en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 411 subscribers, ranking 5 577 in the Religion & Spirituality category and 2 191 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 411 subscribers.

According to the latest data from 11 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 64 over the last 30 days and by 24 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 24.26%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 9.47% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 737 views. Within the first day, a publication typically gains 1 458 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 23.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 12 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 411
Subscribers
+2424 hours
+237 days
+6430 days
Posts Archive
#ምክረ_አበው_ወዝክረ_ቅዱስ_ያሬድ (በቅዱስ ቊርባን ዙሪያ የሚነሱ ጥያቄዎች በአበው መምህራን ምላሽ ይሰጥባቸዋል፡፡)፤ #ዐርብ_ሚያዝያ_11_ከምሽቱ_11፡30-2፡00 ሰዐት፡፡ በታላላቅ ገዳማት የሚጸለየው #የመሐረነ_አብ ጸሎት ይደርሳል፥ የቅዱስ ያሬድ ተዓምር ከጥንታዊ ገድሉ ላይ ይነበባል፡፡ እንደ መድኀኔ ዓለም ፈቃድ በመርሐ ገብሩ ላይ የደብራችን አስተዳዳሪ ይገኛሉ፤ ካህናት በማዕጠንታቸው ያጥናሉ፤ /የዕጣኑ ሽታ ... የናፈቃችሁ ሁሉ እንድትገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን/፡፡

#አስቸኳይ_አስቸኳይ_SHAREEEEEEEE_ሼርርርርር_ማድረጋችሁን_እንዳትዘነጉ_!!!!!! በኢሉባቡር ሀገረ ስብከት ቡኖ በደሌ ዞን በገቺ ወረዳ ሴቀቻ በምትባል ቀበሌ ውስጥ ከሌሊት ፲፩ ሰዓት ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች የሰማዕቱ ቅ/ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ቃጠሎ ደረሰበት፡፡ /ፎቶው ላይ የምታዩዋቸው ምዕመናን፤ ከቃጠሎው በኋላ በዕንባ ጭምር የምሕላ ጸሎት ሲያደርሱ ነው፡፡/ የቤተክርስቲያኑ ተራዳኢ በሆነው ወንድም ላይም ያለጥፋቱ ፖሊስ ድብደባ አካሂዷል፡፡ ይግባኝ ለክርስቶስ ፬፡፡ /መድኀኔ ዓለም ሆይ፤ የዛሬውን የኢሉባቡር ሐዘንና መከራ፤ የቤተ ክርስቲያናችን የኀዘንና የመከራ ማብቃያ (ተፍጻሜት) አድርግልን/ #በጅጅጋ፥ በኤጄሬ፥ በከሚሴና በአጣዬ በኢሉባቡር ያለች ጽዮን ቤተ ክርስቲያንን ባሰብናት፥ ድምጿን በሰማናትና ገጿን ባየናት ጊዜ አለቀስን፤ ቤተ ክርስቲያን ሆይ! ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ፤ ባላስብሽ አንደበቴ ከጕሮሮዬ ጋር ይጣበቅ፡፡ ቤተ ክርስቲያንን እስከ መሠረቷ ድረስ ፈጽሞ አፍርሱ የሚሉትን ጎስቋሎችን የሚበቀላቸው አምላካችን ብፁዕ ነው፡፡ /መዝ. 136/ #መዝሙረ ዳዊት 73፤ ‹‹#መቅደስህንም_በእሳት_አቃጠሉ፤ … #አቤቱ_ተነስ_በቀሌንም_ተበቀል፡፡›› ‹‹በመንጋዎችህ በጎች ላይ መቈጣትን ተቈጣህ፤ መቅደስህንም በእሳት አቃጠሉ፤ አንተ ፀሐይንና ጨረቃን ፈጠርህ፤ ጠላት እግዚአብሔርን ተገዳደረው፤ ሰነፍ ሕዝብም ስሙን አስቈጣው፤ ዘወትርም የድኾችን ነፍስ አትርሳ፤ አቤቱ ተነስ በቀሌንም ተበቀል፤ ሰነፎች ሁልጊዜ የተገዳደሩህን አስብ፤ የአገልጋዮችህን ቃል አትርሳ፡፡›› ጽዋው ሞልቶ ተትረፈረፈ፤ 4ት ጊዜ አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥሉ፡፡ #በጠራሁህ ቀን ፈጥነህ ስማኝ፤ ምንም በመከራ መካከል ብሄድ አንተ ታድነኛለህ፤ በአሕዛብ ቊጣ ላይ እጆቼን ዘረጋህ፤ ቀኝህም አዳነኝ፤ እግዚአብሔር ይበቀልልኛል፤ አቤቱ ይቅርታህ ለዘለዓለም ነው፡፡ /መዝ. 137/ #ኢይትአጸው አናቅጽኪ፤ ክቡራት ዕንቊ መሠረትኪ፥ ሠናይት ሰላማዊት እንተ ናፈቅራ በጽድቅ፤ መዓዛ አፉሃ ከመ ኮል፡፡ /ዚቅ ዘሰኔ 21/ (#በተከበሩ_ዕንቊ_የተመሠረትሽ_ቤተ_ክርስቲያን_ሆይ_ደጆችሽ_አይዘጉ፡፡) ##መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ሆይ፤ አሕዛብ አምላካቸው ማን ነው? ወዴትስ አለ? ቢኖር ኖሮ ለምን ዝም አላቸው? እንዳይሉ ስለ አባቶቻችን ብለህ ተለመንን፤ ኀይልና ብርታቱን፥ ፍቅርና አንድነቱን፥ ጥበብና ማስተዋሉን፥ እውነቱንና ፍርዱን አንተ ስጠን፤ አንተ ተበቀልልን፨ #ነቢያተ ፳ኤል ጸሐፉ በመጽሐፎሙ እሙነ፤ ነገረ ሰቈቃው ወላህ በዘመኖሙ ዘኮነ፡፡ ለኢትዮጵያ ውስተ አድያሚሃ አመ በኀጢአት ነበርነ፤ ውስተ ኲሃቲሃ እንዚራቲነ ሰቀልነ፤ ሶበ ተዘከርናሃ ለጽዮን እምነ፡፡/ነግሥ ዘኅዳር 21/ #በሐ በልዋ ተሳለምዋ፤ ዕግትዋ ለጽዮን ወሕቀፍዋ፤ ደዩ ልበክሙ ውስተ ኃይላ፤ እንተ ተሐንፀት በስሙ፤ ወተቀደሰት በደሙ፤ ወተአትበት በዕፀ መስቀሉ፤ ጊሡ ኀቤሃ፤ እስመ ኃይለ እግዚአብሔር ላዕሌሃ። ቤተ ክርስቲያንን ሰላም በሏት፤¬ ቤተ ክርስቲያን ጽዮንን ክበቧት በመድኀኔ ዓለም በስሙ የታነጸችና የተቀደሰች ናትና፡፡ /ዚቅ ዘሰኔ 21/ #*በአስኬማ ቆብ የተቀዳጃችሁ፤ በፈርጂያ ሰፊ ልብስ የተንቦረቀቃችሁ፤ የመከራ መስቀሉን ምልክት የጨበጣችሁ፤ ….. ለመንግሥትና ለፖለቲካ፤ ለተለያዩ አካላትና ለግለሰቦች ሳይቀር አድር ባይ የሆናችሁ፤ ቤተ ክርስቲያናችንን ያስጎዳችሁ፤ ስትጎዳም እያያችሁ ዝም ያላችሁ፤ ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ አንስቶ እስከ አናጎንስጢስ መዐርግ ድረስ ያላችሁ፤ *የቤተ ክርስቲያናችንን ከመዐርና ከሱካር የጣፈጠውን፥ ከወተትና ከበረዶ የነጻውን ትምህርቷን ግታችሁ የተማራችሁ ሊቃውንትና መምህራን፤ እናት ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚሸረበውን ሴራና ደባ፤ የሚደርሰውን ጥፋትና ውድመት እያያችሁና እየሰማችሁ ባልሰማና ባላየ ያለፋችሁ፤ ለሃይማኖት አባቶች፣ ለመንግሥት አካላትና ለምዕመናን ትክክለኛውንና እውነተኛውን ትምህርት ያላስተማራችሁና ያልገሰጻችሁ፤ *እምየ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስመ ክርስትና ሰጥታ በአገልግሎቷ ተሳታፊ ያደረገቻችሁ ምዕመናን፤ ነገር ግን ጉዳቷን ሰምተን ለሥጋዊ ሕይወታችን ብቻ እየሮጥን ጉዳቷን እንዳልሰማ ዝም ብለን የከረምን፤ *ቤተ ክርስቲያን ልጆቼ ብላ በሰንበት ትምህርት ቤት ያዋቀረችን ሰንበት ትምህርት ቤቶች፤ የእናት ቤተ ክርስቲያንን ጉዳት የኛ ጉዳት መሆኑ ሁሉ እስኪዘነጋን ድረስ በአብዛኛው ዘመነኛ ሆነው በመጡ መዝሙር የደነዘዝን፤ የሰ/ት/ቤት ዋና ተልእኮ መዘመር ብቻ የመሰለን፤ ………. ፡፡ *በአንድ ላይ ቢደራጁ ራሳቸው ተጠቅመው ይጠቅሙኛል ብላ ያደራጀችን ማኅበራት /ማኅበረ ቅዱሳንን ጨምሮ/፤ የቤተ ክርስቲያንን ጥፋት ከመታደግ ይልቅ በጠበልና ጠዲቅ ብቻ የተወሰንን፤ የቲሸርት ልብስ መልበስን ትልቁ ግልጋሎት ያደረግን …… አብዛኞቻችን ዝም አይነቅዝም ያልነው፤ አምላክ ያያል ይፈርድማልና ይህን አትዘንጉ፤ ታሪክም የዘመኑንና የዕለቱን ታሪክ ይቈጥራልና ይህን አትርሱ፤ ዝምታው ይሰበር፤ ሕግ ከቤተ ክርስቲያን ይወጣልና፤ አጥፊዎችን መንግሥት አልቀጣምና በሕጋችን መሠረት አጥፊዎችን እንገሥጻቸው፥ እንቅጣቸው፡፡ #የመንግሥት አካላትም ሥራችሁ ችግሮች ከመከሰታቸው በፊት ቀድማችሁ መጠበቅ፥ መከላከልና መቆጣጠር፤ ችግሮች ሲከሰቱም ባስቸኳይ መፍታት እንጂ፤ …… እንደ ሌላ ሀገር መሪ፤ ችግሩ ከተከሰተ በኋላ፥ ሰው ከሞተ በኋላ፥ አብያተ ክርስቲያናት ከተቃጠሉ በኋላ፤ ሮጦ ዜናና ዲስኩር መልቀቅ፤ መግለጫ ማውጣት፤ እንዲሁም ለይስሙላ ያህል ድርጊቱን አጥብቀን እናወግዛለን በማለት ምዕምናንንና ሕዝቡን መሸበብና መደለል ሥራችሁ አይደለም፤ ካልቻላችሁ አልችልም ብሎ ቦታውን መልቀቅ አዋቂነት ነው!!፡፡ #የመንግሥት አካላት፤ ከጠቅላይ ሚንስትር እስከ ቀበሌ ሹም፤ ከመከላከያ እስከ ፌደራል፤ ከክልል ልዩ ኀይል እስከ ፖሊስ፤ ከሚሊሻ እስከ አካባቢ ጠባቂ፤ ….. ቤተ ክርስቲያናችን ስትቃጠል ካልደረሰ፤ ሕዝባችን ሲሞት ካልታደገ፤ ችግርን ካልቀረፈ፤ ጉዳትን ካላከመ፤ የራሱን ልብስ ለብሰው አደጋ ጣዮችን ካልገሰጸና ፈልጎ ካልቀጣ፤ ምን ሊሠራ፥ ምንስ ሊያደርግ፥ ስሙስ ለምን መንግሥት ይባላልን!!!!!???? **በጅጅጋ 13 አብያተ ክርስቲያናት ተቃጠሉ፤ ካህናትና ምዕመናን በጭካኔ ተገደሉ ዝም አልን በኤጄሬ 2ት አብያተ ክርስቲያናት ተቃጠሉ፣ ካህናት ተደበደቡ ዝም አልን፣ በአጣዬ ካራቆሬና ማጀቴ ቤተ ክርስቲያን ተቃጠለ፡፤ …….… ዛሬ ደግሞ በኢሉባኑር ቤተ ክርስቲያን፡፡ ከእንግዲህ ወዲያ ግን ዝም አንልም!!!፡፡ ከእንግዲህ ወዲያ ስለ ሃይማኖታችንም ሆነ ስለ ሃገራችን ኢትዮጵያ ዝም አንልም!!!፡፡ አንተ የምትተኛ ንቃ! #ምን_እናድርግ_የሚለውን_መፍትሔም_አስቀምጡ_አንብባችሁ_ከንፈር_ብቻ_መምጣት_እንዳይሆን፡፡ #SHAREEEEEEEE_ሼርርርርር_ማድረጋችሁን_እንዳትዘነጉ_!!!!!!

*ኦ እግዚኦ አእርፍ ለነፍሳቲሆሙ አኀው ወአኀት እለ አእረፉ በባሕረ ኤርትራ (ቀይ ባሕር)፡፡ **ቀይ ባሕርን አቋርጠው ወደ ሳውዲ ዓረቢያና የመን በጀልባ ቅዳሜ መጋቢት 28 ሌሊት በመጓዝ ላይ የነበሩ 70 ገደማ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች የመገልበጥ አደጋ ደርሶባቸው ዐርፈዋል፡፡ ***አምላከ አበው መድኀኔ ዓለም ነፍሳቸውን በገነት ከቅዱሳን ጋር ይደምርልን፡፡

ምክረ አበው፤ የዐርብ ጕባኤና ዝክረ ቅዱስ ያሬድ በአንድ ላይ የሚደረጉበት ጕባኤ፤ በምሥጢረ ቊርባን ዙሪያ የሚነሡ ጥያቄዎች የሚመለሱበት፡፡

#ኒቆዲሞስ፤ #ሰባተኛው_ሳምንት ሰባተኛው ሳምንት ኒቆዲሞስ ይባላል፤ በዚህ ሳምንትም ይህ ይታሰብበታል፡፡ ‹‹ኒቆዲሞስ››፤ * አይሁዳዊ ሲሆን ከፈሪሳውያን ወገን የነበረ ነው * በኢየሩሳሌም በሀብት ቢሉ በዕውቀት እንዲሁም በሥልጣን የአይሁድ አለቃ ነበር፡፡ * ማታ ማታ ጌታችን ዘንድ እየተገኘ ይማር ነበር፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ እንዲህ አስቀምጦልናል፦ ፨ ‹‹ከፈሪሳውያን ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የተባለ አንድ ሰው ነበር፤ እርሱም በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ፦ ‹‹መምህር ሆይ እግዚአብሔር ከእሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርጋቸውን እነዚህ ተዓምራቶች ሊያደርግ የሚችል የለምና መምህር ሆነህ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደመጣህ እናውቃለን›› አለው፡፡ ⊚ ጌታችን ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው። ጌታችን ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው። ፨ ኒቆዲሞስም፦ ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል? ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላልን? አለው። ⊚ ጌታችን ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም። ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፥ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው።›› /ዮሐ. ፫፥ ዘ፩-፲፭/ ለምን በሌሊት ይመጣ ነበር? ⊚ አይሁድ ‹‹ማንም ከእኛ ወገን የሆነ የክርስቶስ ደቀ መዝሙር ከሆነ ሀብት ንብረቱ ይወሰድ፣ በቤተመቅደስ አይግባ፣ መሥዋዕት አይሥዋ›› ብለው ነበርና አይሁድን ፈርቶ፥ ሀብት ንብረቱን ወዶ እንዳይታወቅበት በሌሊት ይመጣ ነበር፡፡ ⊚ በሌላ በኩል ደግሞ የቀን ልብ ባካና ነው፤ ዓይን ብዙ ያያል፥ ሐሳብ ይበታተናል፡፡ በተሰበሰበ ልብ ለመማር፤ በተጨማሪ ‹‹ሊቅ ነኝ›› እያለ ‹‹እስከ ዛሬ ትምህርት አልጨረሰም›› እንዳይሉት በሌሊት ይመጣ ነበር፡፡ ⊚ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እንኳን ለመማር የመጣውን እራሱ እየሄደ ያስተምር ነበርና ኒቆዲሞስ ምንም በሌሊት ቢመጣም ማወቅን ፈልጎ ነውና ስለዳግም መወለድ /ስለጥምቀት/ በእግዚአብሔር ልጅ ስለማመንና ስለ ጽድቅ ስራ በዝርዝር አስተምሮታል፡፡ ⊚ ኒቆዲሞስ በመጨረሻው ቀን በዕለተ ዐርብ በስቅለቱ ጊዜ፤ ከመስቀል ላይ ሥጋውን ለማውረድና ገንዞ ለመቅበር ቀድሞ ተገኝቷል፡፡ /ዮሐ. ፲፱፥፴፰/ ከኒቆዲሞስ ሕይወት የምንማረው፡- ፩. ትሕትና፦ ኒቆዲሞስ በትምህርት፣ በሹመት፣ በባለጸግነት የአይሁድ አለቃ ሲሆን አለቅነቱ ግን ከጌታ እግር ስር ቁጭ ብሎ እርሱ ተገኝቶ ለመማር አልከለከለውም፡፡ /በጽሑፉ መጨረሻ ያለውን ቅኔ ተመልከቱ/ ፪. አለማመካኘት፦ ከመጀመሪያ ሰዎች ከአዳምና ከሔዋን ጀምሮ ሰዎች በምክንያተኝነት በአመፅ መንገድ ይጓዛሉ፡፡ ኒቆዲሞስም ወደ ጌታ በመቅረቡ የጸሐፍት ፈሪሳውያን አድማና ግርግር ታላቅ እንቅፋትና ምክንያት መሆን እንደሚችል ያውቃል፡፡ ነገር ግን ይህ ምክንያት በእግዚአብሔር ፊት እንደማያዋጣ አውቆ የሚያወጣውን አደረገ፡፡ ፫. ጥበብ፦ በክርስትና ጉዞ ውስጥ ጥበብ የመጀመሪያ ቦታ ትይዛለች፡፡ ኒቆዲሞስም ጕዞውን በጥበብ አደረገ፡፡ በሌሊት ያደረገበት ምክንያት፡- ራሱ መምህር ሆኖ ሌላ ትምህርት አስፈለገው ብለው ሌሎች እንዳይሰናከሉበት፣ የመዓልት ልቦና ስለሚሰበሰብ በቂ ዕውቀት ለማግኘት፣ መንፈሳዊ ፍሬ ለማፍራት በመዓልትም በሌሊትም ወደ እግዚአብሔር መቅረብ እንዳለብን ለማጠየቅ፣ ከአዳም ጀምሮ እስከ ክርስቶስ ያሉ ነፍሳት በሲዖል ይገኛሉ ሲል፣ በመዓልትም በሌሊትም ብትፈልጉ ትገኛለች ሲል ነው፡፡ በእውነት ግሩም ጥበብ! ፬. የተነገረውን አምኖ በመቀበሉ፡- ጸሐፍት ፈሪሳውያን ብዙ ምክንያቶች እየደረደሩ የጌታን አምላክነት አምኖ መቀበል ሲያቅታቸው እርሱ ግን ጌትነቱን ለመቀበል ጊዜ አልወሰደበትም፡፡ ፭. ለእውነት መመስከር፡- እነርሱ ሲክዱ ጌታ ላይም ትርፍ ቃል ሲናገሩ፤ በድፍረት መክሰሳቸውን እየነገራቸው የጌታችን አምላክነቱን በግልጽ ይመሰክር ነበር፡፡ ፮. ጽንዓት፡- ብዙዎች በመከራ ጊዜ ላይለዩት ቃል ቢገቡም መጨረሻ ላይ ያኔ በመከራ ሰዓት ከመስቀሉ ሥር ሊገኙ የቻሉ ጥቂቶች ናቸው፡፡ ኒቆዲሞስም በዚች ሰዓት ያንን መከራ ታግሶ በጽነዓት ከዮሴፍ ጋር የጌታን ሥጋ ከመስቀል አውርደው በአዲስ መቃብር ቀብረውታል፡፡ ምንጭ፤ የዮሐንስ ወንጌል ትርጓሜ ፠፨፠ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፠፨፠ /የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

ነገ (ቅዳሜ) ምዝገባው ያልቃል፡፡ እንዳያመለጥዎ!! ከ5 በላይ ጥንታዊ ዋሻ ተቁፋሮ ወደ ተገኘባት፤ በጕዟችን ትምህርትና ምክረ አበው ወደ ሚሰጥባት፤ ወደ ኵሉ ወይን ቅድስት አርሴማ፡፡ 0977 30 17 18

ዛሬና የዛሬ ሳምንት ‹‹ቅዱስ ቊርባን›› በሚል ርዕስ በሰ/ት/ቤታችን አዳራሽ በዐርብ የማታ ጕባኤያችን ላይ ትምህርትና ምክረ አበው አለ፡፡ እንዳያመልጥዎ!

#ክተት_ወደ_ሰሜን_ተራሮች!፤ #ክተት_ወደ_ራስ_ደጀን!፡፡ *የበርካታ ቅርሶች ባለቤት ወደሆነው፤ *በዓለም ላይ ብርቅዬና ድንቅ የሆኑ እንስሳት (ዋሊያ ጭላቀዳ ዝንጀሮና ቀይ ቀበሮ) የሚገኙበት ወደሆነው! *ብርቅና ድንቅ የሆኑ አዕዋፋት (እነ ላመርጊየር) ማደሪያቸው ወደሆነው፤ *ልዩ ልዩ ዕጽዋት መገኛቸው ወደሆነው፤ *በዓለም ላይ ረጅሙ ፏፏቴ (ጂምባ ፏፏቴ) የሚፈስስበት ወደሆነው፤ *እግሩ ሊማሊሞ አናቱ ራስ ደጀን ወደሆነው፤ *በርካታ ዕንቊ ዕንቊ የሆኑ ገዳማት (ጨነቅ ዋሻ /ቅዱስ ላሊበላ ያነጸው/፤ ደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ፤ ሳዶቅ አምባና ሌሎችም ያሉበት ወደ ሆነው፡፡ ….. ……… ወደ ሆነው፡፡ ክተት፥ ክተት ወደ ስሜን!፡፡ በተለይም በቅርብ ርቀት ጎንደርና ትግራይ ያላችሁ፤ በአስቸኳይ ክተቱ፡፡ *ከጎንደር 120 ኪ.ሜ (የ1፡30 መንገድ ጕዞ) *ከሽሬ 100 ኪ.ሜ (የ1 ሰዐት ጕዞ) እንዲሁም ደባርቅ፤ገዲቢዬ፤ ዳባት፤ አምባ ጊዮርጊስ (በጎንደርና ዙሪያዋ፤ በባሕርዳርና ዙሪያዋ ያላችሁ) ባስቸኳይ ክተቱ፤ በአዲዓርቃይ፣ ማይፀብሪ፣ እንዳአባ ጉና፣ አኵሱም፣ አዲግራት (በትግራይና በዙሪያዋ ያላችሁ) ባስቸኳይ ክተቱ፤ #በተለይም ….. የጎንደርና የባሕር ዳር፤ የደብረ ታቦርና የደባርቅ፤ የአኵሱምና የሽሬ፤ የመቀለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች … መኪና ከየዩኒቨርሲቲያችሁም ቢሆን ትብብር ጠይቃችሁ ባስቸኳይ ክተቱ፡፡ በአጋጣሚውም የሰሜን ተራሮች እዩ፡፡ #በአካል_መገኘት_ያልቻላችሁ_በጸሎት_አስቡ፡፡ ከአ.አ. ዛሬ ሚያዝያ 4 ያቀኑ ወንድሞቻችንና እኅቶቻችን አሉ፤ ከአ.አ. እስከ ሰሜን ተራሮች ድረስ የምትገኙ በየመንገዱ እንርሱን እየተከታለችሁም ቢሆን ባስቸኳይ ክተቱ፡፡ /ቸር ያሰማን፡፡!!/