Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
#ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ #Orthodox 📜 #የዕለቱ #ስንክሳር (#የቅዱሳን_ታሪክ) 💡 የአባቶች ምክርና ትምህርት 📖 ሕይወትን የሚቀይሩ ጥልቅ የአባቶች ምክር እና ትምህርቶች ይተላለፋሉ። ከቅዱሳት መጻሕፍት የተቀሰሙ ለነፍስ ምግብ የሚሆኑ ቁምነገሮች ይገኛሉ። ጥያቄ? ማስታወቂያ ለማሰራት @Samrina_12_23 Buy ads: https://telega.io/c/OrthodoxTewahedoTrue
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
Channel Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶኦርቶዶክስ ተዋሕዶ (@orthodoxtewahedotrue) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 174 476 subscribers, ranking 139 in the Religion & Spirituality category and 126 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 174 476 subscribers.
According to the latest data from 16 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -3 435 over the last 30 days and by 6 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 4.41%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 2.62% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 7 696 views. Within the first day, a publication typically gains 4 572 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 87.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“#ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ #Orthodox
📜 #የዕለቱ #ስንክሳር (#የቅዱሳን_ታሪክ)
💡 የአባቶች ምክርና ትምህርት
📖 ሕይወትን የሚቀይሩ ጥልቅ የአባቶች ምክር እና ትምህርቶች ይተላለፋሉ።
ከቅዱሳት መጻሕፍት የተቀሰሙ ለነፍስ ምግብ የሚሆኑ ቁምነገሮች ይገኛሉ።
ጥያቄ? ማስታወቂያ ለማሰራት @Samrina_12_23
Buy ads:
https://telega.io/c/OrthodoxTewahed...”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 17 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.
እርሱም በጦርነት ላይ የበረታ ነበር፤ የአንጾኪያ ተወላጆችም ይመኩበት ነበር ።📌ዲዮቅልጥያኖስም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ክዶ አምልኮ ጣዖትን በአጸና ጊዜ እጅግ አዘነ፤ ፊቅጦር የሚባል የኀርማኖስ ልጅ ወዳጅ ነበረው፤ ሁልጊዜም የመጻሕፍትን ቃል ይሰሙ ነበር፤ ስለ ነፍሳቸውም ድኅነት ያነቡ ነበር ። ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደማቸውን ያፈሱ ዘንድ ተስማሙ ። 📌በዚያ ጊዜም ሰይጣን በሽማግሌ አምሳል ታያቸው፤ ለአማልክት እንዲያጥኑ ቢመክራቸውም "ከእኛ ራቅ" ብለው አሳፈሩት ። ሰይጣኑም ወደ ዲዮቅልጥያኖስ ሄዶ "ፊቅጦርንና ገላውዴዎስን ካልገደልካቸው መንግሥትህን ይወስዳሉ" አለው ።
ንጉሡም ወደ ቅዱስ ገላውዴዎስ ልኮ ለጣዖታቱ እንዲሠዋ ለመነው፤ የአባቱንም ሹመት ይሾመው ዘንድ ቃል ገባለት፤ ሰምቶም አልታዘዘለትም ።📌ንጉሡም ወደ እንዴናው ገዥ እንዲህ ብሎ ጻፈ፦ "ገላውዴዎስ ትእዛዛችንን አልተቀበለም፤ አንተም ወደ ትእዛዛችን ይመለስ እንደሆነ በብዙ ድካም ሸንግለው፤ ይህ ካልሆነ ራሱን በሰይፍ ቁረጥ" ።
ቅዱስ ገላውዴዎስም የእኅቱ ባል የሆነ ሲድራማኮስን ጠርቶ ጌታችንን በማመን እንዲጸና ወገኖቹንም እንዲያጸናቸው አደራ አለው ።📌ወደ እንዴናው ገዥ ወደ አርያኖስም በደረሰ ጊዜ አርያኖስ "የንጉሥን ትዕዛዝ አትተላለፍ" ብሎ ለመነው ። ቅዱስ ገላውዴዎስም "ንጉሥ ያዘዘህን ልትፈፅም እንጂ በነገርህ ልታስተኝ አልተላክሁም" አለው ። መኰንኑም ተቆጥቶ በመኰንኑ እጅ ጦር ነበረ፤ ቅዱስ ገላውዴዎስንም ወጋው፤ ነፍሱንም ክብር ይግባውና በጌታችን እጅ ሰጠ፤ በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ ። 📌ምእመናንም የቅዱስ ገላውዴዎስን ሥጋ ወሰዱ፤ ከቅዱስ ፊቅጦር ሥጋ ጋርም በሣጥን ውስጥ አኖሩት ።
ከዚህ በኋላም የቅዱስ ፊቅጦር እናት ቅድስት ሶፍያ የቅዱሳን ገላውዴዎስንና የፊቅጦርን ሥጋቸውንም ወስዳ ወደ አንጾኪያ አደረሰች ። የቅዱስ ገላውዴዎስ ሥጋ አስዩጥ በሚባል አገር ይኖራል የሚልም አለ ። "ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ መስተጋድል ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።" ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን" (የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል) ✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔) ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮ @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯
አዝአንተ ፃኑ አያል ሰው እግዚእብሄር ካንተ ጋርነው ክንድህን ላበረታ ተልኬአለው ከጌታ አይዞህ ጌዲዮን ያለው ቁርባኑን ያሸተተው ከእኛ ጋር ነው ሚካኤል ሰልፋችንን ይመራል የእግዚአብሄር መላክ ስሙ ድንቅ ነው በኦርማ አውድማ ሰይፍን ይዞ ቆሞየታየው ዳዊት በመንቀጥቀጥ ፊቱን ፈለገ አያሉ ሚካኤል ድንቅን አደረገ{፪}
አዝበሶስት ቀን ቸነፈር እንዳትጠፍ ምድር ሰባ ሺ ሰዎች ወድቀው መላኩን በቃ አለው ለምህረት ይመጣሉ ለመሀት ይላካሉ ሰይፉን ባፎቱ ከቷል ሚካኤል ለህዝቡ ቆማል የእግዚአብሄር መልአክ ስሙ ድንቅ ነው ስምኦን ጴጥሮስን ከወድኔ ገብቶ ያወጣው የእጆቹን ሰንሰለት ፈቶ አረገ አያሉ ሚካኤል ድንቅን አደረገ{፪}
አዝበጠባቂዎች መሀል ኬፋል ከእንቅልፋአገታ የተዘጋውን ደጃፍ አልተሳነውም ማለፍ ሚካኤል እየመራው ጴጥሮስ እግሩ የቀናው አውቆታል ልቡ በርቶ ዘለለ ስሙን ጠርቶ የእግዚአብሄር መልአክ ስሙ ድንቅነው ለቶርያስ ሰው ለማኑኤል እንደነገረው በመሰውያው ነበልባል ውስጥ አረገ ሀያሉ ሚካኤል ድንቅን አደረገ ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮ @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯
እንዲህም ሆነ፤ ስሙ ዋርስኖፍ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፤ ኤጲስቆጶስነት ሊሾሙት በወደዱ ጊዜ ሸሽቶ ወደ ናባ አውራጃ እሊህ ደናግል ወዳሉበት ወደ ግሕሙን ደርሶ በዚያ አደረ።📌በዚያችም ሌሊት የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጦለት "ከዚህ ለምን ትተኛለህ? ተነሥተህ ተጋደል፤ ለአንተና ሰማዕት መሆን ለሚሹ ሁሉ አክሊል ተዘጋጅቷልና፤ አሁንም ተነሥተህ ወደ መኰንኑ ሂድ፤ በፊቱም ቆመህ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመን" አለው። 📌ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ ራእይን እንዳየ ለቅዱሳት ደናግል ነገራቸው። ሲነጋም ተነሥተው ከእርሱ ጋራ ወደ መኰንኑ ሄዱ፤ በመኰንኑ ፊት ክብር ይግባውና በጌታችን ታመኑ። መኰንኑም ይዞ ጽኑ ሥቃይን አሠቃያቸውና ወደ ወህኒ ቤት ጨመራቸው፤ ከጥቂት ቀኖችም በኋላ ከዚያ አውጥቶ ከቅዱስ ዋርስኖፍ ጋራ ወደ ስንሑር ላካቸው፤ እናታቸውም ትከትላቸው ነበር። 📌መኰንኑም "ለአማልክት ዕጣን ዕጠኑ" አላቸው፤ ባልታዘዙለትም ጊዜ ጽኑ ሥቃይን አሠቃያቸው፤ እግዚአብሔርም መልአኩን ልኮ አጸናቸው፤ ቊስላቸውንም ፈወሰ። ከዚህም በኋላ መኰንኑ ከእርሱ ጋር ወደ ሀገረ ፃ ይዞአቸው ሄደ። 📌የጣዖታቱ ካህናትም ጣዖታቱን እንደምትረግም ስለ ቅድስት ደባሞን ነገሩት፤ እንዲሁም ባልንጀራዋ ዮና የምትባል ሴት እንዳለች ነገሩት፤ እነርሱም ኅብራቸው በየራሱ የሆኑ መልካም ልብሶችን እየሠሩ ለምግባቸው ይሸጡ ነበር፤ የተረፋቸውንም ይመጸውቱ ነበር። መኰንኑም የዮናን ዜና ሰምቶ ራሷን በሰይፍ እንዲቆርጥ ባለሰይፉን ላከው፤ የሰያፊውም ስም አውሎጊስ ነው።
📌ወደርሷም በቀረበ ጊዜ ፊትዋ እንደ መላእክት ፊት ብርሃንን ተመልቶ አየና ፈራ፤ እርሷንም ወደ መኰንኑ እንዲወስዳት እንጂ እንዳይገድላት የእግዚአብሔር ጸጋ አስገነዘበችው፤ ቤተ ሰቦቿም ተሰነባብተዋት ጸንፋ ከሚባል አገር ወጣች፤ ወደ ሀገረ ፃ ደርሳም መኰንኑን ተገናኘችው፤ ከቅዱስ ዋርስኖፍና ከባልንጀሮቹ ጋራ እርስ በርሳቸው ሰላምታ ተሰጣጡ።📌ሰያፊው አውሎጊስም ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነና ራሱን ቆረጡት፤ የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለ፤ እንዲሁም እሊያን ቅዱሳት ደናግልንም ራሳቸውን ቈረጧቸው፤ ገድላቸውንም ፈጽመው የድል አክሊልን ተቀበሉ። 📌ቅድስት ደባሞንን ግን ጽኑዕ ሥቃይ ያሠቃዩአት ዘንድ በመንኰራኵር ላይ ሰቀሉአት።
በዚህ ሥቃይም ውስጥ ለብዙ ቀኖች ኖረች፤ የእግዚአብሔር መልአክም ያጸናት፣ ያስችላትና ቊስሎቿን ይፈውሳት ነበር፤ መኰንኑም ወደ ወህኒ ቤት አስገባት፤ በዚያም ጥቂት ቀን ኖረች፤ ወደ ፍርድ ሸንጎም አስቀርቦ "ለአማልክት ሠዊ" አላት፤ ባልሰማችውም ጊዜ ራሷን እንዲቆርጡ አዘዘ።📌ራስዋንም ሊቆርጡ ከከተማ ወደ ውጭ ባወጧት ጊዜ ሴቶች ሁሉ እያለቀሱ ከብበዋት ነበር፤ እርሷ ግን ፈጽማ ደስ ይላት ነበር። ራስዋንም በሰይፍ ቆረጧት፤ እንዲሁም እናቷንና እኅቷን በሰይፍ ቆረጧቸው፤ በመንግሥተ ሰማያትም የድል አክሊልን ተቀበለ። "ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእሊህ የቅዱሳት ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ይድረሰን ለዘላለሙ አሜን።" ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን" (የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል) ✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔) ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮ @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯
እስልምና በዓለም ላይ የተስፋፋው በሰይፍ እንደሆነ ሙስሊሞች ራሳቸው ያምናሉ።አምላክ እንዴት ሰውን ወደ መግደል ያነሳሳል? እስልምናን የተወ ሰው (ሙርተድ) እንዲገደል ይታዘዛል። አምላክ ግን ነጻ አድርጎ ነው የፈጠረን። ክርስቶስ ግን በኃይል በተጋፈጡት ጊዜ፣ ጴጥሮስ ሰይፉን ሲመዝ፦ «ሰይፍህን ወደ ስፍራው መልስ፤ ሰይፍ የሚመዙ ሁሉ በሰይፍ ይጠፋሉ» አለው (ማቴዎስ 26:52-54)። ክርስቶስ «ቀኝ ጉንጭህን ለሚመታህ ግራህን ደግሞ ስጠው» በማለት ፍቅርን አስተማረ (ማቴዎስ 5:39)።
በፍርድ ቤት ምስክርነት ላይም፣ ቁርዓን የአንድ ወንድ ምስክርነት ከሁለት ሴቶች ምስክርነት ጋር እኩል እንደሆነ ይናገራል (አንደኛዋ ብትረሳ ሌላኛዋ እንድታስታውሳት!)።የሴት ልጅ አእምሮ ከወንድ ያነሰ መሆኑን የሚያሳይ ምንም የሳይንስ ማረጋገጫ የለም። እኔ ራሴ በ1963 ዓ.ም ከፍተኛ የትምህርት ዲግሪ ይዤ የትምህርት ቤት ርዕሰ መምህርት በነበርኩበት ወቅት፣ የአባቴን የውርስ ጉዳይ ለመፈጸም ፍርድ ቤት ስሄድ፣ የእኔ ምስክርነት ውድቅ ተደርጎ የሌላ ሴት ረዳትነት እንድፈልግ ተደረገ፤ ነገር ግን የ16 ዓመት ዕድሜ የነበረው የወንድሜ ልጅ ምስክርነት ብቻውን ተቀባይነት አገኘ። ይህ ሕግ በበረሃ ለነበሩ የዱሮ ጎሳዎች እንጂ ለዘመናዊው ዓለም የሚሆን አይደለም።
በሃይማኖታዊ መጋረጃ (ኒቃብ/ሒጃብ) ረገድም፣ የወንዶችን ስሜት ለመጠበቅ ሲባል ሴት ልጅ ከራስ ፀጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ እንድትሸፈን መገደዷ ስህተት ነው፤ ክርስቶስ ግን «ሴትን በምኞት ዓይን ያየ ሁሉ በልቡ አመንዝሯል» በማለት ኃጢአቱን ለወንዶችም ጭምር ሰጥቷል (ማቴዎስ 5:28)።ክፍል ፯ ይቀጥላል✍️ ✍️ባለ ታሪክ ጸሐፊ ፦ናህድ ማሕሙድ መተወሊ ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮ @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯
አዝበቃዴስ ክንፍህ ተዘርግቶልን ደመናው በአንተ ተጋረደልን አብረኸን ልትሆን ጌታ የላከህ አንተ ሚካኤል ታዳጊያችን ነህ ከኛ ጋር ነበርክ አርባውን ዘመን እንጠራሃለን ሚካኤል ብለን
አዝሙሴ ሲለየን ደጉ አባታችን ሚካኤል ነበር ከላይ መሪያችን የባርነቱ ጉዞ እስኪያበቃ እጅግ ረዳን የኛ ጠበቃ ከኛ ጋር ነበርክ አርባውን ዘመን እንጠራሃለን ሚካኤል ብለን
አዝሳጥናኤል መክሮ የሐሰት ምክር ሊወስደን ሻተ ሙሴ መቃብር ስለማይጠቅመን አንተ ሰወርከው ምክሩን በታትነህ አስጎነበስከው ከኛ ጋር ነበርክ አርባውን ዘመን እንጠራሃለን ሚካኤል ብለን 🎤ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ🎤 ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮ @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯
አዝከሊቀ ነብያት - - - - ቅዱስ ሚካኤል ከነሙሴ ጋራ - - - - - ቅዱስ ሚካኤል ሕዘበ እሥራኤልን - - - ቅዱስ ሚካኤል ሚካኤል ሲመራ - - - ቅዱስ ሚካኤል ቀን ደመና ጥሎ - - - ቅዱስ ሚካኤል ሌሊት እያበራ - - - - - ቅዱስ ሚካኤል ተሻገሩ ኤርትራን - - - -ቅዱስ ሚካኤል ሁሉም በየተራ - - - - ቅዱስ ሚካኤል 🎤 ዘማሪ ዲ/ን ታዴዎስ ግርማ🎤 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺 📎 👇 ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮ @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯
"ቅዱስ አብ ሆይ ጠብቀን፤ ቅዱስ ወልድ ሆይ አድነን፤ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ ሆይ አጽናን፤ ስምህ ለዘላለሙ የተመሰገነ ይሁን። አሜን።"╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮ @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯
አዝእክህደከ ሰይጣን ጠላቴን ክጃለው ለዚህም ምስክር ማርያም ናት ብያለው በቤተክርስትያን ቆሜ በመቅደሱ ለቅድስት ሥላሴ ዘመርኩ ለንጉሱ
አዝአልነበረም ዘመን እሱ ያል ነበረበት ዳግመኛም አይኖርም እርሱ ማይኖርበት የህይወቴ ጣእም ክብርና ሞገሴ የማይሾሙት ንጉስ ዘላለም ሥላሴ
አዝኪሩቤል ሱራፌል ኃይላት ሊቃናት መናብርት ስልጣናት ቆመው በአንድ ነት ያላንዳች ዝምታ ይሉታል በክብር ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር 🎤ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ🎤 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺 📎 👇 ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮ @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
