en
Feedback
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ-Addis Ababa Labor and Skill Bureau

የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ-Addis Ababa Labor and Skill Bureau

Open in Telegram

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥያቄዎ +251118124566 0900834565

Show more
3 059
Subscribers
+624 hours
+217 days
+7030 days
Posts Archive
በተፈጠረላቸው የስራ ዕድል የዛሬ ገቢ ብቻ ሳይሆን የነገ ህይወታቸውን የተሻለ ለማድረግ በትኩረት እየሰሩ እንደሚገኝ በቆዳና ጨርቃ ጨርቅ ኢንተርፕራይዝ የተደራጁ ወጣቶች ገለፁ። 🇪🇹 ነሐሴ 29 ቀን ፤ 2018 ዓ.ም 🇪🇹 በጉለሌ ክፍለ ከተማ በወረዳ 8 አስተዳደር የአዲሱ ገበያ መስሪያ ቦታዎች ያነጋገርናቸው በኢንተርፕራይዝ ተደራጅተው የሚሰሩ ወጣቶች እንደገለፁት በተፈጠረላቸው ስራ ዕድል ህይወታቸውን የተሻለ ለማድረግ ተደራጅተው መስራተቸው ጥሩ ዕድል እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል ። እንደ ወጣቶች ገለፃ ከዚህ በፊት ስራ ባለመኖሩ ብዙ ወጣ ውረድ እንደገጠማቸው ጠቅሰው መንግስት ይህንን ዕድል በማዘጋጀቱ የተሻለ ገቢ ማግኘት እንደጀመሩና ከሚገኘው ገቢ በየእለቱ እንደሚቆጥቡ ተናግረዋል ። ወጣቶች አያይዘውም ከራሳቸው ተጠቃሚነት ባሻገር በተርሚናሎች ተገልጋዮች የሚፈልጉትን አገልግሎት በትክክል የመስጠትና ከዚህ በፊት ይደርስ የነበሩ ህገወጥ ድርጊቶችን የመከላከል ስራ እየሰሩ እንደሚገኙ ገልፀዋል ። ስራውን ለመጀመር የተመቻቹላቸው ምቹ ሁኔታዎችና የተደረገላቸው ተከታታይ ድጋፍ ውጤታማ እንዲሆኑ እንዳገዛቸው የገለጹት ወጣቶቹ አሁን ላይ በገቢ ደረጃ ራሳቸውን ከመቻል አልፈው የቤተሰቦቻቸውን ኑሮ መደገፍ ወደ ሚችሉበት የኢኮኖሚ ደረጃ ላይ መሸጋገራቸውን ተናግረዋል። በክፍለ ከተማው የወጣቶችን የስራ ባህል ለማሳደግ እየተደረገ ላለው ሁለንተናዊ ጥረት እነዚህ ኢንተርፕራይዞች ትልቅ አቅም እየሆኑ መምጣታቸውን ከጉለሌ ክፍለ ከተማ ይፋዊ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html

የመቀንጨር ችግርን ለመቀነስና የምግብ ዋስትናን በዘላቂነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የተቀናጁ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። 🇪🇹 ነሐሴ 29 ቀን ፤ 2018 ዓ.ም 🇪🇹 በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስርዓተ ምግብ እጥረት፣ የመቀንጨር እና የመቀጨጭ ችግሮችን በዘላቂነት ለመቅረፍና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የተቀናጁ የልማትና የስልጠና ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሞላ በመድረኩ ተገኝተው በሰጡት የስራ አቅጣጫ ቢሮው ከድህነት እና ከምግብ ዋስትና ጋር የተያያዙ ተግዳሮቶችን በዘላቂነት ለመቅረፍ ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በሂደቱም የህብረተሰቡን ተሳትፎ ማጠናከር፣ የባለሙያዎችን አቅም ማሳደግ እና የተሰሩ ስራዎችን ውጤታማነት በቅርበት መከታተል ለቀጣይ ስኬት ቁልፍ ጉዳዮች መሆናቸውን አጽንኦት ሰጥተዋል። የከተማ አስተዳደሩ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመሆን በ11ዱም ክፍለ ከተሞች በሚገኙ 12 ወረዳዎች በፓይለት ደረጃ የተጀመረውን የሥርዓተ ምግብ ማሻሻያ ፕሮግራም በተመለከተ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት የህብረተሰብ ተሳትፎ ቡድን መሪ አቶ አብርሃም እልፌ ማብራሪያ ሰጥተዋል። አቶ አብርሃም እንደገለጹት ፕሮግራሙ 50/50 በሆነ የበጀት ድርሻ የሚከናወን ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም በችግሩ የተጎዱ ነፍሰጡርና አጥቢ እናቶችን እንዲሁም ከሁለት ዓመት በታች የሆኑ ህፃናትን ከሥርዓተ ምግብ እጥረት ማላቀቅና ተጋላጭ ነዋሪዎችን ከተረጂነት ወደ አምራችነት ማሸጋገር ነው። ለዚሁ ተግባር ስኬትም በከተማ አስተዳደሩ ስር የሚገኙ 1,200 የሚያደርሱ ባለሙያዎችን የማብቃት ሥራ እየተሰራ መሆኑን የጠቀሱት አቶ አብርሃም፤ እስከ አሁን 670 ለሚሆኑ ባለሙያዎች የአሰልጣኞች ስልጠና የተሰጠ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ በሚመጣው ሰኞ ሰልጥነው ወደ ማህበረሰቡ በመውረድ ስለ አመጋገብ፣ አካባቢና የግል ንፅህና እንዲሁም የልጆች እንክብካቤ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እንደሚሰሩ አስረድተዋል። በሌላ በኩል፣ በከንቲባ ጽህፈት ቤት የምግብ ስርዓት እና ኒውትሪሽን አስተባባሪና የM&E አማካሪ አቶ ይበልጣል ሽቱ እንደገለጹት፣ የሥርዓተ ምግብ ችግር በኢትዮጵያ በየዓመቱ እስከ 55.5 ቢሊዮን ብር የምታጣበት ትልቅ ሀገራዊ አጀንዳ ነው። ይህንን ችግር ለመቅረፍም ከፈረንጆች አቆጣጠር 2015 ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም በአሁኑ ወቅት በሦስተኛው ምዕራፍ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ በየዓመቱ የመቀንጨር መጠንን በ3% መቀነስ የተቻለበት አዋጭ ስልት መሆኑን ገልጸዋል። አቶ ይበልጣል አክለውም፣ በከተማ ደረጃ 16 ሴክተር መሥሪያ ቤቶች በቅንጅት የሚሰሩ ሲሆን፣ በተለይም አምስቱ ዋና ዋና ሴክተሮች (ጤና፣ ግብርና፣ ትምህርት፣ ሴቶችና ህፃናት እንዲሁም ሥራና ክህሎት/ሴፍቲኔት) በወረዳ ደረጃ ለተመደበው የ10 ሚሊዮን ብር በጀት ተጋላጭ የሆኑ እናቶችንና ህፃናትን በመለየት አልሚ ምግብ ማቅረብን፣ የዶሮ እርባታንና የጓሮ አትክልት ልማትን በጋራ በመተግበር ላይ ይገኛሉ። በተጨማሪም ከመፀነስ ጀምሮ እስከ ስድስት ዓመት ያሉ ህፃናትን ሁሉን አቀፍ እድገት የሚያረጋግጠው የቀዳማዊ ልጅነት ፕሮግራም እና የ1,000 ቀናት ርብርብ የትውልድ የሥርዓተ ምግብ ችግርን በዘላቂነት ለማስቀረት ወሳኝ መሆናቸውን አብራርተዋል። በሁለቱም የሥራ ኃላፊዎች ማብራሪያ መሠረት፣ የሥራና ክህሎት ቢሮ ከሴፍቲኔት እና ከምግብ ዋስትና ጋር በተያያዙ ተግባራት ተጠቃሚዎችን በመለየት፣ አልሚ ምግብ በማቅረብ፣ የቢዝነስና የሕይወት ክህሎት ስልጠናዎችን በመስጠትና በገቢ ማስገኛ ሥራዎች ላይ በማሳተፍ ረገድ በሆሪዞንታልና በቨርቲካል ቅንጅት ትልቅ ሞዴል ሆኖ እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል። ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html