RN.05 - Channel
رفتن به کانال در Telegram
ከኢትዮጵያና አዉሮፓ የሚተላለፍ የራድዮ ፕሮግራም አዲሱን ዩቱብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ: https://www.youtube.com/c/RN05Channel ፌስቡክ ገፃችንን like ያድርጉ: https://www.facebook.com/RNZeroFive/ https://twitter.com/RNZeroFive Support Us: http://bit.ly/3c09jfJ https://RNZeroFive.com
نمایش بیشتر2 345
مشترکین
+524 ساعت
+157 روز
+2330 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
اوت '26
اوت '26
+68
در 0 کانالها
ژوئیه '26
+37
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '26
+34
در 0 کانالها
Get PRO
مه '26
+37
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '26
+45
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '26
+74
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '26
+28
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '26
+28
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '25
+37
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '25
+78
در 1 کانالها
Get PRO
اکتبر '25
+76
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '25
+49
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '25
+39
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '25
+105
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '25
+133
در 0 کانالها
Get PRO
مه '25
+62
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '25
+103
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '25
+68
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '25
+56
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '25
+93
در 1 کانالها
Get PRO
دسامبر '24
+45
در 1 کانالها
Get PRO
نوامبر '24
+61
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '24
+175
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '24
+24
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '24
+32
در 1 کانالها
Get PRO
ژوئیه '24
+12
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '24
+47
در 0 کانالها
Get PRO
مه '24
+111
در 1 کانالها
Get PRO
آوریل '24
+66
در 1 کانالها
Get PRO
مارس '24
+53
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '24
+148
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '24
+126
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '23
+146
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '23
+427
در 1 کانالها
Get PRO
اکتبر '23
+29
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '23
+12
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '23
+29
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '23
+11
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '23
+13
در 0 کانالها
Get PRO
مه '23
+4
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '23
+13
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '23
+40
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '23
+5
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '23
+2
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '22
+36
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '22
+4
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '22
+29
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '22
+12
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '22
+120
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '22
+159
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '22
+9
در 0 کانالها
Get PRO
مه '22
+89
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '22
+9
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '22
+3
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '22
+3
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '22
+5
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '21
+94
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '21
+25
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '21
+7
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '21
+3
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '21
+8
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '21
+39
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '21
+24
در 0 کانالها
Get PRO
مه '21
+1 067
در 0 کانالها
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 26 اوت | +5 | |||
| 25 اوت | +7 | |||
| 24 اوت | +7 | |||
| 23 اوت | +1 | |||
| 22 اوت | 0 | |||
| 21 اوت | +1 | |||
| 20 اوت | +3 | |||
| 19 اوت | +2 | |||
| 18 اوت | +1 | |||
| 17 اوت | +1 | |||
| 16 اوت | +1 | |||
| 15 اوت | 0 | |||
| 14 اوت | +3 | |||
| 13 اوت | +5 | |||
| 12 اوت | +6 | |||
| 11 اوت | +4 | |||
| 10 اوت | 0 | |||
| 09 اوت | +3 | |||
| 08 اوت | +3 | |||
| 07 اوت | +2 | |||
| 06 اوت | +2 | |||
| 05 اوت | +1 | |||
| 04 اوت | 0 | |||
| 03 اوت | +4 | |||
| 02 اوت | +4 | |||
| 01 اوت | +2 |
پستهای کانال
ዋይ! ኢራን "ክፉ" ናት!
~~~~~~
#የአቅል_አይምሮ_ትዝብት_ለRN05
.
| ኔታንያሁ- "ኢራን ልጄን ለመደምሰስ (ለመግደል) ሞክራ ነበር!" |
.
የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ኢራን በልጃቸው ላይ የግድያ ሙከራ አድርጋለች ሲሉ ከሰሱ። ኔታንያሁ ለቻናል 14 (Channel 14) የእስራኤል የቴሌቪዥን ጣቢያ በስልክ በሰጡት ቃል፦ «ኢራን ከልጆቼ አንዱን ኢላማ አድርጋ ነበር፤ አንደኛውን ልጄን ለመግደልም ሞክራለች» ብለዋል። በልጃቸው ዙሪያ የነበሩ የፀጥታ ኃይሎች ባይኖሩ ኖሮ ሙከራው ይሳካ እንደነበርም አክለው ገልጸዋል።
.
ኔታንያሁ ጥቃቱ የተቃጣበት የትኛው ልጃቸው እንደሆነ አልተናገሩም። በተጨማሪም የግድያ ሙከራው የት እንደተደረገ እና እንዴት ማከሸፍ እንደተቻለ የጠቆሙት ነገር የለም። የኤፒ (AP) የዜና ወኪል ላቀረበው ጥያቄም የኔታንያሁ ቢሮ ተጨማሪ ማብራሪያ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም።
አሜሪካ ከእስራኤል ጋር በመሆን በኢራን ላይ የከፈተችውን ጦርነት የጀመረችው በፌብሩዋሪ 28 ነበር። (ምንጭ፦ RND / AP)
.
እነሆ እኔም ይህንን ዜና ከናበብኩ በኋላ "ኢራን ክፉ ናት! ናትያንያሁና ቤተሰቦቻቸው ብሎም ጽዮናዊያን ለመግደል እንጂ ለመገደል እንዳልተፈጠሩ አታውቅምን?" ስል ራሴንም ጠየኩ ኢራንንም ታዘብኩ!
.
የእናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive
| 2 | ከረዥም አመታት ኮማ በዃላ -በአውሮፓ የሙስሊሞች ኔት ወርክ ዳግም ተመሰረተ!
~~~~
ከ #RN05 ዝግጅት ክፍል
.
በአውሮፓ የኢትዮጵያውያን ሙስሊም ማህበራት ኔት ወርክ ምስረታ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ኖርዌይ ኦስሎ የደረስነው ጁመዓ ረፋዱ ላይ ነበር። የጁመዓ ሠላት ኦስሎ ከተማ ከሚገኙት ግዙፍ መሳጂዶች መካከል በአንደኛው ሠገድን። መስጂዱ ግዙፍና ሶስት ፎቆች ያሉት ቢሆንም ጢም ብሎ ሞልቶ ስለነበር በረንዳ ላይ ነበር ተጋፍተን የሠገድነው። በርካታ በቦታ ጥበት የተነሳ ያልሠገዱ ምዕመናን እኛ ሠግደን ቦታ እስከምንለቅላቸው በትዕግሥት ይጠብቁ ነበር። አሥር ደቂቃ ለማይሞላ ጊዜ ለቆምንበት የፓርኪን ከመቶ ክራውን በላይ ከፍለንና በውድነቱ እየተደመምን የኔት ወርኩ ምሥረታ ጉባኤ ወደሚካሄድበት ቦታ አመራን።
.
አዳራሹ በታዳሚዎች ተሞልቶ አቶ አብዬ ያሢን ኔት ወርኩ ምስረታ ዙርያ ገለጻና ማብራሪ ለመስጠት ሲያቆበቁብ ደረስን። አዳራሹ ውስጥ በርካታ የተለመዱ ፊቶች ይታያሉ። የዩኬ ጀመዓ የአዳራሹን ቀኝ ክንፍ ወረውታል። ስዊድኖች መሃል ለመሃል እመድረኩ ፊት አፍጠዋል። በአዳራሹ ግራ ክንፍ የኖርዌይ ጀመዓ አባላት በብዛት ተኮልኩለዋል። ዙሪያውን ደግሞ እህቶች ከበውታል። አብዛኛው ታዳሚ የኖርዌይ ጀመዓ አባላይ ቢሆኑም ሁሌም እስላማዊ እንቅስቃሴዎች ባሉባቸው ስፍራዎች በሙሉ ግንባር ቀደም ከሆኑት ከእንግሊዝና ከስዊድን ጀመዓዎችም በርካቶች ተገኝተዋል። ቁጥራቸው የእንግሊዝና ከስዊድን ጋር ባይስተካከልም የማይናቅ ቁጥር ያላቸው የጉባኤ ተሳታፊዎች ከቤልጂየም፣ ከሆላንድና ፊንላንድ መጥተዋል። አንዳንድ ከጀርመንና ሌሎች የአውሮፓ አገራት የመጡም ታዳሚዎችም ነበሩ።
.
አብዬ ያሲን የኔትወርኩ መመሥረት አስፈላጊ ሆኖ የተገኘበትን ምክንያት ካስረዳና ድርጅታዊ መዋቅሩም ምን ሊመስል እንደሚችል ካብራራ በኋላ መድረኩ ለጥያቄ ክፍት ሲሆን ከዚህ ቀደም ተመስርቶ የነበረው በአውሮፓ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ኔት ወርክ የፈረሰበትን ምክንያት እንዲብራራ ተጠየቀ። የቀሞው ኔት ወርክ የመጀመርያ ጉባኤውን ያደረገው እንደፈረንጆቹ በ2009 በስዊድን አገር ጉተንበርግ ከተማ ነበር። አብዛኞቹን አሁን በቅርበት የምናውቃቸው ወንድሞች ለመጀመርያ ጊዜ በአካል ያገኘናቸው በዚያን ወቅት ነበር። በዚያ በጉተንበርጉ ጉባኤ ላይ ለመጀመርያ ጊዜ በአካል ካገኘናቸው ወንድሞች መካከል አንዳንዶች ወደ አኪራ ሄደዋል፣ አላህ ምህረቱን ያውርድላቸው። አንዳንዶች ጡረታ ውጥተው በአገር ቤትና አውሮፓ ተመላላሾች ሆነዋል። አንዳንዶች አባት ከመሆን ዘለው አያቶች ሆነዋል። በርካቶች ግን በዚህም ጉባኤ ላይ ታድመዋል።ይህ ደግሞ በበኩሉ ምንም እንኳን የመጀመርያው ኔት ወርክ አስደሳች ትዝታዎችን ጥሎ ቢከስምም አባላቱ ግን በእየጀመዓዎቻቸው የነበሯቸው ተሳትፎዎች እንደቀጥሉ መሆናቸውን ማሳያ ስለነበር አስደሳችና ተስፋ ሰጪ ስሜትን የጫረ ነበር። ምንም እንኳን የመጀመርያው ኔት ወርክ ስኬቶችና ክስመት የፈጠሩት ጠንካራ አወንታዊና አሉታዊ ስሜቶች የነበሩ ቢሆንም እነኝህ የቀድሞ አባላት አሁንም በድጋሚ የኔት ወርኩ ምስራታ ላይ መታደማቸው ብቻ ሳይሆን ለመስረታውም ስኬት ሲያሳዩ ያስተዋነው መነሳሳ ምዕመናኑ ኔት ወርኩን ምን ያህል እንደሚፈገው ግልጽ ጠቋሚ ነበር።
.
ምንም እንኳን በአውሮፓ የሙስሊሞች ኔት ወርክ ምስረታ ከዚህም በፊት ተሞክሮና መልካምም ስኬትን አስመዝግቦ በአንዳንድ ምክንያቶች ቢከስምም ኦስሎ ላይ የተመሰረተው አዲሱ ኔት ወርክ ቀደሞ ከነበረው የሚለይባቸው ባህርያት በዝርዝር ገለጻ ተሰጠባቸው። በተለይ አሁን በዲያስፖራውም ሆነ በሃገራችን የሙስሊሙ ሁኔታ ከዚህ ቀደም ከነበረው የሚለይባቸው ባህሪያት አሁን ለተፈጠረው አዲስ ኔት ወርክ የሚፈጥራቸው እድሎችና ተግዳሮቶች በስፋት ተዳሰሱ።
.
የኔት ወርኩን ምስረታ አስመልክቶ የቀረበው ዝግጅት ከተጠናቀቀ በኋላ በምስረታ ጉባኤው ላይ እንዲሳተፉ ተጋብዘው የመጡት ኡስታዝ አቡበከርና ሸይክ መሃመድ ጀማል አጎናፍ ከኢትዮጵያ፣ እንዲሁም ሸይክ ሰይፈሊሳላም ከአሜሪካ በእየተራ እየተነሱ ለታዳሚው ምክር ሲሰጡ አመሸን። እኔ በበኩሌ ከምክሩ ይልቅ ለረጂም ጊዜ ያላገኘኋቸውን ወዳጆቼ አግኝቼ ተቃቅፌ ጠረቤዛ እመካከላችን አድርገን ስናወጋ ማምሸቱን እመርጥ ነበር፣ ነገር ግን ያ አልሆነው።ምክሩ በላይ በላዩ ሲደራረብ በጣም ስለመሸ እራት ከተበላ በኋላ ጉዞ ወደ ማደሪያችን ሆነ።
.
የማደርያ ቦታው ጉባኤው ከተካሄደበት አዳራች 46 ኪሎ ሜትሮች ገደማ ርቆ የሚገኝ ቦታ ነበር። እኛ መኪና ነበረን። መኪና ለሌቸው የኦስሎ ጀመዓ መጓጓዣ አዘጋጅቶ ስለነበር የሎጂስቲክ ችግር አልነበረም። የተዘጋጀው ማረፊያ ቦታም ምቹና ንጽህናውን የጠበቀ ነበር። ሆኖም ማደሪያችን ስንደርስ ግማሽ ለሊት ደርሶ ስለነበርና በማግሥቱ ቅዳሜ በሚደረገው ጉባኤ ላይ በጊዜ መገኘት የግድ ስለሆነ ከመተኛት ሌላ አማራጭ አልነበረንም።
የቅዳሜው የጉባኤ ቀን በርካታ የተለያዩ ዝግጅቶች የተስተናገዱበት ነበር። የደዓዋ ፕሮግራሞች፣ ወርክ ሾፕና ውይይቶች ሲደረጉ ካመሸን በኋላ የጉባኤው ማሳረጊያ የሆነው የኦስሎ ጀመዓ የራሱን መስጂድ ለማቋቋም የጀመረውን እንቅስቃሴ ለማገዝ የሚያስችል የፈንድ ሬዚንግ ዝግጅት ነበር። ዝግጅቱ በሸይክ ሰይፈል ኢስላም ከአሜሪካና ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ከኢትዮጵያ የተመራ ሲሆን ከሁለት ሚሊዮን ክራውን በላይ የተሰበሰበበትና በድምቀት የተከናወነ ነበር።
.
የኔት ወርኩ ጉባኤ የምስረታ መሆኑን ከግምት ውስጥ ስናስገባ በብዙ መልኩ ስኬታማ ነበር ማለት ይቻላል።በተለይ የጉባኤው አዘጋጅ የኦስሎ ጀመዓ እንግዶቻቸውን ያስተናገዱበት መንገድ እንከን የማይወጣለት ነበር። የማረፊያ ቦታው፣ የመጓጓዣ አገልግሎቱ ሎጂስቲኩ በግሩም ሁኔት የተከናወነ ነበር። ምግብን በተመለከት የኖርዌይ ጀመዓ የእንግዶቻቸውን ፍላጎት ለማርካት የሄዱበት ርቀት በሌላው የአውሮፓ ጀመዓ ሊኮረጅ እጅግ የሚከብድ፣ የዝግጅቱን ደረጃ ከቁመት አርቆ የሠቀለ ነበር ስል ማጋነን ከመሰላችሁ ሌሎች በጉባኤው ላይ የተሳተፉ ወንድሞችና እህቶችን ጠይቃችሁ ማረጋገጥ ትችላላችሁ ከማለት በዘለለ የምጨምረው የለኝም።
እኔ በበኩሌ ኔት ወርኩ በድጋሚ መመስረቱ መልካም ዜና ሆኖ ነው ያገኘሁት። ኔት ወርኩ ፍላጎቱን ከአቅሙ ጋር አመጣጥኖ፣ የተወሰኑ በተጨባጭ ሊተገበሩ የሚችሉ ሥራዎች ላይ አተኩሮ ከሠራ ውጤታማ ሊሆን እንደሚችል አምናለሁ። በአውሮፓ ያለው ሙስሊም ማህበረሰብ የጋራ የሆኑ ፍላጎቶችና ተግዳሮቶች አሉት ። እነኝህን ፍላጎቶቹንና ተግዳሮቶችቹን በስኬት ለመወጣት በኔት ወርኩ መተሳሰሩ በርካታ ጠቀሜታዎች አሉት። አሁን የኔት ወርኩ አመራር ማድርግ የሚጠበቅበት እነኝህን ጠቀሜታዎች ተጨባጭ በሆነ መልኩ ለአባላቱ ማሳየት ነው።
.
ከዚህ ሁሉ ሂደት በዃላ በስተመጨረሻም በእለተ ቅዳሜ ኦገስት 22/2026 ከተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት በመጡ በ 8 ያህል ማህበራት ፊርማ ኔትወርኩ በኦስሎ ከተማ ዳግም በይፋ የተመሰረት ሲሆን፣ የቀጣዩ አመት ጉባኤውን ደግሞ በአውሮፓዊትዋ ዋና መዲና በቤጅየም ሀገር እንደሚደረግ ታውጆ መስራች ጉባዬው ተጠናቋል። | 436 |
| 3 | بدون متن... | 369 |
| 4 | بدون متن... | 361 |
| 5 | ጽንፈኛው የእስራኤል ሚኒስትር አወዛጋቢ ግግር ሌላ ዓለም አቀፍ ውግዘት አስከተለ
~~~~~~
#RN05
.
በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት ከርሮ በቀጠለበት በዚህ ወቅት፣ የእስራኤል ጽንፈኛው የብሔራዊ ጸጥታ ሚኒስትር ኢታማር ቤን-ግቪር በጋዛ ላይ የሰጡት ከባድ እና አወዛጋቢ አስተያየት ዓለም አቀፍ አጀንዳ ሆኗል።
.
ሚኒስትሩ በጋዛ ሰርጥ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ በሰጡት ቃለ መጠይቅ ላይ፦ «ሊኖሩ የማይገባቸው ሰዎች፤ እነሱ ሰዎችም አይደሉም!» ማለታቸው ከፍተኛ አዲስ ቁጣና ውግዘት አስከትሏል።
.
የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እና አለም አቀፍ ተቋማት እንደሚያስረዱት፣ የቤን-ግቪር አገላለጽ የፓለስታናውያንን ሰብአዊነት ሙሉ በሙሉ የሚክድ እና የዘር ማጽዳት ወንጀልን የሚያበረታታ አደገኛ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለም ነጸብራቅ ነው።
,
ጽንፈኛው ሚኒስትር በጋዛ ላይ የሚወሰደው ወታደራዊ እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት እና የክልሉ ነዋሪዎች ላይ የሚደርሰው ስቃይ ትክክለኛ እርምጃ መሆኑን ለማሳየት የሞከሩባቸው ሐረጎች በሰላም ድርድር ላይ ትልቅ ጥላ አጥልተዋል።
.
ይህ አባባል የእስራኤልን መንግሥት የውጪ ግንኙነት አቋም የበለጠ አስቸጋሪ ያደረገው ሲሆን፣ የጺዮናዊትዋ አፓርታይድ እና የጦር ወንጀለኞች ሃገር የሆነችው የእስራኤል አጋር ሀገራት ጭምር በንግግሩ ላይ ያላቸውን ጽኑ ተቃውሞ እያሰሙ ይገኛሉ።
.
ተንታኞች እንደሚሉት፣ በኃተታ የተሞሉና የሰዎችን ሕይወት ዋጋ የሚቀንሱ እንዲህ ያሉ ጽንፈኛ መግለጫዎች በቀጣናው ያለውን ዘላቂ ሰላም እና መፍትሔ እጅግ አዳጋች እያደረጉት ይገኛሉ።
.
የብሔራዊ ጸጥታ ሚኒስትር ኢታማር ቤን-ግቪር በጽንፈኛ አቅዋማቸው የሚታወቁ ሲሆን ብዙ አለም አቀፍ ህጎች ጋዛ ዉስጥ የጦር ወንጀል ለመፈጸሙ እንደማሳያ ከሚጠቀሱ የእስራኤል ባለስልጣናት መካከል ከዋነኞቹ ይመደባሉ፡፡ በቅርቡ በእስራኤል ዉስጥ ያሉና ፍልስጤማዊያን በብዛት የታሰሩበት እስር ቤት ዙርያው በአዞዎች እንዲከበብ ሃሳብ ማቅረባቸው ይታወሳል፡፡
.
የእናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive | 687 |
| 6 | بدون متن... | 592 |
| 7 | ስለ #አዲስ_አበባ በጨዋ ደምብ እንወያይ!
~~~~~
1.ለመሆኑ የአዲስ አበቤ ስነ ልቦና ምን አይነት ነው?
2. አዲስ አባባን በአንድ ብሄር ወይንም በአንድ እምነት አልያም በአንድ ባህል መመደብና መፈረጅ ይቻላልን?!
3.ካልሆነስ አስተዳደራዊ መፍትሄው ምን ይመስሎታል?
.
ሀሳብዎን ያካፍሉን!
.
#የአቅል_አይምሮ_ትዝብት_ለRN05 | 835 |
| 8 | የሰው ልጆች ሕሊና የሚመረመርበት አሳዛኝ ምዕራፍ፡ አንዋር መስጂድ እና ሊቀለበስ የማይገባው የሞራል ኃላፊነት
~~~~
#የአቅል_አይምሮ_ትዝብት_ለRN05
.
በዚህ ወንድማችን ላይ የተፈጸመው ኢ-ሰብአዊ እና አጸያፊ ድርጊት የሰብአዊነትን ወሰን የተሻገረ፣ ሕሊናን የሚወቅስ ከባድ ወንጀል ነው። ከጅማ ወደ አዲስ አበባ የመጣ ፣ ሀገር የማያውቅ፣ ለሐይማኖታዊ ትምህርት በማለዳ ወደ ሐረር ለመጓዝ በመዘጋጀት ላይ የነበረ እና መሄጃ ቦታ በማጣቱ ብቻ በግቢው ውስጥ ሌሊቱን እንዲያሳልፍ አጥብቆ የለመነ ደረሳ፣ ጠለላ ሊሰጠው ሲገባ በወከባ ከምፕስጅዱ ግቢ በመባረሩ የጭካኔ ሰለባ ሆኗል።
ለሊቱን ሜዳ ላይ እንዳያሳልፍ አዋክበው ወደ ውጭ የጣሉት የመስጅዱ የጥበቃ አካላት፣ እንዲሁም ይህንን ተከላካይ የሌለውን ወንድም አራት ሆነው በመክበብ አስገድደው የደፈሩት የሰው አውሬዎች የፈጸሙት ድርጊት ከባድ የሞራል እና የሕግ ተጠያቂነትን የሚያነሳ ነው።
በመሠረቱ የሐይማኖት ተቋማት እና መስጂዶች መሠረታዊ መገለጫቸው ለተቸገረ መጠለያ፣ ለተፈናቀለ መታደጊያ እና ለአደጋ ተጋላጭ ወገኖች ሁልጊዜም ክፍት መሆን መሆኑ ይታወቃል። ግቢው ውስጥ ወርቅ፣ አልማዝ ወይም ሌላ ቁሳዊ ሀብት እንደሌለበት የሚታውወቅ ነው ፤በመሆኑም "አደጋ ላይ ነኝ፣ አትርፈኝ" ለሚሉ እንግዶች የአንድ ሌሊት መጠለያ መሆን ካልቻለ፣ የተቋሙ ስዋዊ አገልግሎቱ ትርጉሙን ይስታል። በመሆኑም በዚህ አሳዛኝ ድርጊት በወቅቱ የነበሩት የአንዋር መስጂድ አስተዳደር እና ኃላፊዎች የሞራል እና የተቋማዊ ተጠያቂነት ባለቤት መሆናቸውን አበክሮ መናገር ያስፈልጋል።
* ለተጎጂው ወንድማችን፡ ጉዳዩ ከዓመታት በፊት የተፈጸመ ቢሆንም፣ የደረሰብህን ዘግናኝ ግፍና በደል ብሎም ያንን ተከትሎ ለአመታት ያሳለፍከእን መከራ ባለን ተቋም (መስጂድ) አማካኝነት ማስቀረት ባለመቻላችን እንደ ማህበረሰብ ጥልቅ ጸጸት ይሰማናል። አላህ ጽናቱንና ብርታቱን ይስጥህ!
በዚህ አጋጣሚ "ከሰማነው ይልቅ ያልሰማነው እንደሚበልጥ በመገመት" ሀገራችን በአሁኑ ወቅት በምን ዓይነት ኢ-ሞራላዊና እጅግ አደገኛ ሁናቴ ውስጥ እንደምትገኝ በጥልቀት መገንዘብ ይገባል። እንዲህ ያሉ ዘግናኝ ግፎችን በአስተማማኝ ሁኔታ ለመታገል እና የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅ ጠንካራ፣ ፍትሃዊ እና ውጤታማ የሕግ ዝግጅት ማድረግ ወሳኝ መሆኑን አበክረን ልናስብበት ይገባል።
.
የእናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive | 886 |
| 9 | .
የእናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive | 651 |
| 10 | በወ/ሮ ሙፈሪሃት ከማል የሚመራው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር - ኢትዮጵያ / Ministry of Labor and Skills- Ethiopia መ/ቤት ምን እየሆነ ነው? - ከሚኒስቴር መስርያ ቤቱ አሠራር ጋር ተያይዞ እየወጡ ያሉ መረጃዎች እጅግ አስደንጋጭ ናቸው!
ይህንን ገጽ ከፍተው መረጃዎቹን ይመልከቱ https://www.facebook.com/search/top/?q=seid%20ibrahim | 750 |
| 11 | የመከላከያ ሚስጥሩ አፈተለከ፦ ትራምፕ መረጃ አቀባዮችን 'እያደንን ነው' አሉ
~~~~~~~~~
#RN05
.
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ግጭት ምክንያት የመከላከያ እና የጦር መሳሪያ (በተለይም የሚሳኤል) ክምችቷ አልቋል ወይም ቀንሷል የሚሉ ዘገባዎች በCNN እና Washington Post የመገናኛ ብዙሃን ተሰራጭተዋል።
.
የዶናልድ ትራምፕ ምላሽ፦ የUSA ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እነዚህን ዘገባዎች በጥብቅ አስተባብለዋል። አሜሪካ በቂ የመሳሪያ ክምችት እንዳላትና የጦር መሳሪያ አምራች ፋብሪካዎችም በከፍተኛ ፍጥነት ምርት ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
.
የእስራት ዛቻ፦ ትራምፕ እነዚህን ምስጢራዊ የመከላከያ መረጃዎች ለመገናኛ ብዙሃን አሳልፈው የሰጡ አካላትን "እያደንን ነው" ብለዋል። መረጃውን አሳልፈው የሰጡ አካላት "ከባድ የሀገር ክህደት ወንጀል ፈጽመዋል!" ሲሉ የረጅም ጊዜ የእስራት ቅጣት እንደሚጠብቃቸው አስጠነቅቀዋል።
.
የእናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive | 784 |
| 12 | ያም ሆኖ ጽንፈኛ አካላት ሙስሊሙ ላይ የሚያካሂዱት የማጠልሸት ዘመቻ፣ ሙስሊሙን የማጀት አድርጎ ለመያዝና ችግሮቹን አደባባይ እንዳያወጣ ለመሸፈን ከሚደረግ ጥረትም በላይ መድረኩን በመጠቀም ሙስሊሙ ማህበረሰብ ምናልባትም አንድ ጥያቄዉ ምላሽ እንዳያገኝ ከመስጋት የመነጨ ዘመቻ መሆኑን በግልጽ ያሳያል።
.
ማጠቃለያ፦
~~~~~
የዚህ ጽሑፍ ዋና ዓላማ የምክክር አስፈላጊነትን ማጣጣል አይደለም። በተለይም ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ካሉበት ዘርፈ-ብዙ ችግሮች መካከል ጥቂቶቹንም ቢሆን በአደባባይ በማንሳት ድምፁ እንዲሰማ ማድረጉ ትልቅ ፋይዳ አለው። ሙስሊሙን የወከሉ አካላት የተደቀኑትን መሰናክሎች አልፈው መሠረታዊ ከሆኑት ዉስጥ ኢያንስ የእኩል ውክልና ጥያቄዎቹን በማቅረብ በጎ ውጤት ማምጣት ቢችሉ ቀላል ነገር ሆኖ አይደለም። ምንም እንኳን የሃገሪቱ ፖለቲካዊ ግችሮች እንዳይፈቱ የታገዱ ቢሆንም መድረኩን በመጠቀም ሃገሪቱ ካሉባት ዘርፈ ብዙ ታሪካዊ ችግሮች መሃል አንዱን እንኳን መቅረፍ ከተቻለ ይህም ጥቅም መሆኑ እርግጥ ነው፡፡
.
ይሁን እንጂ፣ «አገራዊ ምክክር» በሚል መጠሪያ የሚካሄደው ይህ ሂደት፣ በኦሮሚያ፣ በአማራ እና በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች ባለው ግጭትና የፖለቲካ ውጥረት ምክንያት "ችግሮችን በውይይት የመፍታት" አቅሙንና ቅቡልነቱን አጥቷል። ውጤቱ አስቀድሞ የተቃኘ የሚመስለው ይህ መድረክ፣ የሚወሰኑት ዋና ዋና ውሳኔዎች ከመንግሥት ፍላጎትና ቀይ መስመሮች የማይወጡ በመሆናቸው፣ አወቃቀሩ ለገዢው ፓርቲ የሥልጣን ማጽኛ ከመሆን የዘለለ መዋቅራዊ ለውጥ ያመጣል ተብሎ አይጠበቅም። በመሆኑም በብዙዎች ዘንድ ኢትዮጵያ ዛሬ «ከእውነተኛ ምክክር» ይልቅ «የዕድል መክሸፍ» የሚታይበት አሳዛኝ የታሪክ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች የሚባለዉም ለዚሁ ነው።
.
ይህም በመሆኑ ሂደቱ የሚያስከትለው መዘዝ ለሀገሪቱ ተስፋ ከባድ ዋጋ የሚያስከፍል ነው። በመሆኑም፣ አገር ወዳድ ዜጎች በሙሉ አሁን ያለው መድረክ በቀጣይ እውነተኛ፣ ሁሉን አካታች እና ነፃ ሌላ የሽግግርና የእርቅ መድረክ ይኖር ዘንድ እንደ መሸጋገርያ ለመጠቀም በጋራና በግልጽ ተፅዕኖ ማሳደር ይኖርባቸዋል።
.
የእናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive | 710 |
| 13 | 🚩 ምክክር ወይንስ መምከን ?፦ የብልፅግና «አገራዊ ምክክር» ፈተናዎች እና የመዋቅራዊ ለውጥ አስፈላጊነት
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ጡፌል ዘሃበሻ (ከመናገሻ)
.
መግቢያ
-------
ይህንን ጽሑፍ እንድጽፍ ያነሳሳኝ በቅርቡ በብሔራዊ የምክክር ኮሚሽኑ መድረክ ላይ የተስተዋሉ አያሌ ጥያቄዎችን የሚያስነሱ ሂደቶች እና ድራማዊ ክስተቶች ናቸው።
1. ሰሞኑን የኮሚሽኑ ሰብሳቢ፦ "እዚህ አዳራሽ ዉስጥ የክልል ባለሥልጣናት፣ የከተማ ከንቲባዎች እና ሚንስትሮች አብረውን ሙሉ ቀን ይገኛሉ፤ ነገር ግን መገኘታቸው እንደ ማንኛውም ተመካካሪ በስነ-ስርዓት ቁጭ ብለው እንዲመካከሩ እንጂ ሥልጣናቸውን ወይንም ጉልበታቸዉን ሊያሳዩን አይደለም!..." ሲሉ ያደመጥናቸው ንግግር፣ የመድረኩን ነፃነት እና የባለሥልጣናቱን የፖለቲካ ተፅዕኖ በተመለከተ ከፍተኛ ሥጋት እንዲፈጠር አድርጓል።
.
2. አጀንዳ በተያዘበት የሙስሊሙ መብት ጉዳይ ላይ በሙስሊም ስም የተሳተፉ የብልፅግና አፈ-ቀላጤ የሰጡትን ተጻራሪ አስተያየት ስንመለከትም፦ "ለመሆኑ ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ይህንን መድረክ እውነተኛ የውይይት መድረክ አድርጎ ቆጥሮታልን? የተሳተፉትስ አንዳንድ ተወካዮች የጠቅላላውን ማኅበረሰብ እውነተኛ ድምፅ ያንፀባርቃሉ ወይስ የመንግሥት ምርጫዎች ናቸው?" የሚሉ መሠረታዊ ጥያቄዎችን እንድንሰነዝር ያደርገናል።
.
3. በሌላ በኩል ደግሞ፣ መድረኩ ላይ ከተሳተፉት ሌሎች ማህበረሰቦች አንጻር ጥቂት የሚባሉ የተወሰኑ ሙስሊሞች ጥያቄዎቻቸዉን ይዘው በመድረኩ በመገኘታቸው ብቻ በሂደቱ ላይ ገንቢ ጥያቄ ከማንሳት ይልቅ፣ አጋጣሚውን ማኅበረሰቡን ለማጠልሸትና የጥላቻ ንግግሮችን ለማስፋፋት የተጠቀሙበትን በተለይ ጽንፈኛ "ጸረ ሙስሊም" ወገኖችን ዘመቻ ስንመለከት፣ የችግሩን መሠረታዊ ጉድለት በግልጽ ማስቀመጥ አስፈላጊ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።
.
እውነተኛ የምክክር አስፈላጊነት፦
--------
ለዘመናት የተከማቹ መዋቅራዊ ስብራቶችን ለማቃናት፣ የታሪክ በደሎችን በሽግግር ፍትሕ ለመፈወስ እና የአገሪቱን የወደፊት ፖለቲካዊ ዕጣ-ፈንታ ለመወሰን እውነተኛ የብሔራዊ ምክክር መድረክ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አምናለሁ። የታሪክ ቁስል የሚድነው፣ የፍትሕ መጓደል የሚታረመው እና የዜጎች የባለቤትነት ጥያቄ እውነተኛ ምላሽ የሚያገኘው መላው የሀገሪቱ ሕዝቦችና ባለድርሻ አካላት በጋራ የዉይይት ማዕድ ዙሪያ ሲሰበሰቡና በአንድነት እና በልዩነታቸው ዙሪያ በግልጽና በነፃነት ሲወያዩ ብቻ ነው።
.
ሆኖም ግን አሁን እየተካሄደ ያለው ሂደት የምክክር ኮምሽነሩ እንዳሉት በባለሥልጣናት ጣልቃ-ገብነት እና በካድሬዎች አማካኝነት ይፋዊውን መስመሩን በመከላከል አዝማሚያ የተሞላ በመሆኑ፣ ከፍትሐዊና አካታች መድረክነት ይልቅ ቅቡልነትን ለማግኘትና ፖለቲካዊ አላማን ለማሳካት የሚደረግ ጥረት አስመስሎታል። ይህም፦ "ኢትዮጵያ እውነት እየመከረች ነው ወይስ በሂደቱ ምክንያት አገራዊ እድሏ እየመከነ ነው?" የሚል ጥልቅ ሥጋት እንድናነሳ ያስገድደናል።
.
ለዚህ ሥጋት ዋና ዋናዎቹ ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው፦
------------
1. የኮሚሽነሮቹ አሰያየም እና የገለልተኝነት ጥያቄ፦
የኮሚሽኑ የመጀመሪያውና መሠረታዊው ጉድለት የአወቃቀሩ ሁኔታ ነው። ኮሚሽነሮቹ የተመረጡበት ሂደት በገዢው ፓርቲ ቁጥጥር ሥር እንደዋለ የሚነሱት ቅሬታዎች ከፍተኛ ናቸው። ጎልተው የወጡ ዋና ዋና የፖለቲካ ተቃዋሚዎች፣ የሲቪል ማኅበራት ተወካዮች እና ነፃ ምሁራን በበቂ ሁኔታ ከሂደቱ መገለላቸው፣ የመድረኩን ገለልተኝነትና ነፃነት ገና ከጅምሩ ጥያቄ ውስጥ ጥሎታል፤ ገለልተኝነት በጎደለበት ሁኔታ የሚደረግ «ብሔራዊ ምክክር» ደግሞ የሚጠበቀውን ዘላቂ ሰላም ማምጣት ይችላል ተብሎ አይጠበቅም።
.
2. የታሪክ ቁርሾዎችን ለፖለቲካ ጥቅም ማዋል፦
ለሕግ የበላይነትና ለፍትሕ በቂ ትኩረት በማይሰጥ ሥርዓት ውስጥ አገራዊ ችግሮችን በቅንነት ለመፍታት ያለው ቁርጠኝነት አጠራጣሪ ነው። ይልቁንም፣ ታሪካዊ ቁርሾዎችን አሁናዊ የፖለቲካ ጥንካሬ ማጠናከሪያ በማድረግ ሕዝብን ከሕዝብ፣ ሃይማኖትን ከሃይማኖት የማጋጨቱ አካሄድ አሁንም ድረስ የብዙ ዜጎችን ሕይወት ለህልፈት እየዳረገ ይገኛል። ልዩነቶችን ከመሠረቱ በቅንነት ከመፍታት ይልቅ ለጊዜያዊ ሥልጣን ማጽኛ የመጠቀም አዝማሚያ ባለበት ሁኔታ፣ ከዚህ ሂደት ዘላቂ አገራዊ መፍትሔ መጠበቅ እጅግ አስቸጋሪ ነው።
.
ይህንን እውነታ ይበልጥ የሚያጠናክረው ራሳቸው ጠ/ሚንስትሩ በመድረኩ መክፈቻ ላይ የተወሰኑ የኅብረተሰብ ክፍሎችን እና የፖለቲካ ኃይሎችን ያገለለ፣ አልፎም ማስፈራራት የተሞላበት ንግግር ማድረጋቸው ነው። ይህም የመድረኩን ጅማሮ እንኳን ቢያንስ በንግግራቸው ገለልተኛ እና ሁሉንም የሚያቅፍ ማድረግ እንዳልተቻለ የሚያሳይ ነው። ለዚህም ነው ሂደቱ የሕዝብ ውይይት ከመሆን ይልቅ የመንግሥትን ፍላጎትንና ፖለቲካዊ እቅድን ብቻ የሚያንፀባርቅ «የአንድ ወገን ትርኢት» ነው የሚሉ ትችቶች የበረቱበት።
.
3. የዋና ዋና ክልሎች እና ባለድርሻ አካላት አሳታፊነት ማነስ፦
ሌላው ጎልቶ የሚታየው መዋቅራዊ ጉድለት የአገሪቱን ፖለቲካዊ ዕድል በጋራ የሚቀርጹ የሚሰኙት የኦሮሚያ፣ የአማራ እና የትግራይ ክልሎች እውነተኛ እና ትርጉም ያለው ውክልና አለመኖሩ ነው። በነዚህ አካባቢዎች ሰፊ ግጭት እና ጥብቅ ፖለቲካዊ ውጥረት ባለበት ሁኔታ፣ መሬት ላይ ያለዉን እውነታ የሚያንፀባርቁ አካላት ሳይወከሉ በመንግሥት በተመረጡ ወገኖች ብቻ «ምክክር» ማካሄድ ሂደቱን ውጫዊና ተፅዕኖ የሌለው ያደርገዋል።
.
4. የጽንፈኛ አካላት ምላሽ እና የውክልና ክፍተቶች፦
በሌላ በኩል ደግሞ፣ የተወሰኑ የሙስሊም ተወካዮች በመድረኩ በመገኘታቸው ብቻ፣ አጋጣሚውን በመጠቀም ማኅበረሰቡን ለማጠልሸት የሚደረጉ የጽንፈኝነት እንቅስቃሴዎች እጅግ አሳሳቢ ሆነው ታይተዋል። እነዚህ እኩልነትን የማይሹ ጽንፈኛ ወገኖች ወገኖች በጥቂት ግለሰቦች ተሳትፎ ምክንያት አጠቃላይ ሂደቱን የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ፍላጎት ማስፈጸምያ አስመስለው ለማቅረብ እና መሠረታዊ ጥያቄዎችን ለማጣጣል ይሞክራሉ። ነገር ግን ሙስሊሙን ወክለዋል ተብለው የተሳተፉት አካላት ቁጥራቸው ከሌሎች አንጻር ሲታይ ከሙስሊሙ ማኅበረሰብ ስፋት አንጻር እጅግ አነስተኛ ነው። ይህም ህዝበ ሙስሊሙ ለዘመናት ሲያነሳው የቆየውን ቁመቱን ያማከለ ተመጣጣኝና ፍትሐዊ የውክልና ጥያቄ ክፍተት የሚያሳይ እንጂ የማኅበረሰቡን እውነተኛ ፍላጎት የሚያስፈጽም በቂ ውክልና አይደለም። | 680 |
| 14 | ይሁን እንጂ፣ «አገራዊ ምክክር» በሚል መጠሪያ የሚካሄደው ይህ ሂደት፣ በኦሮሚያ፣ በአማራ እና በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች ባለው ግጭትና የፖለቲካ ውጥረት ምክንያት "ችግሮችን በውይይት የመፍታት" አቅሙንና ቅቡልነቱን አጥቷል። ውጤቱ አስቀድሞ የተቃኘ የሚመስለው ይህ መድረክ፣ የሚወሰኑት ዋና ዋና ውሳኔዎች ከመንግሥት ፍላጎትና ቀይ መስመሮች የማይወጡ በመሆናቸው፣ አወቃቀሩ ለገዢው ፓርቲ የሥልጣን ማጽኛ ከመሆን የዘለለ መዋቅራዊ ለውጥ ያመጣል ተብሎ አይጠበቅም። በመሆኑም በብዙዎች ዘንድ ኢትዮጵያ ዛሬ «ከእውነተኛ ምክክር» ይልቅ «የዕድል መክሸፍ» የሚታይበት አሳዛኝ የታሪክ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች የሚባለዉም ለዚሁ ነው።
.
ይህም በመሆኑ ሂደቱ የሚያስከትለው መዘዝ ለሀገሪቱ ተስፋ ከባድ ዋጋ የሚያስከፍል ነው። በመሆኑም፣ አገር ወዳድ ዜጎች በሙሉ አሁን ያለው መድረክ በቀጣይ እውነተኛ፣ ሁሉን አካታች እና ነፃ ሌላ የሽግግርና የእርቅ መድረክ ይኖር ዘንድ እንደ መሸጋገርያ ለመጠቀም በጋራና በግልጽ ተፅዕኖ ማሳደር ይኖርባቸዋል።
.
የእናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive | 1 |
| 15 | ምክክር ወይንስ መምከን ?፦ የብልፅግና «አገራዊ ምክክር» ፈተናዎች እና የመዋቅራዊ ለውጥ አስፈላጊነት
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ጡፌል ዘሃበሻ (ከመናገሻ)
.
መግቢያ
-------
ይህንን ጽሑፍ እንድጽፍ ያነሳሳኝ በቅርቡ በብሔራዊ የምክክር ኮሚሽኑ መድረክ ላይ የተስተዋሉ አያሌ ጥያቄዎችን የሚያስነሱ ሂደቶች እና ድራማዊ ክስተቶች ናቸው።
1. ሰሞኑን የኮሚሽኑ ሰብሳቢ፦ "እዚህ እመካከላችን የክልል ባለሥልጣናትና የከተማ ከንቲባዎች አብረውን ይገኛሉ፤ ነገር ግን መገኘታቸው እንደ ማንኛውም ተወያይ ለመወያየት እንጂ ሥልጣናቸውን ለማሳየት ሊሆን አይገባም!..." ሲሉ ያደመጥናቸው ንግግር፣ የመድረኩን ነፃነት እና የባለሥልጣናቱን የፖለቲካ ተፅዕኖ በተመለከተ ከፍተኛ ሥጋት እንዲፈጠር አድርጓል።
.
2. አጀንዳ በተያዘበት የሙስሊሙ መብት ጉዳይ ላይ በሙስሊም ስም የተሳተፉ የብልፅግና አፈ-ቀላጤ የሰጡትን ተጻራሪ አስተያየት ስንመለከትም፦ "ለመሆኑ ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ይህንን መድረክ እውነተኛ የውይይት መድረክ አድርጎ ቆጥሮታልን? የተሳተፉትስ አንዳንድ ተወካዮች የጠቅላላውን ማኅበረሰብ እውነተኛ ድምፅ ያንፀባርቃሉ ወይስ የመንግሥት ምርጫዎች ናቸው?" የሚሉ መሠረታዊ ጥያቄዎችን እንድንሰነዝር ያደርገናል።
.
3. በሌላ በኩል ደግሞ፣ መድረኩ ላይ ከተሳተፉት ሌሎች ማህበረሰቦች አንጻር ጥቂት የሚባሉ የተወሰኑ ሙስሊሞች ጥያቄዎቻቸዉን ይዘው በመድረኩ በመገኘታቸው ብቻ በሂደቱ ላይ ገንቢ ጥያቄ ከማንሳት ይልቅ፣ አጋጣሚውን ማኅበረሰቡን ለማጠልሸትና የጥላቻ ንግግሮችን ለማስፋፋት የተጠቀሙበትን በተለይ ጽንፈኛ "ጸረ ሙስሊም" ወገኖችን ዘመቻ ስንመለከት፣ የችግሩን መሠረታዊ ጉድለት በግልጽ ማስቀመጥ አስፈላጊ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።
.
እውነተኛ የምክክር አስፈላጊነት፦
--------
ለዘመናት የተከማቹ መዋቅራዊ ስብራቶችን ለማቃናት፣ የታሪክ በደሎችን በሽግግር ፍትሕ ለመፈወስ እና የአገሪቱን የወደፊት ፖለቲካዊ ዕጣ-ፈንታ ለመወሰን እውነተኛ የብሔራዊ ምክክር መድረክ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አምናለሁ። የታሪክ ቁስል የሚድነው፣ የፍትሕ መጓደል የሚታረመው እና የዜጎች የባለቤትነት ጥያቄ እውነተኛ ምላሽ የሚያገኘው መላው የሀገሪቱ ሕዝቦችና ባለድርሻ አካላት በጋራ የዉይይት ማዕድ ዙሪያ ሲሰበሰቡና በአንድነት እና በልዩነታቸው ዙሪያ በግልጽና በነፃነት ሲወያዩ ብቻ ነው።
.
ሆኖም ግን አሁን እየተካሄደ ያለው ሂደት የምክክር ኮምሽነሩ እንዳሉት በባለሥልጣናት ጣልቃ-ገብነት እና በካድሬዎች አማካኝነት ይፋዊውን መስመሩን በመከላከል አዝማሚያ የተሞላ በመሆኑ፣ ከፍትሐዊና አካታች መድረክነት ይልቅ ቅቡልነትን ለማግኘትና ፖለቲካዊ አላማን ለማሳካት የሚደረግ ጥረት አስመስሎታል። ይህም፦ "ኢትዮጵያ እውነት እየመከረች ነው ወይስ በሂደቱ ምክንያት አገራዊ እድሏ እየመከነ ነው?" የሚል ጥልቅ ሥጋት እንድናነሳ ያስገድደናል።
.
ለዚህ ሥጋት ዋና ዋናዎቹ ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው፦
------------
1. የኮሚሽነሮቹ አሰያየም እና የገለልተኝነት ጥያቄ፦
የኮሚሽኑ የመጀመሪያውና መሠረታዊው ጉድለት የአወቃቀሩ ሁኔታ ነው። ኮሚሽነሮቹ የተመረጡበት ሂደት በገዢው ፓርቲ ቁጥጥር ሥር እንደዋለ የሚነሱት ቅሬታዎች ከፍተኛ ናቸው። ጎልተው የወጡ ዋና ዋና የፖለቲካ ተቃዋሚዎች፣ የሲቪል ማኅበራት ተወካዮች እና ነፃ ምሁራን በበቂ ሁኔታ ከሂደቱ መገለላቸው፣ የመድረኩን ገለልተኝነትና ነፃነት ገና ከጅምሩ ጥያቄ ውስጥ ጥሎታል፤ ገለልተኝነት በጎደለበት ሁኔታ የሚደረግ «ብሔራዊ ምክክር» ደግሞ የሚጠበቀውን ዘላቂ ሰላም ማምጣት ይችላል ተብሎ አይጠበቅም።
.
2. የታሪክ ቁርሾዎችን ለፖለቲካ ጥቅም ማዋል፦
ለሕግ የበላይነትና ለፍትሕ በቂ ትኩረት በማይሰጥ ሥርዓት ውስጥ አገራዊ ችግሮችን በቅንነት ለመፍታት ያለው ቁርጠኝነት አጠራጣሪ ነው። ይልቁንም፣ ታሪካዊ ቁርሾዎችን አሁናዊ የፖለቲካ ጥንካሬ ማጠናከሪያ በማድረግ ሕዝብን ከሕዝብ፣ ሃይማኖትን ከሃይማኖት የማጋጨቱ አካሄድ አሁንም ድረስ የብዙ ዜጎችን ሕይወት ለህልፈት እየዳረገ ይገኛል። ልዩነቶችን ከመሠረቱ በቅንነት ከመፍታት ይልቅ ለጊዜያዊ ሥልጣን ማጽኛ የመጠቀም አዝማሚያ ባለበት ሁኔታ፣ ከዚህ ሂደት ዘላቂ አገራዊ መፍትሔ መጠበቅ እጅግ አስቸጋሪ ነው።
.
ይህንን እውነታ ይበልጥ የሚያጠናክረው ራሳቸው ጠ/ሚንስትሩ በመድረኩ መክፈቻ ላይ የተወሰኑ የኅብረተሰብ ክፍሎችን እና የፖለቲካ ኃይሎችን ያገለለ፣ አልፎም ማስፈራራት የተሞላበት ንግግር ማድረጋቸው ነው። ይህም የመድረኩን ጅማሮ እንኳን ቢያንስ በንግግራቸው ገለልተኛ እና ሁሉንም የሚያቅፍ ማድረግ እንዳልተቻለ የሚያሳይ ነው። ለዚህም ነው ሂደቱ የሕዝብ ውይይት ከመሆን ይልቅ የመንግሥትን ፍላጎትንና ፖለቲካዊ እቅድን ብቻ የሚያንፀባርቅ «የአንድ ወገን ትርኢት» ነው የሚሉ ትችቶች የበረቱበት።
.
3. የዋና ዋና ክልሎች እና ባለድርሻ አካላት አሳታፊነት ማነስ፦
ሌላው ጎልቶ የሚታየው መዋቅራዊ ጉድለት የአገሪቱን ፖለቲካዊ ዕድል በጋራ የሚቀርጹ የሚሰኙት የኦሮሚያ፣ የአማራ እና የትግራይ ክልሎች እውነተኛ እና ትርጉም ያለው ውክልና አለመኖሩ ነው። በነዚህ አካባቢዎች ሰፊ ግጭት እና ጥብቅ ፖለቲካዊ ውጥረት ባለበት ሁኔታ፣ መሬት ላይ ያለዉን እውነታ የሚያንፀባርቁ አካላት ሳይወከሉ በመንግሥት በተመረጡ ወገኖች ብቻ «ምክክር» ማካሄድ ሂደቱን ውጫዊና ተፅዕኖ የሌለው ያደርገዋል።
.
4. የጽንፈኛ አካላት ምላሽ እና የውክልና ክፍተቶች፦
በሌላ በኩል ደግሞ፣ የተወሰኑ የሙስሊም ተወካዮች በመድረኩ በመገኘታቸው ብቻ፣ አጋጣሚውን በመጠቀም ማኅበረሰቡን ለማጠልሸት የሚደረጉ የጽንፈኝነት እንቅስቃሴዎች እጅግ አሳሳቢ ሆነው ታይተዋል። እነዚህ እኩልነትን የማይሹ ጽንፈኛ ወገኖች ወገኖች በጥቂት ግለሰቦች ተሳትፎ ምክንያት አጠቃላይ ሂደቱን የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ፍላጎት ማስፈጸምያ አስመስለው ለማቅረብ እና መሠረታዊ ጥያቄዎችን ለማጣጣል ይሞክራሉ። ነገር ግን ሙስሊሙን ወክለዋል ተብለው የተሳተፉት አካላት ቁጥራቸው ከሌሎች አንጻር ሲታይ ከሙስሊሙ ማኅበረሰብ ስፋት አንጻር እጅግ አነስተኛ ነው። ይህም ህዝበ ሙስሊሙ ለዘመናት ሲያነሳው የቆየውን ቁመቱን ያማከለ ተመጣጣኝና ፍትሐዊ የውክልና ጥያቄ ክፍተት የሚያሳይ እንጂ የማኅበረሰቡን እውነተኛ ፍላጎት የሚያስፈጽም በቂ ውክልና አይደለም።
ያም ሆኖ ጽንፈኛ አካላት ሙስሊሙ ላይ የሚያካሂዱት የማጠልሸት ዘመቻ፣ ሙስሊሙን የማጀት አድርጎ ለመያዝና ችግሮቹን አደባባይ እንዳያወጣ ለመሸፈን ከሚደረግ ጥረትም በላይ መድረኩን በመጠቀም ሙስሊሙ ማህበረሰብ ምናልባትም አንድ ጥያቄዉ ምላሽ እንዳያገኝ ከመስጋት የመነጨ ዘመቻ መሆኑን በግልጽ ያሳያል።
.
ማጠቃለያ፦
~~~~~
የዚህ ጽሑፍ ዋና ዓላማ የምክክር አስፈላጊነትን ማጣጣል አይደለም። በተለይም ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ካሉበት ዘርፈ-ብዙ ችግሮች መካከል ጥቂቶቹንም ቢሆን በአደባባይ በማንሳት ድምፁ እንዲሰማ ማድረጉ ትልቅ ፋይዳ አለው። ሙስሊሙን የወከሉ አካላት የተደቀኑትን መሰናክሎች አልፈው መሠረታዊ ከሆኑት ዉስጥ ኢያንስ የእኩል ውክልና ጥያቄዎቹን በማቅረብ በጎ ውጤት ማምጣት ቢችሉ ቀላል ነገር ሆኖ አይደለም። ምንም እንኳን የሃገሪቱ ፖለቲካዊ ግችሮች እንዳይፈቱ የታገዱ ቢሆንም መድረኩን በመጠቀም ሃገሪቱ ካሉባት ዘርፈ ብዙ ታሪካዊ ችግሮች መሃል አንዱን እንኳን መቅረፍ ከተቻለ ይህም ጥቅም መሆኑ እርግጥ ነው፡፡
. | 1 |
| 16 | بدون متن... | 546 |
| 17 | ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ "ባንዳ "ይመስል፣ "ባዳ"ን በሀገራችን ጉዳይ ጣልቃ እንዲገባ በማድረጋቸው ተጸጸቱ፣ ሌሎችም ስህተቱን እንዳይደጉ አሳሰቡ!
~~~~~~~~~~~~
#የአቅል_አይምሮ_ትዝብት_ለRN05
.
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአማራ ቲቪ ጋር ባደረጉት ውይይት፣ በትግራይ ጦርነት ወቅት ከኤርትራ ኃይሎች ጋር ያደረጉትን ተጋግዞ ትግራይን የመዉጋት ዘመቻን «ትብብር መሳይ የጥፋት መንገድ» ሲሉ የጠሩት ሲሆን፣ ይህንንም እርምጃ በመዉሰዳቸው «ኢትዮጵያ ላይ ጥቁር ጠባሳ ጥለን አልፈናል» በማለት ተጽጽተውበታል። አያይዘውም አሁን ደግሞ ሌሎች አካላት (ሕወኃት እና ፋኖ) "ከኤርትራ ጋር በማበርና እሳቸዉብ በመግጠም" ተመሳሳይ የጥፋት መንገድ እንዳይከተሉ፣ ያ ካልሆነ ግን ዳግም ሌላ ጥፋት እንደሚያመጣ ተናግረዋል።
.
ጥያቄው «እርሶስ?» የሚለው ነው።
.
ልክ አሁን ሕወኃት እና ፋኖ አጀንዳቸው ምንም ይሁን ምን በሀገራቸው ጉዳይ ለሚያደርጉት ትግል ወይም ጦርነት ኤርትራን አጋር አድርገው ለማምጣት ያላቸው ፍላጎት ትክክል እንዳልሆነው ሁሉ፤ ያኔም ብልፅግና ከትግራይ ጋር ለነበረበት ጦርነት ኤርትራን አሰልፎ የገዛ ዜጎቹን በውጭ ሀገር ወታደሮች ማስደብደቡ ትክክል እንዳልነበረና ወደፊትም በሀገራችን ላይ ይዞት የሚመጣው ጣጣ ሰፊ መሆኑን ያለመሰልቸትና ማቅዋረጥ ስንናገር ነበር።
.
ለ17 ዓመታት ያህል አብሮት ሲታገል ለነበረው እና በስተመጨረሻም የኤርትራን ነፃነት ከነሙሉ የባሕር በር ጥርግ አድርጎ እንዲወስድ እገዛ ላደረገለት ሕወኃት እንኳን ያልተመለሰ፣ እንዲሁም መከታ ለሆነው የትግራይ ሕዝብ ያልራራው ሻዕቢያ፤ አንድ ቀን- ቀን የተገለበጠ እና ፖለቲካ መልኩን የቀየረ ዕለት ለሌላው ኢትዮጵያዊ የሚያዝንና ገደብ የሚያውቅ እንደማይሆን ስንሞግት -በምላሹ ብዙዎች የተለያዩ ስሞችን ስትሰጡን ነበር። ከእናንተ በላይ ለሀገር ተቆርቋሪ እንደሌለ አድርጋችሁ በመቁጠር እኛን ግን «በባንዳነት» እና በሌሎችም ስሞች ስትከሰሱ የነበራችሁ የ«ስካር ፖለቲካ» ተንታኞችና የስሜት ተገዢ ደጋፊዎች፤ አሁን ደግሞ ምንም ሳታፍሩ ወይም ስህተት መሥራታችሁን ሳታምኑ ከኢሳይያስ አፍቃሪነት ያለምንም ማጠንቀቂያ ወደ ጸረ ኢሳይያስነት የተቀየራችሁ ወገኖቻችን ከዚህ ከአሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሃገራችን ጉዳይ ላይ ኤርትራን እስከጥግ በማስገባታቸው የተጸጸቱና ለተገዳዳሪውፕቻቸዉም የእኔን ስህተት አትድገሙ "ባዳን በሃገራችን ጉዳይ አታስገቡ" ያሉበት ከሚመስለው ቃለ-መጠይቅ ምን ተማራችሁ? ለማለት ነው!
.
ኤርትራ ራሷን የቻለች ሀገር እንደመሆንዋ በብልጽግናም በኩል ሆነ በህወሃት ወይንም በፋኖ በኩል ሆና በሃገራችን ጉዳይ ጣልቃ መግባቷ በፍጹም ተቀባይነት የለዉም! ይሄው ነው፡፡
.
የእናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive | 851 |
| 18 | بدون متن... | 846 |
| 19 | ስፔንን የመበቀል ከበባ እና የጂኦፖለቲካ ምስጢራዊ ዳራ፡ የስፔን ቀውስ!
~~~~~~
#የአቅል_አይምሮ_ትዝብት_ለRN05
.
1. አጭር መግብያ
.
የሞሮኮ እና የስፔን ባለሥልጣናት ሕገ-ወጥ ስደተኞች ድንበር ጥሰው ወደ አውሮፓ እንዳይገቡ አጥብቆ የሚቆጣጠር ጠንካራ ስምምነት ያላቸው መሆኑ ይታወቃል። ይሁን እንጂ በቅርቡ በተሰራጨ ሐሰተኛ መረጃ (Fake News) ድንበሩ ክፍት መሆኑ በመነገሩ ብቻ በአንድ ጊዜ ከ 60,000 በላይ ስደተኞች በድንበር በኩል ወደ ስፔን ግዛት ለመግባት ከፍተኛ ሙከራ አድርገዋል።
.
ይህ ድንገተኛ እና ግዙፍ የተደራጀ እንቅስቃሴ ከተለመደው የስደተኞች ፍሰት ፍጹም የተለየ በመሆኑ፣ ጉዳዩን ከቀዝቃዛው ፖለቲካዊ ጦርነት እና ከዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ጋር አያይዞ መገምገም ግድ ይላል።
.
2. የጂኦፖለቲካ ትንተና፡ ከስደተኞች ማዕበል ጀርባ ያለው እውነት
.
ይህንን ክስተት ከላይ ከተጠቀሰው አተያይ እና ከወቅታዊው ዓለም አቀፍ ሁኔታ ጋር ስናስተያየው፣ ጉዳዩ ተራ የስደተኞች እሩጫ ሳይሆን በስፔን መንግሥት ላይ ያነጣጠረ ሆን ተብሎ የተጠነሰሰ የፖለቲካ ሴራ መሆኑ ግልጽ ይሆናል።
.
የስፔን ገለልተኛና ደፋር አቋም:- ስፔን እስራኤል በጋዛ ሕዝብ ላይ እየፈጸመችው ያለው ጂኖሳይድ (ጭፍጨፋ) አጥብቃ በመቃወም ከአውሮፓ አገራት ለየት ያለ እና ገለልተኛ ከዛ ካለፈም ጋዛን የሚደግፍ ፖለቲካዊ አቋም ይዛለች። የፍልስጤምን ግዛት ሕጋዊነት በመቀበልም ከአሜሪካ እና ከእስራኤል የውጭ ጉዳይ መስመሮች ፈቀቅ ማለት ችላለች።
.
የአሜሪካ እና እስራኤል ምላሽ:- ይህ የስፔን ፖለቲካዊ እርምጃ የዋሽንግተንን እና የቴል አቪቭን ባለሥልጣናት ያስቆጣ ሲሆን፣ ስፔንን "ሌላዉን ማስተማርያ -ለአርአያነት የሚሆን ቅጣት" ለመቅጣት እና መንግሥቱን ከህዝቡ ጋር ለማጋጨት የተለያዩ ጫናዎችን መፍጠር መጀመራቸው ግልጽ ነው።
.
የቀውስ ማቀጣጠያ ስልት:-የእስራኤል እና የአሜሪካ የልብ ወዳጅ መንግስት በሚያስተዳድራት በሞሮኮ በኩል የስደተኞች ማእበልን በድንገት በመልቀቅ የስፔን መንግሥት ከቁጥጥር ውጭ በሆኑ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ስደተኞች ድንገተኛ ጫና ውስጥ እንዲገባ ማድረግ፤ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ ዋስትና እና ፀጥታ መንቀጥቀጥ ዐበይት ዓላማዎች ናቸው። ይህ ደግሞ በስፔን ዜጎች ዘንድ በመንግሥት ላይ እምነት ማጣት እንዲፈጠር በማድረግ ፖለቲካዊ አለመረጋጋት እንዲነግሥ ያደርጋል።
3. ስንጠቀልለው
.
በሞሮኮ ድንበር ላይ የተከሰተው ይህ ድንገተኛ እና በውሸት መረጃ የተጠነሰሰ ሰፊ የስደተኞች ሙከራ፣ ከእስራኤል-ጋዛ ጦርነት ጋር ተያይዞ ስፔን የያዘችውን ጽኑ አቋም ለመበቀል የተወሰደ የመሠሪ ጂኦፖለቲካዊ ጦርነት አካል ነው። ዓለም አቀፍ ኃይሎች መንግሥታትን ለማሸበር እና የራሳቸውን ፍላጎት ለማስፈጸም መረጃን እንደ ጦር መሣሪያ በመጠቀም ሕዝብንና መንግሥትን የማጋጨት ስልታቸውን የቀጠሉበት ሌላው ማሳያ ነው።
.
የእናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive | 1 044 |
| 20 | بدون متن... | 793 |
