ch
Feedback
Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

前往频道在 Telegram

#ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ #Orthodox ​📜 #የዕለቱ #ስንክሳር (#የቅዱሳን_ታሪክ) 💡 የአባቶች ምክርና ትምህርት 📖 ​ሕይወትን የሚቀይሩ ጥልቅ የአባቶች ምክር እና ትምህርቶች ይተላለፋሉ። ​ከቅዱሳት መጻሕፍት የተቀሰሙ ለነፍስ ምግብ የሚሆኑ ቁምነገሮች ይገኛሉ።

显示更多

📈 Telegram 频道 Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ 的分析概览

频道 Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ (@orthodoxtewahedotrue) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 171 513 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 139,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 132

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 171 513 名订阅者。

根据 13 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -3 264,过去 24 小时变化为 -173,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 3.68%。内容发布后 24 小时内通常能获得 2.48% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 6 310 次浏览,首日通常累积 4 258 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 53

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
#ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ #Orthodox ​📜 #የዕለቱ #ስንክሳር (#የቅዱሳን_ታሪክ) 💡 የአባቶች ምክርና ትምህርት 📖 ​ሕይወትን የሚቀይሩ ጥልቅ የአባቶች ምክር እና ትምህርቶች ይተላለፋሉ። ​ከቅዱሳት መጻሕፍት የተቀሰሙ ለነፍስ ምግብ የሚሆኑ ቁምነገሮች ይገኛሉ።

凭借高频更新(最新数据采集于 14 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

171 513
订阅者
-17324 小时
-8857
-3 26430
帖子存档
ምስጋና አምልኮ ምስጋና አምልኮ ስግደት ውዳሴ ይገባል በሉ ሰዎች ለቅድስት ስላሴ ዘላለም አለም ቅዱስ ነህ አምሳያም  ወደር የሌለህ መተማመኛም ሆነኸኛል ሥላሴ ባንተ ደስ ይለኛል
አዝ
የታመነ ነው የተፈራ የጽድቅን ፀሐይ የሚያበራ ዓለሙ ፀንታል በሥላሴ ትዘምርለት ለእርሱ ነፍሴ
አዝ
ዘመናት በእጁ በመዳፉ ሁሌም የእርሱ ነው ድሉ ሰልፉ የእሳት መድረኮች ያሉት ጌታ የማያልፍ ነው የማይረታ
አዝ
አብርሃም አምኖ ተሰደደ በእርጅናው ወራት ልጅ ወለደ የተስፋውን ቃል ፈፀመለት ሥላሴ በሉ በቀን በለሊት መዝሙር ዘማሪት ጸዳለ ጎበዜ ❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖ ❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖  ❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖

​📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፯/7 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌በዚች ቀን የባሕታውያንና የቁምተኞች አለቃ፣ የታላቁና የቅዱስ አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ)
📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፯/7 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌በዚች ቀን የባሕታውያንና የቁምተኞች አለቃ፣ የታላቁና የቅዱስ አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ) የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። ​📌ይህ ቅዱስ በታችኛው ግብጽ አክሚም አውራጃ ስንላል ከምትባል አገር የተገኘ ሲሆን፣ ገና ሳይወለድ የመላእክት አምሳል የሆነው አባ ሐርስዮስ "ዜናው በዓለም የሚሰማ የስሙ መዓዛ የሚጥም ፍሬ ከማኅፀንሽ ይወጣል" ብሎ ለእናቱ ትንቢት ተናግሮላት ነበር። በግንቦት ፯ ቀን ተወልዶ ካደገ በኋላ የአባቱን በጎች እየጠበቀ ምሳውን ለእረኞች ሰጥቶ እስከ ማታ ይጾም ነበር፤ በሌሊትም በውኃ ዐዘቅት ውስጥ ቁሞ እስኪነጋ ይጸልይ ነበር። ​📌አባቱ ወደ እናቱ ወንድም ወደ አባ አብጎል ዘንድ ለበረከት በወሰደው ጊዜ፣ አባ አብጎል "ለብዙ ሕዝብ ታላቅ አባት ትሆናለህ" ብሎ ትንቢት ተናገረለት። በኋላም አባ አብጎል ከሰማይ ድምፅ ሰምቶ፣ የእግዚአብሔር መልአክ ያመጣለትን የኤልያስን አስኬማና የመጥምቁ ዮሐንስን ቅናት ለቅዱስ ሲኖዳ አለበሰው። ቅዱስ ሲኖዳም ለመነኰሳት፣ ለመኳንንትና ለሰዎች ሁሉ የሚሆን ሥርዓትን ሠራ። ​📌በኤፌሶን የ፪፻ (200) ሊቃውንት ጉባኤ ስለ ንስጥሮስ ክህደት በተደረገ ጊዜ ከሊቀ ጳጳሳቱ ከቅዱስ ቄርሎስ ጋር አብሮ ሄደ። ሲመለሱም መርከበኞች አብሮ እንዳይሳፈር ቢከለክሉት፣ በጸሎቱ ደመና መጥታ ተሸክማ መርከቡ ካለበት በላይ አድርሳዋለች። ወደ ገዳሙም ደርሶ በተጋድሎ ሲኖር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብዙ ጊዜ እየመጣ ያነጋግረው ነበር፤ እርሱም የጌታን እግር አጥቦ እጣቢውን ይጠጣ ነበር። ​📌ዕድሜው ፻፳ (120) ዓመት ከሁለት ወር በሆነው ጊዜ ጌታችን መጥቶ ሊያሳርፈው ሲያረጋጋው፣ እርሱ ግን "የልዩ ሦስትነትህን ክብር የሚነቅፉትን ለመከራከር ወደ ጉባኤ ልሂድን?" ብሎ ጠየቀው። ጌታችንም "ድካምህ ይብቃህ" ብሎ በክብር ዐረገ። ቅዱስ ሲኖዳም ለልጆቹ አባ ዊዳን ጠባቂ አድርጎ ከሾመላቸው በኋላ ነፍሱን በክብር ለእግዚአብሔር ሰጠ። ​"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ጻድቅ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን።" ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር ​"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን" (የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል) ✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔)   ​❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖   ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ​📌የባሕታውያንን አለቃ የታላቁን የቅዱስ አባ ሲኖዳን ገድልና የበረከት ታሪክ ለወዳጅ ዘመድዎ Share በማድረግ የመንፈሳዊ አገልግሎቱ ተካፋይ ይሁኑ

😇መምህር ገብተዋል 📖📖 📚🏆ምስጢረ ቁርባን 🏆📚 📔 ትምህርት ተጀምሯል ላይቭ ግቡ 🙏 ከታቺ ባለው ሊንክ ግቡ ቭኦይስ ቻት ግቡ 👇👇 https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=132ae57e1a061a7502 https://t.me/Bete_kidus_Michael_12

የዘማሪ አቤል መክብብን ድንቅ የዝማሬዎችን ስራዎችን ማግኘት ይፈልጋልሉ ⁉️ለማግኘት ይቀላቀሉ።🙏🙏
የዘማሪ አቤል መክብብን ድንቅ የዝማሬዎችን ስራዎችን ማግኘት ይፈልጋልሉ ⁉️ለማግኘት ይቀላቀሉ።🙏🙏

🕊️ 🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷 🕊️ 🕯 🕊️ ዘላለም ሥላሴ 🕊️ 🕯 🕊️ 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 🕊️ እንኳን ለአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ 🕊️ 🕯 🕊️
🕊️ 🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷  🕊️ 🕯    🕊️   ዘላለም  ሥላሴ    🕊️   🕯 🕊️    🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿                                           🕊️   እንኳን ለአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ  🕊️                        🕯                       🕊️      ❝   እ  ም  ነ  ታ  ች  ን  ❞  🕯  ከሃይማኖተ አበው የተወሰደ  🕯 * የሥላሴ አንድነትና ሦስትነት፦    "እምነታችን በባሕርይ በመለኮት አንድ፤ በአካልና በገጽ ሦስት ብለን ማመን ነው። እነዚህም አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ናቸው።" * የሐዋርያት ትምህርት፦    "ይህ ከሐዋርያት ሲያያዝ የመጣልን፣ ቅዱሳን ሊቃውንት የገለጡልንና በእውነት የምናምንበት እውነተኛ ሃይማኖታችን ነው።" * የድኅነት መንገድ፦    "በንጹሕ ልቡና፣ በአፋችንና በልባችን ያለ ጥርጥር በዚህ ሃይማኖት እንመን፤ በዚህ እንድንድን መንግሥተ ሰማያትንም እንድንወርስ እንረዳለን።" 🕊️                        🕯                     🕊️      ❝   የ  ሥ  ላ  ሴ    ፍ  ቃ  ር  ❞  🕯  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ  🕯 * የማይበጠሰው ገመድ፦    "በሥላሴ ገመድ ፍጹም ታስረናል፤ ከልባችን በማይነቀል በቅንዋተ ፍቅሩ (በፍቅሩ ምስማር) ተቸንክረናል፤ እርሱ ወዶናልና አይጠላንም። እኛም በእምነት ይዘነዋል አንተወውም።"        🕊️    እንኳን  አደረሰን    🕊️                                              ☦️ ኦርቶዶክስ ☦️ 🕊️                         🕯                       🕊️    ​❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖   ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖

ታላቅ በሆነው ታላቅ በሆነው እምነትሽ ታመንኩኝ     ካለሽበት ገስግሼ መጣሁኝ     እናቴ ክብርሽን አንግሼ     ቆምኩኝ እንደ ህፃን ታድሼ     እናቴ ቅድስት አርሴማ     ዝናሽ ለዓለም ተሰማ /2/
አዝ
ስመጣ ባልጋ ነበረ     ተስፋዬም የተሰበረ     በእምነትሽ በፀበልሽ     ሰው ሆኜ ቆምኩኝ ደጅሽ    ልናገር ዝናሽን ላውራ     ይደነቅ የአምላክሽ ስራ     ተጋድሎሽ የእምነትሽ ፅናት     ሆኖኛል የእምነቴ መብራት    
አዝ
ደምግባት ከንቱ ብለሽ     ለሰማይ ክብር የታጨሽ     የእምነቴ ሐሰረ ፍኖት     በምልጃሽ አለሁኝ በህይወት  የልቡን ለነገረሽ     ፈጥኖ ይደርሳል መልስሽ     ዘንባባሽ ህይወት ይዘራል     የጠራሽ ማን አፍሮ ያውቃል    
አዝ
እርዳታሽ የደረሰለት     ያመጣል የልቡን ስለት     ላመኑሽ ፈውስሽ ቅርብ ነው     ባንቺ አፍሮ የሄደ ማነው የልቡን ለነገረሽ     ፈጥኖ ይደርሳል መልስሽ     ዘንባባሽ ህይወት ይዘራል     የጠራሽ ማን አፍሮ ያውቃል      
አዝ
ስመጣ ባልጋ ነበረ     ተስፋዬም የተሰበረ     በእምነትሽ በፀበልሽ     ሰው ሆኜ ቆምኩኝ ደጅሽ     ልናገር ዝናሽን ላውራ     ይደነቅ የአምላክሽ ስራ     ተጋድሎሽ የእምነትሽ ፅናት     ሆኖኛል የእምነቴ መብራት                 መዝሙር 🎙ዘማሪት ሲስተር ልድያ ታደሰ ❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖ ❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖  ❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖

​📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፮/6 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌 በዚች ቀን ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ የሆነውና ሐዋርያትን በትጋት ያገለገለው ቅዱስ መርቄሎ
📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፮/6 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌 በዚች ቀን ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ የሆነውና ሐዋርያትን በትጋት ያገለገለው ቅዱስ መርቄሎስ (ጳውሎስ የተባለ) በሰማዕትነት አረፈ። ​📌ይህ ቅዱስ ረድእ ወንጌልን ለመስበክ ከሐዋርያት ጋር የሄደ፣ የቅዱስ ጴጥሮስን መልእክቶች ያደረሰና በመከራው ጊዜ ሁሉ አብሮት የነበረ ታማኝ አገልጋይ ነው። ወደ ሮሜ አገርም አብሮት በመግባት ብዙ አረማውያንን ወደ ቀናች ሃይማኖት መልሷል። ታላቁ ሐዋርያ ቅዱስ ጴጥሮስ በሰማዕትነት በሞተ ጊዜም፣ መርቄሎስ መጥቶ ከመስቀል ላይ አውርዶት በከበሩ ልብሶችና በሽቱ ገንዞ በሣጥን አድርጎ በምእመናን ቤት በክብር አኑሮታል። ​📌የቅዱስ ጴጥሮስ ደቀ መዝሙር መሆኑ በክፉው ንጉሥ በኔሮን ዘንድ በተከሰሰ ጊዜ፣ ንጉሡ ፊት ቀርቦ ስለ መምህሩና ስለ ጌታችን አምላክነት በግልጽ መሰከረ። ንጉሡም በጽኑ አስገረፈው፤ ዘቅዝቆም ሰቅሎ ከበታቹ ጢስ አጤሰበት። በኋላም ንጉሡ "በምን ዓይነት ሞት መሞት ትሻለህ?" ብሎ በጠየቀው ጊዜ፣ ቅዱሱ "እኔ በክርስቶስ ስም መሞትን እሻለሁ፤ አንተ በፈለግኸው ዓይነት ግደለኝ" በማለት በጽናት መለሰለት። ​📌ያን ጊዜም ንጉሡ ኔሮን እንደ መምህሩ እንደ ቅዱስ ጴጥሮስ ዘቅዝቀው እንዲሰቅሉት አዘዘ፤ እርሱም በታላቅ ትዕግሥት ተቀብሎ የሰማዕታትንና የሐዋርያትን የክብር አክሊል ተቀዳጀ። ​"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሐዋርያት በጸሎታቸው ይማረን ለዘላለሙ አሜን።" ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር ​"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን" (የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል) ✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔) ​  ​ ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖    ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ​📌እስከ ፍጻሜው ለመምህሩ የታመነውን የታላቁን የሐዋርያውና የሰማዕቱ የቅዱስ መርቄሎስን የበረከት ታሪክ ለወዳጅ ዘመድዎ Share በማድረግ የመንፈሳዊ አገልግሎቱ ተካፋይ ይሁኑ

ታላቅ በሆነው ታላቅ በሆነው እምነትሽ ታመንኩኝ     ካለሽበት ገስግሼ መጣሁኝ     እናቴ ክብርሽን አንግሼ     ቆምኩኝ እንደ ህፃን ታድሼ     እናቴ ቅድስት አርሴማ     ዝናሽ ለዓለም ተሰማ /2/
አዝ
ስመጣ ባልጋ ነበረ     ተስፋዬም የተሰበረ     በእምነትሽ በፀበልሽ     ሰው ሆኜ ቆምኩኝ ደጅሽ    ልናገር ዝናሽን ላውራ     ይደነቅ የአምላክሽ ስራ     ተጋድሎሽ የእምነትሽ ፅናት     ሆኖኛል የእምነቴ መብራት    
አዝ
ደምግባት ከንቱ ብለሽ     ለሰማይ ክብር የታጨሽ     የእምነቴ ሐሰረ ፍኖት     በምልጃሽ አለሁኝ በህይወት  የልቡን ለነገረሽ     ፈጥኖ ይደርሳል መልስሽ     ዘንባባሽ ህይወት ይዘራል     የጠራሽ ማን አፍሮ ያውቃል    
አዝ
እርዳታሽ የደረሰለት     ያመጣል የልቡን ስለት     ላመኑሽ ፈውስሽ ቅርብ ነው     ባንቺ አፍሮ የሄደ ማነው የልቡን ለነገረሽ     ፈጥኖ ይደርሳል መልስሽ     ዘንባባሽ ህይወት ይዘራል     የጠራሽ ማን አፍሮ ያውቃል      
አዝ
ስመጣ ባልጋ ነበረ     ተስፋዬም የተሰበረ     በእምነትሽ በፀበልሽ     ሰው ሆኜ ቆምኩኝ ደጅሽ     ልናገር ዝናሽን ላውራ     ይደነቅ የአምላክሽ ስራ     ተጋድሎሽ የእምነትሽ ፅናት     ሆኖኛል የእምነቴ መብራት                 መዝሙር 🎙ዘማሪት ሲስተር ልድያ ታደሰ

🇪🇹 የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ የትኞቹን መዝሙራት ማግኝት ይፈልጋሉ❓

Repost from N/a
የኦርቶዶክስ መዝሙር ይፈልጋሉ?

እኛም የክርስቶስ ተከታዮች የተባልን ምዕመናን፣ ከእነዚህ ብርሃናት ተቀብለን በቃላችንና በምግባራችን ለዓለም ብርሃን ልንሆን ይገባል። ጨለማውን ዓለም መለወጥ የሚቻለው በክፉ ፈንታ ክፉ በማድረግ ሳይሆ
እኛም የክርስቶስ ተከታዮች የተባልን ምዕመናን፣ ከእነዚህ ብርሃናት ተቀብለን በቃላችንና በምግባራችን ለዓለም ብርሃን ልንሆን ይገባል። ጨለማውን ዓለም መለወጥ የሚቻለው በክፉ ፈንታ ክፉ በማድረግ ሳይሆን፣ የእውነትንና የፍቅርን ብርሃን በማብራት ብቻ ነው። ​የቅዱሳን ሐዋርያት የጴጥሮስና የጳውሎስ በረከትና ረድኤት፣ በእነርሱ ላይ ያደረው የክርስቶስ ፍቅርና የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን ​✍️​ ​“ለግሪክ ሰዎችና ላልተማሩም፥ ለጥበበኞችና ለማያስተውሉም ዕዳ አለብኝ፤” በወንጌል አላፍርምና፤ አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ የእግዚአብሔር ጽድቅ ከእምነት ወደ እምነት በእርሱ ይገለጣልና። ሮሜ 1÷14 እግዚአብሔር ሆይ የሚሳንህ ነገር የለምና የራቀውን አቅርበህ የረቀቀውን አጉልተህ እየሰማነው ካለነው መርዶና ሰቀቀን ዕረፍተ ሥጋንና ዕረፍተ ነፍስን አትንሣን አሜን 🙏 ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖    ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖

🌿እንኳን ለብርሃናተ ዓለም ለቅዱስ ጴጥሮስ፣ቅዱስ ጳውሎስ ለዕረፍታቸው መታሰቢያ ዓመታዊ በዓል አደረሳችሁ🌿 ብርሃናተ ዓለም ​ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቅዱስወንጌል «እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ» (ማቴ. ፭፥፲፬) ብሎ እንደተናገረ፥ ቅዱስ ጴጥሮስና ቅዱስ ጳውሎስ በሕይወታቸውና በትምህርታቸው፣ በደማቸውና በጭንቃቸው ዓለምን ከክህደትና ከውድቀት ጨለማ ወደ እውነተኛው የእግዚአብሔር መንግሥት ብርሃን የመለሱ የዓለም መብራቶች ናቸው ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ እነዚህ ቅዱሳን ሲመሰክር፦ «ጴጥሮስና ጳውሎስ የዓለም ዓይኖች፣ የቤተክርስቲያን ምሶሶዎች፣ የወንጌል ፈረሶችና የጽድቅ አርበኞች ናቸው» ይላቸዋል ዛሬ በዓለ ዕረፍታቸውን ስናስብ፣ እግዚአብሔር በእነርሱ ላይ የገለጠውን ድንቅ ጥበብና ፍቅር እንመለከታለን ​፩. የክርስቶስ ፍቅር፡ ቅዱስ ጴጥሮስን ከክህደት ወደ ንስሐ፣ ቅዱስ ጳውሎስን ከአሳዳጅነት ወደ ተሳዳጅነት መልሷቸዋል ​ሀ/ ቅዱስ ጴጥሮስ፦ ከክህደት በንስሐ ወደ መታመን ​ቅዱስ ጴጥሮስ በፍርሃት ምክንያት ጌታውን ሦስት ጊዜ ቢክደውም (ማቴ. ፳፮፥፷፱-፸፭)፣ የክርስቶስ ፍቅር ግን ፈጽሞ አልጣለውም። ጌታችን ዘወር ብሎ በተመለከተው ጊዜ፣ ያቺ የእይታ ፍቅር የጴጥሮስን ልብ ሰብራ ታላቅ ልቅሶንና ንስሐን ወለደች ​የማር አፍቅሮት የተባለው ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በትርጓሜ ወንጌሉ ላይ እንዲህ ይላል፦ «ጌታ ጴጥሮስን የተመለከተው በዓይኑ ብቻ ሳይሆን በቸርነቱ ብርሃን ጭምር ነው። ያ እይታ ጴጥሮስን ከውድቀቱ አንሥቶ የሐዋርያት አለቃ አደረገው።» ከትንሣኤ በኋላም ጌታችን «ትወደኛለህን?» እያለ ሦስት ጊዜ በመጠየቅ፣ በሦስቱ ክህደት ፋንታ ሦስት ጊዜ የፍቅር ቃል ኪዳን አጽንቶለታል (ዮሐ. ፳፩፥፲፭) ​የሰው ውድቀት የቱንም ያህል የከፋ ቢሆን፣ የእግዚአብሔር ምሕረትና የንስሐ በር ሁልጊዜ ክፍት ነው። ንስሐ የወደቀውን አንሥታ ከቀድሞው ክብር በላይ ታደርሳለች ፍርሃት ሲያሸንፈን፣ ወደ ክርስቶስ ቸርነት ዓይኖች መመልከት ይገባናል ​ለ/ ቅዱስ ጳውሎስ፦ ከአሳዳጅነት ወደ ተሳዳጅነት ​ሳውል (ጳውሎስ) ቤተክርስቲያንን የሚያሳድድ፣ ምዕመናንን የሚያስርና የሚገድል ኃያል ነበረ (ሐዋ. ፱፥፩-፪) ነገር ግን በደማስቆ መንገድ ላይ የወረደለት ሰማያዊ ብርሃንና «ሳውል ሳውል ስለ ምን ታሳድደኛለህ?» የሚለው ድምፅ ከአሳዳጅነት ወደ ክርስቶስ ምስክርነት አሻገረው። ​የቤተክርስቲያን መተርጉማን እንደሚያስተምሩት፣ ክርስቶስ «ስለ ምን ታሳድደኛለህ?» ያለው ራሱ ሰማይ ስላለ ሳይሆን፣ በምድር ያሉትን ምዕመናን ማሳደድ ራሱን ክርስቶስን ማሳደድ መሆኑን ለማወቅ ነው ጳውሎስ ከዚያን ዕለት ጀምሮ ስለ ክርስቶስ ስም መከራን የሚቀበል፣ የሚሰደድና የሚገረፍ ታላቅ የዓለም ሐዋርያ ሆነ እርሱ ራሱ «ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ ነው ወይስ ጭንቀት ወይስ ስደት?» (ሮሜ ፰፥፴፭) በማለት ያንን ፍቅር ገልጦታል ​ የእግዚአብሔር ፍቅር ጠላትን ወዳጅ፣ አሳዳጅን ወንጌላዊ የማድረግ መለኮታዊ ኃይል አለው። እግዚአብሔር ሰውን የሚመዝነው በያዘው ክፉ ታሪክ ሳይሆን ሊሆን በሚችለው ቅዱስ ማንነት ነው ​፪. በሐዋርያት ሥራ የተደረገላቸውና እነርሱም ያደረጓቸው ድንቅ ተአምራት ​የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ በሁለቱ ታላላቅ ብርሃናት ላይ የተደረጉትንና በእነርሱ እጅ የተፈጸሙትን ተአምራት በስፋት ይተርካል የቤተክርስቲያን ሊቃውንት «የሐዋርያት ሥራ የወንጌል ፍሬና የመንፈስ ቅዱስ ኃይል መገለጫ ነው» ይሉታል ​ሀ/ ለእነርሱ የተደረገላቸው ድንቅ ተአምር ​ለቅዱስ ጴጥሮስ፦ ሄሮድስ አግሪጳ በወህኒ ቤት አሳስሮት፣ በአራት ፈራቃ ወታደሮች እየተጠበቀ ሳለ፣ የእግዚአብሔር መልአክ በድንገት ወርዶ በብርሃን አበራው፤ ሰንሰለቱም ከእጁ ወደቀ፣ የብረቱም መዝጊያ በራሱ ተከፍቶለት ከሞት አምልጧል (ሐዋ. ፲፪፥፭-፲፩) ​ለቅዱስ ጳውሎስ፦ ከሲላስ ጋር በፊልጵስዩስ ወህኒ ቤት ተጥለው፣ እግራቸው በግንድ ታስሮ ሳለ፣ በመንፈቀ ሌሊት እግዚአብሔርን በቅኔና በምስጋና ሲያከብሩ ታላቅ የምድር መንቀጥቀጥ ሆኖ የወህኒው መሠረት ተናወጠ፤ ደጆቹም ተከፍተው ሰንሰለታቸው ተፈታ (ሐዋ. ፲፮፥፳፭-፳፮) ​ለ/ እነርሱ ያደረጉት ድንቅ ተአምር ​በቅዱስ ጴጥሮስ እጅ፦ በቤተ መቅደስ ደጅ (በመልካሟ በር) ይለምን የነበረውን ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ አንካሳ የሆነውን ሰው «ብርና ወርቅ የለኝም፤ ይህን ያለኝን ግን እሰጥሃለሁ፤ በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሣና ተመላለስ» ብሎ አስነስቶታል (ሐዋ. ፫፥፩-፲)። እንዲያውም የጴጥሮስ ጥላ እንኳ በሕመምተኞች ላይ ሲያርፍ ይፈወሱ ነበር (ሐዋ. ፭፥፲፭) ​በቅዱስ ጳውሎስ እጅ፦ በኤፌሶን ሳለ እግዚአብሔር በእጁ ታላቅ ተአምር ያደርግ ነበር። ከሰውነቱ ጨርቅ ወይም መጥረጊያ ወስደው በሕመምተኞች ላይ ቢያኖሩ ደዌያቸው ይለቃቸው፣ አጋንንትም ይወጡ ነበር (ሐዋ. ፲፱፥፲፩-፲፪) እንዲሁም ከአጥር ላይ ወድቆ የሞተውን አውጤክስን በጸሎት አስነስቶታል (ሐዋ. ፪፲፥፱-፲፪)። ቅዱሳኑ የእግዚአብሔር የጸጋ ዕቃዎች ናቸው ጥላና ጨርቃቸው እንኳ ሳይቀር ኃይልን ማድረጉ፣ እግዚአብሔር በቅዱሳኑ አጥንትና ንዋያት ላይ የሚያድረውን ጸጋ ያሳያል እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑ ነፍሳት ደግሞ በየትኛውም የወህኒና የጭንቅ ጨለማ ውስጥ ቢሆኑ ሰማያዊ ነፃነት አላቸው ​፫. ፍጻሜያቸው (የሰማዕትነት ክብር) ​የእነዚህ ቅዱሳን ፍጻሜ በምድር ላይ በደም የተፈጸመ፣ በሰማይ ግን በክብር አክሊል የተሸለመ ነበረ ሁለቱም በሮም ንጉሥ በኔሮን ዘመን በሰማዕትነት ዐረፉ ​ቅዱስ ጴጥሮስ፦ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን (እንደ አውሳቢዮስ ዘቂሣርያ ያሉ የታሪክ ጸሐፊዎች) እንደዘገቡት፣ ቅዱስ ጴጥሮስ ሊሰቅሉት በወሰዱት ጊዜ «ከጌታዬ ጋር እኩል ልሰቀል አይገባኝም፣ እርሱ ሰማይንና ምድርን የፈጠረ ጌታ ነውና እኔን ቁልቁል ስቀሉኝ» በማለት በትሕትና ራሱን ዝቅ አድርጎ ዘቅዝቀው ሰቅለውታል ​ቅዱስ ጳውሎስ፦ የሮም ዜግነት ስላለው እንዳይሰቀል ተከልክሎ፣ በሰይፍ ራሱን ተቆርጧል አንገቱ በተቆረጠ ጊዜ ከደሙ ጋር ወተት እንደፈሰሰና የተቆረጠው ራሱ ሦስት ጊዜ እየተንጠረጠረ «ክርስቶስ» የሚል ድምፅ እንደሰጠ ሊቃውንቱ በትርጓሜያቸው ይናገራሉ ቅዱስ ጳውሎስ አስቀድሞ «መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ፥ ሩጫውን ጨርሻለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤ ወደፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል» (፪ ጢሞ. ፬፥፯-፰) እንዳለ፣ የቃሉ ፍጻሜ ተፈጸመ የቅዱሳን ሕይወት ፍጻሜ ሞት ሳይሆን ወደ ዘለዓለም ክብር መሸጋገሪያ ድልድይ ነው። ቅዱስ ጴጥሮስ እስከ ሞት ድረስ ያሳየው ትሕትና፣ ቅዱስ ጳውሎስም ለአምላኩ ያፈሰሰው ደም እውነተኛ ክርስትና መስዋዕትነትን የምትጠይቅ መሆኗን ያስተምረናል ​፬. ብርሃናተ ዓለም (ዓለምን በስብከታቸውና በሕይወታቸው ማብራታቸው) ​ጌታችን «እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ» ሲል፣ ሐዋርያት በጨለማ ለነበረው ዓለም የእውነትን መብራት ይዘው እንደሚወጡ የተናገረው ትንቢት ነው ​ቅዱስ ጴጥሮስ፦ ለአይሁድ ወገን ሐዋርያ በመሆን፣ በበዓለ ኃምሳ በአንድ ስብከት ሦስት ሺሕ፣ በሌላም ጊዜ አምስት ሺሕ ሕዝብ ወደ ማመን በመመለስ (ሐዋ. ፪፥፵፩፣ ፬፥፬) የኦሪትን ጥላነት ገፎ የወንጌልን ብርሃን አብርቷል ​ቅዱስ ጳውሎስ፦ ከአሕዛብ ወገን እስከ ምዕራብ ዳርቻ («እስከ ምዕራብ ዳርቻ እስከ እስፔን ድረስ ») በመጓዝ፣ አራት ታላላቅ የስብከት ጉዞዎችን በማድረግ፣ ፲፬ቱን መልእክታት በመጻፍ፣ ጣዖት ያመልኩ የነበሩ አሕዛብን የእግዚአብሔር የጸጋ ልጆች አድርጓቸዋል

አመ አመ ሰበክሙ አመ አመ ሰበክሙ(፪) ቅዱሳን ሐዋርያት ቅዱሳን ሐዋርያት - - - ሐዋርያት የዓለም ብርሃን ናችሁ - - - ሐዋርያት መጀመሪያ ጴጥሮስ - - - ሐዋርያት አለና ጳውሎስ - - - ሐዋርያት    
አዝ
ብርሃናተ ዓለም - - - ሐዋርያት ጴጥሮስ ወጳውሎስ- - - ሐዋርያት በእውነት ተሰየፉ - - - ሐዋርያት ስለ ክርስቶስ - - - ሐዋርያት  
አዝ
ሐዋርያት ፈርተው - - - ሐዋርያት ሲለቅሙ በሻማ - - - ሐዋርያት ሰዎች አትለዩ - - -ሐዋርያት ከወንጌል አውድማ - - - ሐዋርያት     
አዝ
የዘላለም ሕይወት - - - ሐዋርያት ማደስ ካማራችሁ - - - ሐዋርያት የሐዋርያት ሥራ - - - ሐዋርያት ይሁን አላማችሁ - - - ሐዋርያት      
አዝ
ውኆች ቀለም ሆነው - - - ሐዋርያት እንጨቶች ብዕር - - - ሐዋርያት ቢፅፉት አያልቅም - - - ሐዋርያት የሐዋርያት ክብር - - - ሐዋርያት    
አዝ
ሐምሌ አምስት ቀን - - - ሐዋርያት ማኅበራችን - - - ሐዋርያት በክርስቶስ መስቀል - - - ሐዋርያት ተባረከልን - - - ሐዋርያት                  መዝሙር በጴጥሮስ ወ ጳውሎስ ቤ/ክ ሰ/ት/ቤት ዘማርያን 📖"ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን"              ሮሜ ፰ ፥ ፴፮   ​ ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖    ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖

😇መምህር ገብተዋል 📖📖 📚😇ነገረ ክርስቶስ😇📖📚 📔 ትምህርት ተጀምሯል ላይቭ ግቡ 🙏 ከታቺ ባለው ሊንክ ግቡ ቭኦይስ ቻት ግቡ 👇👇 https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=132ae57e1a061a7502 https://t.me/Bete_kidus_Michael_12

✝️ የዕለቱ ቅዱስ ወንጌል ቃል ✝️ ​« ማንም ሊከተለኝ የሚወድ ቢኖር፥ ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ። ነፍሱን ሊያድን የሚወድ ሁሉ ያጠፋታልና፤ ስለ እኔና ስለ ወንጌል ነፍሱን የሚያጠፋት
✝️ የዕለቱ ቅዱስ ወንጌል ቃል ✝️ ​« ማንም ሊከተለኝ የሚወድ ቢኖር፥ ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ። ነፍሱን ሊያድን የሚወድ ሁሉ ያጠፋታልና፤ ስለ እኔና ስለ ወንጌል ነፍሱን የሚያጠፋት ሁሉ ግን ያድናታል። ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል ሰውስ ስለ ነፍሱ ቤዛ ምን ይሰጣል »
​✥ የማርቆስ ወንጌል ምዕራፍ 8 ÷ 34-37 ✥
💡ከቃሉ ምን እንማራለን (ለዕለት ተዕለት ሕይወታችን)ለወጣቶችና ለልጆች፦ በዚህ ዓለም ላይ የምናሳድደው ዝና፣ ሀብት ወይም ጊዜያዊ ደስታ ሁሉ ከነፍሳችን መዳን ጋር ሊወዳደር አይችልም። እውነተኛ ስኬት ክርስቶስን አርአያ አድርጎ በቅንነትና በሥነ-ምግባር መኖር ነው።ለእናቶችና ለአባቶች፦ ልጆቻችን የዚህን ዓለም ትምህርትና እውቀት ብቻ ሳይሆን፣ የነፍሳቸውን ዋጋ እንዲያውቁና ሃይማኖታቸውን ጠብቀው እንዲያድጉ በትዕግሥትና በጸሎት መምራት ይገባናል። ​« ዓለምን ከማተርፍ ይልቅ ነፍሴን ማዳን ይሻለኛል »   ​ ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖    ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖

​📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፬/4 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌በዚች ቀን የከበሩ ታላላቅ ሰማዕታት የቅዱስ አቡቂርና ዮሐንስ የሥጋቸው ፍልሰት (ከቦታ ወደ ቦ
📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፬/4 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌በዚች ቀን የከበሩ ታላላቅ ሰማዕታት የቅዱስ አቡቂርና ዮሐንስ የሥጋቸው ፍልሰት (ከቦታ ወደ ቦታ መፍለስ) ሆነ። ​📌እሊህ ቅዱሳን የካቲት ፮ ቀን በሰማዕትነት በሞቱ ጊዜ፣ ምእመናን ሥጋቸውን ወስደው በእስክንድርያ ከተማ በቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሥውር አኑረውት ነበር። እስከ ሊቀ ጳጳሳቱ እስከ ቅዱስ ቄርሎስ ዘመንም ድረስ በዚያው ቆየ። ​📌ከዚህ በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ለሊቀ ጳጳሳቱ ለቅዱስ ቄርሎስ ተገልጦለት፣ የቅዱሳኑን የአቡቂርንና የዮሐንስን ሥጋ አውጥቶ እንዲያፈልስ አዘዘው። ቅዱስ ቄርሎስም ከብዙ ሕዝብ ጋር ሄዶ በጸሎት ምድሩን ሲቆፍሩ ሥጋቸው ያለበት ቦታ ተገለጠላቸው። የቅዱሳኑንም ሥጋ በታላቅ ክብር ተሸክመው በባሕር ዳርቻ ወደምትገኝ ሌላኛዋ የቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን አድርሰው አኖሩት። ​📌በዚያም ቦታ ላይ ቤተ ክርስቲያን የሠሩላቸው ሲሆን፣ በዚህች ቀን ታላቅ በዓል አደረጉ። ከቅዱሳኑ ሥጋ ብዙ ድንቅ ተአምራትና የበሽተኞች ፈውስ በመገለጡ፣ አረማውያኑ ሳይቀሩ ጣዖቶቻቸውን ትተው በጌታ አመኑ፤ ክርስቲያኖችም ሆኑ። የነበረችውም የጣዖት ቤት በአሸዋ ተከምራ ታላቅ ኮረብታ ሆነች። ​"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።"ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር ​"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን" (የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል) ✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔)   ​ ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖    ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ​ ​📌የታላላቆቹ ቅዱሳን ሰማዕታት የአቡቂርና የዮሐንስን የሥጋ ፍልሰት በዓል ታሪክ ለወዳጅ ዘመድዎ Share በማድረግ የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ

​✝️ የዕለቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ✝️ ​« የአባትን ተግሣጽ ስሙ፥ ማስተዋልንም ታውቁ ዘንድ አድምጡ፤ መልካም ትምህርትን እሰጣችኋለሁና ሕጌን አትተዉ። ​እኔም አባቴን የምሰማ ልጅ ነበርሁና፥ በእናቴ
✝️ የዕለቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ✝️ ​« የአባትን ተግሣጽ ስሙ፥ ማስተዋልንም ታውቁ ዘንድ አድምጡ፤ መልካም ትምህርትን እሰጣችኋለሁና ሕጌን አትተዉ።እኔም አባቴን የምሰማ ልጅ ነበርሁና፥ በእናቴም ዘንድ እወደድ ነበር። ያስተምረኝም ነበር እንዲህም ይለኝ ነበር፦ ልብህ ቃሌን ይቀበል፥ ትእዛዜን ጠብቅ በሕይወትም ትኖራለህ።ጥበብን አግኝ፥ ማስተዋልን አግኝ፤ አትርሳም፥ ከአፌም ቃል ፈቀቅ አትበል »
​✥ መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ 4 ÷ 1-5 ✥
💡ከቃሉ ምን እንማራለን (ለዕለት ተዕለት ሕይወታችን)ለወጣቶችና ለልጆች፦ የእግዚአብሔርን ቃልና የወላጆቻችንን ምክር (ተግሣጽ) መስማት የቅድስና፣ የጥበብና የረጅም ዕድሜ መሠረት ነው። የወላጅ ምክር ከክፉ መንገድ ይጠብቀናል።ለእናቶችና ለአባቶች፦ ልጆቻችንን በእግዚአብሔር ቃልና በጥሩ ስነ-ምግባር ኮትኩቶ ማሳደግ፣ ነገ በሕይወታቸው ስኬታማና ለሀገር የሚጠቅሙ ትውልድ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል። ​« ጥበብንና ማስተዋልን ፍለጋ ከቅዱሳት መጻሕፍት አንራቅ »   ​ ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖    ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖

​📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፫/3 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌በዚች ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሃያ አራተኛ የሆነው፣ የዓለም ብርሃንና የቤተ ክርስቲያን ዓ
📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፫/3 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌በዚች ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሃያ አራተኛ የሆነው፣ የዓለም ብርሃንና የቤተ ክርስቲያን ዓምድ ታላቁ ቅዱስ አባት ቄርሎስ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት (ዓምደ ሃይማኖት) አረፈ። ​📌ይህ ቅዱስ አባት የእናቱ ወንድም በሆነው በሊቀ ጳጳሳቱ በአባ ቴዎፍሎስ ዘንድ ያደገ ሲሆን፣ ወደ አስቄጥስ (ቅዱስ መቃርስ) ገዳም ተልኮ አምላካውያን መጻሕፍትን ተምሯል። እግዚአብሔርም መጽሐፍን አንድ ጊዜ አንብቦ እስከሚያጸናው ድረስ ታላቅ ዕውቀትንና ማስተዋልን ሰጠው። በኋላም ለአባ ሰራብዮን ተሰጥቶ ትምህርቱን በፈጸመ ጊዜ ወደ አባ ቴዎፍሎስ ተመለሰ፤ እርሱም በሊቀ ጵጵስና ሥራ ውስጥ በመሾም ሁልጊዜ ሕዝቡን እንዲያስተምር አደረገው። ከትምህርቱ ጣዕም የተነሣም ሕዝቡ ዝም እንዲል አይፈልግም ነበር። ​📌አባ ቴዎፍሎስ ካረፈ በኋላ በእስክንድርያ መንበር ላይ ተሾመ፤ በዘመኑም በትምህርቱና በድርሳናቱ ቤተ ክርስቲያንን አበራት። የቁስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳት የነበረው ንስጥሮስ በካደ ጊዜ፣ በንጉሥ ቴዎዶስዮስ ዘመን በኤፌሶን ከተማ የ፪፻ (200) ኤጲስቆጶሳት ጉባኤ እንዲሰበሰብ አደረገ። ቅዱስ ቄርሎስም የዚህ ጉባኤ መሪ (ሊቀ ጉባኤ) በመሆን ንስጥሮስን ተከራክሮ ረታው፤ ከክህደቱም ለመመለስ ፈቃደኛ ባለመሆኑ አውግዞ ከመንበሩ አሳደደው። ​📌ይህ አባት የቀናች ሃይማኖትን የገለጠባቸውን ፲፪ (12) አንቀጾችን (የቄርሎስ መዓዛ/ሃይማኖት) የደረሰ ሲሆን፣ ከእነርሱም በኋላ ብዙ ድርሳናትን፣ ተግሣጻትንና መልእክቶችን ጥሏል። እግዚአብሔር ቃል ከሥጋ ጋር ከተዋሐደ በኋላ "ተዋሕዶ ዘእንበለ ፍልጠት" (ያለ መለየት) አንድ አካል አንድ ባሕርይ (አሐዱ አካል ወአሐዱ ባሕርይ) መሆኑን በሚገባ አስረድቷል። ክርስቶስን ወደ ሁለት ባሕርይ የሚከፍሉትን መናፍቃን ሁሉ አውግዞ ለይቷል። ​📌በወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ መንበር ላይ ፴፪ (32) ዓመታት በትጋት ካገለገለ በኋላ፣ መልካሙን ገድሉን ፈጽሞ በዚህች ዕለት በሰላም አረፈ። ​"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።"ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር ​"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን" (የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል) ✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔) ​ ​╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯ ​📌የእምነት ጠበቃና የቤተ ክርስቲያን ጌጥ የሆነውን የታላቁን የቅዱስ አባ ቄርሎስን (ዓምደ ሃይማኖት) የበረከት ታሪክ ለወዳጅ ዘመድዎ Share በማድረግ የመንፈሳዊ አገልግሎቱ ተካፋይ ይሁኑ

🫶⛪️የኢኦተቤክ አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ መዝሙራት ማግኝት ይፈልጋሉ⁉️