜት ማሳያ ነው።
..
ሶስቱም ከመንግሥት ጋር ተፋላሚ ወገኖች የእየብሄሮቻቸውን ጥቅም ማስከበርን ተቀዳሚ አላማቸው አድርገው የሚንቀሳቀሱ እንደሆነ ይታወቃል። ፋኖን እንደምሣሌ ብንወስድ በግልጽ የአማራንና የኦርቶዶክስን የበላይነት ለማስመለስ እንደሆነ ነፍጥ ያነገበው በተለያዩ አጋጣሚዎች ሲገልጽ ቆይቷል። እንደሚታወቀው ደግሞ ኢትዮጵያ የበርካታ ብሄር ብሄረሰቦችና ሃይማኖቶች አገር ናት። ታድያ ይህን የመሰለውን የኮሎንያል ፖለቲካዊ ትርክት አንግቦ ከሚንቀሳቀስ ቀኝ አክራሪ አማፂ ጋር የሚፈጠር ጥምረት ሌሎች ህዝቦች ላይ የስጋት ስሜትን መጫሩ ተፈጥሮዋዊ ነው።
.
ብዙዎች ለአማፅያኑ አለመግባባት ዋናው እንቅፋት ሊሆን የሚችለው ጉዳይ የወልቃይትና የራያ ይገባኛል ጥያቄ እንደሆነ አድርገው አስተያየት ሲሰጡ ይደመጣሉ። ለእኔ ግን ችግሩ ከወልቃይትና ራያ በጣም የገዘፈ እንደሆነ ነው የሚሰማኝ። ፋኖ ልክ እንደ ነገሥታቱ ዘመን መላዋን ኢትዮጵያ ጠቅልሎ ለመግዛት ነው እያለመ ያለው። ይህ ህልሙ ደግሞ ሃገሪቱን ወደለየለት የእርስ በርስ እልቂት እንዳይወስዳት ከተፈለገ ገና ከአሁን አስፈላጊ የሆኑ እርምጃዎች መወሰዳቸውን ህዝብ አምኖ መቀበል ይኖርበታል። ፋኖ ገና ለገና ለታክቲክ ብሎ ከቀድሞ ደመኞቹ ጋር ጥምረት ፈጠርኩ ስላለ ብቻ አመኔታ ሊሰጠው አይችልም። ይልቅስ ህልሙን/ቅዠቱን መሬት ላይ ለማውረድ መሞከር ሳይሆን እንዳያስበው እንኳን መንገዱ ከአሁን መዘጋቱን ማረጋገጥ አስፈላጊ ነው።
.
እርግጥ ነው አማፅያኑ አንዳንድ ያሉባቸውን ችግሮች ለመፍታት የሚያስችል ቀመር እንዳዘጋጁና በቀመሩም ላይ እንደተስማሙ ሲገልጽ ይደመጣል፤ ነገር ግን ቀመሩ ምን እንደሚመስል ለህዝብ እይታ የቀረበ ነገር የለም። የህዝብን አመኔታ ማግኘት ካስፈለግ ደግሞ አማጽያኑ የተስማሙባቸውን ጉዳዮች ለህዝብ አቅርበው ህዝብ አስተያየት ሊሰጥባቸው ይገባል።ይሄ ጉዳይ የፖለቲካ እንጂ ወታደራዊ ጉዳይ ስላልሆነ በሚስጢር የሚያዝበት ምንም ምክንያት የለም። ስምምነት ካለ የስምምነቱ ጭብጥ ለህዝብ ይፋ ሊሆን ይገባል። አለበለዚያ ግን ኋላ ላይ “አለባብሰው ቢያርሱ” የሚለውን ተረት የመተረት እጣ ላያችን ላይ ሊወድቅ ይችላል የሚል ስጋት አለኝ።
የእናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive | 432 |
| 4 | Sin texto... | 383 |
| 5 | ~የካርታ ትረካና የእውነት ሚዛን፡ የአፍሪካ ትክክለኛ ስፋት በካርታ ላይ
~አፍሪካ በአዲሱ ካርታ አህጉር ሳይሆን ፕላኔት አክላለች!!
~~~
#RN05
.
ለዘመናት በዓለም ዙሪያ በትምህርት ቤቶች፣ በጽህፈት ቤቶችና በብዙኃን መገናኛዎች ስንጠቀምበት የቆየነውና "ሜርኬተር" (Mercator projection) በመባል የሚታወቀው የዓለም ካርታ፣ የአህጉራትን እውነተኛ መጠን በተሳሳተ መንገድ ሲያሳይ ቆይቷል። በተለይም ወደ ሰሜንና ደቡብ ዋልታዎች የተጠጉ ሀገራትን አጉልቶ በማሳየት፣ በምድር ወገብ (Equator) አካባቢ የሚገኙትን ደግሞ እጅግ አናሳ አድርጎ ያቀርባል። በዚህም ምክንያት አፍሪካ በካርታ ላይ ከትክክለኛ መጠኗ እጅግ አንሳ እንድትታይ ሆናለች።
.
በቅርብ ጊዜያት ትኩረት እያገኘ የመጣውና "ጋል-ፒተርስ" (Gall-Peters projection) ወይም የተለያዩ "እኩል ስፋት ያላቸው" (Equal-area projections) የዓለም ካርታዎች ይህንን ታሪካዊ ስህተት ለማስተካከል ያለሙ ናቸው።
.
የአፍሪካ እውነተኛ ስፋት በቁጥር:-
.
የካርታዎችን ስህተት ለማረም የሚደረገው ጥረት የአፍሪካን እውነተኛ ግዙፍነት በግልጽ ያሳያል፡
የቦታ ስፋት፡ አፍሪካ 30.3 ሚሊዮን ካሬ ኪሎ ሜትር ስፋት አላት። ይህም ከሰሜን አሜሪካ፣ ከቻይና፣ ከህንድ እና ከአብዛኛው የአውሮፓ አህጉር አጠቃላይ ስፋት ጋር እኩል ነው።
የተሳሳተ ንፅፅር፡ በባህላዊው የሜርኬተር ካርታ ላይ ግሪንላንድና አፍሪካ እኩል መጠን ያላቸው ይመስላሉ፤ በእውነቱ ግን አፍሪካ ግሪንላንድን በ14 እጥፍ ትበልጣለች። የካርታው ተፅዕኖ፡ አዲሶቹ የዓለም ካርታዎች አህጉራት ያላቸውን ትክክለኛ የመሬት ስፋት መጠን ይዘው እንዲቀርቡ በማድረግ የጂኦግራፊያዊ እውቀትን ሚዛን ያጠበቃሉ።
የአሜሪካ (USA) የተቃውሞ ምክንያትና ክርክሮች:-
በተመድ ጉባዬ ላይ የጋል-ፒተርስ ካርታ ሲተወወቅና ድምጽ ሲሰጥበት ብቸኛ የተቃወመች ሀገር አሜሪካ ነች:: የአሜሪካ የገጽታና ፖለቲካ የበላይነት ፍላጎት እንዳለ ሆኖ ፣ አዲሱ ካርታ በተለይም በአሜሪካ የጂኦግራፊ ባለሙያዎችና ተቋማት በኩል ተቃውሞ አስተናግዷል፡
.
የቅርጽ መዛባት፡ የባለሙያዎቹ ዋና ክርክር አዲሱ ካርታ የመሬትን ስፋት በትክክል ቢያስቀምጥም፣ የአህጉራቱን ትክክለኛ ቅርጽ (Shape) እጅግ ያበላሸዋል የሚል ነው። አህጉራቱ ወደ ታች የተጎተቱና የተዘረጉ ይመስላሉ።
የፖለቲካ ፍላጎት ስጋት፡ የጋል-ፒተርስ ካርታን የፈጠሩት አርኖ ፒተርስ ካርታውን ያስወወቁበት መንገድ "ዩሮሴንትሪክ (የአውሮፓ ማዕከል) አመለካከትን ለመታገል" በሚል የፖለቲካ አጀንዳ በመሆኑ፣ በርካታ የአሜሪካ ጂኦግራፈሮች "ሳይንሳዊ መፍትሔ ሳይሆን የፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ ነው" በማለት ተችተውታል።
.
የባለሙያዎች ስምምነት፡ የአሜሪካ የጂኦግራፊ ማህበር (AAG) እና የካርታ ስራ ማህበራት ድንቡልቡሏን ምድር ወደ ጠፍጣፋ ወረቀት ሲቀይሩ ስፋትንና ቅርጽን በአንድ ጊዜ ሙሉ በሙሉ ፍፁም አድርጎ ማሳየት አይቻልም በሚል፣ የትኛውንም ነጠላ ካርታ በብቸኝነት መጠቀምን ተቃውመዋል።
.
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) አቋምና እርምጃ:-
.
በሌላ በኩል የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና አካላቱ (በተለይም UNESCO) ለጉዳዩ የተለየ ምላሽ ሰጥተዋል፡ ኦፊሴላዊ አጠቃቀም፡ UNESCO እና በርካታ አለም አቀፍ የልማት ድርጅቶች የጋል-ፒተርስን ካርታ በይፋ በመቀበል በህትመቶቻቸውና በስብሰባ አዳራሾቻቸው መጠቀም ጀምረዋል። የእኩልነትና ፍትህ ምልክት፡ UN አዲሱን ካርታ የተቀበለበት ዋና ምክንያት ታዳጊ ሀገራትና የደቡብ ንፍቀ ክበብ አህጉራት (በተለይም አፍሪካና ደቡብ አሜሪካ) በዓለም አቀፍ ትረካ ውስጥ የሚገባቸውን ትክክለኛ ቦታና ግዙፍነት እንዲያገኙ ለማስቻል ነው።
ከትምህርት ጋር ማያያዝ፡ የካርታው አጠቃቀም በዓለም አቀፍ ደረጃ በትምህርት ስርዓት ውስጥ የነበረውን የታሪክና የጂኦግራፊ ማዘባት ለማስተካከል አዎንታዊ አስተዋፅኦ እንዳለው ድርጅቱ ያምናል።
.
የአዲሱ ካርታ ዘላቂ አስፈላጊነት:-
.
የካርታ ለውጥ የጂኦግራፊያዊ ትክክለኛነት ጉዳይ ብቻ አይደለም፤ የባህል፣ የፖለቲካና የስነ-ልቦና እይታንም ያካትታል። የአፍሪካን እውነተኛ ስፋት በትክክል ማሳየት ለወጣት ትውልድ ስለ ዓለም አቀፍ ስነ-መልካምድር ትክክለኛ እውቀት ከመስጠቱም በላይ፣ የአህጉሪቱን የተፈጥሮ ሀብትና የጂኦ-ፖለቲካዊ አቅም በትክክለኛው ሚዛን እንድናይ ይረዳል።
.
በአጠቃላይ፣ አዲሱ የዓለም ካርታ አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላትን እውነተኛ ቦታና ግዙፍነት በግልጽ የሚያሳይ አስፈላጊ እርምጃ ነው። አፍሪካ በእዲሱና ትክክለኛ በተባለው ካርታ እጅግ ገዝፋ ራሷን የቻለች ፕላኔት መስላለች ያለው፣ ከታች በምስሉ ላይ እንደሚታየው በውስጧ ሰሜን አሜሪካን፣ ቻይናን፣ መላ አውሮፓን ብሎም ህንድን አቅፋ ስታበቃ አሁንም እጅግ ሰፊ ምድር የሚተርፋት ሆና በመገኘነው።ከሷ አንጻር ሌሎች አህጉራት ሲታዩ ትናንሽ ከዋክብት መስለው በመከሰታቸው ነው።
.
የእናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive | 426 |
| 6 | Sin texto... | 352 |
| 7 | ? ትግሉ ኢህአዴግ ሳልሳዊን ለማዋለድ ወይንስ አዲስ ሥርዓት ለመመስረት?!
"ራስን በመስታወት የመመልከት" ፖለቲካ!
~~~~~~~~~~~
#የአቅል_አእምሮ_ትዝብት_ለRN05
.
ያኔ በፖለቲካው የለውጥ ሞቅታ ዘመን፣ “ኢህአዴግን ማፍረስ ሀገር ማፍረስ ነው፤ ስለዚህ ሀገሪቱ በሰላም እንድትቀጥል ከተፈለገ ሥርዓቱን እንዳለ አቅፎና ደግፎ መሪውን ብቻ መቀየር ይበቃል!” የሚለው አካሄድ አደገኛ መሆኑን ገና ከጥንስሱ ጀምሮ በፅኑ ስንቃወመው እንደነበር ይታወቃል። ለዚህም ግልፅ ማረጋገጫ የሚሆኑ በርካታ ማስረጃዎች በዚህ በፌስቡክ ገፃችን ላይ በፅሁፍ እንዲሁም በዩቲዩብ ስርጭታችን በስፋት ያነሳናቸውና የተሟገትንባቸው ሀሳቦች ለታሪክ ተሰነደው ይገኛሉ።
.
ሆኖም ግን ያ የሰጋነው አልቀረም። የመጀመሪያውን ኢህአዴግ አቀናጅቶ የነበረው አወቃቀር በደንብ ሳይፈተሽ፣ ከነበረው ጥፋትና ወንጀል ማፅዳት ሳይቻል፣ በኃላፊነት መጠየቅ የነበረባቸው አካላት ሳይጠየቁ ቀሩ። እንዲያውም በተቃራኒው “ለውጥ” በሚል ሽፋን ተለዋውጠውና ተቀባብተው ሁለተኛው ኢህአዴግ (ብልፅግና) ውስጥ በጥፋታቸው እንደቀጥሉ ሰፊ እድል ተመቻቸላቸው። "ራስን በመስታወት የመመልከት" አይነት ተመሳሳይ አካሄድ በመከተላችን ውጤቱ ዛሬ ሀገራችን ያለችበት ውስብስብ ቀውስ ሆነ።
.
ታሪክ ራሱን ሲደግም ደግሞ ይበልጥ ያሳዝናል። አሁንም በሀገራችን “ለውጥ ያስፈልጋል” የሚሉ ሀይሎች በተለይም እንደ አቶ ጃዋር መሐመድ እና መሰል አስተሳሰብ ያላቸው ፖለቲከኞች—ያንኑ የቀድሞውን የተሳሳተ አካሄድ ሲደግሙት ይስተዋላል። የብልፅግና ፓርቲ የሚያካሂዳቸውን ልማቶችም ሆነ የሚፈፅማቸውን ገዝፈው የወጡ ጥፋቶች በአንድ ግለሰብ (በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ) ትከሻ ላይ ብቻ የመጫን አዝማሚያ ይታያል።
.
የእነሱ መከራከሪያም፦ “ጠቅላይ ሚኒስትሩን መቀየር ብቻ ሀገርን ያድናል፤ አጠቃላይ የመንግስትን መዋቅርና ሥርዓት ተጠያቂ ማድረግ ወይም በሌላ ተቋማዊ ሥርዓት ለመተካት መታገል ግን ሀገረ-መንግስቱን ማፍረስ ነው” የሚል ይመስላል። ይህ ዓይነቱ አስተሳሰብ በርግጥም እጅግ የሚያስገርም ብቻ ሳይሆን ከቀደመው ስህተት አለመማርን ያሳያል።
.
እውነታው ግን ይህ ነው፦
.
የስም ለውጥ ተቋማዊ ለውጥ አይደለም፦ የኢህአዴግን ስም በመሰረዝ አዲስ ስም በመለጠፍ ብቻ የሚፈለገው መዋቅራዊና ፖለቲካዊ ለውጥ ሊመጣ አልቻለም።
.
አሁንም ቢሆን ግለሰብን ብቻ ነጥሎ መታገል አደጋው፦ ሙሉውን የብልፅግና መዋቅርና አስተሳሰብ ሳይነኩ፣ አንድን ግለሰብ ብቻ ነጥሎ በመታገልና በመጣል፣ አሁንም በዚያው ነባር ካቢኔና መዋቅር ሌላ ስም ሰጥቶ ለመቀጠል ማሰብ ከንቱ ልፋት ነው።
.
በመሰረታዊ ህዝባዊና ተቋማዊ ለውጥ ላይ ሳያተኩሩ፣ የፖለቲካ ተዋንያንን ብቻ በመቀያየር የሚደረግ ጉዞ ከ "ኢህአዴግ ዳግማዊ" ወደ “ኢህአዴግ ሳልሳዊ” ከመሸጋገር ባለፈ፤ እንዴት አዲስ አስተሳሰብ፣ ዴሞክራሲያዊ ባህል እና አስተማማኝ ተቋም ያለው ሀገራዊ ሥርዓት ሊፈጥር ይችላል?!
.
ስለዚህ ትግሉ ከሆነም መሆን ያለበት ግለሰቦችን የመቀየር ጨዋታ ላይ ያተኮረ ሳይሆን፣ የሀገሪቱን ስር የሰደደ የፖለቲካ ቀውስ የሚፈታ አዲስና ፍፁም ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የመገንባት አቅጣጫን መከተል ይኖርበታል። ለማለት ነው፡፡ ይሄው ነው!
.
የእናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive | 448 |
| 8 | Sin texto... | 435 |
| 9 | https://www.facebook.com/RNZeroFive/posts/pfbid02b5mV2H3y6WQtxc4PC5rQ8bt5JCDoBgPXSeTaFK8TW2yeaVomkneQuAFgqxrYN9QMl | 747 |
| 10 | https://www.facebook.com/RNZeroFive/posts/pfbid021yR43dEXHnNxKygraK41M4s68UN5VHUTG2qzg2vYTvW2xytLohBRGxMxwZPBWe31l | 904 |
| 11 | https://www.facebook.com/RNZeroFive/posts/pfbid02hKuXE9Z8NcthsSiaNYZDBkAmMqE3R6XxU5SSiTdePHwn79DpJ9bKRiehnUzcnCxUl | 830 |
| 12 | ዋይ! ኢራን "ክፉ" ናት!
~~~~~~
#የአቅል_አይምሮ_ትዝብት_ለRN05
.
| ኔታንያሁ- "ኢራን ልጄን ለመደምሰስ (ለመግደል) ሞክራ ነበር!" |
.
የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ኢራን በልጃቸው ላይ የግድያ ሙከራ አድርጋለች ሲሉ ከሰሱ። ኔታንያሁ ለቻናል 14 (Channel 14) የእስራኤል የቴሌቪዥን ጣቢያ በስልክ በሰጡት ቃል፦ «ኢራን ከልጆቼ አንዱን ኢላማ አድርጋ ነበር፤ አንደኛውን ልጄን ለመግደልም ሞክራለች» ብለዋል። በልጃቸው ዙሪያ የነበሩ የፀጥታ ኃይሎች ባይኖሩ ኖሮ ሙከራው ይሳካ እንደነበርም አክለው ገልጸዋል።
.
ኔታንያሁ ጥቃቱ የተቃጣበት የትኛው ልጃቸው እንደሆነ አልተናገሩም። በተጨማሪም የግድያ ሙከራው የት እንደተደረገ እና እንዴት ማከሸፍ እንደተቻለ የጠቆሙት ነገር የለም። የኤፒ (AP) የዜና ወኪል ላቀረበው ጥያቄም የኔታንያሁ ቢሮ ተጨማሪ ማብራሪያ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም።
አሜሪካ ከእስራኤል ጋር በመሆን በኢራን ላይ የከፈተችውን ጦርነት የጀመረችው በፌብሩዋሪ 28 ነበር። (ምንጭ፦ RND / AP)
.
እነሆ እኔም ይህንን ዜና ከናበብኩ በኋላ "ኢራን ክፉ ናት! ናትያንያሁና ቤተሰቦቻቸው ብሎም ጽዮናዊያን ለመግደል እንጂ ለመገደል እንዳልተፈጠሩ አታውቅምን?" ስል ራሴንም ጠየኩ ኢራንንም ታዘብኩ!
.
የእናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive | 1 120 |
| 13 | ከረዥም አመታት ኮማ በዃላ -በአውሮፓ የሙስሊሞች ኔት ወርክ ዳግም ተመሰረተ!
~~~~
ከ #RN05 ዝግጅት ክፍል
.
በአውሮፓ የኢትዮጵያውያን ሙስሊም ማህበራት ኔት ወርክ ምስረታ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ኖርዌይ ኦስሎ የደረስነው ጁመዓ ረፋዱ ላይ ነበር። የጁመዓ ሠላት ኦስሎ ከተማ ከሚገኙት ግዙፍ መሳጂዶች መካከል በአንደኛው ሠገድን። መስጂዱ ግዙፍና ሶስት ፎቆች ያሉት ቢሆንም ጢም ብሎ ሞልቶ ስለነበር በረንዳ ላይ ነበር ተጋፍተን የሠገድነው። በርካታ በቦታ ጥበት የተነሳ ያልሠገዱ ምዕመናን እኛ ሠግደን ቦታ እስከምንለቅላቸው በትዕግሥት ይጠብቁ ነበር። አሥር ደቂቃ ለማይሞላ ጊዜ ለቆምንበት የፓርኪን ከመቶ ክራውን በላይ ከፍለንና በውድነቱ እየተደመምን የኔት ወርኩ ምሥረታ ጉባኤ ወደሚካሄድበት ቦታ አመራን።
.
አዳራሹ በታዳሚዎች ተሞልቶ አቶ አብዬ ያሢን ኔት ወርኩ ምስረታ ዙርያ ገለጻና ማብራሪ ለመስጠት ሲያቆበቁብ ደረስን። አዳራሹ ውስጥ በርካታ የተለመዱ ፊቶች ይታያሉ። የዩኬ ጀመዓ የአዳራሹን ቀኝ ክንፍ ወረውታል። ስዊድኖች መሃል ለመሃል እመድረኩ ፊት አፍጠዋል። በአዳራሹ ግራ ክንፍ የኖርዌይ ጀመዓ አባላት በብዛት ተኮልኩለዋል። ዙሪያውን ደግሞ እህቶች ከበውታል። አብዛኛው ታዳሚ የኖርዌይ ጀመዓ አባላይ ቢሆኑም ሁሌም እስላማዊ እንቅስቃሴዎች ባሉባቸው ስፍራዎች በሙሉ ግንባር ቀደም ከሆኑት ከእንግሊዝና ከስዊድን ጀመዓዎችም በርካቶች ተገኝተዋል። ቁጥራቸው የእንግሊዝና ከስዊድን ጋር ባይስተካከልም የማይናቅ ቁጥር ያላቸው የጉባኤ ተሳታፊዎች ከቤልጂየም፣ ከሆላንድና ፊንላንድ መጥተዋል። አንዳንድ ከጀርመንና ሌሎች የአውሮፓ አገራት የመጡም ታዳሚዎችም ነበሩ።
.
አብዬ ያሲን የኔትወርኩ መመሥረት አስፈላጊ ሆኖ የተገኘበትን ምክንያት ካስረዳና ድርጅታዊ መዋቅሩም ምን ሊመስል እንደሚችል ካብራራ በኋላ መድረኩ ለጥያቄ ክፍት ሲሆን ከዚህ ቀደም ተመስርቶ የነበረው በአውሮፓ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ኔት ወርክ የፈረሰበትን ምክንያት እንዲብራራ ተጠየቀ። የቀሞው ኔት ወርክ የመጀመርያ ጉባኤውን ያደረገው እንደፈረንጆቹ በ2009 በስዊድን አገር ጉተንበርግ ከተማ ነበር። አብዛኞቹን አሁን በቅርበት የምናውቃቸው ወንድሞች ለመጀመርያ ጊዜ በአካል ያገኘናቸው በዚያን ወቅት ነበር። በዚያ በጉተንበርጉ ጉባኤ ላይ ለመጀመርያ ጊዜ በአካል ካገኘናቸው ወንድሞች መካከል አንዳንዶች ወደ አኪራ ሄደዋል፣ አላህ ምህረቱን ያውርድላቸው። አንዳንዶች ጡረታ ውጥተው በአገር ቤትና አውሮፓ ተመላላሾች ሆነዋል። አንዳንዶች አባት ከመሆን ዘለው አያቶች ሆነዋል። በርካቶች ግን በዚህም ጉባኤ ላይ ታድመዋል።ይህ ደግሞ በበኩሉ ምንም እንኳን የመጀመርያው ኔት ወርክ አስደሳች ትዝታዎችን ጥሎ ቢከስምም አባላቱ ግን በእየጀመዓዎቻቸው የነበሯቸው ተሳትፎዎች እንደቀጥሉ መሆናቸውን ማሳያ ስለነበር አስደሳችና ተስፋ ሰጪ ስሜትን የጫረ ነበር። ምንም እንኳን የመጀመርያው ኔት ወርክ ስኬቶችና ክስመት የፈጠሩት ጠንካራ አወንታዊና አሉታዊ ስሜቶች የነበሩ ቢሆንም እነኝህ የቀድሞ አባላት አሁንም በድጋሚ የኔት ወርኩ ምስራታ ላይ መታደማቸው ብቻ ሳይሆን ለመስረታውም ስኬት ሲያሳዩ ያስተዋነው መነሳሳ ምዕመናኑ ኔት ወርኩን ምን ያህል እንደሚፈገው ግልጽ ጠቋሚ ነበር።
.
ምንም እንኳን በአውሮፓ የሙስሊሞች ኔት ወርክ ምስረታ ከዚህም በፊት ተሞክሮና መልካምም ስኬትን አስመዝግቦ በአንዳንድ ምክንያቶች ቢከስምም ኦስሎ ላይ የተመሰረተው አዲሱ ኔት ወርክ ቀደሞ ከነበረው የሚለይባቸው ባህርያት በዝርዝር ገለጻ ተሰጠባቸው። በተለይ አሁን በዲያስፖራውም ሆነ በሃገራችን የሙስሊሙ ሁኔታ ከዚህ ቀደም ከነበረው የሚለይባቸው ባህሪያት አሁን ለተፈጠረው አዲስ ኔት ወርክ የሚፈጥራቸው እድሎችና ተግዳሮቶች በስፋት ተዳሰሱ።
.
የኔት ወርኩን ምስረታ አስመልክቶ የቀረበው ዝግጅት ከተጠናቀቀ በኋላ በምስረታ ጉባኤው ላይ እንዲሳተፉ ተጋብዘው የመጡት ኡስታዝ አቡበከርና ሸይክ መሃመድ ጀማል አጎናፍ ከኢትዮጵያ፣ እንዲሁም ሸይክ ሰይፈሊሳላም ከአሜሪካ በእየተራ እየተነሱ ለታዳሚው ምክር ሲሰጡ አመሸን። እኔ በበኩሌ ከምክሩ ይልቅ ለረጂም ጊዜ ያላገኘኋቸውን ወዳጆቼ አግኝቼ ተቃቅፌ ጠረቤዛ እመካከላችን አድርገን ስናወጋ ማምሸቱን እመርጥ ነበር፣ ነገር ግን ያ አልሆነው።ምክሩ በላይ በላዩ ሲደራረብ በጣም ስለመሸ እራት ከተበላ በኋላ ጉዞ ወደ ማደሪያችን ሆነ።
.
የማደርያ ቦታው ጉባኤው ከተካሄደበት አዳራች 46 ኪሎ ሜትሮች ገደማ ርቆ የሚገኝ ቦታ ነበር። እኛ መኪና ነበረን። መኪና ለሌቸው የኦስሎ ጀመዓ መጓጓዣ አዘጋጅቶ ስለነበር የሎጂስቲክ ችግር አልነበረም። የተዘጋጀው ማረፊያ ቦታም ምቹና ንጽህናውን የጠበቀ ነበር። ሆኖም ማደሪያችን ስንደርስ ግማሽ ለሊት ደርሶ ስለነበርና በማግሥቱ ቅዳሜ በሚደረገው ጉባኤ ላይ በጊዜ መገኘት የግድ ስለሆነ ከመተኛት ሌላ አማራጭ አልነበረንም።
የቅዳሜው የጉባኤ ቀን በርካታ የተለያዩ ዝግጅቶች የተስተናገዱበት ነበር። የደዓዋ ፕሮግራሞች፣ ወርክ ሾፕና ውይይቶች ሲደረጉ ካመሸን በኋላ የጉባኤው ማሳረጊያ የሆነው የኦስሎ ጀመዓ የራሱን መስጂድ ለማቋቋም የጀመረውን እንቅስቃሴ ለማገዝ የሚያስችል የፈንድ ሬዚንግ ዝግጅት ነበር። ዝግጅቱ በሸይክ ሰይፈል ኢስላም ከአሜሪካና ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ከኢትዮጵያ የተመራ ሲሆን ከሁለት ሚሊዮን ክራውን በላይ የተሰበሰበበትና በድምቀት የተከናወነ ነበር።
.
የኔት ወርኩ ጉባኤ የምስረታ መሆኑን ከግምት ውስጥ ስናስገባ በብዙ መልኩ ስኬታማ ነበር ማለት ይቻላል።በተለይ የጉባኤው አዘጋጅ የኦስሎ ጀመዓ እንግዶቻቸውን ያስተናገዱበት መንገድ እንከን የማይወጣለት ነበር። የማረፊያ ቦታው፣ የመጓጓዣ አገልግሎቱ ሎጂስቲኩ በግሩም ሁኔት የተከናወነ ነበር። ምግብን በተመለከት የኖርዌይ ጀመዓ የእንግዶቻቸውን ፍላጎት ለማርካት የሄዱበት ርቀት በሌላው የአውሮፓ ጀመዓ ሊኮረጅ እጅግ የሚከብድ፣ የዝግጅቱን ደረጃ ከቁመት አርቆ የሠቀለ ነበር ስል ማጋነን ከመሰላችሁ ሌሎች በጉባኤው ላይ የተሳተፉ ወንድሞችና እህቶችን ጠይቃችሁ ማረጋገጥ ትችላላችሁ ከማለት በዘለለ የምጨምረው የለኝም።
እኔ በበኩሌ ኔት ወርኩ በድጋሚ መመስረቱ መልካም ዜና ሆኖ ነው ያገኘሁት። ኔት ወርኩ ፍላጎቱን ከአቅሙ ጋር አመጣጥኖ፣ የተወሰኑ በተጨባጭ ሊተገበሩ የሚችሉ ሥራዎች ላይ አተኩሮ ከሠራ ውጤታማ ሊሆን እንደሚችል አምናለሁ። በአውሮፓ ያለው ሙስሊም ማህበረሰብ የጋራ የሆኑ ፍላጎቶችና ተግዳሮቶች አሉት ። እነኝህን ፍላጎቶቹንና ተግዳሮቶችቹን በስኬት ለመወጣት በኔት ወርኩ መተሳሰሩ በርካታ ጠቀሜታዎች አሉት። አሁን የኔት ወርኩ አመራር ማድርግ የሚጠበቅበት እነኝህን ጠቀሜታዎች ተጨባጭ በሆነ መልኩ ለአባላቱ ማሳየት ነው።
.
ከዚህ ሁሉ ሂደት በዃላ በስተመጨረሻም በእለተ ቅዳሜ ኦገስት 22/2026 ከተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት በመጡ በ 8 ያህል ማህበራት ፊርማ ኔትወርኩ በኦስሎ ከተማ ዳግም በይፋ የተመሰረት ሲሆን፣ የቀጣዩ አመት ጉባኤውን ደግሞ በአውሮፓዊትዋ ዋና መዲና በቤጅየም ሀገር እንደሚደረግ ታውጆ መስራች ጉባዬው ተጠናቋል። | 1 086 |
| 14 | Sin texto... | 672 |
| 15 | Sin texto... | 736 |
| 16 | ጽንፈኛው የእስራኤል ሚኒስትር አወዛጋቢ ግግር ሌላ ዓለም አቀፍ ውግዘት አስከተለ
~~~~~~
#RN05
.
በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት ከርሮ በቀጠለበት በዚህ ወቅት፣ የእስራኤል ጽንፈኛው የብሔራዊ ጸጥታ ሚኒስትር ኢታማር ቤን-ግቪር በጋዛ ላይ የሰጡት ከባድ እና አወዛጋቢ አስተያየት ዓለም አቀፍ አጀንዳ ሆኗል።
.
ሚኒስትሩ በጋዛ ሰርጥ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ በሰጡት ቃለ መጠይቅ ላይ፦ «ሊኖሩ የማይገባቸው ሰዎች፤ እነሱ ሰዎችም አይደሉም!» ማለታቸው ከፍተኛ አዲስ ቁጣና ውግዘት አስከትሏል።
.
የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እና አለም አቀፍ ተቋማት እንደሚያስረዱት፣ የቤን-ግቪር አገላለጽ የፓለስታናውያንን ሰብአዊነት ሙሉ በሙሉ የሚክድ እና የዘር ማጽዳት ወንጀልን የሚያበረታታ አደገኛ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለም ነጸብራቅ ነው።
,
ጽንፈኛው ሚኒስትር በጋዛ ላይ የሚወሰደው ወታደራዊ እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት እና የክልሉ ነዋሪዎች ላይ የሚደርሰው ስቃይ ትክክለኛ እርምጃ መሆኑን ለማሳየት የሞከሩባቸው ሐረጎች በሰላም ድርድር ላይ ትልቅ ጥላ አጥልተዋል።
.
ይህ አባባል የእስራኤልን መንግሥት የውጪ ግንኙነት አቋም የበለጠ አስቸጋሪ ያደረገው ሲሆን፣ የጺዮናዊትዋ አፓርታይድ እና የጦር ወንጀለኞች ሃገር የሆነችው የእስራኤል አጋር ሀገራት ጭምር በንግግሩ ላይ ያላቸውን ጽኑ ተቃውሞ እያሰሙ ይገኛሉ።
.
ተንታኞች እንደሚሉት፣ በኃተታ የተሞሉና የሰዎችን ሕይወት ዋጋ የሚቀንሱ እንዲህ ያሉ ጽንፈኛ መግለጫዎች በቀጣናው ያለውን ዘላቂ ሰላም እና መፍትሔ እጅግ አዳጋች እያደረጉት ይገኛሉ።
.
የብሔራዊ ጸጥታ ሚኒስትር ኢታማር ቤን-ግቪር በጽንፈኛ አቅዋማቸው የሚታወቁ ሲሆን ብዙ አለም አቀፍ ህጎች ጋዛ ዉስጥ የጦር ወንጀል ለመፈጸሙ እንደማሳያ ከሚጠቀሱ የእስራኤል ባለስልጣናት መካከል ከዋነኞቹ ይመደባሉ፡፡ በቅርቡ በእስራኤል ዉስጥ ያሉና ፍልስጤማዊያን በብዛት የታሰሩበት እስር ቤት ዙርያው በአዞዎች እንዲከበብ ሃሳብ ማቅረባቸው ይታወሳል፡፡
.
የእናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive | 1 163 |
| 17 | Sin texto... | 772 |
| 18 | ስለ #አዲስ_አበባ በጨዋ ደምብ እንወያይ!
~~~~~
1.ለመሆኑ የአዲስ አበቤ ስነ ልቦና ምን አይነት ነው?
2. አዲስ አባባን በአንድ ብሄር ወይንም በአንድ እምነት አልያም በአንድ ባህል መመደብና መፈረጅ ይቻላልን?!
3.ካልሆነስ አስተዳደራዊ መፍትሄው ምን ይመስሎታል?
.
ሀሳብዎን ያካፍሉን!
.
#የአቅል_አይምሮ_ትዝብት_ለRN05 | 1 129 |
| 19 | የሰው ልጆች ሕሊና የሚመረመርበት አሳዛኝ ምዕራፍ፡ አንዋር መስጂድ እና ሊቀለበስ የማይገባው የሞራል ኃላፊነት
~~~~
#የአቅል_አይምሮ_ትዝብት_ለRN05
.
በዚህ ወንድማችን ላይ የተፈጸመው ኢ-ሰብአዊ እና አጸያፊ ድርጊት የሰብአዊነትን ወሰን የተሻገረ፣ ሕሊናን የሚወቅስ ከባድ ወንጀል ነው። ከጅማ ወደ አዲስ አበባ የመጣ ፣ ሀገር የማያውቅ፣ ለሐይማኖታዊ ትምህርት በማለዳ ወደ ሐረር ለመጓዝ በመዘጋጀት ላይ የነበረ እና መሄጃ ቦታ በማጣቱ ብቻ በግቢው ውስጥ ሌሊቱን እንዲያሳልፍ አጥብቆ የለመነ ደረሳ፣ ጠለላ ሊሰጠው ሲገባ በወከባ ከምፕስጅዱ ግቢ በመባረሩ የጭካኔ ሰለባ ሆኗል።
ለሊቱን ሜዳ ላይ እንዳያሳልፍ አዋክበው ወደ ውጭ የጣሉት የመስጅዱ የጥበቃ አካላት፣ እንዲሁም ይህንን ተከላካይ የሌለውን ወንድም አራት ሆነው በመክበብ አስገድደው የደፈሩት የሰው አውሬዎች የፈጸሙት ድርጊት ከባድ የሞራል እና የሕግ ተጠያቂነትን የሚያነሳ ነው።
በመሠረቱ የሐይማኖት ተቋማት እና መስጂዶች መሠረታዊ መገለጫቸው ለተቸገረ መጠለያ፣ ለተፈናቀለ መታደጊያ እና ለአደጋ ተጋላጭ ወገኖች ሁልጊዜም ክፍት መሆን መሆኑ ይታወቃል። ግቢው ውስጥ ወርቅ፣ አልማዝ ወይም ሌላ ቁሳዊ ሀብት እንደሌለበት የሚታውወቅ ነው ፤በመሆኑም "አደጋ ላይ ነኝ፣ አትርፈኝ" ለሚሉ እንግዶች የአንድ ሌሊት መጠለያ መሆን ካልቻለ፣ የተቋሙ ስዋዊ አገልግሎቱ ትርጉሙን ይስታል። በመሆኑም በዚህ አሳዛኝ ድርጊት በወቅቱ የነበሩት የአንዋር መስጂድ አስተዳደር እና ኃላፊዎች የሞራል እና የተቋማዊ ተጠያቂነት ባለቤት መሆናቸውን አበክሮ መናገር ያስፈልጋል።
* ለተጎጂው ወንድማችን፡ ጉዳዩ ከዓመታት በፊት የተፈጸመ ቢሆንም፣ የደረሰብህን ዘግናኝ ግፍና በደል ብሎም ያንን ተከትሎ ለአመታት ያሳለፍከእን መከራ ባለን ተቋም (መስጂድ) አማካኝነት ማስቀረት ባለመቻላችን እንደ ማህበረሰብ ጥልቅ ጸጸት ይሰማናል። አላህ ጽናቱንና ብርታቱን ይስጥህ!
በዚህ አጋጣሚ "ከሰማነው ይልቅ ያልሰማነው እንደሚበልጥ በመገመት" ሀገራችን በአሁኑ ወቅት በምን ዓይነት ኢ-ሞራላዊና እጅግ አደገኛ ሁናቴ ውስጥ እንደምትገኝ በጥልቀት መገንዘብ ይገባል። እንዲህ ያሉ ዘግናኝ ግፎችን በአስተማማኝ ሁኔታ ለመታገል እና የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅ ጠንካራ፣ ፍትሃዊ እና ውጤታማ የሕግ ዝግጅት ማድረግ ወሳኝ መሆኑን አበክረን ልናስብበት ይገባል።
.
የእናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive | 1 002 |
| 20 | .
የእናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive | 787 |
