ar
Feedback
ሰሜን ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን ✨ Semien Full Gospel Local Church

ሰሜን ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን ✨ Semien Full Gospel Local Church

الذهاب إلى القناة على Telegram
1 159
المشتركون
+124 ساعات
+27 أيام
+4630 أيام

جاري تحميل البيانات...

سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
يوليو '26
يوليو '26
+60
في 0 قنوات
يونيو '26
+40
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '26
+26
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+22
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '26
+21
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+11
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '26
+17
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+16
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+49
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '25
+26
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '25
+33
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '25
+38
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '25
+18
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '25
+18
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '25
+26
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '25
+50
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '25
+146
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '25
+18
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '25
+186
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '24
+63
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '24
+39
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '24
+33
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '24
+51
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '24
+39
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '24
+28
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '24
+43
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '24
+45
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '24
+61
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '24
+39
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '24
+354
في 0 قنوات
التاريخ
نمو المشتركين
الإشارات
القنوات
25 يوليو+4
24 يوليو+2
23 يوليو+2
22 يوليو+1
21 يوليو+1
20 يوليو+1
19 يوليو+1
18 يوليو+2
17 يوليو+2
16 يوليو0
15 يوليو+2
14 يوليو+1
13 يوليو+6
12 يوليو+3
11 يوليو+5
10 يوليو+1
09 يوليو+3
08 يوليو+2
07 يوليو+2
06 يوليو+5
05 يوليو+3
04 يوليو+2
03 يوليو+4
02 يوليو+3
01 يوليو+2
منشورات القناة
🗓 18/11/2018 ቅዳሜ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 559⏳ መዝሙር ምዕራፍ 83 1 አቤቱ፥ እንደ አንተ ማን ነው? አቤቱ፥ ዝም አትበል፥ ቸልም አትበል። 2 እነሆ፥ ጠላቶችህ ጮኽዋልና፥ የሚጠሉህም ራሳቸውን አንሥተዋልና። 3 ሕዝብህን በምክር ሸነገሉአቸው፥ በቅዱሳንህም ላይ ተማከሩ። 4 ኑ ከሕዝብ እናጥፋቸው፥ ደግሞም የእስራኤል ስም አይታሰብ፡ አሉ። 5 አንድ ሆነው በአንተ ላይ ተማከሩ፤ በአንተ ላይ ቃል ኪዳን አደረጉ፤ 6 የኤዶማውያን ድንኳኖች እስማኤላውያንም፥ ሞዓብም አጋራውያንም፥ 7 ጌባል አሞንም አማሌቅም፥ ፍልስጥኤማውያንም ከጢሮስ ሰዎች ጋር፤ 8 አሦርም ከእነርሱ ጋር ተባበረ፥ ለሎጥ ልጆችም ረዳት ሆኑአቸው። 9 እንደ ምድያምና እንደ ሲሣራ፥ በቂሶንም ወንዝ እንደ ኢያቢስ አድርግባቸው። 10 በዓይንዶር ጠፉ፥ እንደ ምድርም ጕድፍ ሆኑ። 11 አለቆቻቸውን እንደ ሔሬብና እንደ ዜብ፥ ታላላቆቻቸውንም እንደ ዛብሄልና እንደ ስልማና አድርጋቸው፡— 12 የእግዚአብሔርን መሠዊያ እንወርሳለን የሚሉትን። 13 አምላኬ ሆይ፥ እንደ ትቢያ በነፋስ ፊትም እንደ ገለባ አድርጋቸው። 14 እሳት ዱርን እንደሚያቃጥል፥ ነበልባልም ተራሮች እንደሚያነድድ፥ 15 እንዲሁ በቍጣህ አሳድዳቸው፥ በመቅሠፍትህም አስደንግጣቸው። 16 ፊታቸውን እፍረት ሙላው፥ አቤቱ፥ ስምህንም ይፈልጋሉ። 17 ይፈሩ ለዘላለሙም ይታወኩ፤ ይጐስቍሉ ይጥፉም። 18 ስምህም እግዚአብሔር እንደ ሆነ፥ በምድር ሁሉ ላይም አንተ ብቻ ልዑል እንደ ሆንህ ይወቁ። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook

2
+1
لا يوجد نص...
294
3
+1
لا يوجد نص...
1
4
🗓 17/11/2018 አርብ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 558⏳ መዝሙር ምዕራፍ 82 1 እግዚአብሔር በአማልክት ማኅበር ቆመ፥ በአማልክትም መካከል ይፈርዳል። 2 እስከ መቼ ሐሰትን ትፈርዳላችሁ? እስከ መቼ ለኃጢአተኞች ፊት ታደላላችሁ? 3 ለድሆችና ለድሀ አደጎች ፍረዱ፤ ለችግረኛውና ለምስኪኑ ጽድቅ አድርጉ፤ 4 ብቸኛውንና ችግረኛውን አድኑ፤ ከኃጢአተኞችም እጅ አስጥሉአቸው። 5 አያውቁም፥ አያስተውሉም፤ በጨለማ ውስጥ ይመላለሳሉ፤ የምድር መሠረቶች ሁሉ ተናወጡ። 6 እኔ ግን፡— አማልክት ናችሁ፥ ሁላችሁም የልዑል ልጆች ናችሁ፤ 7 ነገር ግን እንደ ሰው ትሞታላችሁ፥ ከአለቆችም እንደ አንዱ ትወድቃላችሁ አልሁ። 8 አቤቱ፥ ተነሥ፥ በምድር ላይ ፍርድ፥ አንተ አሕዛብን ሁሉ ትወርሳለህና። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
311
5
لا يوجد نص...
325
6
لا يوجد نص...
322
7
🗓 16/11/2018 ሀሙስ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 557⏳ መዝሙር ምዕራፍ 81 1 በረድኤታችን በእግዚአብሔር ደስ ይበላችሁ፥ ለያዕቆብም አምላክ እልል በሉ። 2 ዝማሬውን አንሡ ከበሮንም ስጡ፥ ደስ የሚያሰኘውን በገና ከመሰንቆ ጋር፤ 3 በመባቻ ቀን በከፍተኛው በዓላችን ቀን መለከትን ንፉ፤ 4 ለእስራኤል ሥርዓቱ ነውና፥ የያዕቆብም አምላክ ፍርድ። 5 ከግብፅ በወጣ ጊዜ ለዮሴፍ ምስክር አቆመው። ያላወቅሁትን ቋንቋ ሰማሁ። 6 ጫንቃውን ከሸክም፥ እጆቹንም በቅርጫት ከመገዛት አራቅሁ። 7 በመከራህ ጊዜ ጠራኸኝ አዳንሁህም፥ በተሰወረ ዐውሎም መለስሁልህ፥ በክርክር ውኃ ዘንድም ፈተንሁህ። 8 ሕዝቤ ሆይ፥ ስማኝ እነግርሃለሁም፤ እስራኤል ሆይ፥ እመሰክርልሃለሁ። 9 አንተስ ብትሰማኝ ሌላ አምላክ አይሆንልህም፥ ለሌላ አምላክም አትሰግድም። 10 ከግብፅ ምድር ያወጣሁህ እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ነኝና፤ አፍህን አስፋ እሞላዋለሁም። 11 ሕዝቤ ግን ቃሌን አልሰሙኝም፥ እስራኤልም አላዳመጠኝም። 12 እንደ ልባቸው ሥራ ተውኋቸው፥ በልባቸውም አሳብ ሄዱ። 13 ሕዝቤስ ሰምቶኝ ቢሆን፥ እስራኤልም በመንገዴ ሄደው ቢሆን፤ 14 ጠላቶቻቸውን ፈጥኜ ባዋረድኋቸው ነበር፥ በሚያስጨንቋቸውም ላይ እጄን በጣልሁ ነበር፤ 15 የእግዚአብሔር ጠላቶችም በተገዙለት ነበር፥ ዘመናቸውም ለዘላለም በሆነ ነበር፤ 16 ከስንዴም ስብ ባበላቸው ነበር፥ ከዓለቱም ማር ባጠገባቸው ነበር። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
322
8
لا يوجد نص...
336
9
🗓 15/11/2018 ዕሮብ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 556⏳ መዝሙር ምዕራፍ 80 1 ዮሴፍን እንደ መንጋ የምትመራ፥ የእስራኤል ጠባቂ ሆይ፥ አድምጥ፤ በኪሩቤል ላይ የምትቀመጥ፥ ተገለጥ። 2 በኤፍሬምና በብንያም በምናሴም፤ ኃይልህን አንሣ እኛንም ለማዳን ና። 3 አቤቱ፥ መልሰን፥ ፊትህንም አብራ፥ እኛም እንድናለን። 4 የሠራዊት አምላክ አቤቱ፥ በባሪያህ ጸሎት ላይ እስከ መቼ ትቈጣለህ? 5 የእንባ እንጀራን ትመግበናለህ፥ እንባም በስፍር ታጠጣናለህ። 6 ለጎረቤቶቻችን ክርክር አደረግኸን፥ ጠላቶቻችንም በላያችን ተሣለቁብን። 7 የሠራዊት አምላክ አቤቱ፥ መልሰን፥ ፊትህንም አብራ፥ እኛም እንድናለን። 8 ከግብፅ የወይን ግንድ አመጣህ፤ አሕዛብን አባረርህ እርስዋንም ተከልህ። 9 በፊትዋም ስፍራን አዘጋጀህ፥ ሥሮችዋንም ተከልህ ምድርንም ሞላች። 10 ጥላዋ ተራሮችን ከደነ፥ ጫፎችዋም እንደ እግዚአብሔር ዝግባ ሆኑ። 11 ቅርንጫፎችዋንም እስከ ባሕር፥ ቡቃያዋንም እስከ ወንዙ ዘረጋች። 12 አጥርዋን ለምን አፈረስህ? መንገድ አላፊም ሁሉ ይቀጥፋታል። 13 የዱር እርያ አረከሳት፥ የአገር አውሬም ተሰማራባት። 14 የሠራዊት አምላክ ሆይ፥ እንግዲህ ተመለስ፤ ከሰማይ ተመልከት፥ እይም፥ ይህችንም የወይን ግንድ ጐብኝ። 15 በሰው ልጅ ለአንተ ያጸናኸውን ቀኝህ የተከላትን አንሣ። 16 በእሳት ተቃጥላለች ተነቅላማለች፤ ከፊትህ ተግሣጽም የተነሣ ይጠፋሉ። 17 ለአንተ ባጸናኸው በሰው ልጅ ላይ፥ በቀኝህ ሰው ላይ እጅህ ትሁን። 18 ከአንተም አንራቅ፤ አድነን ስምህንም እንጠራለን። 19 የሠራዊት አምላክ አቤቱ፥ መልሰን፥ ፊትህንም አብራ፥ እኛም እንድናለን። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
344
10
لا يوجد نص...
382
11
🗓 14/11/2018 ማክሰኞ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 555⏳ መዝሙር ምዕራፍ 79 1 አቤቱ፥ አሕዛብ ወደ ርስትህ ገቡ፤ የቅድስናህንም መቅደስ አረከሱ፥ ኢየሩሳሌምንም እንደ መደብ አደረጉአት። 2 የባሪያዎችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የጻድቃንህንም ሥራ ለምድር አራዊት፤ 3 ደማቸውንም በኢየሩሳሌም ዙሪያ እንደ ውኃ አፈሰሱ፥ የሚቀብራቸውም አጡ። 4 ለጎረቤቶቻችንም ስድብ ሆንን፥ በዙሪያችንም ላሉ ሣቅና ዘበት። 5 አቤቱ፥ እስከ መቼ ለዘላለም ትቈጣለህ? ቅንዓትህም እንደ እሳት ይነድዳል? 6 ስምህን በማይጠሩ መንግሥታት ላይ በማያውቁህም አሕዛብ ላይ መዓትህን አፍስስ፤ 7 ያዕቆብን በልተውታልና፥ ስፍራውንም ባድማ አድርገዋልና። 8 የቀደመውን በደላችንን አታስብብን፥ ምሕረትህ በቶሎ ታግኘን፥ እጅግ ተቸግረናልና። 9 አምላካችንና መድኃኒታችን ሆይ፥ እርዳን፤ ስለ ስምህ ክብር፥ አቤቱ፥ ታደገን፥ ስለ ስምህም ኃጢአታችንን አስተሰርይልን። 10 አሕዛብ፡— አምላካቸው ወዴት ነው? እንዳይሉ፥ የፈሰሰውን የባሪያዎችህን ደም በቀል በዓይኖቻችን ፊት አሕዛብ ያወቁ፤ 11 የእስረኞች ጩኸት ወደ ፊትህ ይግባ፤ እንደ ክንድህም ታላቅነት ሊገደሉ የተፈረደባቸውን አድን። 12 አቤቱ፥ የተዘባበቱብህን መዘባበታቸውን ለጎረቤቶቻችን ሰባት እጥፍ በብብታቸው ክፈላቸው። 13 እኛ ሕዝብህ ግን፥ የማሰማርያህም በጎች፥ ለዘላለም እናመሰግንሃለን፤ ለልጅ ልጅም ምስጋናህን እንናገራለን። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
422
12
لا يوجد نص...
348
13
2026-07-14-131325023.mp4
375
14
🗓 13/11/2018 ሰኞ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 554⏳ መዝሙር ምዕራፍ 78 1 ሕዝቤ ሆይ፥ ሕጌን አድምጡ፤ ጆሮአችሁንም ወደ አፌ ቃል አዘንብሉ። 2 አፌን በምሳሌ እከፍታለሁ፤ ከቀድሞ ጀምሮ፥ ያለውንም ተምሳሊት እናገራለሁ። 3 የሰማነውንና ያውቅነውን፥ አባቶቻችንም የነገሩንን፥ ለሚመጣ ትውልድ ከልጆቻቸው አልሰወሩም። 4 የእግዚአብሔርን ምስጋናና ኃይሉን ያደረገውንም ተኣምራት ተናገሩ። 5 ለልጆቻቸው ያስታውቅ ዘንድ ለአባቶቻችን ያዘዘውን ምስክር በያዕቆብ አቆመ፥ በእስራኤልም ሕግን ሠራ፤ 6 የሚመጣ፥ ትውልድ የሚወለዱም ልጆች ያውቁ ዘንድ፥ ተነሥተው ለልጆቻቸው ይነግራሉ፤ 7 ተስፋቸውን በእግዚአብሔር እንዲያደርጉ፥ የእግዚአብሔርንም ሥራ እንዳይረሱ፥ ትእዛዙንም እንዲጠብቁ፤ 8 እንደ አባቶቻቸው እንዳይሆኑ ጠማማና የምታስመርር ትውልድ፥ ልብዋን ያላቀናች ትውልድ፥ ነፍስዋ በእግዚአብሔር ዘንድ ያልታመነች። 9 የኤፍሬም ልጆች ለሰልፍ ታጥቀው ቀስትንም ገትረው በሰልፍ ቀን ወደ ኋላ ተመለሱ። 10 የእግዚአብሔርን ኪዳን አልጠበቁም፥ በሕጉም ለመመላለስ እንቢ አሉ፤ 11 መልካም ሥራውንና ያሳያቸውን ተኣምራቱን ረሱ፥ 12 በግብፅ አገርና በጣኔዎስ በረሃ በአባቶቻቸው ፊት የሠራውን ተኣምራት። 13 ባሕርን ከፍሎ አሳለፋቸው፤ ውኆችን እንደ ክምር አቆመ። 14 ቀን በደመና መራቸው፥ ሌሊቱንም ሁሉ በእሳት ብርሃን። 15 ዓለቱን በምድረ በዳ ሰነጠቀ፤ ከጥልቅ እንደሚገኝ ያህል በብዙ አጠጣቸው። 16 ውኃን ከጭንጫ አወጣ፥ ውኃንም እንደ ወንዞች አፈሰሰ። 17 ነገር ግን ይበድሉት ዘንድ እንደ ገና ደገሙ፥ ልዑልንም በምድረ በዳ አስቈጡት። 18 ለነፍሳቸው መብልን ይፈልጉ ዘንድ፥ እግዚአብሔርን በልባቸው ፈተኑት። 19 እግዚአብሔርን እንዲህ ብለው አሙት፡— እግዚአብሔር በምድረ በዳ ማዕድን ያሰናዳ ዘንድ ይችላልን? 20 ዓለቱን መታ፤ ውኆችም ወጡ፥ ወንዞችም ጐረፉ፤ እንጀራን መስጠትስ ይችላልን? ለሕዝቡስ ማዕድን ያዘጋጃልን? 21 እግዚአብሔርም ይህን ሰምቶ ተቈጣ፤ በያዕቆብም ላይ እሳት ነደደ፥ መዓትም በእስራኤል ላይ መጣ፤ 22 በእግዚአብሔር አላመኑምና፥ በመድኃኒቱም አልተማመኑምና። 23 ደመናውንም ከላይ አዘዘ፥ የሰማይንም ደጆች ከፈተ፤ 24 ይበሉም ዘንድ መናን አዘነበላቸው፥ የሰማይንም እንጀራ ሰጣቸው። 25 የመላክትንም እንጀራ ሰው በላ ስንቅንም እስኪተርፋቸው ላከላቸው። 26 ከሰማይ የምሥራቅን ነፋስ አስነሣ፥ በኃይሉም የደቡብን ነፋስ አመጣ፤ 27 ሥጋን እንደ አፈር፥ የሚበርሩትንም ወፎች እንደ ባሕር አሸዋ አዘነበላቸው፤ 28 በሰፈራቸው መካከል፥ በድንኳናቸውም ዙሪያ ወደቀ። 29 በሉ እጅግም ጠገቡ፤ ምኞታቸውንም ሰጣቸው። 30 ከወደዱትም አላሳጣቸውም፤ መብላቸውም ገና በአፋቸው ሳለ፥ 31 የእግዚአብሔር ቍጣ በላያቸው መጣ፥ ከእነርሱም ከፍ ያሉትን ገደለ፥ የእስራኤልንም ምርጦች አሰናከለ። 32 ከዚህም ሁሉ ጋር እንደ ገና በደሉ፥ ተኣምራቱንም አላመኑም፤ 33 ቀኖቻቸውም በከንቱ አለቁ፥ ዓመቶቻቸውም በችኰላ። 34 በገደላቸውም ጊዜ ወዲያው ፈለጉት፤ ተመለሱ ወደ እግዚአብሔርም ገሠገሡ፤ 35 ረዳታቸውም እግዚአብሔር፥ መድኃኒታቸውም ልዑል አምላክ እንደ ሆነ አሰቡ። 36 በአፋቸው ብቻ ወደዱት፤ በአንደበታቸውም ዋሹበት፤ 37 ልባቸውም ከእርሱ ጋር አልቀናም፥ በቃል ኪዳኑም አልተማመኑትም። 38 እርሱ ግን መሓሪ ነው፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር አላቸው፥ አላጠፋቸውምም፤ ቍጣውንም መመለስ አበዛ፥ መዓቱንም ሁሉ አላቃጠለም። 39 ወጥቶ የማይመለስ መንፈስ፥ ሥጋም እንደ ሆኑ አሰበ። 40 በምድረ በዳ ምን ያህል አስቈጡት፥ በበረሃም አሳዘኑት። 41 ተመለሱ፥ እግዚአብሔርንም ፈተኑት፥ የእስራኤልንም ቅዱስ አሳዘኑት። 42 እነርሱም እጁን አላሰቡም፥ ከጠላቶቻቸው እጅ ያዳነበትን ቀን፥ 43 በግብፅ ያደረገውን ተኣምራቱን፥ በጣኔዎስም በረሃ ያደረገውን ድንቁን። 44 ወንዞቻቸውንም ወደ ደም ለወጠ፥ ምንጮቻቸውን ደግሞ እንዳይጠጡ። 45 ዝንቦችንም በላያቸው ሰደደባቸው፥ በሉአቸውም፤ በጓጉንቸርም አጠፋቸው። 46 ፍሬያቸውን ለኩብኩባ፥ ሥራቸውንም ለአንበጣ ሰጠ። 47 ወይናቸውን በበረዶ፥ በለሳቸውንም በአመዳይ አጠፋ። 48 እንስሶቻቸውን ለበረዶ፥ ሀብታቸውንም ለእሳት ሰጠ። 49 የመዓቱን መቅሠፍት በላያቸው ሰደደ፤ መቅሠፍትን መዓትንም መከራንም በክፉዎች መላእክት ሰደደ። 50 ለቍጣው መንገድን ጠረገ፤ ነፍሳቸውንም ከሞት አላዳናትም፥ እንስሶቻቸውንም በሞት ውስጥ ዘጋ፤ 51 በኵሮቻቸውን ሁሉ በግብፅ፥ የድካማቸውንም መጀመሪያ በካም ድንኳኖች ገደለ። 52 ሕዝቡን ግን እንደ በጎች አሰማራቸው፥ እንደ መንጋም በምድረ በዳ መራቸው። 53 በተስፋም መራቸው አልፈሩምም፥ ጠላቶቻቸውንም ባሕር ደፈናቸው። 54 ወደ መቅደሱም ተራራ አገባቸው፥ ቀኙ ወደ ፈጠረችው ወደዚህች ተራራ፤ 55 ከፊታቸውም አሕዛብን አባረረ፥ ርስቱንም በገመድ አካፈላቸው፥ የእስራኤልንም ወገኖች በቤታቸው አኖረ። 56 ነገር ግን ልዑል እግዚአብሔርን ፈተኑት አስቈጡትም፥ ምስክሩንም አልጠበቁም፤ 57 ተመለሱም እንደ አባቶቻቸውም ከዱ፤ እንደ ጠማማ ቀስትም ተገለበጡ፤ 58 በኰረብታ መስገጃዎቻቸውም አስቈጡት፥ በተቀረጹ ምስሎቻቸውም አስቀኑት። 59 እግዚአብሔርም ይህን ሰምቶ ተቈጣ፥ እስራኤልንም እጅግ ናቀ፤ 60 የሴሎምን ማደሪያ ተዋት፥ በሰዎች መካከል ያደረገባትን ድንኳኑን፤ 61 ኃይላቸውን ለምርኮ፥ ሽልማቱንም በጠላት እጅ ሰጠ። 62 ሕዝቡንም በጦር ውስጥ ዘጋቸው፥ ርስቱንም ቸል አላቸው። 63 ጕልማሶቻቸውን እሳት በላቸው፥ ቈነጃጅቶቻቸውም አላዘኑም፤ 64 ካህናቶቻቸውም በሰይፍ ወደቁ፥ ባልቴቶቻቸውም አላለቀሱላቸውም። 65 እግዚአብሔርም ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ፥ የወይን ስካር እንደ ተወው እንደ ኃያልም ሰው፤ 66 ጠላቶቹንም በኋላቸው መታ፤ የዘላለምን ኀሣር ሰጣቸው። 67 የዮሴፍንም ድንኳን ተዋት፥ የኤፍሬምንም ወገን አልመረጠውም፤ 68 የይሁዳን ወገን ግን መረጠ፥ የወደደውን የጽዮንን ተራራ። 69 መቅደሱን እንደ አርያም ሠራ፥ ለዘላለምም በምድር ውስጥ መሠረታት። 70 ዳዊትንም ባሪያውን መረጠው፥ ከበጎቹም መንጋ ውስጥ ወሰደው፤ 71 ከሚያጠቡ በጎችም በኋላ፥ ባሪያውን ያዕቆብን ርስቱንም እስራኤልን ይጠብቅ ዘንድ ወሰደው። 72 በልቡ ቅንነት ጠበቃቸው፥ በእጁም ብልሃት መራቸው። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
444
15
🗓 12/11/2018 እሀድ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 553⏳ መዝሙር ምዕራፍ 77 1 በቃሌ ወደ እግዚአብሔር ጮኽሁ፥ ቃሌም ወደ እግዚአብሔር ነው፥ እርሱም አደመጠኝ። 2 በመከራዬ ቀን እግዚአብሔርን ፈለግሁት፤ እጆቼ በሌሊት በፊቱ ናቸው፥ አላረፍሁምም፥ ነፍሴም መጽናናትን አልቻለችም። 3 እግዚአብሔርን አሰብሁት ደስ አለኝም፤ ተናገርሁ፥ ነፍሴም ፈዘዘች። 4 ዓይኖቼ እንዲተጉ ያዝሃቸው፤ ደነገጥሁ አልተናገርሁም። 5 የዱሮውን ዘመን አሰብሁ፤ የዘላለሙን ዓመታት አሰብሁ፤ አጠናጠንሁም 6 በሌሊት ከልቤ ጋር ተጫወትሁ፥ ነፍሴንም አነቃቃኋት። 7 እግዚአብሔር ለዘላለም ይጥላልን? እንግዲህስ ቸርነቱን አይጨምርምን? 8 ለዘላለምስ ምሕረቱ ለልጅ ልጅ ተቈረጠችን? የተናገረውስ ቃል አልቆአልን? 9 እግዚአብሔርስ ሞገሱን ረሳን? በቍጣውስ ምሕረቱን ዘጋውን? 10 ይህ ድካሜ ነው አልሁ፥ የልዑል ቀኝ እንደ ተለወጠ። 11 የእግዚአብሔርን ሥራ አስታወስሁ፤ የቀደመውን ተአምራትህን አስታወሳለሁና፤ 12 በምግባርህም ሁሉ እናገራለሁ፥ በሥራህም እጫወታለሁ። 13 አቤቱ፥ መንገድህ በመቅደስ ውስጥ ነው፤ እንደ አምላካችን ያለ ታላቅ አምላክ ማን ነው? 14 ተኣምራትን የምታደርግ አምላክ አንተ ነህ። ለሕዝብህ ኃይልን አስታወቅሃቸው። 15 የያዕቆብንና የዮሴፍን ልጆች፥ ሕዝብህን በክንድህ አዳንሃቸው። 16 አቤቱ፥ ውኆች አዩህ፥ ውኆችም አይተውህ ፈሩ፤ ጥልቆች ተነዋወጡ፥ ውኆችም ጮኹ። 17 ደመኖች ድምፅን ሰጡ፥ ፍላጾችህም ወጡ። 18 የነጐድጓድህ ድምፅ በዐውሎ ነበረ፤ መብረቆች ለዓለም አበሩ፤ ምድር ተናወጠች ተንቀጠቀጠችም። 19 መንገድህ በባህር ውስጥ ነው፥ ፍለጋህም በብዙ ውኆች ነው፥ አረማመድህም አልታወቀም። 20 በሙሴና በአሮን እጅ ሕዝብህን እንደ በጎች መራሃቸው። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
441
16
🗓 11/11/2018 ቅዳሜ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 552⏳ መዝሙር ምዕራፍ 76 1 እግዚአብሔር በይሁዳ ታወቀ፥ ስሙም በእስራኤል ታላቅ ነው። 2 ስፍራው በሳሌም፥ ማደሪያውም በጽዮን ነው። 3 በዚያም የቀስትን ኃይል፥ ጋሻን ሰይፍን ሰልፍንም ሰበረ፤ በዚያም ቀንዶችን ሰበረ። 4 አንተ በዘላለም ተራሮች ሆነህ በድንቅ ታበራለህ። 5 ልበ ሰነፎች ሁሉ ደነገጡ፥ እንቅልፋቸውንም አንቀላፉ፤ ባለጠጎች ሁሉ በእነርሱ እጅ ምንም አላገኙም። 6 የያዕቆብ አምላክ ሆይ፥ ከተግሣጽህ የተነሣ ፈረሰኞች ሁሉ አንቀላፉ። 7 አንተ ግን፥ አንተ ግሩም ነህ፤ ቍጣህን ማን ይቃወማል? 8 ፍርድን ከሰማይ አሰማህ፤ ምድር ፈራች ዝምም አለች፥ 9 ልበ የዋሃን ያድን ዘንድ እግዚአብሔር ለፍርድ በተነሣ ጊዜ። 10 ሰው በፈቃዱ ያመሰግንሃልና፥ ከሕሊናቸው ትርፍም በዓልህን ያደርጋሉ። 11 ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ስእለትን ክፈሉ፤ በዙሪያው ያሉ ሁሉ እጅ መንሻን ለሚያስፈራው ያገባሉ። 12 የመኳንንትን ነፍስ ያወጣል፤ በምድርም ነገሥታት ዘንድ ያስፈራል። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
437
17
🗓 10/11/2018 አርብ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 551⏳ መዝሙር ምዕራፍ 75 1 አቤቱ፥ እናመሰግንሃለን እናመሰግንሃለን ስምህንም እንጠራለን፤ ተኣምራትህን ሁሉ እናገራለሁ። 2 ጊዜውን ስቀበል እኔ በቅን እፈርዳለሁ። 3 ምድርና በእርስዋ ውስጥ የሚኖሩት ሁሉ ቀለጡ፥ እኔም ምሰሶችዋን አጠናሁ። 4 ዓመፀኞችን፡— አትበድሉ አልኋቸው፥ ኃጢአተኞችንም፡— ቀንዳችሁን አታንሡ፤ 5 ቀንዳችሁን እስከ ላይ አታንሡ፥ በእግዚአብሔርም ላይ ዓመፅን አትናገሩ። 6 ክብር ከምሥራቅ ወይም ከምዕራብ ወይም ከምድረ በዳ የለምና፤ 7 እግዚአብሔር ፈራጅ ነውና ይህን ያዋርዳል ይህንም ያከብራል። 8 ጽዋ በእግዚአብሔር እጅ ነውና፤ ያልተቀላቀለ የወይን ጠጅ ሞላበት፤ ከዚህ ወደዚያ አገላበጠው፥ ነገር ግን አተላው አልፈሰሰም፤ የምድር ኃጢአተኞች ሁሉ ይጠጡታል። 9 እኔ ግን ለዘላለም ደስ ይለኛል፥ ለያዕቆብም አምላክ ዝማሬን አቀርባለሁ። 10 የኅጥኣንን ቀንዶች ሁሉ እሰብራለሁ፤ የጻድቃን ቀንዶች ግን ከፍ ከፍ ይላሉ። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
479
18
🗓 09/11/2018 ሀሙስ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 550⏳ መዝሙር ምዕራፍ 74 1 አቤቱ፥ ስለ ምን ለዘወትር ጣልኸኝ? በማሰማርያህ በጎች ላይስ ቍጣህን ስለ ምን ተቈጣህ? 2 አስቀድመህ የፈጠርሃትን ማኅበርህን፥ የተቤዤሃትንም የርስትህን በትር፥ በእርስዋ ያደርህባትን የጽዮንን ተራራ አስብ። 3 ጠላት በቅዱሳንህ ላይ እንደ ከፋ መጠን፥ ሁልጊዜም በትዕቢታቸው ላይ እጅህን አንሣ። 4 ጠላቶችህ በበዓል መካከል ተመኩ፤ የማያውቁትንም ምልክት ምልክታቸው አደረጉ። 5 እንደ ላይኛው መግቢያ ውስጥ በዱር እንዳሉም እንጨቶች፥ በመጥረቢያ በሮችዋን ሰበሩ። 6 እንዲሁ በመጥረቢያና በመዶሻ ሰበሩአት። 7 መቅደስህን በእሳት አቃጠሉ፤ የስምህንም ማደሪያ በምድር ውስጥ አረከሱ። 8 አንድ ሆነው በልባቸው በየሕዝባቸው፡— ኑ፥ የእግዚአብሔርን በዓሎች ከምድር እንሻር፡ አሉ። 9 ምልክታችንን አናይም ከእንግዲህ ወዲህም ነቢይ የለም፤ እስከ መቼ እንዲኖር የሚያውቅ በኛ ዘንድ የለም። 10 አቤቱ፥ ጠላት እስከ መቼ ይሳደባል? ስምህን ጠላት ሁልጊዜ ያቃልላልን? 11 ቀኝህንም በብብትህ መካከል፥ እጅህንም ፈጽመህ ለምን ትመልሳለህ? 12 እግዚአብሔር ግን ከዓለም አስቀድሞ ንጉሥ ነው፥ በምድርም መካከል መድኃኒትን አደረገ። 13 አንተ ባሕርን በኃይልህ አጸናሃት፤ አንተ የእባቦችን ራስ በውኃ ውስጥ ሰበርህ። 14 አንተም የዘንዶውን ራሶች ቀጠቀጥህ፤ ለኢትዮጵያ ሰዎችም ምግባቸውን ሰጠሃቸው። 15 አንተ ምንጮቹንና ፈሳሾቹን ሰነጠቅህ፤ አንተ ሁልጊዜ የሚፈስሱትን ወንዞች አደረቅህ። 16 ቀኑ የአንተ ነው ሌሊቱም የአንተ ነው፤ አንተ ፀሓዩንና ጨረቃውን አዘጋጀህ። 17 አንተ የምድርን ዳርቻ ሁሉ ሠራህ፤ በጋንም ክረምትንም አንተ አደረግህ። 18 ይህን ፍጥረትህን አስብ። ጠላት እግዚአብሔርን ተላገደ፥ ሰነፍ ሕዝብም ስሙን አስቈጣ። 19 የምትገዛልህን ነፍስ ለአራዊት አትስጣት፤ የችግረኞችህን ነፍስ ለዘወትር አትርሳ። 20 ወደ ኪዳንህ ተመልከት፥ የምድር የጨለማ ስፍራዎች በኅጥኣን ቤቶች ተሞልተዋልና። 21 ችግረኛ አፍሮ አይመለስ፤ ችግረኛና ምስኪን ስምህን ያመሰግናሉ። 22 አቤቱ፥ ተነሥ በቀልህንም ተበቀል፤ ሰነፎች ሁልጊዜም የተላገዱህን አስብ። 23 የባሪያዎችህን ቃል አትርሳ፤ የጠላቶችህ ኵራት ሁልጊዜ ወደ አንተ ይወጣል። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook
518
19
لا يوجد نص...
508
20
لا يوجد نص...
1