ar
Feedback
Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

الذهاب إلى القناة على Telegram

#ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ #Orthodox ​📜 #የዕለቱ #ስንክሳር (#የቅዱሳን_ታሪክ) 💡 የአባቶች ምክርና ትምህርት 📖 ​ሕይወትን የሚቀይሩ ጥልቅ የአባቶች ምክር እና ትምህርቶች ይተላለፋሉ። ​ከቅዱሳት መጻሕፍት የተቀሰሙ ለነፍስ ምግብ የሚሆኑ ቁምነገሮች ይገኛሉ። ​ Buy ads: https://telega.io/c/OrthodoxTewahedoTrue

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

تُعد قناة Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶኦርቶዶክስ ተዋሕዶ (@orthodoxtewahedotrue) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 174 729 مشتركاً، محتلاً المرتبة 140 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 126 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 174 729 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 15 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -3 435، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -89، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 4.19‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 2.71‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 7 314 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 4 733 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 84.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
#ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ #Orthodox ​📜 #የዕለቱ #ስንክሳር (#የቅዱሳን_ታሪክ) 💡 የአባቶች ምክርና ትምህርት 📖 ​ሕይወትን የሚቀይሩ ጥልቅ የአባቶች ምክር እና ትምህርቶች ይተላለፋሉ። ​ከቅዱሳት መጻሕፍት የተቀሰሙ ለነፍስ ምግብ የሚሆኑ ቁምነገሮች ይገኛሉ። ​ Buy ads: https://telega.io/c/OrthodoxTewahedoTrue

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 16 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

174 729
المشتركون
-8924 ساعات
-7987 أيام
-3 43530 أيام
أرشيف المشاركات
ከእስልምና ወደ☦️ክርስትና ​ ✍️ ክፍል ፮ ​📌(ኃይል በቁርዓን፣ ሰላም በወንጌል እና የሴቶች መብት) ​ቁርዓን አማኞችን ወደ መግደልና ወደ ጦርነት የሚጠሩ ስፍር ቁጥር የሌላቸው ጥቅሶች አሉት። እ
ከእስልምና ወደ☦️ክርስትና     ​      ✍️ ክፍል ፮ 📌(ኃይል በቁርዓን፣ ሰላም በወንጌል እና የሴቶች መብት) ​ቁርዓን አማኞችን ወደ መግደልና ወደ ጦርነት የሚጠሩ ስፍር ቁጥር የሌላቸው ጥቅሶች አሉት።
እስልምና በዓለም ላይ የተስፋፋው በሰይፍ እንደሆነ ሙስሊሞች ራሳቸው ያምናሉ።
አምላክ እንዴት ሰውን ወደ መግደል ያነሳሳል? እስልምናን የተወ ሰው (ሙርተድ) እንዲገደል ይታዘዛል። አምላክ ግን ነጻ አድርጎ ነው የፈጠረን። ክርስቶስ ግን በኃይል በተጋፈጡት ጊዜ፣ ጴጥሮስ ሰይፉን ሲመዝ፦ «ሰይፍህን ወደ ስፍራው መልስ፤ ሰይፍ የሚመዙ ሁሉ በሰይፍ ይጠፋሉ» አለው (ማቴዎስ 26:52-54)። ክርስቶስ «ቀኝ ጉንጭህን ለሚመታህ ግራህን ደግሞ ስጠው» በማለት ፍቅርን አስተማረ (ማቴዎስ 5:39)።
በፍርድ ቤት ምስክርነት ላይም፣ ቁርዓን የአንድ ወንድ ምስክርነት ከሁለት ሴቶች ምስክርነት ጋር እኩል እንደሆነ ይናገራል (አንደኛዋ ብትረሳ ሌላኛዋ እንድታስታውሳት!)።
የሴት ልጅ አእምሮ ከወንድ ያነሰ መሆኑን የሚያሳይ ምንም የሳይንስ ማረጋገጫ የለም። እኔ ራሴ በ1963 ዓ.ም ከፍተኛ የትምህርት ዲግሪ ይዤ የትምህርት ቤት ርዕሰ መምህርት በነበርኩበት ወቅት፣ የአባቴን የውርስ ጉዳይ ለመፈጸም ፍርድ ቤት ስሄድ፣ የእኔ ምስክርነት ውድቅ ተደርጎ የሌላ ሴት ረዳትነት እንድፈልግ ተደረገ፤ ነገር ግን የ16 ዓመት ዕድሜ የነበረው የወንድሜ ልጅ ምስክርነት ብቻውን ተቀባይነት አገኘ። ይህ ሕግ በበረሃ ለነበሩ የዱሮ ጎሳዎች እንጂ ለዘመናዊው ዓለም የሚሆን አይደለም።
በሃይማኖታዊ መጋረጃ (ኒቃብ/ሒጃብ) ረገድም፣ የወንዶችን ስሜት ለመጠበቅ ሲባል ሴት ልጅ ከራስ ፀጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ እንድትሸፈን መገደዷ ስህተት ነው፤ ክርስቶስ ግን «ሴትን በምኞት ዓይን ያየ ሁሉ በልቡ አመንዝሯል» በማለት ኃጢአቱን ለወንዶችም ጭምር ሰጥቷል (ማቴዎስ 5:28)።
ክፍል ፯ ይቀጥላል✍️ ✍️ባለ ታሪክ ጸሐፊ ፦ናህድ ማሕሙድ መተወሊ ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

✞♡​​የአፎምያ ረዳት ነህ♡✞ የአፎሚያ ረዳት ነህ ሚካኤል(፪) ቅሩበ እግዚአብሔር የልዑል ፈጥነህ ድረስልን ስንጠራህ ሚካኤል ፊት ለፊታችን አምላክ ሰደደህ አቀናህልን መንገዱን ጠርገህ የቤልሆርን ምክር አፈረስክ ከልጆችህ ጋር ከነአን ደረስክ    ከኛ ጋር ነበርክ አርባውን ዘመን    እንጠራሃለን ሚካኤል ብለን
አዝ
በቃዴስ ክንፍህ ተዘርግቶልን ደመናው በአንተ ተጋረደልን አብረኸን ልትሆን ጌታ የላከህ አንተ ሚካኤል ታዳጊያችን ነህ   ከኛ ጋር ነበርክ አርባውን ዘመን   እንጠራሃለን ሚካኤል ብለን
አዝ
ሙሴ ሲለየን ደጉ አባታችን ሚካኤል ነበር ከላይ መሪያችን የባርነቱ ጉዞ እስኪያበቃ እጅግ ረዳን የኛ ጠበቃ   ከኛ ጋር ነበርክ አርባውን ዘመን   እንጠራሃለን ሚካኤል ብለን
አዝ
ሳጥናኤል መክሮ የሐሰት ምክር ሊወስደን ሻተ ሙሴ መቃብር ስለማይጠቅመን አንተ ሰወርከው ምክሩን በታትነህ አስጎነበስከው    ከኛ ጋር ነበርክ አርባውን ዘመን    እንጠራሃለን ሚካኤል ብለን                         🎤ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ🎤 ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

✞♡አይኑ ዘርግብ♡✞ አይኑ ዘርግብ ልብሱ ዘመብረቅ ሊቀ መላእክት ሚካኤል ልዑለ መንበር ሐመልማለ ወርቅ ሰዐሌ ምሕረት ወመተንብል ረዳኤ ምንዱባን ዘአስተዓፀቡ ያቀልል በነ ሰናክሬም ላይ ሰይፍን የመዘዘ የሕዝቅያስ ምሕረት በእጁ የተያዘ መዓቱን ለአህዛብ በሞት የገለጠ የሕዝቅያስን ሞት በሕይወት የለወጠ የእስራኤል ድንኳኖች በደስታ ተሞሉ ክብር ለአምላካችን ይገባል እያሉ መልአኩን የላከ ሕዝቡንም የረዳ ግሩም ነው እግዚአብሔር ያወጣን ከእዳ የሰናክሬም ቁጥሩ እጅግ ብዙ ነው የኔ ረዳቴ ግን ቅዱስ ሚካኤል ነው ከፈረሰኞች በላይ ነው ፍጥነቱ ከተዋጊዎቹ ይበልጣል ብርታቱ እስራኤልን መና እንደመገባቸው ባሕታውያንን በዱር የረዳቸው ተክለኃይማኖትን ከጉድጓድ ያወጣ እኔንም ሳይንቀኝ ሊያድነኝ መጣ ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

​📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሰኔ ፱/9 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌ሰኔ ዘጠኝ በዚች ዕለት የታላቁ ነቢይ ሳሙኤል የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። የዚህ ቅዱስ አባቱ ሕልቃ
📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሰኔ ፱/9 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌ሰኔ ዘጠኝ በዚች ዕለት የታላቁ ነቢይ ሳሙኤል የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። የዚህ ቅዱስ አባቱ ሕልቃና ይባላል የእናቱም ስሟ ሐና ነው። እነርሱም ከሌዊ ነገድ ከካህኑ አሮን ወገን ናቸው። ሐናም መካን ነበረች፤ ክብር ይግባውና ወደ እግዚአብሔር እያለቀሰች አዘውትራ ስለ ማለደች ይህን የተባረከ ልጅ ሰጣት፤ በቤቷም ሦስት ዓመት አሳደገችው። ​📌ከዚህም በኋላ ገና ስትፀንሰው እንደተሳለች ወደ እግዚአብሔር መቅደስ አቀረበችው፤ ካህኑ ኤሊንም በመላላክ የሚያገለግለው ሆነ። የካህኑ የኤሊ ልጆች ግን ክፉዎች ነበሩ፤ እግዚአብሔርንም አይፈሩም ነበር፤ በቅዱስ መሥዋዕቱም ላይ በደሉ። ይህ ሕፃን ሳሙኤል ግን በኤሊ ፊት ለእግዚአብሔር ሲያገለግል ኖረ፤ በነዚያ ወራቶችም ቃለ እግዚአብሔር ውድ ነበር፤ የሚታይ ራእይም አልነበረም። ​📌ከዚህም በኋላ በአንዲት ሌሊት እንዲህ ሆነ፤ ኤሊ በመኝታው ተኝቶ ሳለ ዐይኖቹም መፍዘዝ ጀምረው ነበር፤ ማየትም አይችልም ነበር። የእግዚአብሔርንም መብራት አብርቶ ለማሳደር ገና አላዘጋጁም ነበር፤ ሳሙኤል ግን በቤተ መቅደስ በእግዚአብሔር ማደሪያ ታቦት አጠገብ ተኝቶ ነበር። ​📌እግዚአብሔርም ሳሙኤልን "ሳሙኤል ሳሙኤል" ብሎ ጠራው፤ እነሆ እኔ አለሁ አለ። ወደ ኤሊም ፈጥኖ ሄደ "ስለጠራኸኝ እነሆ እኔ መጣሁ" አለው፤ ኤሊም "አልጠራሁህም ተመልሰህ ተኛ" አለው፤ ሄዶም ተኛ። ​📌እግዚአብሔርም ዳግመኛ "ሳሙኤል ሳሙኤል" ብሎ ጠራው፤ ሳሙኤልም ተነሥቶ ወደ ኤሊ ሄደ "ስለጠራኸኝ እነሆ መጣሁ" አለው። ኤሊም "አልጠራሁህም ተመልሰህ ተኛ" አለው። ሳሙኤልም ከዚህ አስቀድሞ እግዚአብሔርን በራእይ ገና አላወቀውም ነበር፤ ቃለ እግዚአብሔርም አልተገለጠለትም ነበር። ​📌ዳግመኛም እግዚአብሔር ሳሙኤልን ሦስተኛ ጊዜ ጠራው፤ ተነሥቶም ወደ ኤሊ ሄደ "ስለጠራኸኝ እነሆ መጣሁ" አለው፤ ኤሊም ያንን ልጅ እግዚአብሔር እንደጠራው አሰበ። "ልጄ ተመልሰህ ተኛ፤ የሚጠራህ ካለ 'እኔ ባሪያህ እሰማለሁና ጌታዬ ተናገር' በለው" አለው፤ ሳሙኤልም ሄዶ በመኝታው ተኛ። ​📌እግዚአብሔርም መጥቶ እንደ መጀመሪያው በፊቱ ቆሞ ጠራው። ሳሙኤልም "እኔ ባሪያህ እሰማሃለሁና ጌታዬ በል ተናገር" አለው፤ እግዚአብሔርም ሳሙኤልን "የሰማው ሁሉ ሁለቱን ጆሮዎቹን ይይዝ ዘንድ እነሆ እኔ በእስራኤል ላይ የተናገርሁት ቃሌን አደርጋለሁ። ​📌በዚያችም ቀን በኤሊና በወገኑ ላይ የተናገርሁትን ሁሉ አጸናለሁ፤ እጀምራለሁ እፈጽማለሁም። ልጆቹ የእግዚአብሔርን ቃል አቃልለዋልና እርሱም አልገሠጻቸውምና በልጆቹ ኃጢአት እኔ ወገኑን ለዘላለም እንደምበቀለው ነገርሁት። ስለዚህም ነገር በዕጣንም ቢሆን በመሥዋዕትም ቢሆን የኤሊ የወገኑ ኃጢአት እስከ ዘላለሙ ድረስ እንዳይሠረይ ራሴ እንዲህ ብዬ ማልሁ" አለው። በኤሊ ወገኖችና ልጆች ላይ እግዚአብሔር የተናገረው ሁሉ ተፈጸመ። ​📌ከዚህም በኋላ የቂስ ልጅ ሳኦልን ቀብቶ ለእስራኤል ልጆች ያነግሠው ዘንድ እግዚአብሔር ሳሙኤልን አዘዘው፤ እንዲያነግሥላቸው ለምነዋልና። ሳኦልም የልዑልን ትእዛዝ በተላለፈ ጊዜ፣ ዳግመኛ ለእስራኤል ንጉሥ ሊሆን የዕሴይ ልጅ ዳዊትን ይቀባው ዘንድ ይህን ነቢይ ሳሙኤልን ዳግመኛ አዘዘው። ይህም ነቢይ ሳሙኤል በሕይወት በኖረበት ዘመን ሁሉ እስራኤልን አስተዳደራቸው። ከዚህም በኋላ በሰላም አረፈ። ​"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ታላቅ ነቢይ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።" ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር ​"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን" (የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል) ✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔) ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

Repost from N/a
📍 ለመሆኑ በቴሌግራም ትልቁን የኦርቶዶክስ መዝሙር ቻናል ተቀላቅለዋል ? የሰርግ ፣ የሀዘን ፣ የንግስ መዝሙራት ፣ የተለያዩ ወረባት ፣ የመዝሙር ግጥሞችን ያገኛሉ ። አብረውንም መዝሙራትን ያጠናሉ
📍 ለመሆኑ በቴሌግራም ትልቁን የኦርቶዶክስ መዝሙር ቻናል ተቀላቅለዋል ? የሰርግ ፣ የሀዘን ፣ የንግስ መዝሙራት ፣ የተለያዩ ወረባት ፣ የመዝሙር ግጥሞችን ያገኛሉ ። አብረውንም መዝሙራትን ያጠናሉ ። # ይቀላቀሉን  👇👇 https://t.me/+_R21gL_5brU5MDRk https://t.me/+_R21gL_5brU5MDRk

የዘማሪ አቤል መክብብን ድንቅ የዝማሬዎችን ስራዎችን ማግኘት ይፈልጋልሉ ⁉️ለማግኘት ይቀላቀሉ።🙏🙏
የዘማሪ አቤል መክብብን ድንቅ የዝማሬዎችን ስራዎችን ማግኘት ይፈልጋልሉ ⁉️ለማግኘት ይቀላቀሉ።🙏🙏

https://t.me/synergycounseling ሲነርጂ መንፈሳዊ ፔጅ ነው ፤ አላማውም በሥነ ልቦና ቀውስ ውስጥ የገቡ ሰዎችን በመንፈሳዊ(Orthodox Psychotherapy) እንዲሁም በሥነ ልቦና (Counselling Psychology) መርዳት ነው ፤

ባሕራንኒ ይቤ /፮/ ባሕራንኒ ይቤ ኦ ዘነገደ ባህር /፪/ ርዒክዎ ለሚካኤል ወስዕንኩ ጠይቆቱ ዘይብል/፪/ ባህራንኒ ይቤ /፮/ የሞቱን ደብዳቤ - - -  ቅዱስ ሚካኤል ሚካኤል አጥፍቶ - - -  ቅዱስ ሚካኤል ባሕራንን አዳነው - - -   ቅዱስ ሚካኤል   በሠርግ ተክቶ - - -  -    ቅዱስ ሚካኤል ሠዳዴ ሳጥናኤል - - -  ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት - - - -    ቅዱስ ሚካኤል እኛንም አድነን - - - -    ቅዱስ ሚካኤል  ከሲኦል እሳት - - - - -   ቅዱስ ሚካኤል
አዝ
ከሊቀ ነብያት - - -  -     ቅዱስ ሚካኤል ከነሙሴ ጋራ - - - -  -   ቅዱስ ሚካኤል ሕዘበ እሥራኤልን - - - ቅዱስ ሚካኤል ሚካኤል ሲመራ - - -  ቅዱስ ሚካኤል ቀን ደመና ጥሎ - - -   ቅዱስ ሚካኤል ሌሊት እያበራ - - - -  -  ቅዱስ ሚካኤል ተሻገሩ ኤርትራን - -  - -ቅዱስ ሚካኤል ሁሉም በየተራ - - -  -   ቅዱስ ሚካኤል        🎤 ዘማሪ ዲ/ን  ታዴዎስ  ግርማ🎤 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺                      📎 👇 ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

​📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሰኔ ፰/8 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌ሰኔ ስምንት በዚች ቀን አምላክን የወለደች በሁለት ወገን ድንግል የሆነች የእመቤታችን ማርያም የታወ
📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሰኔ ፰/8 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌ሰኔ ስምንት በዚች ቀን አምላክን የወለደች በሁለት ወገን ድንግል የሆነች የእመቤታችን ማርያም የታወቀችው በውኃ ምንጭ ዘንድ ያለች የቤተ ክርስቲያንዋ ቅዳሴ ነው። እርሱም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሷ ጋር ወደ ግብፅ አገር ተሰዶ ሲመለስ ያፈለቀው የተባረከ መታጠቢያ ነው። ​📌ይህም እንዲህ ነው፤ ለጻድቁ ዮሴፍ የእግዚአብሔር መልአክ በሕልም ተገልጾለት "ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብፅ አገር ሂድ" አለው። ዮሴፍም ነቅቶ ተነሣ፤ ክብር ይግባውና ሕፃኑን ጌታችንን፣ እናቱንና እኅቷ ሰሎሜን ይዞ ወደ ግብፅ አገር ሄዱ፤ በዚያም በውስጧ ባሉ በብዙ አገሮች እየዞሩ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር ኖሩ። ​📌ሄሮድስም ከሞተ በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ለዮሴፍ ሁለተኛ ተገለጠለት፤ ወደ እስራኤልም አገር ሕፃኑንና እናቱን ይዞ እንዲመለስ አዘዘው ። በሚመለሱም ጊዜ ወደ መዓልቃ ደረሱ፤ ከዚያም ወደ መጣርያ አገር ደረሱ፤ ይቺም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ውኃ ያፈለቀባትና የመታጠቢያ ቦታ የሆነች ናት፤ እርሷም እስከ ዛሬ አለች ። ​📌ሰዎችም ከአገሩ ሁሉ ከየነገዱ ሁሉ መጥተው አምላክን ወደ ወለደችና በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ወደ ጸናች ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም ይለምናሉ፤ ከተባረከውም የውኃ ምንጭ ታጥበው ከደዌያቸው ሁሉ ይድናሉ፤ በዛሬዪቱ ቀን ከከበረች ቤተ ክርስቲያንም ይባረካሉ። ​"እርሷን እመቤታችንን ለመረጣትና ለወደዳት፣ በሥጋም እናቱ ላደረጋት፣ ስለ እርሷም ዘመድ ለሆነንና ወደ እርሱ ላቀረበን፣ ወራሾቹም ላደረገን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን ።" ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር ​"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን" (የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል) ✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔) 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺                      📎 👇 ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

Repost from N/a
✝ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር ይፈልጋሉ?

🇪🇹 የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ የትኞቹን መዝሙራት ማግኝት ይፈልጋሉ❓

ምን ልክፈልህ ምን ልክፈልህ የኔ ጌታ አይረሳም ያ ውለታ የመረጥቀኝ የወደድከኝ በዝማሬ ያሳደከኝ ክበርልኝ ከታናሽዋ ከተማ ታላቁ ተገኝተሃል ከድካሜ ቀስቅሰህ እግሬን አስከትለሀል ስትመራኝ በፅድቅህ ጀርባህን አየዋለው ብርሃኔ ቀድመህልኝ ጨለማን ሰብርያለው ዝቅ ብለህ ወዳጄ አኖርከኝ በከፍታ ከሰማዩ በረከት ሰተከኝ እድል ፈንታ ተባረክ እልሀለው ይኸው መሽቶ እስኪነጋ አፈሳለው ምወድስ ልሳኔ ሳይዘጋ ገና ከእናቴ ማህፀን አካሌ ሳይሰራ አንተ ታውቀኝ ነበር በስሜ ሳልጠራ ተክለኸኝ በወንዙ ዳር በፀጋ ለምለሚያለው ለነብሴ ፀሀይ ሆነህ በደምህ ፈክቻለው ታላቅ መዝገብ ወስጄ ፈጣን ብዕር ብመዝም ውዴ የዋልክልኝን ያንተን ፍቅር አይደርስም ከመሰውያዬ ላይ ቅኔ እንባዬ ከአይኔ ስር ከተሰበረው ልቤ ይፈልቃል አዲስ መዝሙር 🎤ዘማሪ እዝራ ኃይለ ሚካኤል🎤 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺                      📎 👇 ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​እንኳን ለሥሉስ ቅዱስ (አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ) ወርሃዊ የክብር በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ! ​ዛሬ ሰኔ ሰባት ቀን ቅድስት ቤተክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።እንኳን ለሥሉስ ቅዱስ (አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ) ወርሃዊ የክብር በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ! ​ዛሬ ሰኔ ሰባት ቀን ቅድስት ቤተክርስቲያናችን የሥሉስ ቅዱስን ወርሃዊ በዓል በደስታ ታስባለች። ይህ ዕለት እግዚአብሔር አምላክ ለአባታችን ለአብርሃም በመምሬ ዛፍ ሥር በሦስትነቱና በአንድነቱ የተገለጠበትን ታላቅ ምስጢር የምናስብበት ነው (ዘፍጥረት ፲፰)። ​📌ከበዓሉ የምንማረውየደግነት ፍሬ አብርሃም እንግዶችን በቅንነትና በትሕትና በመቀበሉ የይስሐቅን መወለድ አገኘ። እኛም የተቸገሩትን በደግነት ስንረዳ የእግዚአብሔርን በረከት ወደ ቤታችን እንጋብዛለን። ​በንጽሕና መኖር ልባችንን ከክፋትና ከቂም አጥርተን በሃይማኖት ስንጸና፣ ቅድስት ሥላሴ በሕይወታችንና በቤታችን ማደሪያ ያደርጋሉ። ​የቤተሰብ ሰላም ባለ ትዳሮችና ቤተሰቦች በፍቅርና በጸሎት በአንድነት ሲኖሩ፣ እግዚአብሔር በዚያ ቤት ውስጥ የኑሮና የጤና በረከትን ያፈስሳል።
"ቅዱስ አብ ሆይ ጠብቀን፤ ቅዱስ ወልድ ሆይ አድነን፤ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ ሆይ አጽናን፤ ስምህ ለዘላለሙ የተመሰገነ ይሁን። አሜን።"
  ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

ገጼን አማትቤ ገጼን አማትቤ ልጀምር ውዳሴ በትምህርተ መስቀል በስመ ሥላሴ ይርቃል ከጎኔ ጠላት ዳቢሎስ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ከትቢያ ከአፈር አንስቶ የሰራኝ በአፉም እስትንፋስ ህይወትን ያደለኝ የሥላሴ ስራ ድንቅ ነው ጥበቡ ከአይምሮ በላይ ነው የእግዚአብሔር ሀሳቡ
አዝ
እክህደከ ሰይጣን ጠላቴን ክጃለው ለዚህም ምስክር ማርያም ናት ብያለው በቤተክርስትያን ቆሜ በመቅደሱ ለቅድስት ሥላሴ ዘመርኩ ለንጉሱ
አዝ
አልነበረም ዘመን እሱ ያል ነበረበት ዳግመኛም አይኖርም እርሱ ማይኖርበት የህይወቴ ጣእም ክብርና ሞገሴ የማይሾሙት ንጉስ ዘላለም ሥላሴ
አዝ
ኪሩቤል ሱራፌል ኃይላት ሊቃናት መናብርት ስልጣናት ቆመው በአንድ ነት ያላንዳች ዝምታ ይሉታል በክብር ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር 🎤ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ🎤 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺                      📎 👇 ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

😇መምህር ገብተዋል 📖📖 📚😇ነገረ ክርስቶስ😇📖📚 📔 ትምህርት ተጀምሯል ላይቭ ግቡ 🙏 ከታቺ ባለው ሊንክ ግቡ ቭኦይስ ቻት ግቡ 👇👇 https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=132ae57e1a061a7502 https://t.me/Bete_kidus_Michael_12

የርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማን ትምህርቶች በቀላሉ በትንሽ MB የምታገኙበት የ Telegram ቻናል እንሆ ቤተሰብ ሁኑ👇
የርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማን ትምህርቶች በቀላሉ በትንሽ MB የምታገኙበት የ Telegram ቻናል እንሆ ቤተሰብ ሁኑ👇

መምህር ገብቶል የትምህርቱ እርስ👇
📖ገድላት ምንድናቸው ??📚
ተጀምሯል ቮይስ ቻት ግቡ ከታቺ በለው ሊንክ ግቡ 👇👇 https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=132ae57e1a061a7502 https://t.me/Bete_kidus_Michael_12

ይሄንን የሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍን መዝሙሮችን የሚተላለፉበት ቴሌግራም ቻናል መቀላቀል አለባችሁ!!! 👇👇👇 https://t.me/+2ua4-eAbNTI1MTRk https://t.me/+2ua4-e
ይሄንን የሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍን መዝሙሮችን የሚተላለፉበት ቴሌግራም ቻናል መቀላቀል አለባችሁ!!!               👇👇👇 https://t.me/+2ua4-eAbNTI1MTRk https://t.me/+2ua4-eAbNTI1MTRk

✞♡ ቀኑን በሙሉ እንከፋለን ♡✞ ቀኑን በሙሉ እንከፋለን የሚረግሙንን እንመርቃለን ልምዳችን ሆኗል ስደት በማታ ያልሆነው የለም ባንተማ ጌታ ባንተማ ጌታ እጅግ ብዙ ነገር ባንተ ደርሶብናል እየተገፈተርን ከሙክራብ ወተናል ባያቁት ነው እንጂ ባያስተውሉት ኢየሱስ ፍቅር ነው ያለም መዳኒት            
አዝ
እብዶች አይደለን እናስተውላለን ለዘመን የማይቆም የፀና ቃል አለን አይዟችሁ አትፍሩ ተፅናኑ በጌታ ይፍታ ሲል ይፈታል የሲኦል ጅማቷ       
አዝ
ፈተናና ስቃይ መከራ ቢበዛ ሰለቸኝ አያቅም በደም የተገዛ ሁሉም ለበጎ ነው ሁሉም ለክብራችን እስካለም ዳርቻ ተሰምቷል ድምፃችን
አዝ
የቀደሙት ሁሉ ባንተ ተሰደዋል በሠንሠለት ታስረው ሸንጎ ፊት ቆመዋል በቀስትና በጦር በፊትህ እረገፉ ወጡ ከዚች አለም ታሪክ እየፃፉ 🎤 ዘማሪ ዲ/ን እንዳልካቸው ዳኘው🎤 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺                      📎 👇 ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯

አንተ ብቻ ንጉስ አንተ ብቻ ንጉሥ አንተ ብቻ ዳኛ/2/ ተመስገን ኢየሱስ የነፍሴ መጽናኛ
አዝ
ስለፍቅርህ ቆሜ ባነባ ባፈስልህ የቅኔ መባ አልጠግብ እኔ አይሆንም ካሳ እስከ ሽበት ስምክን ባነሳ/2/
አዝ
ያስተማርከኝ የውጤት ፊደል የተከልከው በልቤ ወደብ እያነቃኝ አመልክሀለሁ ከአንተ ወዲያ ማንን አውቃለሁ /2/
አዝ
ሰውነቴ ከግፍ ቢፀዳ ህሊናዬ አንተን ቢረዳ ተፀየፈ የሰውን ምርኩዝ ብታበራው የልቤን መቅረዝ /2/
አዝ
ከእንቅብ በታች መቼ ተነሳሁ በተራራ እግሬን አፀናው መገዛቴ ለፍቅርህ ቀንበር ሰው አረገኝ አንስቶ ካፈር/2/ 🎤ዘማሪ እስጢፋኖስ ሣህሌ🎤 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺                      📎 👇 ╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯