en
Feedback
Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

Open in Telegram

#ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ #Orthodox ​📜 #የዕለቱ #ስንክሳር (#የቅዱሳን_ታሪክ) 💡 የአባቶች ምክርና ትምህርት 📖 ​ሕይወትን የሚቀይሩ ጥልቅ የአባቶች ምክር እና ትምህርቶች ይተላለፋሉ። ​ከቅዱሳት መጻሕፍት የተቀሰሙ ለነፍስ ምግብ የሚሆኑ ቁምነገሮች ይገኛሉ። ጥያቄ? ማስታወቂያ ለማሰራት @Samrina_12_23 ​ Buy ads: https://telega.io/c/OrthodoxTewahedoTrue

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

Channel Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶኦርቶዶክስ ተዋሕዶ (@orthodoxtewahedotrue) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 174 476 subscribers, ranking 139 in the Religion & Spirituality category and 126 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 174 476 subscribers.

According to the latest data from 16 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -3 435 over the last 30 days and by 6 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 4.41%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 2.62% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 7 696 views. Within the first day, a publication typically gains 4 572 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 87.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
#ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ #Orthodox ​📜 #የዕለቱ #ስንክሳር (#የቅዱሳን_ታሪክ) 💡 የአባቶች ምክርና ትምህርት 📖 ​ሕይወትን የሚቀይሩ ጥልቅ የአባቶች ምክር እና ትምህርቶች ይተላለፋሉ። ​ከቅዱሳት መጻሕፍት የተቀሰሙ ለነፍስ ምግብ የሚሆኑ ቁምነገሮች ይገኛሉ። ጥያቄ? ማስታወቂያ ለማሰራት @Samrina_12_23 ​ Buy ads: https://telega.io/c/OrthodoxTewahed...

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 17 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

174 476
Subscribers
+624 hours
-6967 days
-3 43530 days
Posts Archive
​📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሰኔ ፲፩/11 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌ሰኔ ዐሥራ አንድ በዚችው ቀን በጦርነት ድል አድራጊው ከቤተ መንግሥት ወገን የሆነ የመላእክት
📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሰኔ ፲፩/11 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌ሰኔ ዐሥራ አንድ በዚችው ቀን በጦርነት ድል አድራጊው ከቤተ መንግሥት ወገን የሆነ የመላእክት አርአያ ያለው የከበረ ሰማዕት ገላውዴዎስ የተጋድሎው ፍጻሜ ነው ። የዚህ ቅዱስ የአባቱ ስም አብጥልዎስ ነው፤ እርሱም ለሮም ንጉሥ ለኑማርያኖስ ወንድሙ ነው፤ መልኩም እንደ እስራኤል ያዕቆብ ልጅ እንደ ዮሴፍ እጅግ ውብ ነበር ።
እርሱም በጦርነት ላይ የበረታ ነበር፤ የአንጾኪያ ተወላጆችም ይመኩበት ነበር ።
​📌ዲዮቅልጥያኖስም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ክዶ አምልኮ ጣዖትን በአጸና ጊዜ እጅግ አዘነ፤ ፊቅጦር የሚባል የኀርማኖስ ልጅ ወዳጅ ነበረው፤ ሁልጊዜም የመጻሕፍትን ቃል ይሰሙ ነበር፤ ስለ ነፍሳቸውም ድኅነት ያነቡ ነበር ። ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደማቸውን ያፈሱ ዘንድ ተስማሙ ። ​📌በዚያ ጊዜም ሰይጣን በሽማግሌ አምሳል ታያቸው፤ ለአማልክት እንዲያጥኑ ቢመክራቸውም "ከእኛ ራቅ" ብለው አሳፈሩት ። ሰይጣኑም ወደ ዲዮቅልጥያኖስ ሄዶ "ፊቅጦርንና ገላውዴዎስን ካልገደልካቸው መንግሥትህን ይወስዳሉ" አለው ።
ንጉሡም ወደ ቅዱስ ገላውዴዎስ ልኮ ለጣዖታቱ እንዲሠዋ ለመነው፤ የአባቱንም ሹመት ይሾመው ዘንድ ቃል ገባለት፤ ሰምቶም አልታዘዘለትም ።
​📌ንጉሡም ወደ እንዴናው ገዥ እንዲህ ብሎ ጻፈ፦ "ገላውዴዎስ ትእዛዛችንን አልተቀበለም፤ አንተም ወደ ትእዛዛችን ይመለስ እንደሆነ በብዙ ድካም ሸንግለው፤ ይህ ካልሆነ ራሱን በሰይፍ ቁረጥ" ።
ቅዱስ ገላውዴዎስም የእኅቱ ባል የሆነ ሲድራማኮስን ጠርቶ ጌታችንን በማመን እንዲጸና ወገኖቹንም እንዲያጸናቸው አደራ አለው ።
​📌ወደ እንዴናው ገዥ ወደ አርያኖስም በደረሰ ጊዜ አርያኖስ "የንጉሥን ትዕዛዝ አትተላለፍ" ብሎ ለመነው ። ቅዱስ ገላውዴዎስም "ንጉሥ ያዘዘህን ልትፈፅም እንጂ በነገርህ ልታስተኝ አልተላክሁም" አለው ። መኰንኑም ተቆጥቶ በመኰንኑ እጅ ጦር ነበረ፤ ቅዱስ ገላውዴዎስንም ወጋው፤ ነፍሱንም ክብር ይግባውና በጌታችን እጅ ሰጠ፤ በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ ። ​📌ምእመናንም የቅዱስ ገላውዴዎስን ሥጋ ወሰዱ፤ ከቅዱስ ፊቅጦር ሥጋ ጋርም በሣጥን ውስጥ አኖሩት ።
ከዚህ በኋላም የቅዱስ ፊቅጦር እናት ቅድስት ሶፍያ የቅዱሳን ገላውዴዎስንና የፊቅጦርን ሥጋቸውንም ወስዳ ወደ አንጾኪያ አደረሰች ። የቅዱስ ገላውዴዎስ ሥጋ አስዩጥ በሚባል አገር ይኖራል የሚልም አለ ።
"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ መስተጋድል ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።" ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር ​"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን" (የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል) ✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔) ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

✨የቤተ ቅዱስ ሚካኤል 4ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በታላቅ ድምቀት! ✨ ​እንኳን አደረሳችሁ! "ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ" (መዝ📖📖 122፡1)። ​የቤተ ቅዱስ ሚካኤል የት
የቤተ ቅዱስ ሚካኤል 4ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በታላቅ ድምቀት! ​እንኳን አደረሳችሁ! "ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ" (መዝ📖📖 122፡1)። ​የቤተ ቅዱስ ሚካኤል የትምህርትና የበጎ አድራጎት መንፈሳዊ ማህበር 4ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ በግሩፖችን ላይ ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ፕሮግራሞችን አዘጋጅቷል! 🗓 ቀን፡ ሰኔ 12 እስከ ሰኔ 14 🌟በዕለቱ ምን ይጠብቅዎታል❔ ​አስተማሪ መንፈሳዊ ትምህርቶች (ከታላላቅ መምህራን) ​ልዩ የመዝሙር ግብዣዎች (ከሚወዷቸው ዘማሪያን) ​የኪነ-ጥበብ ስራዎች እና ሌሎች አዳዲስ ዝግጅቶች❕ ​በዚህ በረከት በተሞላበት የምስረታ በዓል ላይ በመገኘት፣ በሊቃውንት ትምህርት እና በዘማሪያን መንፈሳዊ ዝማሬዎች ለመንፈስዎ ምግብ ይሁኑ። ​✅አሁኑኑ ይቀላቀሉን፡ 👉https://t.me/Bete_kidus_Michael_12 https://t.me/Bete_kidus_Michael_12 https://t.me/Bete_kidus_Michael_12

የእግዚአብሄር መልአክ ስሙ ድንቅ ነው የእግዚአብሄር መልአክ ስሙ ድንቅ ነው ለቶርያስ ሰው ለማኑኤል እንደነገረው በመሰውያው ነበልባል ውስጥ አረገ አያሉ ሚካኤል ድንቅን አደረግ{፪} ከዳን ወገን የሆነው በእግዚአብሄር ያመነው ባኑሄ የሚባል ሰው የጌታ መልአክ ታየው ሚስቱ መካን ነበረች ልጅንም ያልወለደች ሚካኤል ተገልጦላት በዘር ፍሬ ባረካት    የእግዚአብሄር መልአክ ስሙ ድንቅ ነው    በኦፍራ አድባር ለጌድዮን የተገለጠው    እስራኤልን ከመድያን ኑ  ታደገ    አያሉ ሚካኤል ድንቅን አደረገ{፪}
አዝ
አንተ ፃኑ አያል ሰው እግዚእብሄር ካንተ ጋርነው ክንድህን ላበረታ ተልኬአለው ከጌታ አይዞህ ጌዲዮን ያለው ቁርባኑን ያሸተተው ከእኛ ጋር ነው  ሚካኤል ሰልፋችንን ይመራል     የእግዚአብሄር መላክ ስሙ ድንቅ ነው    በኦርማ አውድማ ሰይፍን ይዞ ቆሞየታየው    ዳዊት በመንቀጥቀጥ ፊቱን ፈለገ    አያሉ ሚካኤል ድንቅን አደረገ{፪}
አዝ
በሶስት ቀን ቸነፈር እንዳትጠፍ ምድር ሰባ ሺ ሰዎች ወድቀው መላኩን በቃ አለው ለምህረት ይመጣሉ ለመሀት ይላካሉ ሰይፉን ባፎቱ ከቷል ሚካኤል ለህዝቡ ቆማል    የእግዚአብሄር መልአክ ስሙ ድንቅ ነው    ስምኦን ጴጥሮስን ከወድኔ ገብቶ ያወጣው    የእጆቹን ሰንሰለት ፈቶ አረገ    አያሉ ሚካኤል ድንቅን አደረገ{፪}
አዝ
በጠባቂዎች መሀል ኬፋል ከእንቅልፋአገታ የተዘጋውን ደጃፍ አልተሳነውም ማለፍ ሚካኤል እየመራው ጴጥሮስ እግሩ የቀናው አውቆታል ልቡ በርቶ ዘለለ ስሙን ጠርቶ    የእግዚአብሄር መልአክ ስሙ ድንቅነው    ለቶርያስ ሰው ለማኑኤል እንደነገረው    በመሰውያው ነበልባል ውስጥ አረገ    ሀያሉ ሚካኤል ድንቅን አደረገ ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሰኔ ፲/10 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌ሰኔ ዐሥር በዚች ቀን ቅዱሳት ደናግል ደባሞንና ብስጣሞን እናታቸውም ሶፍያ በሰማዕትነት ሞቱ።
እንዲህም ሆነ፤ ስሙ ዋርስኖፍ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፤ ኤጲስቆጶስነት ሊሾሙት በወደዱ ጊዜ ሸሽቶ ወደ ናባ አውራጃ እሊህ ደናግል ወዳሉበት ወደ ግሕሙን ደርሶ በዚያ አደረ።
​📌በዚያችም ሌሊት የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጦለት "ከዚህ ለምን ትተኛለህ? ተነሥተህ ተጋደል፤ ለአንተና ሰማዕት መሆን ለሚሹ ሁሉ አክሊል ተዘጋጅቷልና፤ አሁንም ተነሥተህ ወደ መኰንኑ ሂድ፤ በፊቱም ቆመህ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመን" አለው። ​📌ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ ራእይን እንዳየ ለቅዱሳት ደናግል ነገራቸው። ሲነጋም ተነሥተው ከእርሱ ጋራ ወደ መኰንኑ ሄዱ፤ በመኰንኑ ፊት ክብር ይግባውና በጌታችን ታመኑ። መኰንኑም ይዞ ጽኑ ሥቃይን አሠቃያቸውና ወደ ወህኒ ቤት ጨመራቸው፤ ከጥቂት ቀኖችም በኋላ ከዚያ አውጥቶ ከቅዱስ ዋርስኖፍ ጋራ ወደ ስንሑር ላካቸው፤ እናታቸውም ትከትላቸው ነበር። ​📌መኰንኑም "ለአማልክት ዕጣን ዕጠኑ" አላቸው፤ ባልታዘዙለትም ጊዜ ጽኑ ሥቃይን አሠቃያቸው፤ እግዚአብሔርም መልአኩን ልኮ አጸናቸው፤ ቊስላቸውንም ፈወሰ። ከዚህም በኋላ መኰንኑ ከእርሱ ጋር ወደ ሀገረ ፃ ይዞአቸው ሄደ። ​📌የጣዖታቱ ካህናትም ጣዖታቱን እንደምትረግም ስለ ቅድስት ደባሞን ነገሩት፤ እንዲሁም ባልንጀራዋ ዮና የምትባል ሴት እንዳለች ነገሩት፤ እነርሱም ኅብራቸው በየራሱ የሆኑ መልካም ልብሶችን እየሠሩ ለምግባቸው ይሸጡ ነበር፤ የተረፋቸውንም ይመጸውቱ ነበር። መኰንኑም የዮናን ዜና ሰምቶ ራሷን በሰይፍ እንዲቆርጥ ባለሰይፉን ላከው፤ የሰያፊውም ስም አውሎጊስ ነው።
​📌ወደርሷም በቀረበ ጊዜ ፊትዋ እንደ መላእክት ፊት ብርሃንን ተመልቶ አየና ፈራ፤ እርሷንም ወደ መኰንኑ እንዲወስዳት እንጂ እንዳይገድላት የእግዚአብሔር ጸጋ አስገነዘበችው፤ ቤተ ሰቦቿም ተሰነባብተዋት ጸንፋ ከሚባል አገር ወጣች፤ ወደ ሀገረ ፃ ደርሳም መኰንኑን ተገናኘችው፤ ከቅዱስ ዋርስኖፍና ከባልንጀሮቹ ጋራ እርስ በርሳቸው ሰላምታ ተሰጣጡ።
​📌ሰያፊው አውሎጊስም ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነና ራሱን ቆረጡት፤ የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለ፤ እንዲሁም እሊያን ቅዱሳት ደናግልንም ራሳቸውን ቈረጧቸው፤ ገድላቸውንም ፈጽመው የድል አክሊልን ተቀበሉ። ​📌ቅድስት ደባሞንን ግን ጽኑዕ ሥቃይ ያሠቃዩአት ዘንድ በመንኰራኵር ላይ ሰቀሉአት።
በዚህ ሥቃይም ውስጥ ለብዙ ቀኖች ኖረች፤ የእግዚአብሔር መልአክም ያጸናት፣ ያስችላትና ቊስሎቿን ይፈውሳት ነበር፤ መኰንኑም ወደ ወህኒ ቤት አስገባት፤ በዚያም ጥቂት ቀን ኖረች፤ ወደ ፍርድ ሸንጎም አስቀርቦ "ለአማልክት ሠዊ" አላት፤ ባልሰማችውም ጊዜ ራሷን እንዲቆርጡ አዘዘ።
​📌ራስዋንም ሊቆርጡ ከከተማ ወደ ውጭ ባወጧት ጊዜ ሴቶች ሁሉ እያለቀሱ ከብበዋት ነበር፤ እርሷ ግን ፈጽማ ደስ ይላት ነበር። ራስዋንም በሰይፍ ቆረጧት፤ እንዲሁም እናቷንና እኅቷን በሰይፍ ቆረጧቸው፤ በመንግሥተ ሰማያትም የድል አክሊልን ተቀበለ። ​"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእሊህ የቅዱሳት ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ይድረሰን ለዘላለሙ አሜን።" ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር ​"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን" (የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል) ✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔) ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

ከእስልምና ወደ☦️ክርስትና ​ ✍️ ክፍል ፮ ​📌(ኃይል በቁርዓን፣ ሰላም በወንጌል እና የሴቶች መብት) ​ቁርዓን አማኞችን ወደ መግደልና ወደ ጦርነት የሚጠሩ ስፍር ቁጥር የሌላቸው ጥቅሶች አሉት። እ
ከእስልምና ወደ☦️ክርስትና     ​      ✍️ ክፍል ፮ 📌(ኃይል በቁርዓን፣ ሰላም በወንጌል እና የሴቶች መብት) ​ቁርዓን አማኞችን ወደ መግደልና ወደ ጦርነት የሚጠሩ ስፍር ቁጥር የሌላቸው ጥቅሶች አሉት።
እስልምና በዓለም ላይ የተስፋፋው በሰይፍ እንደሆነ ሙስሊሞች ራሳቸው ያምናሉ።
አምላክ እንዴት ሰውን ወደ መግደል ያነሳሳል? እስልምናን የተወ ሰው (ሙርተድ) እንዲገደል ይታዘዛል። አምላክ ግን ነጻ አድርጎ ነው የፈጠረን። ክርስቶስ ግን በኃይል በተጋፈጡት ጊዜ፣ ጴጥሮስ ሰይፉን ሲመዝ፦ «ሰይፍህን ወደ ስፍራው መልስ፤ ሰይፍ የሚመዙ ሁሉ በሰይፍ ይጠፋሉ» አለው (ማቴዎስ 26:52-54)። ክርስቶስ «ቀኝ ጉንጭህን ለሚመታህ ግራህን ደግሞ ስጠው» በማለት ፍቅርን አስተማረ (ማቴዎስ 5:39)።
በፍርድ ቤት ምስክርነት ላይም፣ ቁርዓን የአንድ ወንድ ምስክርነት ከሁለት ሴቶች ምስክርነት ጋር እኩል እንደሆነ ይናገራል (አንደኛዋ ብትረሳ ሌላኛዋ እንድታስታውሳት!)።
የሴት ልጅ አእምሮ ከወንድ ያነሰ መሆኑን የሚያሳይ ምንም የሳይንስ ማረጋገጫ የለም። እኔ ራሴ በ1963 ዓ.ም ከፍተኛ የትምህርት ዲግሪ ይዤ የትምህርት ቤት ርዕሰ መምህርት በነበርኩበት ወቅት፣ የአባቴን የውርስ ጉዳይ ለመፈጸም ፍርድ ቤት ስሄድ፣ የእኔ ምስክርነት ውድቅ ተደርጎ የሌላ ሴት ረዳትነት እንድፈልግ ተደረገ፤ ነገር ግን የ16 ዓመት ዕድሜ የነበረው የወንድሜ ልጅ ምስክርነት ብቻውን ተቀባይነት አገኘ። ይህ ሕግ በበረሃ ለነበሩ የዱሮ ጎሳዎች እንጂ ለዘመናዊው ዓለም የሚሆን አይደለም።
በሃይማኖታዊ መጋረጃ (ኒቃብ/ሒጃብ) ረገድም፣ የወንዶችን ስሜት ለመጠበቅ ሲባል ሴት ልጅ ከራስ ፀጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ እንድትሸፈን መገደዷ ስህተት ነው፤ ክርስቶስ ግን «ሴትን በምኞት ዓይን ያየ ሁሉ በልቡ አመንዝሯል» በማለት ኃጢአቱን ለወንዶችም ጭምር ሰጥቷል (ማቴዎስ 5:28)።
ክፍል ፯ ይቀጥላል✍️ ✍️ባለ ታሪክ ጸሐፊ ፦ናህድ ማሕሙድ መተወሊ ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

✞♡​​የአፎምያ ረዳት ነህ♡✞ የአፎሚያ ረዳት ነህ ሚካኤል(፪) ቅሩበ እግዚአብሔር የልዑል ፈጥነህ ድረስልን ስንጠራህ ሚካኤል ፊት ለፊታችን አምላክ ሰደደህ አቀናህልን መንገዱን ጠርገህ የቤልሆርን ምክር አፈረስክ ከልጆችህ ጋር ከነአን ደረስክ    ከኛ ጋር ነበርክ አርባውን ዘመን    እንጠራሃለን ሚካኤል ብለን
አዝ
በቃዴስ ክንፍህ ተዘርግቶልን ደመናው በአንተ ተጋረደልን አብረኸን ልትሆን ጌታ የላከህ አንተ ሚካኤል ታዳጊያችን ነህ   ከኛ ጋር ነበርክ አርባውን ዘመን   እንጠራሃለን ሚካኤል ብለን
አዝ
ሙሴ ሲለየን ደጉ አባታችን ሚካኤል ነበር ከላይ መሪያችን የባርነቱ ጉዞ እስኪያበቃ እጅግ ረዳን የኛ ጠበቃ   ከኛ ጋር ነበርክ አርባውን ዘመን   እንጠራሃለን ሚካኤል ብለን
አዝ
ሳጥናኤል መክሮ የሐሰት ምክር ሊወስደን ሻተ ሙሴ መቃብር ስለማይጠቅመን አንተ ሰወርከው ምክሩን በታትነህ አስጎነበስከው    ከኛ ጋር ነበርክ አርባውን ዘመን    እንጠራሃለን ሚካኤል ብለን                         🎤ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ🎤 ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

✞♡አይኑ ዘርግብ♡✞ አይኑ ዘርግብ ልብሱ ዘመብረቅ ሊቀ መላእክት ሚካኤል ልዑለ መንበር ሐመልማለ ወርቅ ሰዐሌ ምሕረት ወመተንብል ረዳኤ ምንዱባን ዘአስተዓፀቡ ያቀልል በነ ሰናክሬም ላይ ሰይፍን የመዘዘ የሕዝቅያስ ምሕረት በእጁ የተያዘ መዓቱን ለአህዛብ በሞት የገለጠ የሕዝቅያስን ሞት በሕይወት የለወጠ የእስራኤል ድንኳኖች በደስታ ተሞሉ ክብር ለአምላካችን ይገባል እያሉ መልአኩን የላከ ሕዝቡንም የረዳ ግሩም ነው እግዚአብሔር ያወጣን ከእዳ የሰናክሬም ቁጥሩ እጅግ ብዙ ነው የኔ ረዳቴ ግን ቅዱስ ሚካኤል ነው ከፈረሰኞች በላይ ነው ፍጥነቱ ከተዋጊዎቹ ይበልጣል ብርታቱ እስራኤልን መና እንደመገባቸው ባሕታውያንን በዱር የረዳቸው ተክለኃይማኖትን ከጉድጓድ ያወጣ እኔንም ሳይንቀኝ ሊያድነኝ መጣ ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

​📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሰኔ ፱/9 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌ሰኔ ዘጠኝ በዚች ዕለት የታላቁ ነቢይ ሳሙኤል የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። የዚህ ቅዱስ አባቱ ሕልቃ
📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሰኔ ፱/9 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌ሰኔ ዘጠኝ በዚች ዕለት የታላቁ ነቢይ ሳሙኤል የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። የዚህ ቅዱስ አባቱ ሕልቃና ይባላል የእናቱም ስሟ ሐና ነው። እነርሱም ከሌዊ ነገድ ከካህኑ አሮን ወገን ናቸው። ሐናም መካን ነበረች፤ ክብር ይግባውና ወደ እግዚአብሔር እያለቀሰች አዘውትራ ስለ ማለደች ይህን የተባረከ ልጅ ሰጣት፤ በቤቷም ሦስት ዓመት አሳደገችው። ​📌ከዚህም በኋላ ገና ስትፀንሰው እንደተሳለች ወደ እግዚአብሔር መቅደስ አቀረበችው፤ ካህኑ ኤሊንም በመላላክ የሚያገለግለው ሆነ። የካህኑ የኤሊ ልጆች ግን ክፉዎች ነበሩ፤ እግዚአብሔርንም አይፈሩም ነበር፤ በቅዱስ መሥዋዕቱም ላይ በደሉ። ይህ ሕፃን ሳሙኤል ግን በኤሊ ፊት ለእግዚአብሔር ሲያገለግል ኖረ፤ በነዚያ ወራቶችም ቃለ እግዚአብሔር ውድ ነበር፤ የሚታይ ራእይም አልነበረም። ​📌ከዚህም በኋላ በአንዲት ሌሊት እንዲህ ሆነ፤ ኤሊ በመኝታው ተኝቶ ሳለ ዐይኖቹም መፍዘዝ ጀምረው ነበር፤ ማየትም አይችልም ነበር። የእግዚአብሔርንም መብራት አብርቶ ለማሳደር ገና አላዘጋጁም ነበር፤ ሳሙኤል ግን በቤተ መቅደስ በእግዚአብሔር ማደሪያ ታቦት አጠገብ ተኝቶ ነበር። ​📌እግዚአብሔርም ሳሙኤልን "ሳሙኤል ሳሙኤል" ብሎ ጠራው፤ እነሆ እኔ አለሁ አለ። ወደ ኤሊም ፈጥኖ ሄደ "ስለጠራኸኝ እነሆ እኔ መጣሁ" አለው፤ ኤሊም "አልጠራሁህም ተመልሰህ ተኛ" አለው፤ ሄዶም ተኛ። ​📌እግዚአብሔርም ዳግመኛ "ሳሙኤል ሳሙኤል" ብሎ ጠራው፤ ሳሙኤልም ተነሥቶ ወደ ኤሊ ሄደ "ስለጠራኸኝ እነሆ መጣሁ" አለው። ኤሊም "አልጠራሁህም ተመልሰህ ተኛ" አለው። ሳሙኤልም ከዚህ አስቀድሞ እግዚአብሔርን በራእይ ገና አላወቀውም ነበር፤ ቃለ እግዚአብሔርም አልተገለጠለትም ነበር። ​📌ዳግመኛም እግዚአብሔር ሳሙኤልን ሦስተኛ ጊዜ ጠራው፤ ተነሥቶም ወደ ኤሊ ሄደ "ስለጠራኸኝ እነሆ መጣሁ" አለው፤ ኤሊም ያንን ልጅ እግዚአብሔር እንደጠራው አሰበ። "ልጄ ተመልሰህ ተኛ፤ የሚጠራህ ካለ 'እኔ ባሪያህ እሰማለሁና ጌታዬ ተናገር' በለው" አለው፤ ሳሙኤልም ሄዶ በመኝታው ተኛ። ​📌እግዚአብሔርም መጥቶ እንደ መጀመሪያው በፊቱ ቆሞ ጠራው። ሳሙኤልም "እኔ ባሪያህ እሰማሃለሁና ጌታዬ በል ተናገር" አለው፤ እግዚአብሔርም ሳሙኤልን "የሰማው ሁሉ ሁለቱን ጆሮዎቹን ይይዝ ዘንድ እነሆ እኔ በእስራኤል ላይ የተናገርሁት ቃሌን አደርጋለሁ። ​📌በዚያችም ቀን በኤሊና በወገኑ ላይ የተናገርሁትን ሁሉ አጸናለሁ፤ እጀምራለሁ እፈጽማለሁም። ልጆቹ የእግዚአብሔርን ቃል አቃልለዋልና እርሱም አልገሠጻቸውምና በልጆቹ ኃጢአት እኔ ወገኑን ለዘላለም እንደምበቀለው ነገርሁት። ስለዚህም ነገር በዕጣንም ቢሆን በመሥዋዕትም ቢሆን የኤሊ የወገኑ ኃጢአት እስከ ዘላለሙ ድረስ እንዳይሠረይ ራሴ እንዲህ ብዬ ማልሁ" አለው። በኤሊ ወገኖችና ልጆች ላይ እግዚአብሔር የተናገረው ሁሉ ተፈጸመ። ​📌ከዚህም በኋላ የቂስ ልጅ ሳኦልን ቀብቶ ለእስራኤል ልጆች ያነግሠው ዘንድ እግዚአብሔር ሳሙኤልን አዘዘው፤ እንዲያነግሥላቸው ለምነዋልና። ሳኦልም የልዑልን ትእዛዝ በተላለፈ ጊዜ፣ ዳግመኛ ለእስራኤል ንጉሥ ሊሆን የዕሴይ ልጅ ዳዊትን ይቀባው ዘንድ ይህን ነቢይ ሳሙኤልን ዳግመኛ አዘዘው። ይህም ነቢይ ሳሙኤል በሕይወት በኖረበት ዘመን ሁሉ እስራኤልን አስተዳደራቸው። ከዚህም በኋላ በሰላም አረፈ። ​"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ታላቅ ነቢይ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።" ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር ​"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን" (የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል) ✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔) ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

Repost from N/a
📍 ለመሆኑ በቴሌግራም ትልቁን የኦርቶዶክስ መዝሙር ቻናል ተቀላቅለዋል ? የሰርግ ፣ የሀዘን ፣ የንግስ መዝሙራት ፣ የተለያዩ ወረባት ፣ የመዝሙር ግጥሞችን ያገኛሉ ። አብረውንም መዝሙራትን ያጠናሉ
📍 ለመሆኑ በቴሌግራም ትልቁን የኦርቶዶክስ መዝሙር ቻናል ተቀላቅለዋል ? የሰርግ ፣ የሀዘን ፣ የንግስ መዝሙራት ፣ የተለያዩ ወረባት ፣ የመዝሙር ግጥሞችን ያገኛሉ ። አብረውንም መዝሙራትን ያጠናሉ ። # ይቀላቀሉን  👇👇 https://t.me/+_R21gL_5brU5MDRk https://t.me/+_R21gL_5brU5MDRk

የዘማሪ አቤል መክብብን ድንቅ የዝማሬዎችን ስራዎችን ማግኘት ይፈልጋልሉ ⁉️ለማግኘት ይቀላቀሉ።🙏🙏
የዘማሪ አቤል መክብብን ድንቅ የዝማሬዎችን ስራዎችን ማግኘት ይፈልጋልሉ ⁉️ለማግኘት ይቀላቀሉ።🙏🙏

https://t.me/synergycounseling ሲነርጂ መንፈሳዊ ፔጅ ነው ፤ አላማውም በሥነ ልቦና ቀውስ ውስጥ የገቡ ሰዎችን በመንፈሳዊ(Orthodox Psychotherapy) እንዲሁም በሥነ ልቦና (Counselling Psychology) መርዳት ነው ፤

ባሕራንኒ ይቤ /፮/ ባሕራንኒ ይቤ ኦ ዘነገደ ባህር /፪/ ርዒክዎ ለሚካኤል ወስዕንኩ ጠይቆቱ ዘይብል/፪/ ባህራንኒ ይቤ /፮/ የሞቱን ደብዳቤ - - -  ቅዱስ ሚካኤል ሚካኤል አጥፍቶ - - -  ቅዱስ ሚካኤል ባሕራንን አዳነው - - -   ቅዱስ ሚካኤል   በሠርግ ተክቶ - - -  -    ቅዱስ ሚካኤል ሠዳዴ ሳጥናኤል - - -  ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት - - - -    ቅዱስ ሚካኤል እኛንም አድነን - - - -    ቅዱስ ሚካኤል  ከሲኦል እሳት - - - - -   ቅዱስ ሚካኤል
አዝ
ከሊቀ ነብያት - - -  -     ቅዱስ ሚካኤል ከነሙሴ ጋራ - - - -  -   ቅዱስ ሚካኤል ሕዘበ እሥራኤልን - - - ቅዱስ ሚካኤል ሚካኤል ሲመራ - - -  ቅዱስ ሚካኤል ቀን ደመና ጥሎ - - -   ቅዱስ ሚካኤል ሌሊት እያበራ - - - -  -  ቅዱስ ሚካኤል ተሻገሩ ኤርትራን - -  - -ቅዱስ ሚካኤል ሁሉም በየተራ - - -  -   ቅዱስ ሚካኤል        🎤 ዘማሪ ዲ/ን  ታዴዎስ  ግርማ🎤 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺                      📎 👇 ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

​📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሰኔ ፰/8 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌ሰኔ ስምንት በዚች ቀን አምላክን የወለደች በሁለት ወገን ድንግል የሆነች የእመቤታችን ማርያም የታወ
📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሰኔ ፰/8 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌ሰኔ ስምንት በዚች ቀን አምላክን የወለደች በሁለት ወገን ድንግል የሆነች የእመቤታችን ማርያም የታወቀችው በውኃ ምንጭ ዘንድ ያለች የቤተ ክርስቲያንዋ ቅዳሴ ነው። እርሱም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሷ ጋር ወደ ግብፅ አገር ተሰዶ ሲመለስ ያፈለቀው የተባረከ መታጠቢያ ነው። ​📌ይህም እንዲህ ነው፤ ለጻድቁ ዮሴፍ የእግዚአብሔር መልአክ በሕልም ተገልጾለት "ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብፅ አገር ሂድ" አለው። ዮሴፍም ነቅቶ ተነሣ፤ ክብር ይግባውና ሕፃኑን ጌታችንን፣ እናቱንና እኅቷ ሰሎሜን ይዞ ወደ ግብፅ አገር ሄዱ፤ በዚያም በውስጧ ባሉ በብዙ አገሮች እየዞሩ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር ኖሩ። ​📌ሄሮድስም ከሞተ በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ለዮሴፍ ሁለተኛ ተገለጠለት፤ ወደ እስራኤልም አገር ሕፃኑንና እናቱን ይዞ እንዲመለስ አዘዘው ። በሚመለሱም ጊዜ ወደ መዓልቃ ደረሱ፤ ከዚያም ወደ መጣርያ አገር ደረሱ፤ ይቺም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ውኃ ያፈለቀባትና የመታጠቢያ ቦታ የሆነች ናት፤ እርሷም እስከ ዛሬ አለች ። ​📌ሰዎችም ከአገሩ ሁሉ ከየነገዱ ሁሉ መጥተው አምላክን ወደ ወለደችና በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ወደ ጸናች ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም ይለምናሉ፤ ከተባረከውም የውኃ ምንጭ ታጥበው ከደዌያቸው ሁሉ ይድናሉ፤ በዛሬዪቱ ቀን ከከበረች ቤተ ክርስቲያንም ይባረካሉ። ​"እርሷን እመቤታችንን ለመረጣትና ለወደዳት፣ በሥጋም እናቱ ላደረጋት፣ ስለ እርሷም ዘመድ ለሆነንና ወደ እርሱ ላቀረበን፣ ወራሾቹም ላደረገን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን ።" ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር ​"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን" (የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል) ✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔) 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺                      📎 👇 ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

Repost from N/a
✝ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር ይፈልጋሉ?

🇪🇹 የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ የትኞቹን መዝሙራት ማግኝት ይፈልጋሉ❓

ምን ልክፈልህ ምን ልክፈልህ የኔ ጌታ አይረሳም ያ ውለታ የመረጥቀኝ የወደድከኝ በዝማሬ ያሳደከኝ ክበርልኝ ከታናሽዋ ከተማ ታላቁ ተገኝተሃል ከድካሜ ቀስቅሰህ እግሬን አስከትለሀል ስትመራኝ በፅድቅህ ጀርባህን አየዋለው ብርሃኔ ቀድመህልኝ ጨለማን ሰብርያለው ዝቅ ብለህ ወዳጄ አኖርከኝ በከፍታ ከሰማዩ በረከት ሰተከኝ እድል ፈንታ ተባረክ እልሀለው ይኸው መሽቶ እስኪነጋ አፈሳለው ምወድስ ልሳኔ ሳይዘጋ ገና ከእናቴ ማህፀን አካሌ ሳይሰራ አንተ ታውቀኝ ነበር በስሜ ሳልጠራ ተክለኸኝ በወንዙ ዳር በፀጋ ለምለሚያለው ለነብሴ ፀሀይ ሆነህ በደምህ ፈክቻለው ታላቅ መዝገብ ወስጄ ፈጣን ብዕር ብመዝም ውዴ የዋልክልኝን ያንተን ፍቅር አይደርስም ከመሰውያዬ ላይ ቅኔ እንባዬ ከአይኔ ስር ከተሰበረው ልቤ ይፈልቃል አዲስ መዝሙር 🎤ዘማሪ እዝራ ኃይለ ሚካኤል🎤 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺                      📎 👇 ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​እንኳን ለሥሉስ ቅዱስ (አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ) ወርሃዊ የክብር በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ! ​ዛሬ ሰኔ ሰባት ቀን ቅድስት ቤተክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።እንኳን ለሥሉስ ቅዱስ (አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ) ወርሃዊ የክብር በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ! ​ዛሬ ሰኔ ሰባት ቀን ቅድስት ቤተክርስቲያናችን የሥሉስ ቅዱስን ወርሃዊ በዓል በደስታ ታስባለች። ይህ ዕለት እግዚአብሔር አምላክ ለአባታችን ለአብርሃም በመምሬ ዛፍ ሥር በሦስትነቱና በአንድነቱ የተገለጠበትን ታላቅ ምስጢር የምናስብበት ነው (ዘፍጥረት ፲፰)። ​📌ከበዓሉ የምንማረውየደግነት ፍሬ አብርሃም እንግዶችን በቅንነትና በትሕትና በመቀበሉ የይስሐቅን መወለድ አገኘ። እኛም የተቸገሩትን በደግነት ስንረዳ የእግዚአብሔርን በረከት ወደ ቤታችን እንጋብዛለን። ​በንጽሕና መኖር ልባችንን ከክፋትና ከቂም አጥርተን በሃይማኖት ስንጸና፣ ቅድስት ሥላሴ በሕይወታችንና በቤታችን ማደሪያ ያደርጋሉ። ​የቤተሰብ ሰላም ባለ ትዳሮችና ቤተሰቦች በፍቅርና በጸሎት በአንድነት ሲኖሩ፣ እግዚአብሔር በዚያ ቤት ውስጥ የኑሮና የጤና በረከትን ያፈስሳል።
"ቅዱስ አብ ሆይ ጠብቀን፤ ቅዱስ ወልድ ሆይ አድነን፤ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ ሆይ አጽናን፤ ስምህ ለዘላለሙ የተመሰገነ ይሁን። አሜን።"
  ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

ገጼን አማትቤ ገጼን አማትቤ ልጀምር ውዳሴ በትምህርተ መስቀል በስመ ሥላሴ ይርቃል ከጎኔ ጠላት ዳቢሎስ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ከትቢያ ከአፈር አንስቶ የሰራኝ በአፉም እስትንፋስ ህይወትን ያደለኝ የሥላሴ ስራ ድንቅ ነው ጥበቡ ከአይምሮ በላይ ነው የእግዚአብሔር ሀሳቡ
አዝ
እክህደከ ሰይጣን ጠላቴን ክጃለው ለዚህም ምስክር ማርያም ናት ብያለው በቤተክርስትያን ቆሜ በመቅደሱ ለቅድስት ሥላሴ ዘመርኩ ለንጉሱ
አዝ
አልነበረም ዘመን እሱ ያል ነበረበት ዳግመኛም አይኖርም እርሱ ማይኖርበት የህይወቴ ጣእም ክብርና ሞገሴ የማይሾሙት ንጉስ ዘላለም ሥላሴ
አዝ
ኪሩቤል ሱራፌል ኃይላት ሊቃናት መናብርት ስልጣናት ቆመው በአንድ ነት ያላንዳች ዝምታ ይሉታል በክብር ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር 🎤ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ🎤 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺                      📎 👇 ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

😇መምህር ገብተዋል 📖📖 📚😇ነገረ ክርስቶስ😇📖📚 📔 ትምህርት ተጀምሯል ላይቭ ግቡ 🙏 ከታቺ ባለው ሊንክ ግቡ ቭኦይስ ቻት ግቡ 👇👇 https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=132ae57e1a061a7502 https://t.me/Bete_kidus_Michael_12

የርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማን ትምህርቶች በቀላሉ በትንሽ MB የምታገኙበት የ Telegram ቻናል እንሆ ቤተሰብ ሁኑ👇
የርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማን ትምህርቶች በቀላሉ በትንሽ MB የምታገኙበት የ Telegram ቻናል እንሆ ቤተሰብ ሁኑ👇