en
Feedback
🇵🇭 @BaMaung336_larkyikya2568_moe25588_vcvc555_zzzworld0_hihi1500_vvvd77_supermax124_seewq97_sos1900_jkp885_phoocar2_keelay1

🇵🇭 @BaMaung336_larkyikya2568_moe25588_vcvc555_zzzworld0_hihi1500_vvvd77_supermax124_seewq97_sos1900_jkp885_phoocar2_keelay1188

Open in Telegram
1 103
Subscribers
-124 hours
-727 days
-6630 days

Data loading in progress...

Attracting Subscribers
September '26
September '26
+33
in 0 channels
August '26
+55
in 0 channels
Get PRO
July '26
+76
in 0 channels
Get PRO
June '26
+40
in 0 channels
Get PRO
May '26
+26
in 0 channels
Get PRO
April '26
+22
in 0 channels
Get PRO
March '26
+21
in 0 channels
Get PRO
February '26
+11
in 0 channels
Get PRO
January '26
+17
in 0 channels
Get PRO
December '25
+16
in 0 channels
Get PRO
November '25
+49
in 0 channels
Get PRO
October '25
+26
in 0 channels
Get PRO
September '25
+33
in 0 channels
Get PRO
August '25
+38
in 0 channels
Get PRO
July '25
+18
in 0 channels
Get PRO
June '25
+18
in 0 channels
Get PRO
May '25
+26
in 0 channels
Get PRO
April '25
+50
in 0 channels
Get PRO
March '25
+146
in 0 channels
Get PRO
February '25
+18
in 0 channels
Get PRO
January '25
+186
in 0 channels
Get PRO
December '24
+63
in 0 channels
Get PRO
November '24
+39
in 0 channels
Get PRO
October '24
+33
in 0 channels
Get PRO
September '24
+51
in 0 channels
Get PRO
August '24
+39
in 0 channels
Get PRO
July '24
+28
in 0 channels
Get PRO
June '24
+43
in 0 channels
Get PRO
May '24
+45
in 0 channels
Get PRO
April '24
+61
in 0 channels
Get PRO
March '24
+39
in 0 channels
Get PRO
February '24
+354
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
08 September+9
07 September+8
06 September+5
05 September+7
04 September+1
03 September+2
02 September0
01 September+1
Channel Posts
🗓 28/12/2018 ሀሙስ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 598⏳ መዝሙር ምዕራፍ 123 1 በሰማይ የምትኖር ሆይ፥ ዓይኖቼን ወደ አንተ አነሣሁ። 2 እነሆ፥ የባሪያዎች ዓይኖች ወደ ጌታቸው እጅ እንደ ሆኑ፥ የባሪያይቱም ዓይን ወደ እመቤትዋ እጅ እንደ ሆነ፥ እንዲሁ እስኪምረን ድረስ ዓይናችን ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ነው። 3 ማረን፥ አቤቱ፥ ማረን፤ ንቀትን እጅግ ጠግበናልና፤ 4 የባለጠጎች ስድብና የትዕቢተኞችን ንቀት ነፍሳችን እጅግ ጠገበች። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook

2
🗓 27/12/2018 ዕሮብ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 597⏳ መዝሙር ምዕራፍ 122 1 ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሄድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ። 2 ኢየሩሳሌም ሆይ፥ እግሮቻችን በአደባባይሽ ቆሙ። 3 ኢየሩሳሌምስ እርስ በርስዋ እንደ ተገጠገጠች ከተማ ተሠርታለች። 4 የእግዚአብሔርን ስም ያመስግኑ ዘንድ፥ ለእስራኤል ምስክር ሊሆኑ የእግዚአብሔር ነገዶች ወደዚያ ይወጣሉ። 5 ዙፋኖች በዚያ ለፍርድ ተቀምጠዋልና፥ የዳዊት ቤት ዙፋኖች። 6 ለኢየሩሳሌም ሰላምን ለምኑ፤ አንተንም ለሚወድዱ ልማት ይሁን። 7 በኃይልህ ሰላም፥ በጌጠኛ ቤትህም ልማት ይሁን። 8 ስለ ወንድሞቼ ስለ ባልንጀሮቼም፡— በውስጥሽ ሰላም ይሁን፡ አልሁ። 9 ስለ አምላካችን ስለ እግዚአብሔር ቤት ላንቺ መልካምነትሽን ፈለግሁ። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
5 759
3
🗓 26/12/2018 ማክሰኞ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 596⏳ መዝሙር ምዕራፍ 121 1 ዓይኖቼ ወደ ተራሮች አነሣሁ፤ ረዳቴ ከወዴት ይምጣ? 2 ረዳቴ ሰማይና ምድርን ከሠራ ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው። 3 እግርህን ለመናወጥ አይሰጠውም፤ የሚጠብቅህም አይተኛም። 4 እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም። 5 እግዚአብሔር ይጠብቅሃል፥ እግዚአብሔርም በቀኝ እጅህ በኩል ይጋርድሃል። 6 ፀሐይ በቀን አያቃጥልህም ጨረቃም በሌሊት። 7 እግዚአብሔር ከክፉ ሁሉ ይጠብቅሃል፥ ነፍስህንም ይጠብቃታል። 8 ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም እግዚአብሔር መውጣትህና መግባትህን ይጠብቃል። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
5 170
4
🗓 25/12/2018 ሰኞ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 595⏳ መዝሙር ምዕራፍ 120 1 በተጨነቅሁ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ጮኽሁ፥ ሰማኝም። 2 ከዓመፀኛ ከንፈር ከሸንጋይም አንደበት፥ አቤቱ፥ ነፍሴን አድናት። 3 ስለ ሽንገላ አንደበት ምንም ይሰጡሃል? ምንስ ይጨምሩልሃል? 4 እንደ በረሃ እንጨት ፍም የኃያላን ፍላጾች የተሳሉ ናቸው። 5 መኖሪያዬ የራቀ እኔ ወዮልኝ፤ በቄዳር ድንኳኖች አደርሁ። 6 ሰላምን ከሚጠሉ ጋር ነፍሴ ብዙ ጊዜ ኖረች። 7 እኔ ሰላማዊ ነኝ፤ በተናገኋቸው ጊዜ ግን በከንቱ ተሰለፉብኝ። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
3 942
5
No text...
3 042
6
+8
No text...
2 880
7
+9
No text...
3 885
8
104 ከትእዛዝህ የተነሣ አስተዋልሁ፤ ስለዚህ የሐሰትን መንገድ ጠላሁ። 105 ሕግህ ለእግሬ መብራት፥ ለመንገዴ ብርሃን ነው። 106 የጽድቅህን ፍርድ እጠብቅ ዘንድ ማልሁ፥ አጸናሁም። 107 እጅግ ተቸገርሁ፤ አቤቱ፥ እንደ ቃልህ ሕያው አድርገኝ። 108 አቤቱ፥ ከአፌ የሚወጣውን ቃል ውደድ፥ ፍርድህንም አስተምረኝ። 109 ነፍሴ ሁልጊዜ በእጅህ ውስጥ ናት፤ ሕግህን ግን አልረሳሁም። 110 ኃጢአተኞች ወጥመድን ዘረጉብኝ፤ ከትእዛዝህ ግን አልሳትሁም። 111 የልቤ ደስታ ነውና ምስክርህን ለዘላለም ወረስሁ። 112 ለዘላለም ለፍጻሜውም ትእዛዝህን አደርግ ዘንድ ልቤን አዘነበልሁ። 113 ዓመፀኞችን ጠላሁ፥ ሕግህን ግን ወደድሁ። 114 አንተ ረዳቴና መጠጊያዬ ነህ፥ በቃልህም ተማመንሁ። 115 እናንተ ኃጢአተኞች፥ ከእኔ ራቁ፥ የአምላኬንም ትእዛዝ ልፈልግ። 116 እንደ ቃልህ ደግፈኝ፥ ሕያውም እሆናለሁ። ከተስፋዬም አልፈር። 117 እርዳኝ እድናለሁም፥ ሁልጊዜም ሥርዓትህን እመረምራለሁ። 118 ምኞታቸው ዓመፃ ነውና ከሥርዓትህ የሚርቁትን ሁሉ አጐሳቈልሃቸው። 119 የምድርን ኃጢአተኞች ሁሉ እንደ ርኵሰት አጠፋሃቸው፤ ስለዚህ ምስክርህን ወደድሁ። 120 ሥጋዬ አንተን ከመፍራት የተነሣ ደንገጠ፤ ከፍርድህ የተነሣ ፈርቻለሁ። 121 ፍርድንና ጽድቅን ሠራሁ፤ ለሚያስጨንቁኝ አሳልፈህ አትስጠኝ። 122 ባሪያህን በመልካም ጠብቀው፤ ትዕቢተኞችም አይጋፉኝ። 123 ዓይኖቼ ለማዳንህ፥ ለጽድቅህም ቃል ፈዘዙ። 124 ለባሪያህ እንደ ምሕረትህ አድርግ፥ ሥርዓትህንም አስተምረኝ። 125 እኔ ባሪያህ ነኝ፤ እንዳስተውል አድርገኝ፥ ምስክርህንም አውቃለሁ። 126 ለእግዚአብሔር የሥራ ጊዜ ነው፥ ሕግህንም ሻሩት። 127 ስለዚህ ከወርቅና ከዕንቍ ይልቅ ትእዛዝህን ወደድሁ። 128 ስለዚህ ወደ ትእዛዝህ ሁሉ አቀናሁ፥ የዓመፅንም መንገድ ሁሉ ጠላሁ። 129 ምስክሮችህ ድንቆች ናቸው፤ ስለዚህ ነፍሴ ፈለገቻቸው። 130 የቃልህ ፍቺ ያበራል፥ ሕፃናትንም አስተዋዮች ያደርጋል። 131 አፌን ከፈትሁ፥ አለከለክሁም፤ ወደ ትእዛዝህ ናፍቄአለሁና። 132 ስምህን ለሚወድዱ እንድምታደርገው ፍርድ፥ ወደ እኔ ተመልከተ ማረኝም። 133 አካሄድን እንደ ቃልህ አቅና፤ ኃጢአትም ሁሉ አይግዛኝ። 134 ከሰው ግፍ አድነኝ፤ ትእዛዝህንም እጠብቃለሁ። 135 በባሪያህ ላይ ፊትህን አብራ፥ ሥርዓትህንም አሰተምረኝ። 136 ሕግህን አልጠበቅሁምና የውኃ ፈሳሽ ከዓይኖቼ ፈሰሰ። 137 አቤቱ፥ አንተ ጻድቅ ነህ፥ ፍርድህም ቅን ነው። 138 ምስክርህን በጽድቅ አዘዝህ፥ እጅግም ቅን ነው። 139 ጠላቶቼ ቃልህን ረስተዋልና የቤትህ ቅንዓት አቀለጠኝ። 140 ቃልህ እጅግ የነጠረ ነው፥ ባሪያህም ወደደው። 141 እኔ ታናሽና የተናቅሁ ነኝ፤ ትእዛዛትህን ግን አልረሳሁም። 142 ጽድቅህ የዘላለም ጽድቅ ነው፥ ቃልህም እውነት ነው። 143 መከራና ችግር አገኙኝ፤ ትእዛዛትህ ግን ተድላዬ ናቸው። 144 ምስክርህ ለዘላለም ጽድቅ ነው፤ እንዳስተውል አድርገኝ፥ በሕይወትም አኑረኝ። 145 በፍጹም ልቤ ጮኽሁ፥ አቤቱ፥ ስማኝ፤ ሥርዓትህን እፈልጋለሁ። 146 ወደ አንተ ጮኽሁ፤ አድነኝ፥ ምስክርህንም እጠብቃለሁ። 147 ማለዳ ጮኽሁ፤ ቃልህንም ተስፋ አድርጌአለሁ። 148 ቃልህን አስብ ዘንድ ዓይኖቼ ለመማለድ ቀደሙ። 149 አቤቱ፥ እንደ ቸርነትህ ድምፄን ስማ፤ እንደ ፍርድህ ሕያው አድርገኝ። 150 በዓመፃ የሚያሳድዱኝ ቀረቡ፥ ከሕግህም ራቁ። 151 አቤቱ፥ አንተ ቅርብ ነህ፥ መንገዶችህም ሁሉ ቅኖች ናቸው። 152 ከዘላለም እንደ መሠረትኸው ከቀድሞ ጀምሮ ከምስክርህ የተነሣ አወቅሁ። 153 ሕግህን አልረሳሁምና ችግሬን ተመልከት አድነኝም። 154 ፍርዴን ፍረድ አድነኝም፤ ስለ ቃልህ ሕያው አድርገኝ። 155 መድኃኒት ከኅጥኣን ሩቅ ነው፥ ሥርዓትህን አልፈለጉምና። 156 አቤቱ፥ ቸርነትህ እጅግ ብዙ ነው፤ እንደ ፍርድህ ሕያው አድርገኝ። 157 ያሳደዱኝና ያስጨነቁኝ ብዙዎች ናቸው፤ ከምስክር ግን ፈቀቅ አላልሁም። 158 ቃልህን አልጠበቁምና ሰነፎችን አይቼ አዘንሁ። 159 ትእዛዝህን እንደ ወደድሁ ተመልከት፤ አቤቱ፥ በምሕረትህ ሕያው አድርገኝ። 160 የቃልህ መጀመሪያ እውነት ነው፥ የጽድቅህንም ፍርድ ሁሉ ለዘላለም ነው። 161 ገዢዎች በከንቱ አሳደዱኝ፤ ከቃልህ የተነሣ ግን ልቤ ደነገጠብኝ። 162 ብዙ ምርኮ እንዳገኘ በቃልህ ደስ አለኝ። 163 ዓመፃን ጠላሁ ተጸየፍሁም፤ ሕግን ግን ወደድሁ። 164 ስለ ጽድቅህ ፍርድ ሰባት ጊዜ በቀን አመሰግንሃለሁ። 165 ሕግህን ለሚወድዱ ብዙ ሰላም ነው፥ ዕንቅፋትም የለባቸውም። 166 አቤቱ፥ ማዳንህን ተስፋ አደርግሁ፥ ትእዛዛትህንም ጠበቅሁ። 167 ነፍሴ ምስክርህን ጠበቀች እጅግም ወደደችው። 168 መንገዶቼ ሁሉ በፊትህ ናቸውና ትእዛዝህንና ምስክርህን ጠበቅሁ። 169 አቤቱ፥ ጸሎቴ ወደ ፊትህ ትቅረብ፤ እንደ ቃልህም አስተዋይ አድርገኝ። 170 ልመናዬ ወደ ፊትህ ትድረስ፤ እንደ ቃልህ አድነኝ። 171 ሥርዓትህን አስተምረኸኛልና ከንፈሮቼ ምስጋናን አወጡ። 172 ትእዛዛትህ ሁሉ ጽድቅ ናቸውና አንደበቴ ቃልህን ተናገረ። 173 ትእዛዛትህን መርጫለሁና እጅህ የሚያድነኝ ይሁን። 174 አቤቱ፥ ማዳንህን ናፈቅሁ፤ ሕግህም ተድላዬ ነው። 175 ነፍሴ ትኑርልኝ ታመሰግንህማለች፥ ፍርድህም ይርዳኝ። 176 እንደ ጠፉ በግ ተቅበዘበዝሁ፤ ትእዛዛትህን አልረሳሁምና ባሪያህን ፈልገው። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
2 765
9
🗓 24/12/2018 እሁድ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 595⏳ መዝሙር ምዕራፍ 119 1 በመንገዳቸው ንጹሐን የሆኑ፥ በእግዚአብሔርም ሕግ የሚሄዱ ምስጉኖች ናቸው። 2 ምስክሩን የሚፈልጉ፥ በፍጹም ልብ የሚሹት ምስጉኖች ናቸው፤ 3 ዓመፅንም አያደርጉም፥ በመንገዶቹም ይሄዳሉ። 4 ትእዛዛትህን እጅግ እንጠብቅ ዘንድ አንተ አዘዝህ። 5 ሥርዓትህን ለመጠበቅ፤ መንገዶቼ ይቀኑ ዘንድ እወድድ ነበር። 6 ትእዛዝህን ሁሉ ስመለከት በዚያን ጊዜ አላፍርም። 7 አቤቱ፥ የጽድቅህን ፍርድ ስማር በቅን ልብ አመሰግንሃለሁ። 8 ሥርዓትህን እጠብቃለሁ፤ በፍጹም አትጣለኝ። 9 ጕልማሳ መንገዱን በምን ያነጻል? ቃልህን በመጠበቅ ነው። 10 በፍጹም ልቤ ፈለግሁህ፥ ከትእዛዝህ አታርቀኝ። 11 አንተ እንዳልበድል፥ ቃልህን በልቤ ሰወርሁ። 12 አቤቱ፥ አንተ ቡሩክ ነህ፤ ሥርዓትህን አስተምረኝ። 13 የአፍህን ፍርድ ሁሉ በከንፈሬ ነገርሁ። 14 እንደ ብልጥግና ሁሉ በምስክርህ መንገድ ደስ አለኝ። 15 ትእዛዝህን አሰላስላለሁ፥ መንገድህንም እፈልጋለሁ። 16 በትእዛዝህ ደስ ይለኛል፤ ቃልህንም አልረሳም። 17 ለባሪያህ መልካም አድርግ ሕያው እንድሆን፥ ቃልህንም እንድጠብቅ። 18 ዓይኖቼን ክፈት፥ ከሕግህም ተኣምራትህን አያለሁ። 19 እኔ በምድር እንግዳ ነኝ፤ ትእዛዛትህን ከእኔ አትሰውር። 20 ነፍሴ ሁልጊዜ ፍርድህን እጅግ ናፈቀች። 21 ከትእዛዛትህ የሳቱትን ትዕቢተኞችንና ርጉማንን ዘለፍህ። 22 ምስክርህን ፈልጌአለሁና። ስድብንና ነውርን ከእኔ አርቅ። 23 አለቆች ደግሞ ተቀምጠው እኔን አሙኝ፤ ባሪያህ ግን ሕግህን ያሰላስል ነበር። 24 ምስክርህም ተድላዬ ነው፥ ሥርዓትህም መካሪዬ ነው። 25 ነፍሴ ወደ ምድር ተጠጋች፤ እንደ ቃልህ ሕያው አድርገኝ። 26 መንገድህን ነገርሁ ሰማኸኝም፤ ሥርዓትህን አስተምረኝ። 27 የሥርዓትህን መንገድ እንዳስተውል አድርገኝ፥ ተኣምራትህንም አሰላስላለሁ። 28 ከኀዘን የተነሣ ነፍሴ አንቀላፋች፤ በቃልህ አጠንክረኝ። 29 የዓመፅን መንገድ ከእኔ አርቅ፥ በሕግህም ማረኝ፤ 30 የእውነትህን መንገድ መረጥሁ፥ ፍርድህንም አልረሳሁም። 31 አቤቱ፥ ምስክርህን ተጠጋሁ፤ አታሳፍረኝ። 32 ልቤን ባሰፋኸው ጊዜ፥ በትእዛዝህ መንገድ ሮጥሁ። 33 አቤቱ፥ የሥርዓትህን መንገድ አስተምረኝ፥ ሁልጊዜም እፈልገዋለሁ። 34 እንዳስተውል አድርገኝ፥ ሕግህንም እፈልጋለሁ፤ በፍጹም ልቤም እጠብቀዋለሁ። 35 እርስዋን ወድጃለሁና የትእዛዝህን መንገድ ምራኝ። 36 ልቤን ወደ ምስክርህ አዘንብል፥ ወደ ስስትም አይሁን። 37 ከንቱ ነገርን እንዳያዩ ዓይኖቼን መልስ፤ በመንገድህ ሕያው አድርገኝ። 38 እንዲፈራህ ባሪያህን በቃልህ አጽና። 39 ፍርድህ መልካም ናትና የተጠራጠርሁትን ስድብ ከእኔ አርቅ። 40 እነሆ፥ ትእዛዝህን ናፈቅሁ፤ በጽድቅህ ሕያው አድርገኝ 41 አቤቱ፥ እንደ ቃልህ፥ ምሕረትህና መድኃኒትህ ይምጡልኝ። 42 በቃልህ ታምኛለሁና ለሚሰድቡኝ በነገር እመልስላቸዋለሁ። 43 በፍርድህም ታምኛለሁና የእውነትን ቃል ከአፌ ፈጽመህ አታርቅ። 44 ለዘላለም ዓለም ሁልጊዜ ሕግህን እጠብቃለሁ። 45 ትእዛዛትህንም ፈልጌአለሁና አስፍቼ እሄዳለሁ። 46 በነገሥታት ፊት ምስክርህን እናገራለሁ፥ አላፍርምም፤ 47 እጅግም በወደድኋቸው በትእዛዛትህ ደስ ይለኛል። 48 እጆቼንም ወደ ወደድኋቸው ወደ ትእዛዛትህ አነሣለሁ፤ ሥርዓትህንም አሰላስላሁ። 49 ለባሪያህ ተስፋ ያስደረግኸውን ቃልህን አስብ። 50 ቃልህ ሕያው አድርጎኛልና ይህች በመከራዬ ደስ አሰኘችኝ። 51 ትዕቢተኞች እጅግ ዐመፁ፤ እኔ ግን ከሕግህ አልራቅሁም። 52 ከጥንት የነበረውን ፍርድህን አሰብሁ፥ አቤቱ፥ ተጽናናሁም። 53 ሕግህን ከተዉ ከኃጢአተኞች የተነሣ ኅዘን ያዘኝ። 54 በእንግድነቴ አገር ሥርዓትህ መዝሙር ሆነችኝ። 55 አቤቱ፥ በሌሊት ስምህን አሰብሁ፥ ሕግህንም ጠበቅሁ። 56 ትእዛዛትህንም ፈልጌአለሁና፤ ይህች ሆነችልኝ። 57 እግዚአብሔር ክፍሌ ነው፤ ሕግህን እጠብቃለሁ አልሁ። 58 በፍጹም ልቤ ወደ ፊትህ ተማለልሁ፤ እንደ ቃልህ ማረኝ። 59 ስለ መንገዶችህ አሰብሁ፥ እግሬንም ወደ ምስክሮችህ መለስሁ። 60 ትእዛዝህን ለመጠበቅ ጨከንሁ አልዘገየሁምም። 61 የኃጥኣን ገመዶች ተተበተቡብኝ፤ ሕግህን ግን አልረሳሁም። 62 ስለ ጽድቅህ ፍርድ፥ በእኩለ ሌሊት አመሰግንህ ዘንድ እነሣለሁ። 63 እኔ ለሚፈሩህ ሁሉ፥ ትእዛዝህንም ለሚጠብቁ ባልንጀራ ነኝ። 64 አቤቱ፥ ምሕረትህ በምድር ሁሉ ሞላች፤ ሥርዓትህን አስተምረኝ። 65 አቤቱ፥ እንደ ቃልህ ለባሪያህ መልካም አደረግህ። 66 በትእዛዛትህ ታምኛለሁና መልካም ምክርና እውቀትን አስተምረኝ። 67 እኔ ሳልጨነቅ ሳትሁ፤ አሁን ግን ቃልህን ጠበቅሁ። 68 አቤቱ፥ አንተ ቸር ነህ፥ በቸርነትህም ሥርዓትህን አስተምረኝ። 69 የትዕቢተኞች ዓመፅ በላዬ በዛ፤ እኔ ግን በፍጹም ልቤ ትእዛዛትህን እፈልጋለሁ። 70 ልባቸው እንደ ወተት ረጋ፤ እኔ ግን በሕግህ ደስ ይለኛል። 71 ሥርዓትህን እማር ዘንድ ያስጨነቅኸኝ መልካም ሆነልኝ። 72 ከአእላፋት ወርቅና ብር ይልቅ የአፍህ ሕግ ይሻለኛል። 73 እጆችህ ሠሩኝ አበጃጁኝም፤ እንዳስተውል አድርገኝ፥ ትእዛዛትህንም እማራለሁ። 74 በቃልህ ታምኛለሁና የሚፈሩህ እኔን አይተው ደስ ይላቸዋል። 75 አቤቱ፥ ፍርድህ ጽድቅ እንደ ሆነች፥ በእውነትህም እንዳስቸገርኸኝ አወቅሁ። 76 ምሕረትህ ለመጽናናቴ ትሁነኝ፥ እንደ ቃልህም ለባሪያህ ይሁነው። 77 ሕግህ ተድላዬ ናትና ቸርነትህ ትምጣልኝ፥ በሕይወትም ልኑር። 78 ትዕቢተኞች በዓመፅ ጠምመውብኛልና ይፈሩ፤ እኔ ግን በትእዛዝህ እጫወታለሁ። 79 የሚፈሩህና ምስክሮችህን የሚያውቁ ወደ እኔ ይመለሱ። 80 እንዳላፍር ልቤ በሥርዓትህ የቀና ይሁን። 81 ነፍሴ መድኃኒትህን ናፈቀች፤ በቃልህም ታመንሁ። 82 መቼ ታጽናናኛለህ እያልሁ ዓይኖቼ ስለ ቃልህ ፈዘዙ። 83 በጢስ እንዳለ አቁማዳ ሆኛለሁና፤ ሥርዓትህን ግን አልረሳሁም። 84 የባሪያህ ዘመኖች ስንት ናቸው? በሚያሳድዱኝስ ላይ መቼ ትፈርድልኛለህ? 85 ኃጢአተኞች ጨዋታን ነገሩኝ፥ አቤቱ፥ እንደ ሕግህ ግን አይደለም። 86 ትእዛዛትህ ሁሉ እውነት ናቸው፤ በዓመፅ አሳድደውኛል፤ እርዳኝ። 87 ከምድር ሊያጠፉኝ ጥቂት ቀርቶአቸው ነበር፤ እኔ ግን ትእዛዛትህን አልተውሁም። 88 እንደ ምሕረትህ ሕያው አድርገኝ፤ የአፍህንም ምስክር እጠብቃለሁ። 89 አቤቱ፥ ቃልህ በሰማይ ለዘላለም ይኖራል። 90 እውነትህ ለልጅ ልጅ ናት፤ ምድርን መሠረትሃት እርስዋም ትኖራለች። 91 ሁሉም ባሪያዎችህ ናቸውና ቀኑ በትእዛዝህ ይኖራል። 92 ሕግህ ተድላዬ ባይሆን፥ ቀድሞ በጐስቍልናዬ በጠፋሁ ነበር። 93 በእርሱ ሕያው አድርገኸኛልና ፍርድህን ለዘላለም አልረሳም። 94 እኔ የአንተ ነኝ፤ ፍርድህን ፈልጌአልሁና አድነኝ። 95 ኃጢአተኞች ያጠፉኝ ዘንድ ጠበቁኝ፤ ምስክርህን ግን መረመርሁ። 96 የሥራህን ሁሉ ፍጻሜ አየሁ፤ ትእዛዝህ ግን እጅግ ሰፊ ነው። 97 አቤቱ፥ ሕግህን እንደ ምን እጅግ ወደድሁ! ቀኑን ሁሉ እርሱ ትዝታዬ ነው። 98 ለዘላለም ለእኔ ነውና ትእዛዝህ ከጠላቶቼ ይልቅ አስተዋይ አደረገኝ። 99 ምስክርህ ትዝታዬ ነውና ካስተማሩኝ ሁሉ ይልቅ አስተዋልሁ። 100 ትእዛዝህን ፈልጌአለሁና ከሽማግሌዎች ይልቅ አስተዋልሁ። 101 ቃልህን እጠብቅ ዘንድ ከክፉ መንገድ ሁሉ እግሬን ከለከልሁ። 102 አስተምረኸኛልና ከፍርድህ አልራቅሁም። 103 ቃልህ ለጕሮሮዬ ጣፋጭ ነው፤ ከማርና ከወለላ ይልቅ ለአፌ ጣፈጠኝ።
1 129
10
No text...
709
11
🗓 23/12/2018 ቅዳሜ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 594⏳ መዝሙር ምዕራፍ 118 1 እግዚአብሔርን አመስግኑ፥ ቸር ነውና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ናትና። 2 ቸር እንደ ሆነ፥ ምሕረቱ ለዘላለም እንደ ሆነች የእስራኤል ቤት አሁን ይንገሩ። 3 ቸር እንደ ሆነ፥ ምሕረቱ ለዘላለም እንደ ሆነች የአሮን ቤት አሁን ይንገሩ። 4 ቸር እንደ ሆነ፥ ምሕረቱ ለዘላለም እንደ ሆነች እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሁሉ አሁን ይንገሩ። 5 በተጨነቅሁ ጊዜ እግዚአብሔርን ጠራሁት፤ ሰማኝ አሰፋልኝም። 6 እግዚአብሔር ረዳቴ ነው፥ አልፈራም ሰው ምን ያደርገኛል? 7 እግዚአብሔር ረዳቴ ነው፥ እኔም በጠላቶቼ ላይ አያለሁ። 8 በሰው ከመታመን ይልቅ በእግዚአብሔር መታመን ይሻላል። 9 በገዦች ተስፋ ከማድረግ ይልቅ በእግዚአብሔር ተስፋ ማድረግ ይሻላል። 10 አሕዛብ ሁሉ ከበቡኝ፥ በእግዚአብሔርም ስም አሸነፍኋቸው፤ 11 መክበቡንስ ከበቡኝ፥ በእግዚአብሔርም ስም አሸነፍኋቸው፤ 12 ንብ ማርን እንዲከብብ ከበቡኝ፥ እሳትም በእሾህ ውስጥ እንዲነድድ ነደዱ፥ በእግዚአብሔርም ስም አሸነፍኋቸው። 13 ገፋኸኝ፥ ለመውደቅም ተንገዳገድሁ፤ እግዚአብሔር ግን አገዘኝ። 14 ኃይሌም ዝማሬዬም እግዚአብሔር ነው፥ እርሱም መድኃኒት ሆነልኝ። 15 የእልልታና የመድኃኒት ድምፅ በጻድቃን ድንኳን ነው፤ የእግዚአብሔር ቀኝ ኃይልን አደረገች። 16 የእግዚአብሔር ቀኝ ከፍ ከፍ አደረገችኝ፤ የእግዚአብሔር ቀኝ ኃይልን አደረገች። 17 አልሞትም በሕይወት እኖራለሁ እንጂ፥ የእግዚአብሔርንም ሥራ እናገራለሁ። 18 መገሠጽስ እግዚአብሔር ገሠጸኝ፤ ለሞት ግን አልሰጠኝም። 19 የጽድቅን ደጆች ክፈቱልኝ፤ ወደ እነርሱ ገብቼ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ። 20 ይህች የእግዚአብሔር ደጅ ናት፤ ወደ እርስዋ ጻድቃን ይገባሉ። 21 ሰምተኸኛልና፥ መድኃኒትም ሆነኸኛልና አመሰግንሃለሁ። 22 ግንበኞች የናቁት ድንጋይ፥ እርሱ የማዕዘን ራስ ሆነ፥ 23 ይህች ከእግዚአብሔር ዘንድ ሆነች፥ ለዓይናችንም ድንቅ ናት። 24 እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት፤ ሐሤትን እናድርግ፥ በእርስዋም ደስ ይበለን። 25 አቤቱ፥ እባክህ፥ አሁን አድን፤ አቤቱ፥ እባክህ፥ አሁን አቅና። 26 በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው፤ ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ። 27 እግዚአብሔር አምላክ ነው፥ ለእኛም በራልን፤ እስከ መሠዊያው ቀንዶች ድረስ የበዓሉን መሥዋዕት በገመድ እሰሩት። 28 አንተ አምላኬ ነህ አመሰግንህማለሁ። አንተ አምላኬ ነህ፥ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ፤ ሰምተኸኛልና፥ መድኃኒትም ሆነኸኛልና አመሰግንሃለሁ። 29 እግዚአብሔርን አመስግኑ፥ ቸር ነውና፤ ምሕረቱ ለዘላለም ናትና። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
728
12
🗓 22/12/2018 አርብ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 593⏳ መዝሙር ምዕራፍ 117 1 አሕዛብ ሁላችሁ፥ እግዚአብሔርን አመስግኑት፥ ወገኖችም ሁሉ ያመስግኑት፤ 2 ምሕረቱ በእኛ ላይ ጸንታለችና፤ የእግዚአብሔርም እውነት ለዘላለም ትኖራለች። ሃሌ ሉያ። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
644
13
+8
No text...
800
14
+9
No text...
648
15
+9
No text...
524
16
+9
No text...
717
17
🗓 21/12/2018 ሀሙስ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 592⏳ መዝሙር ምዕራፍ 116 1 እግዚአብሔር የልመናዬን ድምፅ ሰምቶአልና ወደድሁት። 2 ጆሮውን ወደ እኔ አዘንብሎአልና በዘመኔ ሁሉ እጠራዋለሁ። 3 የሞት ጣር ያዘኝ፥ የሲኦልም ሕማም አገኘኝ፤ ጭንቀትንና መከራን አገኘሁ። 4 የእግዚአብሔርንም ስም ጠራሁ፡— አቤቱ፥ ነፍሴን አድናት። 5 እግዚአብሔር መሓሪና ጻድቅ ነው፥ አምላካችንም ይቅር ባይ ነው። 6 እግዚአብሔር ሕፃናትን ይጠብቃል፤ ተቸገርሁ እርሱም አዳነኝ። 7 ነፍሴ ሆይ፥ ወደ ዕረፍትሽ ተመለሺ፥ እግዚአብሔር መልካም አድርጎልሻልና፤ 8 ነፍሴን ከሞት፥ ዓይኔንም ከእንባ፥ እግሬንም ከመሰናከል አድኖአልና። 9 በሕያዋን አገር በእግዚአብሔር ፊት እሄዳለሁ። 10 አመንሁ ስለዚህም ተናገርሁ፤ እኔም እጅግ ተቸገርሁ። 11 እኔም ከድንጋጤዬ የተነሣ፡— ሰው ሁሉ ሐሰተኛ ነው፡ አልሁ። 12 ስላደረገልኝ ሁሉ ለእግዚአብሔር ምንን እመልሳለሁ? 13 የመድኃኒትን ጽዋ እቀበላለሁ፥ የእግዚአብሔርንም ስም እጠራለሁ። 14 በሕዝቡ ሁሉ ፊት ስእለቴን ለእግዚአብሔር እፈጽማለሁ። 15 የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው። 16 አቤቱ፥ እኔ ባሪያህ ነኝ፥ ባሪያህ ነኝ፥ የሴት ባሪያህም ልጅ ነኝ፤ ሰንሰለቴን ሰበርህ። 17 ለአንተ የምስጋና መሥዋዕትን እሠዋለሁ፥ የእግዚአብሔርንም ስም እጠራለሁ። 18 በሕዝቡ ሁሉ ፊት ስእለቴን ለእግዚአብሔር እፈጽማለሁ፥ 19 በእግዚአብሔር ቤት አደባባይ፥ ኢየሩሳሌም ሆይ፥ በመካከልሽም። ሃሌሉያ 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
428
18
🗓 20/12/2018 ዕሮብ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 591⏳ መዝሙር ምዕራፍ 115 1 ለእኛ አይደለም፥ አቤቱ፥ ለእኛ አይደለም፥ ነገር ግን ለስምህ ስለ ምሕረትህ ስለ እውነትህም ምስጋናን ስጥ። 2 አሕዛብ፡— አምላካቸው ወዴት ነው? አይበሉ። 3 አምላካችንስ በላይ በሰማይ ነው፤ በሰማይም በምድርም የፈቀደውን ሁሉ አደረገ። 4 የአሕዛብ ጣዖታቶች የወርቅና የብር፥ የሰው እጅ ሥራ ናቸው። 5 አፍ አላቸው አይናገሩምም፤ ዓይን አላቸው አያዩምም፤ 6 ጆሮ አላቸው አይሰሙምም፤ አፍንጫ አላቸው አያሸትቱምም፤ 7 እጅ አላቸው አይዳሰሱምም፤ እግር አላቸው አይሄዱምም፤ በጕሮሮአቸውም አይናገሩም። 8 የሚሠሩአቸውም የሚያምኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ። 9 የእስራኤል ቤት ሆይ፥ በእግዚአብሔር ታመኑ፤ ረድኤታቸውና መታመኛቸው እርሱ ነው። 10 የአሮን ቤት ሆይ፥ በእግዚአብሔር ታመኑ ረድኤታቸውና መታመኛቸው እርሱ ነው። 11 እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሆይ፥ በእግዚአብሔር ታመኑ፤ ረድኤታቸውና መታመኛቸው እርሱ ነው። 12 እግዚአብሔር አሰበን ይባርከንማል፤ የእስራኤልን ቤት ይባረካል፥ የአሮንንም ቤት ይባረካል። 13 እግዚአብሔርን የሚፈሩትን፥ ትንንሾችንና ትልልቆችን ይባርካል። 14 እግዚአብሔር በላያችሁ፥ በላያችሁና በልጆቻችሁ ላይ ይጨምር። 15 እናንተ ሰማይንና ምድርን ለሠራ ለእግዚአብሔር የተባረካችሁ ናችሁ። 16 የሰማያት ሰማይ ለእግዚአብሔር ነው፤ ምድርን ግን ለሰው ልጆች ሰጣት። 17 አቤቱ፥ ሙታን የሚያመሰግኑህ አይደሉም ወደ ሲኦልም የሚወርዱ ሁሉ፤ 18 እኛ ሕያዋን ግን ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም እግዚአብሔርን እንባርካለን። ሃሌ ሉያ። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
453
19
No text...
423
20
🗓 19/12/2018 ማክሰኞ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 590⏳ መዝሙር ምዕራፍ 114 1 እስራኤል ከግብፅ፥ የያዕቆብም ቤት ከእንግዳ ሕዝብ በወጣ ጊዜ፥ 2 ይሁዳ መቅደሱ፥ እስራኤልም ግዛቱ ሆነ። 3 ባሕር አየች ሸሸችም፥ ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ። 4 ተራሮች እንደ ኮርማዎች፥ ኮረብቶችም እንደ ጠቦቶች ዘለሉ። 5 አንቺ ባሕር የሸሸሽ፥ አንቺም ዮርዳኖስ ወደ ኋላሽ የተመለስሽ፥ ምን ሆናችኋል? 6 እናንተም ተራሮች፥ እንደ ኮርማዎች፥ ኮረብቶችስ፥ እንደ ጠቦቶች ለምን ዘለላችሁ? 7 ከያዕቆብ አምላክ ፊት፥ ከጌታ ፊት ምድር ተናወጠች፤ 8 ድንጋዩን ወደ ውኃ መቆሚያ፥ ጭንጫውንም ወደ ውኃ ምንጭ ከለወጠ። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
425