uk
Feedback
ሰሜን ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን ✨ Semien Full Gospel Local Church

ሰሜን ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን ✨ Semien Full Gospel Local Church

Відкрити в Telegram
1 168
Підписники
+324 години
+97 днів
+4130 день

Триває завантаження даних...

Хмара тегів
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Вхідні та вихідні згадування
---
---
---
---
---
---
Залучення підписників
серпень '26
серпень '26
+6
в 0 каналах
липень '26
+76
в 0 каналах
Get PRO
червень '26
+40
в 0 каналах
Get PRO
травень '26
+26
в 0 каналах
Get PRO
квітень '26
+22
в 0 каналах
Get PRO
березень '26
+21
в 0 каналах
Get PRO
лютий '26
+11
в 0 каналах
Get PRO
січень '26
+17
в 0 каналах
Get PRO
грудень '25
+16
в 0 каналах
Get PRO
листопад '25
+49
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '25
+26
в 0 каналах
Get PRO
вересень '25
+33
в 0 каналах
Get PRO
серпень '25
+38
в 0 каналах
Get PRO
липень '25
+18
в 0 каналах
Get PRO
червень '25
+18
в 0 каналах
Get PRO
травень '25
+26
в 0 каналах
Get PRO
квітень '25
+50
в 0 каналах
Get PRO
березень '25
+146
в 0 каналах
Get PRO
лютий '25
+18
в 0 каналах
Get PRO
січень '25
+186
в 0 каналах
Get PRO
грудень '24
+63
в 0 каналах
Get PRO
листопад '24
+39
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '24
+33
в 0 каналах
Get PRO
вересень '24
+51
в 0 каналах
Get PRO
серпень '24
+39
в 0 каналах
Get PRO
липень '24
+28
в 0 каналах
Get PRO
червень '24
+43
в 0 каналах
Get PRO
травень '24
+45
в 0 каналах
Get PRO
квітень '24
+61
в 0 каналах
Get PRO
березень '24
+39
в 0 каналах
Get PRO
лютий '24
+354
в 0 каналах
Дата
Залучення підписників
Згадування
Канали
02 серпня0
01 серпня+6
Дописи каналу
🗓 26/11/2018 እሁድ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 567⏳ መዝሙር ምዕራፍ 91 1 በልዑል መጠጊያ የሚኖር ሁሉን በሚችል አምላክ ጥላ ውስጥ ያድራል። 2 እግዚአብሔርን፡— አንተ መታመኛዬ ነህ፡ እለዋለሁ፤ አምላኬና መሸሸጊያዬ ነው፥ በእርሱም እታመናለሁ። 3 እርሱ ከአዳኝ ወጥመድ ከሚያስደነግጥም ነገር ያድንሃልና። 4 በላባዎቹ ይጋርድሃል፥ በክንፎቹም በታች ትተማመናለህ፤ እውነት እንደ ጋሻ ይከብብሃል። 5 ከሌሊት ግርማ፥ በቀን ከሚበርር ፍላጻ፥ 6 በጨለማ ከሚሄድ ክፉ ነገር፥ ከአደጋና ከቀትር ጋኔን አትፈራም። 7 በአጠገብህ ሺህ በቀኝህም አሥር ሺህ ይወድቃሉ፤ ወደ አንተ ግን አይቀርብም። 8 በዓይኖችህ ብቻ ትመለከታለህ፥ የኃጥኣንንም ብድራት ታያለህ። 9 አቤቱ፥ አንተ ተስፋዬ ነህና፤ ልዑልን መጠጊያህ አደረግህ። 10 ክፉ ነገር ወደ አንተ አይቀርብም፥ መቅሠፍትም ወደ ቤትህ አይገባም። 11 በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤ 12 እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል። 13 በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ። 14 በእኔ ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ፤ ስሜንም አውቆአልና እጋርደዋለሁ። 15 ይጠራኛል እመልስለትማለሁ፥ በመከራውም ጊዜ ከእርሱ ጋራ እሆናለሁ፤ አድነዋለሁ አከብረውማለሁ። 16 ረጅምን ዕድሜ አጠግበዋለሁ፥ ማዳኔንም አሳየዋለሁ። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook

2
🗓 25/11/2018 ቅዳሜ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 566⏳ መዝሙር ምዕራፍ 90 1 አቤቱ፥ አንተ ለትውልድ ሁሉ መጠጊያ ሆንህልን። 2 ተራሮች ሳይወለዱ፥ ምድርም ዓለምም ሳይሠሩ፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ አንተ ነህ። 3 ሰውን ወደ ኅሳር አትመልስም፤ የሰው ልጆች ሆይ፥ ተመለሱ ትላለህ፤ 4 ሺህ ዓመት በፊትህ እንዳለፈች እንደ ትናንት ቀን፥ እንደ ሌሊትም ትጋት ነውና። 5 ዘመኖች የተናቁ ይሆናሉ፥ በማለዳም እንደ ሣር ያልፋል። 6 ማልዶ ያብባል ያልፋልም፥ በሠርክም ጠውልጎና ደርቆ ይወድቃል። 7 እኛ በቍጣህ አልቀናልና፥ በመዓትህም ደንግጠናልና። 8 የተሰወረውን ኃጢአታችንን በፊትህ ብርሃን፥ በደላችንንም በፊትህ አስቀመጥህ። 9 ዘመናችን ሁሉ አልፎአልና፥ እኛም በመዓትህ አልቀናልና፤ ዘመኖቻችንም እንደ ሸረሪት ድር ይሆናሉ። 10 የዘመኖቻችንም ዕድሜ ሰባ ዓመት፥ ቢበረታም ሰማንያ ዓመት ነው፤ ቢበዛ ግን ድካምና መከራ ነው፤ ከእኛ ቶሎ ያልፋልና፥ እኛም እንገሠጻለንና። 11 የቍጣህን ጽናት ማን ያውቃል? ከቍጣህ ግርማ የተነሣ አለቁ። 12 በልብ ጥበብን እንድንማር፥ ቀኝህን እንዲህ አስታውቀን። 13 አቤቱ፥ ተመለስ፥ እስከ መቼስ ነው? ስለ ባሪያዎችህም ተምዋገት። 14 በማለዳ ምሕረትህን እንጠግባለን፤ በዘመናችን ሁሉ ደስ ይለናል ሐሤትም እናደርጋለን። 15 መከራ ባሳየኸን ዘመን ፈንታ፥ ክፉም ባየንባቸው ዘመኖች ፋንታ ደስ ይለናል። 16 ባሪያዎችህንና ሥራህን እይ፥ ልጆቻቸውንም ምራ። 17 የአምላካችን የእግዚአብሔር ብርሃን በላያችን ይሁን። የእጆቻችንንም ሥራ በላያችን አቅና። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
197
3
Немає тексту...
263
4
🗓 24/11/2018 አርብ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 565⏳ መዝሙር ምዕራፍ 89 1 አቤቱ፥ ምሕረትህን ለዘላለም እዘምራለሁ፥ እውነትህንም በአፌ ለልጅ ልጅ እናገራለሁ። 2 እንዲህ ብለሃልና፡— ምሕረት ለዘላለም ይመሠረታል፥ እውነትህም በሰማይ ይጸናል። 3 ከመረጥሁት ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ፥ ለባሪያዬም ለዳዊት ማልሁ፡— 4 ዘርህን ለዘላለም አዘጋጃለሁ፥ ዙፋንህንም ለልጅ ልጅ እመሠርታለሁ። 5 አቤቱ፥ ሰማያት ተኣምራትህን እውነትህንም ደግሞ በቅዱሳን ማኅበር ያመሰግናሉ። 6 እግዚአብሔርን በሰማይ የሚተካከለው ማን ነው? ከአማልክትስ ልጆች እግዚአብሔርን ማን ይመስለዋል? 7 በቅዱሳን ምክር እግዚአብሔር ክቡር ነው፤ በዙሪያው ባሉት ሁሉ ላይ ታላቅና ግሩም ነው። 8 አቤቱ የሠራዊት አምላክ፥ እንደ አንተ ያለ ማን ነው? አቤቱ፥ አንተ ብርቱ ነህ፥ እውነትህም ይከብብሃል። 9 የባሕርን ኃይል አንተ ትገዛለህ፥ የሞገዱንም መናወጥ አንተ ዝም ታሰኘዋለህ። 10 አንተ ረዓብን እንደ ተገደለ አዋረድኸው፥ በኃይልህም ክንድ ጠላቶችህን በተንሃቸው። 11 ሰማያት የአንተ ናቸው፥ ምድርም የአንተ ናት፤ ዓለምንና ሞላውም አንተ መሠረትህ። 12 ሰሜንና ደቡብን አንተ ፈጠርህ፤ ታቦርና አርሞንዔም በስምህ ደስ ይላቸዋል። 13 ክንድህ ከኃይልህ ጋር ነው፤ እጅህ በረታች ቀኝህም ከፍ ከፍ አለች። 14 የዙፋንህ መሠረት ጽድቅና ፍርድ ነው፤ ምሕረትና እውነት በፊትህ ይሄዳሉ። 15 እልልታ የሚያውቅ ሕዝብ ምስጉን ነው፤ አቤቱ፥ በፊትህ ብርሃን ይሄዳሉ። 16 በስምህ ቀኑን ሁሉ ደስ ይላቸዋል፥ በጽድቅህም ከፍ ከፍ ይላሉ፤ 17 የኃይላቸው ትምክሕት አንተ ነህና፥ በሞገስህም ቀንዳችን ከፍ ከፍ ይላልና። 18 ረድኤታችን ከእግዚአብሔር ከንጉሣችንም ከእስራኤል ቅዱስ ነውና። 19 በዚያ ጊዜ ለልጆችህ በራእይ ተናገርህ እንዲህም አልህ፡— ረድኤቴን በኃይል ላይ አኖርሁ፤ ከሕዝቤ የተመረጠውን ከፍ ከፍ አደረግሁ። 20 ባሪያዬን ዳዊትን አገኘሁት፥ ቅዱስ ዘይትም ቀባሁት። 21 እጄም ትረዳዋለች፥ ክንዴም ታጸናዋለች። 22 ጠላት በእርሱ ላይ አይጠቀምም፥ የዓመፃ ልጅም መከራ አይጨምርበትም። 23 ጠላቶቹን ከፊቱ አጠፋለሁ፥ የሚጠሉትንም አዋርዳቸዋለሁ። 24 እውነቴና ምሕረቴም ከእርሱ ጋር ነው፥ በስሜም ቀንዱ ከፍ ከፍ ይላል። 25 እጁን በባሕር ላይ ቀኙንም በወንዞች ላይ አኖራለሁ። 26 እርሱ፡— አባቴ አንተ ነህ፥ አምላኬ የመድኃኒቴም መጠጊያ፡ ይላል። 27 እኔም ደግሞ በኵሬ አደርገዋለሁ፥ ከምድር ነገሥታትም ከፍ ይላል። 28 ለዘላለምም ምሕረቴን ለእርሱ እጠብቃለሁ፥ ኪዳኔም በእርሱ ዘንድ የታመነ ነው። 29 ዘሩንም ለዓለምና ለዘላለም፥ ዙፋኑንም እንደ ሰማይ ዘመን አደርጋለሁ። 30 ልጆቹ ግን ሕጌን ቢተዉ፥ በፍርዴም ባይሄዱ፤ 31 ሥርዓቴንም ቢያረክሱ፥ ትእዛዜንም ባይጠብቁ፤ 32 ኃጢአታቸውን በበትር፥ በደላቸውንም በመቅሠፍት እጐበኛታለሁ። 33 ምሕረቴን ግን ከእርሱ አላርቅም፥ በእውነቴም አልበድልም፤ 34 ኪዳኔንም አላረክስም፥ ከከንፈሬም የወጣውን አልለውጥም። 35 ዳዊትን እንዳልዋሸው አንድ ጊዜ በቅዱስነቴ ማልሁ። 36 ዘሩ ለዘላለም፥ ዙፋኑም በፊቴ እንደ ፀሐይ ይኖራል። 37 ለዘላለም እንደ ጨረቃ ይጸናል፤ ምስክርነቱ በሰማይ የታመን ነው። 38 አንተ ግን ናቅኸው ጣልኸውም፥ የቀባኸውንም ጣልኸው። 39 የባሪያህንም ኪዳን አፈረስህ፥ መቅደሱንም በምድር አረከስህ። 40 ቅጥሩን ሁሉ ጣልህ፥ አምባዎቹንም አጠፋህ። 41 መንገድ አላፊም ሁሉ ተናጠቀው፥ ለጎረቤቶቹም ስድብ ሆነ። 42 የጠላቶቹንም ቀኝ ከፍ ከፍ አደረግህ፥ ጠላቶቹንም ሁሉ ደስ አሰኘህ። 43 የሰይፉንም ረድኤት መለስህ፥ በሰልፍም ውስጥ አልደገፍኸውም። 44 ከንጽሕናውም ሻርኸው፥ ዙፋኑንም በምድር ጣልህ። 45 የዙፋኑንም ዘመን አሳነስህ፥ በእፍረትም ሸፈንኸው። 46 አቤቱ፥ እስከ መቼ ለዘላለም ፊትህን ትመልሳለህ? እስከ መቼስ ቍጣህ እንደ እሳት ይነድዳል? 47 ችሎታዬ ምን እንደ ሆነ አስብ፤ በውኑ የሰውን ልጅ ሁሉ ለከንቱ ፈጠርኸውን? 48 ሕያው ሆኖ የሚኖር፥ ሞትንስ የማያይ ማን ነው? ነፍሱንስ ከሲኦል እጅ የሚያድን ማን ነው? 49 ለዳዊት በእውነት የማልህ፥ አቤቱ፥ የቀድሞ ምሕረትህ ወዴት ነው? 50 አቤቱ፥ የባሪያዎችህን ስድብ፥ በብብቴ ብዙ አሕዛብን የተቀበልሁትን፥ 51 አቤቱ፥ ጠላቶችህን የሰደቡትን የቀባኸውን ዘመን የሰደቡትን አስብ። 52 እግዚአብሔር ለዘላለም ይባረክ። ይሁን ይሁን። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
261
5
+4
Немає тексту...
289
6
+9
Немає тексту...
269
7
+9
Немає тексту...
223
8
+8
Немає тексту...
253
9
+9
Немає тексту...
194
10
19/11/2018 ፓስተር አበራ በላይ ኢየሱስን እንዴት እንጠበቅ? 1 ተሰሎንቄ 5:1-11 1 ወንድሞች ሆይ፥ ስለ ዘመናትና ስለ ወራት ምንም እንዲጻፍላችሁ አያስፈልጋችሁም፤ 2 የጌታ ቀን፥ ሌባ በሌሊት እንደሚመጣ፥ እንዲሁ ይመጣ ዘንድ ራሳችሁ አጥብቃችሁ አውቃችኋልና። 3 ሰላምና ደኅንነት ነው ሲሉ ያን ጊዜ ምጥ እርጕዝን እንደሚይዛት ጥፋት በድንገት ይመጣባቸዋል ከቶም አያመልጡም። 4 እናንተ ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ቀኑ እንደ ሌባ ይደርስባችሁ ዘንድ በጨለማ አይደላችሁም፥ 5 ሁላችሁ የብርሃን ልጆች የቀንም ልጆች ናችሁና። እኛ ከሌሊት ወይም ከጨለማ አይደለንም፤ 6 እንግዲያስ እንንቃ በመጠንም እንኑር እንጂ እንደ ሌሎች አናንቀላፋ። 7 የሚያንቀላፉ በሌሊት ያንቀላፋሉና፥ የሚሰክሩም በሌሊት ይሰክራሉና፤ 8 እኛ ግን ከቀን ስለ ሆንን፥ የእምነትንና የፍቅርን ጥሩር የመዳንንም ተስፋ እንደ ራስ ቁር እየለበስን በመጠን እንኑር፤ 9 እግዚአብሔር ለቍጣ አልመረጠንምና፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መዳንን ለማግኘት ነው እንጂ። 10 የምንነቃም ብንሆን፥ የምናንቀላፋም ብንሆን፥ ከእርሱ ጋር አብረን በሕይወት እንኖር ዘንድ ስለ እኛ ሞተ። 11 ስለዚህ እናንተ ደግሞ እንደምታደርጉ፥ እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ አንዱም አንዱም ሌላውን ያንጸው። • የጌታ አመጣጥ 1. እንደ ሌባ ነው። (....ሌባ በሌሊት እንደሚመጣ፥ እንዲሁ ይመጣ....) 2. እንደ ምጥ ነው። (ምጥ እርጕዝን እንደሚይዛት ጥፋት በድንገት ይመጣባቸዋል) 3. እንደ ወጥመድ ነው። (❨ሉቃስ 21:35❩በምድር ሁሉ ላይ በሚቀመጡ ሁሉ እንደ ወጥመድ ይደርስባቸዋልና።) ራእይ 22:12 “እነሆ፥ በቶሎ እመጣለሁ፥ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ። ማቴዎስ 16:27 “የሰው ልጅ ከመላእክቱ ጋር በአባቱ ክብር ይመጣ ዘንድ አለውና፤ ያን ጊዜም ለሁሉ እንደ ሥራው ያስረክበዋል። ፨ እንዴት እንጠብቀው? ፩, በንቃት እንግዲያስ እንንቃ በመጠንም እንኑር እንጂ እንደ ሌሎች አናንቀላፋ። (1 ተሰሎንቄ 5፡6) ፪, በመታጠቅ እኛ ግን ከቀን ስለ ሆንን፥ የእምነትንና የፍቅርን ጥሩር የመዳንንም ተስፋ እንደ ራስ ቁር እየለበስን በመጠን እንኑር፤ (1 ተሰሎንቄ 5፡8) ፫, እርስ በርስ በመተናነፅ ስለዚህ እናንተ ደግሞ እንደምታደርጉ፥ እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ አንዱም አንዱም ሌላውን ያንጸው። (1 ተሰሎንቄ 5፡11) ራእይ 22:7 “እነሆም፥ በቶሎ እመጣለሁ። የዚህን መጽሐፍ ትንቢት ቃል የሚጠብቅ ብፁዕ ነው፡” አለኝ። ራእይ 22:20 ይህን የሚመሰክር፦ “አዎን፥ በቶሎ እመጣለሁ፡” ይላል። አሜን፥ ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ና።
193
11
+4
Немає тексту...
1
12
+9
Немає тексту...
1
13
+9
Немає тексту...
1
14
+8
Немає тексту...
1
15
+9
Немає тексту...
1
16
🗓 23/11/2018 ሀሙስ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 564⏳ መዝሙር ምዕራፍ 88 1 አቤቱ፥ የመድኃኒቴ አምላክ፥ በቀንና በሌሊት በፊትህ ጮኽሁ፤ 2 ጸሎቴ ወደ ፊትህ ትግባ፥ ጆሮህንም ወደ ጩኸቴ አዘንብል፤ 3 ነፍሴ መከራን ጠግባለችና፥ ሕይወቴም ወደ ሲኦል ቀርባለችና። 4 ወደ ጓድጓድ ከሚወርዱ ጋር ተቈጠርሁ፥ ረዳትም እንደሌለው ሰው ሆንሁ። 5 ለዘላለም እንደማታስባቸው፥ እንደ ተገደሉና በመቃብር ውስጥ እንደ ተጣሉ፥ በሙታን ውስጥ እንዳሉ የተጣልሁ ሆንሁ፤ እነርሱም ከእጅህ ተለዩ። 6 በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ፥ በታችኛው ጕድጓድ አስቀመጥኸኝ። 7 በእኔ ላይ ቍጣህ ጸና፥ መቅሠፍትህን ሁሉ በእኔ ላይ አመጣህ። 8 የሚያውቁኝን ከእኔ አራቅህ፤ በእነርሱ ዘንድ ርኵስ አደረግኸኝ፤ ያዙኝ፥ መውጫም የለኝም። 9 ዓይኖቼም በመከራ ፈዘዙ፤ አቤቱ፥ ሁልጊዜ ወደ አንተ ጮኽሁ፥ እጆቼንም ወደ አንተ ዘረጋሁ፥ 10 በውኑ ለሙታን ተኣምራት ታደርጋለህን? የሞቱትስ ተነሥተው ያመሰግኑሃልን? 11 በመቃብርስ ውስጥ ቸርነትህን፥ እውነትህንስ በጥፋት ስፍራ ይናገራሉን? 12 ተአምራትህ በጨለማ፥ ጽድቅህንም በመርሳት ምድር ትታወቃለችን? 13 አቤቱ፥ እኔ ግን ወደ አንተ ጮኽሁ፤ በጥዋት ጸሎቴ ወደ ፊትህ ትደርሳለች። 14 አቤቱ፥ ነፍሴን ለምን ትጥላለህ? ፊትህንስ ከእኔ ለምን ትሰውራለህ? 15 እኔ ከታናሽነቴ ችግረኛ ለሞትም የቀረብሁ ነኝ፤ ከፍ ከፍ ካልሁ በኋላ ግን ተዋረድሁ ተናቅሁም። 16 መቅሠፍትህ በላዬ አለፈ፥ ግርማህም አስደነገጠኝ። 17 ሁልጊዜ እንደ ውኃ ከበቡኝ፥ በአንድነትም ያዙኝ። 18 ወዳጄንና ባልንጀራዬን ዘመዶቼንም ከመከራ የተነሣ ከእኔ አራቅህ። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
221
17
Немає тексту...
302
18
🗓 22/11/2018 ዕሮብ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 563⏳ መዝሙር ምዕራፍ 87 1 መሠረቶቹ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው፤ 2 ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ፥ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወድዳቸዋል። 3 የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ፥ በአንቺ የተከበረ ነገር ይባላል። 4 የሚያውቁኝን ረዓብንና ባቢሎንን አስባቸዋለሁ፤ እነሆ፥ ፍልስጥኤማውያን ጢሮስም የኢትዮጵያም ሕዝብ፥ እነዚህ በዚያ ተወለዱ። 5 ሰው እናታችን ጽዮን ይላል፥ በውስጥዋም ሰው ተወለደ፤ እርሱ ራሱም ልዑል መሠረታት። 6 እግዚአብሔር ለሕዝቡ፥ በውስጥዋም ለተወለዱት አለቆችዋ በመጽሐፍ ይነግራቸዋል። 7 በአንቺ የሚኖሩ ሁሉ ደስ እንደሚላቸው ይነግራቸዋል። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
301
19
🗓 21/11/2018 ማክሰኞ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 562⏳ መዝሙር ምዕራፍ 86 1 አቤቱ፥ ጆሮህን ወደ እኔ አዘንብል አድምጠኝም፥ ችግረኛና ምስኪን ነኝና። 2 ቅዱስ ነኝና ነፍሴን ጠብቅ፤ አምላኬ ሆይ፥ አንተን የታመነውን ባሪያህን አድነው። 3 አቤቱ፥ ቀኑን ሁሉ ወደ አንተ እጮኻለሁና ማረኝ። 4 የባሪያህን ነፍስ ደስ አሰኛት፥ አቤቱ፥ ነፍሴን ወደ አንተ አነሣለሁና። 5 አቤቱ፥ አንተ መሓሪና ይቅር ባይ ነህና፥ ምሕረትህም ለሚጠሩህ ሁሉ ብዙ ነውና። 6 አቤቱ፥ ጸሎቴን አድምጥ፥ የልመናዬንም ድምፅ ስማ። 7 ትመልስልኛለህና በመከራዬ ቀን ወደ አንተ እጠራለሁ። 8 አቤቱ፥ ከአማልክት የሚመስልህ የለም፥ እንደ ሥራህም ያለ የለም። 9 ያደረግሃቸው አሕዛብ ሁሉ ይመጣሉ፥ አቤቱ፥ በፊትህም ይሰግዳሉ፥ ስምህንም ያከብራሉ፤ 10 አቤቱ፥ ድንቅ የምታደርግ አንተ ታላቅ ነህና፥ አንተም ብቻህን ታላቅ አምላክ ነህና። 11 አቤቱ፥ መንገድህን ምራኝ፥ በእውነትህም እሄዳለሁ፤ ስምህን ለመፍራት ልቤ ደስ ይለዋል። 12 አቤቱ አምላኬ ሆይ፥ በልቤ ሁሉ አመሰግንሃለሁ፥ ለዘላለምም ስምህን አከብራለሁ፤ 13 ምሕረትህ በእኔ ላይ ታላቅ ናትና፥ ነፍሴንም ከታችኛይቱ ሲኦል አድነሃታልና። 14 አቤቱ፥ ዓመፀኞች በእኔ ላይ ተነሥተዋል፥ የክፉዎችንም ማኅበር ነፍሴን ፈለጉአት፤ በፊታቸውም አላደረጉህም። 15 አቤቱ፥ አንተ ግን መሓሪና ርኅሩኅ አምላክ ነህ፤ መዓትህ የራቀ ምሕረትህም እውነትህም የበዛ፤ 16 ወደ እኔ ተመልከት ማረኝም፤ ለባሪያህ ኃይልህን ስጥ፥ የሴት ባሪያህንም ልጅ አድን። 17 ምልክትንም ለመልካም ከእኔ ጋር አድርግ፤ የሚጠሉኝ ይዩ ይፈሩም፥ አቤቱ፥ አንተ ረድተኸኛልና፥ አጽንተኸኛልምና። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
316
20
🗓 20/11/2018 ሰኞ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 561⏳ መዝሙር ምዕራፍ 85 1 አቤቱ፥ ለምድርህ ሞገስን አደረግህ፥ የያዕቆብንም ምርኮ መለስህ። 2 የሕዝብህን ኃጢአት አስቀረህ፥ አበሳቸውንም ሁሉ ከደንህ። 3 መዓትህንም ሁሉ አስወገድህ፤ ከቍጣህ መቅሠፍት ተመለስህ። 4 የመድኃኒታችን አምላክ ሆይ፥ መልሰን፥ ቍጣህንም ከእኛ መልስ። 5 በውኑ ለዘላለም ትቈጣናለህን? ቍጣህንስ ለልጅ ልጅ ታስረዝማለህን? 6 አቤቱ፥ ትመለሳለህ ታድነንማለህ፤ ሕዝቡም በአንተ ደስ ይላቸዋል። 7 አቤቱ፥ ምሕረትህን አሳየን፥ አቤቱ፥ መድኃኒትህንም ስጠን። 8 እግዚአብሔር አምላክ የሚናገረውን እሰማለሁ፤ ሰላምን ለሕዝቡና ለቅዱሳኑ ልባቸውንም ወደ እርሱ ለሚመልሱ ይናገራልና። 9 ነገር ግን ክብር በምድራችን ያድር ዘንድ ማዳኑ ለሚፈሩት ቅርብ ነው፤ 10 ምሕረትና እውነት ተገናኙ፤ ጽድቅና ሰላም ተስማሙ። 11 እውነት ከምድር በቀለች፥ ጽድቅም ከሰማይ ተመለከተች። 12 እግዚአብሔርም በጎ ነገርን ይሰጣል፥ ምድራችንም ፍሬዋን ትሰጣለች። 13 ጽድቅ በፊቱ ይሄዳል፥ ፍለጋውንም በመንገድ ውስጥ ያኖራል። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
350