en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 411 subscribers, ranking 5 577 in the Religion & Spirituality category and 2 191 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 411 subscribers.

According to the latest data from 11 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 64 over the last 30 days and by 24 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 24.26%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 9.47% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 737 views. Within the first day, a publication typically gains 1 458 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 23.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 12 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 411
Subscribers
+2424 hours
+237 days
+6430 days
Posts Archive
#SHAREEEEEEEE_ሼርርርርር_ማድረጋችሁን_እንዳትዘነጉ_!!!!!! መዝሙረ ዳዊት 73፤ ‹‹#መቅደስህንም_በእሳት_አቃጠሉ፤ … #አቤቱ_ተነስ_በቀሌንም_ተበቀል፡፡›› ‹‹በመንጋዎችህ በጎች ላይ መቈጣትን ተቈጣህ፤ መቅደስህንም በእሳት አቃጠሉ፤ አንተ ፀሐይንና ጨረቃን ፈጠርህ፤ ጠላት እግዚአብሔርን ተገዳደረው፤ ሰነፍ ሕዝብም ስሙን አስቈጣው፤ ዘወትርም የድኾችን ነፍስ አትርሳ፤ አቤቱ ተነስ በቀሌንም ተበቀል፤ ሰነፎች ሁልጊዜ የተገዳደሩህን አስብ፤ የአገልጋዮችህን ቃል አትርሳ፡፡›› ጽዋው ሞልቶ ተትረፈረፈ፤ 3ት ጊዜ አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥሉ፡፡ በጅጅጋ 13 አብያተ ክርስቲያናት ተቃጠሉ፤ ካህናትና ምዕመናን በጭካኔ ተገደሉ ዝም አልን በኤጄሬ 2ት አብያተ ክርስቲያናት ተቃጠሉ፣ ካህናት ተደበደቡ ዝም አልን፣ ** ዛሬ ደግሞ በአጣዬ ካራቆሬና ማጀቴ ቤተ ክርስቲያን ተቃጠለ፡፤ …….… ከእንግዲህ ወዲያ ግን ዝም አንልም!!!፡፡ ከእንግዲህ ወዲያ ስለ ሃይማኖታችንም ሆነ ስለ ሃገራችን ኢትዮጵያ ዝም አንልም!!!፡፡ #*በአስኬማ ቆብ የተቀዳጃችሁ፤ በፈርጂያ ሰፊ ልብስ የተንቦረቀቃችሁ፤ የመከራ መስቀሉን ምልክት የጨበጣችሁ፤ ….. ለመንግሥትና ለፖለቲካ፤ ለተለያዩ አካላትና ለግለሰቦች ሳይቀር አድር ባይ የሆናችሁ፤ ቤተ ክርስቲያናችንን ያስጎዳችሁ፤ ስትጎዳም እያያችሁ ዝም ያላችሁ፤ ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ አንስቶ እስከ አናጎንስጢስ መዐርግ ድረስ ያላችሁ፤ *የቤተ ክርስቲያናችንን ከመዐርና ከሱካር የጣፈጠውን፥ ከወተትና ከበረዶ የነጻውን ትምህርቷን ግታችሁ የተማራችሁ ሊቃውንትና መምህራን፤ እናት ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚሸረበውን ሴራና ደባ፤ የሚደርሰውን ጥፋትና ውድመት እያያችሁና እየሰማችሁ ባልሰማና ባላየ ያለፋችሁ፤ ለሃይማኖት አባቶች፣ ለመንግሥት አካላትና ለምዕመናን ትክክለኛውንና እውነተኛውን ትምህርት ያላስተማራችሁና ያልገሰጻችሁ፤ *እምየ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስመ ክርስትና ሰጥታ በአገልግሎቷ ተሳታፊ ያደረገቻችሁ ምዕመናን፤ ነገር ግን ጉዳቷን ሰምተን ለሥጋዊ ሕይወታችን ብቻ እየሮጥን ጉዳቷን እንዳልሰማ ዝም ብለን የከረምን፤ *ቤተ ክርስቲያን ልጆቼ ብላ በሰንበት ትምህርት ቤት ያዋቀረችን ሰንበት ትምህርት ቤቶች፤ የእናት ቤተ ክርስቲያንን ጉዳት የኛ ጉዳት መሆኑ ሁሉ እስኪዘነጋን ድረስ በአብዛኛው ዘመነኛ ሆነው በመጡ መዝሙር የደነዘዝን፤ የሰ/ት/ቤት ዋና ተልእኮ መዘመር ብቻ የመሰለን፤ ………. ፡፡ *በአንድ ላይ ቢደራጁ ራሳቸው ተጠቅመው ይጠቅሙኛል ብላ ያደራጀችን ማኅበራት፤ የቤተ ክርስቲያንን ጥፋት ከመታደግ ይልቅ በጠበልና ጠዲቅ ብቻ የተወሰንን፤ የቲሸርት ልብስ መልበስን ትልቁ ግልጋሎት ያደረግን …… አብዛኞቻችን ዝም አይነቅዝም ያልነው፤ አምላክ ያያል ይፈርድማልና ይህን አትዘንጉ፤ ታሪክም የዘመኑንና የዕለቱን ታሪክ ይቈጥራልና ይህን አትርሱ፤ ዝምታው ይሰበር፤ ሕግ ከቤተ ክርስቲያን ይወጣልና፤ አጥፊዎችን መንግሥት አልቀጣምና በሕጋችን መሠረት አጥፊዎችን እንገሥጻቸው፥ እንቅጣቸው፡፡ #የመንግሥት አካላትም ሥራችሁ ችግሮች ከመከሰታቸው በፊት ቀድማችሁ መጠበቅ፥ መከላከልና መቆጣጠር፤ ችግሮች ሲከሰቱም ባስቸኳይ መፍታት እንጂ፤ …… እንደ ሌላ ሀገር መሪ፤ ችግሩ ከተከሰተ በኋላ፥ ሰው ከሞተ በኋላ፥ አብያተ ክርስቲያናት ከተቃጠሉ በኋላ፤ ሮጦ ዜናና ዲስኩር መልቀቅ፤ መግለጫ ማውጣት፤ እንዲሁም ለይስሙላ ያህል ድርጊቱን አጥብቀን እናወግዛለን በማለት ምዕምናንንና ሕዝቡን መሸበብና መደለል ሥራችሁ አይደለም፤ ካልቻላችሁ አልችልም ብሎ ቦታውን መልቀቅ አዋቂነት ነው!!፡፡ #የመንግሥት አካላት፤ ከጠቅላይ ሚንስትር እስከ ቀበሌ ሹም፤ ከመከላከያ እስከ ፌደራል፤ ከክልል ልዩ ኀይል እስከ ፖሊስ፤ ከሚሊሻ እስከ አካባቢ ጠባቂ፤ ….. ቤተ ክርስቲያናችን ስትቃጠል ካልደረሰ፤ ሕዝባችን ሲሞት ካልታደገ፤ ችግርን ካልቀረፈ፤ ጉዳትን ካላከመ፤ የራሱን ልብስ ለብሰው አደጋ ጣዮችን ካልገሰጸና ፈልጎ ካልቀጣ፤ ምን ሊሠራ፥ ምንስ ሊያደርግ፥ ስሙስ ለምን መንግሥት ይባላልን!!!!!???? ይግባኝ ለክርስቶስ ፫፡፡ #በጅጅጋ፥ በኤጄሬ፥ በከሚሴና በአጣዬ ያለች ጽዮን ቤተ ክርስቲያንን ባሰብናት፥ ድምጿን በሰማናትና ገጿን ባየናት ጊዜ አለቀስን፤ ቤተ ክርስቲያን ሆይ! ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ፤ ባላስብሽ አንደበቴ ከጕሮሮዬ ጋር ይጣበቅ፡፡ ቤተ ክርስቲያንን እስከ መሠረቷ ድረስ ፈጽሞ አፍርሱ የሚሉትን ጎስቋሎችን የሚበቀላቸው አምላካችን ብፁዕ ነው፡፡ /መዝ. 136/ #በጠራሁህ ቀን ፈጥነህ ስማኝ፤ ምንም በመከራ መካከል ብሄድ አንተ ታድነኛለህ፤ በአሕዛብ ቊጣ ላይ እጆቼን ዘረጋህ፤ ቀኝህም አዳነኝ፤ እግዚአብሔር ይበቀልልኛል፤ አቤቱ ይቅርታህ ለዘለዓለም ነው፡፡ /መዝ. 137/ #ኢይትአጸው አናቅጽኪ፤ ክቡራት ዕንቊ መሠረትኪ፥ ሠናይት ሰላማዊት እንተ ናፈቅራ በጽድቅ፤ መዓዛ አፉሃ ከመ ኮል፡፡ /ዚቅ ዘሰኔ 21/ (#በተከበሩ_ዕንቊ_የተመሠረትሽ_ቤተ_ክርስቲያን_ሆይ_ደጆችሽ_አይዘጉ፡፡) ##መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ሆይ፤ አሕዛብ አምላካቸው ማን ነው? ወዴትስ አለ? ቢኖር ኖሮ ለምን ዝም አላቸው? እንዳይሉ ስለ አባቶቻችን ብለህ ተለመንን፤ ኀይልና ብርታቱን፥ ፍቅርና አንድነቱን፥ ጥበብና ማስተዋሉን፥ እውነቱንና ፍርዱን አንተ ስጠን፤ አንተ ተበቀልልን፨ #SHAREEEEEEEE_ሼርርርርር_ማድረጋችሁን_እንዳትዘነጉ_!!!!!!

#ፍኖተ_ሕይወት_/#የሕይወት_ጕዞ/፤ #ሚያዝያ_06/2011ዓ.ም.፡፡ ወደ #ኵሉ_ወይን_ቅድስት_አርሴማ፡፡ **በብዙሃን ዘንድ ዜናው ያልተሰማው፤ 3ት ትላልቅና ሌሎችም ክፍሎች ያሉት፤ ብዙ ንዋያተ ቅድሳት የተገኙበትና በቁፋሮ የተገኘው ጥንታዊ ዋሻ ይጎበኛል፤ **ምክረ አበው በሊቃውንት መምህራን፣ ዝማሬ በዘማርያን ይቀርባል፡፡ **ከሰ/ትቤታችን ምሥረታ ጀምሮ የነበሩና አሁንም ያሉ አባላት በአንድነት የሚሳተፉበት ዐቢይ ጕዞ፡፡ **ለበለጠ መረጃ፤ 0977 30 17 18 (ፎቶው ላይ የምታዩት ተጓዦች፤ ከዚህ በ1990ዎቹ ወደ ደብረ ሊባኖስ የተጓዙ አባላቶቻችን ናቸው፡፡)፡፡

ገብርኄር፤ ስድስተኛው ሳምንት #ገብር ኄር፥ ገብር ምዕመን ፥ ገብር ሀካይ ስድስተኛ ሳምንት ገብርኄር ይባላል፡፡ ገብርኄር ማለት ታማኝ አገልጋይ ማለት ነው፡፡ በዚህ ሳምንት ስለ ስም አጠራሩ ክብር ይግባውና ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለኄር /ስለታማኝ/ አገልጋይ ያስተማረውን ትምህርት ይነገራል ይህንንም የሚያዘክር ምስጋና ይቀርብበታል፡፡ ይኸውም ማቴ 25፥14-30 ላይ ይገኛል፡፡ (ይህም ክፍል ጌታችን በማቴዎስ ወንጌል በምሳሌ ካስተማራቸው ትምህርቶች አንዱ ነው)፡፡ ወደ ሌላ አገር የሚሄድ ሰው ባሮቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንደ ሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና፤ ለእያንዳንዱ እንደ ዐቅሙ፡ ለአንዱ አምስት መክሊት፥ ለአንዱ ሁለት፥ ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ አገር ወዲያው ሄደ፡፡ መክሊት የወርቅ መለኪያ /መስፈሪያ/ ነው፡፡ አምስት መክሊትም የተቀበለው ሄዶ ነገደበት ሌላም አምስት አተረፈ፡፡ እንዲሁም ሁለት የተቀበለው ሌላ ሁለት አተረፈ ፡፡ አንድ ተቀበለው ግን ሄዶ ምድርን ቆፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ፡፡ ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቈጣጠራቸው፡፡ *አምስት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምስት መክሊት አስረክ፤ ‹‹ ጌታ ሆይ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ ሌላ አምስት መክሊት አተረፍሁበት›› አለ፡፡ ጌታውም፦ ‹‹መልካም አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ (ገብር ኄር)፤ በጥቂቱ ታምነሃል በቡዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ፡፡›› አለው፡፡ *ሁለት መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፡፡ ‹‹ጌታ ሆይ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ ሌላ ሁለት መክሊት አተረፍሁበት፡፡›› አለ፡፡ ጌታውም፡፡ መልካም፡ ‹‹ አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ (ገብር ምዕመን) በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሃለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው፡፡ *አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፡፡ ‹‹ጌታ ሆይ ካልዘራህባት የምታጭድ፥ ካልበተንህበትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ሌቦች እንዳይሠርቁኝ አታላዮች እንዳይቀሙኝ ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ መክሊትህ እነሆ›› አለው፡፡ ጌታውም መልሶ እንዲህ አለው፡- ‹‹አንተ ክፋና ሃኬተኛ ባሪያ (ገብር ሀካይ) ካልዘራሁበት እንደማጭድ ፥ ካልበተንሁበትም እንድሰበስብ ታውቃለህን? ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር፤ እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር፡፡ ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት አስር መክሊትም ላለው ስጡት፤ እሱን ደግሞ ወደ ዘለዓለም ሐዘንና መከራ ወዳለብት ወደ ጨለማው አውጥታችሁ ጣሉት›› አላቸው፡፡ ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል፤ ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳ ይወስድበታል፡፡ አገልጋዮችም ይህንን ክፉ አገልጋይ ወደ ጨለማው አውጥተው ጣሉት፡፡ በዚህ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል፡፡ † መክሊት የተባለ ጸጋ ስጦታ ሲሆን፤ እግዚአብሔር ለእያንዳንዳችን የተለያየ ስጦታ ተሰጥቶናል በተሰጠንም ስጦታ ልናገለግልበት ያስፈልጋል፡፡ † በተጨማሪ መክሊት ቃለ እግዚአብሔር ነው፤ የሰማነውን ቃለ እግዚአብሔር ለመተግበር እየበረታን ለሌላው ማሰማት ይገባናል፤ ከእኛ የሚጠበቀው ማሰማቱ ብቻ ነው፤ በልቦናው አድሮ ሥራ የሚያሠራ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ነውና፡፡ እኛም በሃይማኖት ጠንክረን በምግባር በርትተን ታማኝ ባርያ ልንሆን ይገባል፡፡ ፠፨፠ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፠፨፠

ማስታወቂያ፤ የጠቅላላ ጕባኤ ጥሪ፤ የሰንበት ትምህርት ቤታችን የ6 ወር ሪፖርት ቅዳሜ መጋቢት 28 ከቀኑ በ11፡30 ስለሚቀርብ አባላት ሁሉ እንድትገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ /የቀ.ደ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት/

በቅርበት ላልተገኛችሁ በዓሉን እናስቃኛችሁ፤ ሌሊት ማኅሌቱ በደብሩ ብቻ በሚባሉ የወረብ ቀለማትና በጎንደር የወረብ ቀለማት በድመቅት አደረ፤ (በይበልጥም በመጋቢት መድኀኔ ዓለምና በሐምሌ ገብርኤል ብቻ ተራ በተራ በሚባሉት የዝክረ ስምከ ረግድ ከነቂቃቸው ዕፁብ ነበሩ፡፡/ ሰዐታት ምኑ ይነገራል፤ ጠዋት ኪዳኑን ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ መሩት፤ ረፋድ ላይ ታቦተ ሕጉ ወጣ ብፁዕነታቸውም ካስተማሩት መካከል፤ ‹‹ እግዚአብሔር ንጉሥ ነው፤ በምድርም መካከል መድኀኒትን አደረገ›› በሚል ርዕስ *መድኀኒትን ለምን ማድረግ አስፈለገው፤ *የማይሞተው ሞተ /ቅዳሴ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ፥ ዮሐንስ አፈወርቅ/ *የእኛን ሞት ወስዶ እርሱ ሞተ /ኤፍሬም ሶርያዊ፣ ውዳሴ ማርያም ዘዐርብ/ *የመዳን ቀን ዛሬ ነው፡፡ /ቅዱስ ጳውሎስ/ *በዓሉ ለክርስቲያኖች በንቻ ሳይሆን ለመላው ሕዝበ አዳም ነው፡፡ /እነሆ ለሰው ሁሉ የሚሆን የምሥራች እንግራችኋለሁ፡፡/

#ወጸሐፈ ጲላጦስ መጽሐፈ፤ ወይብል መጽሐፉ ኢየሱስ ናዝራዊ ንጉሠ አይሁድ፡፡ (መስፍኑ ጲላጦስ በመጽሐፉ ‹‹ኢ.ና.ን.አ›› (ኢየሱስ ናእራዊ ንጉሠ አይሁድ ብሎ) ጻፈ፡፡ /ዛሬም በአንገታችን መስቀል ላይ መቀረጽ ያለበት ‹‹ኢ.ና.ን.አ.›› የሚል እንጂ የራሳችንና የሌሎች ስም መሆን የለበትም!!! #አውረድዎ እምዕፅ፤ ወአምጽኡ አፈዋተ ከርቤ ሕውሰ፡፡ ዘንብን የምትሰጥ ጌታችን መድኀኔ ዓለም ሆይ ተጠማሁ ባልክ ጊዜ፤ ከርቤና ሐሞት የተቀላቀለበትን አጠጡህ!! ከእንጨት መስቀል ላይ አወረዱህ፤ (ሥዕሉ ከጥንታዊቷ ገዳም ከተድባበ ማርያም ፎቶ የተነሣ ጥኝታዊ ስዕል ነው፡፡)

#ስለ እናትህ ስለ ድንግል ማርያም ብለህ ምሬሃለሁ ይቅር ብዬሃለሁ በለኝ፤ ከአንተ በቀር ቸር ይቅር ባይ የለምና፡፡ በለኒ መሐርኩከ በእንተ ማርያም፤ እስመ አልቦ ዘእንበሌከ ዘይሜሕር ቃል መድኀኔዓለም፡፡ #በእንተ ማርያም ወላዲትከ፤ ወበእንተ ዮሐንስ መጥምቅከ፤ እግዚኦ ኢታስተሃፍረነ በቅድሜከ መድኔዓለም፡፡ (ስለ ወለደችህ እናትህ ማርያም፤ ስለ አጠመቅህ ዮሐንስ ብለህ አቤቱ አምላካችን ሆይ፤ በፊትህ በቆምን ጊዜ እንዳታሳፍረን፡፡

በኢትዮጵያ በዋነኛነትና በግንባር ቀደምትነት የስቅለት በዓል የሚከበርበት ታላቁ ገዳም #ዋልድባ (ዋሊ)፡፡ የሕማማትህንና የሞትህን ዜና ስለሰማች ዋልድባ ቅድስት ከዓመት እስከ ዓመት ታለቅሳለች፤ ፈጣሪዋ አምላኳ ስለሆንክ፥ በስደትህ ጊዜ የባረካትና የመሠረትሃት፥ ኋላም እንደ ተሰቀልክ ሆነህ የተገለጽክባትና የቀደስካት በመሆኗ ዓመት እስከ ዓመት በሱባዔ ታስብሃለች፡፡ ዛሬ መጋቢት 27 ግን እንባዋን በቅዳሴ ጭምር የምታብስበት የደስታዋ ቀን ነው፤ ሰብዐ ዓለም ወሰብአ ኢትዮጵያ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ፤ ከሰሜን እስከ ደቡብ ተሰብስበው በኢትዮጵያ ደረጃ በዋነኛነትና በግንባር ቀደምትነት የስቅለት በዓልህን ያስባሉ፤ ማዕከላዊና ደቡባዊ የኢትዮጵያ ክፍሎች ከዋልድባ ገዳም በመራቃቸው ብዙሃን ሕዝብ ለክብረ በዓሉ ወደ ዋልድባ ባይሄድም፤ በሰሜናዊ ኢትዮጵያ በተለይም ከጎንደርና ከትግራይ የ7 ዓመት ሕፃናት ሳይቀር ያን በረሐ አቋርጠው ወደ ገዳሙ ይተማሉ ፤ መነኰሳቱም እንደ አሸን ለበዓሉ የሚመጣውን ምዕመን በቋርፍና በጭልቃ፣ በሰሊጥና በሻይ ይቀበሉታል፡፡ ቅዳሴው እንዳበቃም ነፋስ እንደበተነው አሸዋ ባንዴ ሕዝቡ ወደ መንደሩ ይተምማል፡፡ /ዛሬ ወደ ማምሻው ላይ በወር 1ዴ በገዳማትና አድባራት መርሐ ግብራችን ላይ ዋልድባን እንድምንዘግብ በገባነው ቃል መሠረት ገዳሙን እንዘግበዋለን፤ ይጠብቁን፡፡/

142 ዓመታትን ያስቈጠረው ጥንታዊው የጮቢ ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለም፡፡ በ1868ዓ.ም. የተመሠረተ፡፡ በምዕራብ ሸዋ ዞን በጀልዱ ወረዳ በጮቢ የሚገኝ፡፡

#ፍኖተ_ሕይወት_/#የሕይወት_ጕዞ/፤ #ሚያዝያ_06/2011ዓ.ም.፡፡ ወደ #ኵሉ_ወይን_ቅድስት_አርሴማ፡፡ **በብዙሃን ዘንድ ዜናው ያልተሰማው፤ 3ት ትላልቅና ሌሎችም ክፍሎች ያሉት፤ ብዙ ንዋያተ ቅድሳት የተገኙበትና በቁፋሮ የተገኘው ጥንታዊ ዋሻ ይጎበኛል፤ **ምክረ አበው በሊቃውንት መምህራን፣ ዝማሬ በዘማርያን ይቀርባል፡፡ **ከሰ/ትቤታችን ምሥረታ ጀምሮ የነበሩና አሁንም ያሉ አባላት በአንድነት የሚሳተፉበት ዐቢይ ጕዞ፡፡ **ለበለጠ መረጃ፤ 0977 30 17 18 (ፎቶው ላይ የምታዩት ተጓዦች፤ ከዚህ በፊት ወደ ኤረር ካደረግነው ጕዞ ላይ የተወሰደ ነው)፡፡