💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
Open in Telegram
💎ሀያዕ ሲወሳ ለሴት ልጅ ጌጧ ነውና ሁሌም አብራ ትወሳለች፣ #ሴት ልጅና #ሀያዕ አብረው የሚኖሩ መቼም የማይነጣጠሉ ጥምሮች ናቸው። 👉 ሴት ልጅ ስትፈጠርም በሀያዕ ዘውድ አሸብርቃ ነው። 💎ይህንን ዘውድ ከራሷ የገፈፈች ሴት ግን ህያው ከሆኑ ሰዎች መሀል እንደምትንቀሳቀስ በድን ትሆናለች።
Show more9 037
Subscribers
-424 hours
-177 days
-6830 days
Posts Archive
~በነገራችን ላይ አሁን ላይ ሴቶች የኔ የምለዉ ነገር ሊኖር ይገባል ብለዉ በራሳቸዉ ለመቋቋም ጥረት ሲያደርጉ፦ ወንድ ልጅ ግን የራሱ የሚለዉ የሆነ ስራ ፦የሆነ ነገር ሳይኖረዉ...ተዘሎ ትዳር ይገባል ።
እንዲሁም ስራ እያላቸዉ እንኳን ሴት በሰራቸዉ ቤት ገብቶ የቤት ወጭ እንኳ አላሞላም ያለ ሰዉ አዉቃለሁ አስቡት እንግዲህ !! ወንዶች ጠንካራ ቆራጥ የስራ ሰዉ ለሚስቶቻችሁ አዛኝ ሁኑ በቃ ጀግና ሁኑ።እንደዉ የሠዉ አትከጅሉ ። ሲሆን ሲሆን ቶሎ እንደተጋባችሁ ሴት ቤት ዘላችሁ አትግቡ ።ወደፊት ከወለዳችሁ ከከበዳችሁ ማን ይወስዲባችኋል። ማንም!!ስለዚህ ጠንክረህ ስራ ተብለሀል።
~~በነገራችን ላይ…ፍቅር ስላለ ብቻ ከሰዎች ጋር መኗኗር አንችላለን ማለት አይደለም። ፍቅር ብቻውን ሁሉንም ነገር ሊሆን አይችልም። መረር ያለ እውነት ቢሆንም ይህን ልናውቅ ይገባል። ፍቅራችን ብቻ በቂ ነው ተብሎ ትዳር አይጀመርም። ፍቅር አስፈላጊ ነው፣ ነገር ግን ፍቅር ብቻውን እስትንፋስ አይደለም። ሰዎች ፍቅራቸው ስላለቀ ብቻ አይደለም የሚለያዩት። ሰዎች እየተዋደዱ፣ እየተፋቀሩ እንኳ አንድ ላይ መኖር ሊያቅታቸው ይችላል።
ሲርብህ በምግብ እንጂ በፍቅር አትጠግብም። ሲርብሽ ፍቅር ሲሰጥሽ የረሀብሽን ጩኸት ላለመስማት ትኩረትሽ ይቀየራል እንጂ ርሀቡ ይጠፋል ማለት አይደለም።ፍቅር አስፈላጊ ከመሆኑ ጋር ብቻውን ህይወት ሊሆን አይችልም። ህይወት እንዲሆን የሚያስችለው ሌሎች ደጋፊ ነገሮች ያስፈልጉታል። ህይወት በልቦለድ እንደተሰበከው፣ በፊልም እንደሚሽሞነሞነው አይደለም።ሐቢቢ ጠንከር ብለህ ስራህን ስራ!
=t.me/AbuSufiyan_Albenan
🔖 አይንህን ስበር ሲባል መንገድ ላይ ብቻ
አይደለም ።ስበር የተባልከው/ሽው የትም ቦታ አይናችንን እንሰበር።ቲቪ ፣ሚድያም ላይ ይሁን የትም ቦታ ቢሆን አይናችንን እንስበር።
~
🎙በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወርRepost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ልብ ከፈራ ሁሉም ቀላል ነው
~
ስንቶች አካለ ጎደሎ ሆነው፣ በሰው ተደግፈው፣ በዊልተር እየተገፉ፣ በዱላ እየታገዙ መስጂድ ሲመላለሱ ይታያሉ።
ሌሎች ሙሉ አካል ይዘው፣ ጤነኛ ሆነው ጀማዐው ቀርቶ እቤታቸው እንኳ ለመስገድ ከብዷቸዋል። በዚህ ሁኔታ ላይ ያለ ሰው በጣም ሊያፍር ይገባዋል። የሰው ልጅ አላህን ካልፈራ፣ ህሊናው ካላስተዋለ በዚህ መጠን ይደነዝዛል። ጉዳዩ የተቅዋ ጉዳይ ነው። ተቅዋ ሲኖር ከባዱ ይቀላል። ልብ ከተቅዋ ሲራቆት ቀላሉ ይከብዳል። ጌታ እንዲህ ሲል እውነት ተናገረ፦
{ وَٱسۡتَعِینُوا۟ بِٱلصَّبۡرِ وَٱلصَّلَوٰةِۚ وَإِنَّهَا لَكَبِیرَةٌ إِلَّا عَلَى ٱلۡخَـٰشِعِینَ }
"በመታገስና በሶላትም ታገዙ። እርሷም (ሶላት) በፈሪዎች ላይ እንጅ በሌላው ላይ በእርግጥ ከባድ ናት።" [አልበቀረህ፡ 45]
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
🔖 ገንዘብ ባይኖራት ፦ የጥሩ ዘር ልጅ ባትሆን ፦ቆንጆ ባትሆንም እንኳ፥
~ ሰለይ ከሆነች፦ ጠንካራ ከሆነች አላህን የምፈራ ከሆነች፦ አንተን በመልካም የምታጠናክርህ ከሆነች ያን ሁሉ ይተካልሐል።
~
🔖የትዳርን ዋና አላማ ለማሳካት የሚያግዙ አጋዠ ነጥቦች ዉስጥ .....!
➀)ትልቁና ቀዳሚዉ ነገር ተቅዋ ነዉ። አላህን መፍራት.
⓶)ሁለት ተጣማሪዎች ባልና ሚስት እያንዳንዱ በላዩ ላይ ያለበትን ሀቅ ማሠብ .
=
t.me/https_Asselfya
Repost from የሱናዋ~ቆንጆ በተውሂድ ያበበች
ትዳር ለሰዉ ልጅ አስፈላጊ ነው የትዳራችን መስተካከል የሂወታችን ስኬታማነቱ አንዱ ምልክት ነው ትዳር ዝም ብሎ በአንድ ጥምረት ብቻ ስኬት ላይ አይደርስም ከጥምረት ብሆላ ቡዙ ጥረት ልናደርግ እና ሰበብ ልናደርስ ይገባል ለትዳራችን ጊዜ ልንሰጥ ይገባናል ፡፡ቤታችንን ልብሳችንን እንደምናድሰዉ ሁሉ ትዳርም ማደስ ይኖርብናል! ትኩረታችን በአንድ ነገር ላይ ብቻ አይሁን፡፡
@t.me/yesunawakonjobetwuhidyabebechRepost from ስለ ቀልባችን
📚ከተፍሲር ...
﴿ سِيمَاهُمْ فِي وُجُوهِهِمْ مِنْ أَثَرِ السُّجُودِ ﴾
ጥሩ መለያ
ابن عباس
ከፊል ሰለፎች እንዳሉት
በለሊት ሰላቱ የበዛች በቀን ፊቱ ታምራለች !!
📖ابن كثير📖
ገላሽ መንገድ አይደለም ማንም አይመላለስበት። እቴ የክብር ልብስሽን ካወለቅሽ ወዲህ ራቁትሽን ነሽ። መራቆት ልብስ ማውለቅ ብቻ አይደለም። የሁሉንም አውቃለሁ ልብስ መልበስም መራቆት ነው።
ደናቁራን የሞከሩትን ሁሉ መሞከር አያልቅሽም። ውበትሽን ካሜራ አይንገርሽ። የሚያስፈልግሽን፣ የሚገባሽን ሚድያ ሰፍሮ አይስጥሽ። አላደረግክልኝም፣ ከፍቶኛል ለማለት ብቻም ሳይሆን አመሰግንሀለሁ ለማለት አላህ ይናፍቅሽ።
እቴ ሁሉም ወንድ ፊርዓውን አይደለም አሲያ ነኝ አትበይ። ሁሉም ወንድ ቀይስ አይደለም ለይላ ነኝ እያልሽ አትጃጃዩ!
ቢመርሽም ዋጪው፣ ብትጠዪውም ተቀበዪው! በምናብ እንዳሰብሽው፣ በመፅሀፍት እንደቃረምሻቸው ታሪኮች፣ በስብከቶች እንደተመሰጥሽባቸው ሰዎች ህይወት ሳይሆን በዘመንሽ እራስሽን የገነባሽውን ያህል፣ ስብዕናሽን ያነፅሽውን ያህል ነው የምትኖሪው።
እቴ መኖር ማለት መመኘት አይደለም። መኖር ማለት ጌታሽን ማወቅ፣ ካንቺ ለሚፈልገው መፍጨርጨር ነው።....ስነ ምግባርሽን በደንብ ሳታስውቢ፣ እንደ ሉጥ ሚስት ሆነሽ አላህ የጠየቅኩትን ከለከለኝ ለማለት ዘግናኝ ድፍረት አትታጠቂ! ቀድመሽ ወድቀሽ ጣሉኝ አትበይ!
ቀና እንድትይ የሚያጎብጥሽን ፀፀት አትሸከሚ። የምትመኚውን እንድታገኚ ለተመኘሽው የምትገቢ ለመሆን ሞክሪ!
t.me/abdu/rheman_aman
Repost from Mohammed Siraj Al kemissie
🛑ቀጥታ ስርጭት ተስሒሑ ቲላዋ
──────⊹⊱✫⊰⊹──────
🎙በወንድማችን ሙሀመድ ሲራጅ
ጀ
መ
ረ
https://t.me/Ibnu_siraj_Alkemissie?livestream
﴿وَقَضَى رَبُّكَ أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا إِيَّاهُ وَبِالْوَالِدَيْنِ إِحْسَانًا﴾.
~
~ቀልብ ሲሞት እዝነት ይጠፋል፣
ህሊና ሲሞት ጥበብ ይጠፋል፣
ሰብዓዊነት ሲሞት ሁሉ ነገር ይጠፋል።
አላህ ሆይ!
በአዛኝ ቀልብ፣ በንፁህ ህሊና፣ አመስጋኝ እና የአላህን ፀጋ አስተዋሽ በሆነች ታጋሽ ነፍስ አስዉበን።
ዉስጣችንን ሕያው በሆነ ሰብዓዊነት ሙላን፣ እዝነትን ፈጽሞ ከዉስጣችን አታስወግድ።
t.me/https_Asselfya
ማግባትሽ ካልቀረ......
ጩኸት አትከተይ ጥመት አያፍዝዝሽ፡
አዳዲስ ፈጠራ ተይ አያደንዝዝሽ፡
የዋህ አትሁኝ ማንም አይጠምዝዝሽ፡
በተውሒድ በሱና ሰትሮ ይያዝሽ፡
የስኬትሽ ጣሪያ ሐቅ ይሁን መቅረዝሽ፡
---------------------------------
ከአህባሽ ከኢኽዋን ከሀጁሪ አደጋ፡
ፊትናን ከሚያራግብ ከቆላ አስከ ደጋ፡
የኔ ይሁን ከሚል ጭፍንተኛ መንጋ፡
----------------------------------
ተጠንቀቂ እህቴ ጫት ካዛገው ወጣት፡
ይገጥምሻል እና ሁለት ሀገር ቅጣት፡
ሰለፍዩን ምረጭ ያንን አንድ ቅንጣት፡
--------------------------------
መቼም ሰው ነውና ስህተት ባያጣውም፡
መንሀጁ ንፁህ ነው ኮተት አያውቀውም፡
ሽርክና ቢዲዐ ኹራፋት የለውም፡
---------------------------------
ፈጥነሽ አትደሰች ፈጥነሽ አትክሰሚ፡
ከሐቅ ጠላቶች ነገር አትቅሰሚ፡
በትዳርሽ ጉዳይ ነገረኛ አትስሚ፡
---------------------------------
አግቢ ጎበዝ ጀግና የሱና ሰባኪ፡
ከዘመኑ ፊትና የሌለው ንክኪ፡
የተውሒድ አፍቃሪ የሐቅ ነበልባል፡
በሩቅ ያስታውቃል ምን ግራ ያጋባል፡
ማግባትሽ ካልቀረ አግቢ የሱና ባል፡
-------------------------------
በዘመኑ ፊትና ያልተደናቆረ፡
በስሜት ተጠምዶ ውስጡ ያልጠቆረ፡
በማይችለው ጉዳይ ያልተሰነቀረ፡
ጀግና ሰው ምረጭ ማግባትሽ ካልቀረ፡
-------------------------------
በኑረዲን አል-አረቢ1444
--------------------------------
https://t.me/nuredinal_arebi
https://t.me/nuredinal_arebi
🔖የመጀመሪያ ፕሮግራም
➖➖➖➖➖➖➖➖
🎙በአብዱረሕማን አቡ ዑሰይሚን
ጀ
መ
ረ
=
https://t.me/https_Asselefya1?livestream
قال أبو داود السجستاني رحمه الله:
يكفي الإنسان لدينه أربعة أحاديث:
-«إنما الأعمال بالنيات»
-و«من حسن إسلام المرء تركه ما لا يعنيه»
-و«لا يكون المؤمن مؤمنا حتى يحب لأخيه ما يحب لنفسه»
-و«الحلال بيِّن، والحرام بيِّن، وبينهما أمور متشابهات».
[معالم السنن ٣٦٥/٤]
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
