en
Feedback
ሱፊይ አሕለሱና ወልጀመዐህ

ሱፊይ አሕለሱና ወልጀመዐህ

Open in Telegram

╔════◈◉◈════╗                      أهل السنة والجماعة             ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⚪️አህለሱና ወልጀመዓህ ስንል የሰለፎችንና የኸለፎችን የግንዛቤ ዘይቤ የሚከተሉ ማለት ነው። 🔴ይህ መንገድ ሌሎች የኢስላም አስተሳሰብ ተከታዮችን አያከፍርም 🔎አመላካች የሰሪን ምንዳ ያገኛልና ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩልን ╚════◈◉◈════╝

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ሱፊይ አሕለሱና ወልጀመዐህ

Channel ሱፊይ አሕለሱና ወልጀመዐህ (@sufiyahlesuna) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 11 990 subscribers, ranking 7 570 in the Religion & Spirituality category and 2 803 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 11 990 subscribers.

According to the latest data from 09 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -8 over the last 30 days and by -7 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 14.80%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 7.36% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 1 775 views. Within the first day, a publication typically gains 882 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 32.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
╔════◈◉◈════╗                      أهل السنة والجماعة             ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⚪️አህለሱና ወልጀመዓህ ስንል የሰለፎችንና የኸለፎችን የግንዛቤ ዘይቤ የሚከተሉ ማለት ነው። 🔴ይህ መንገድ ሌሎች የኢስላም አስተሳሰብ ተከታዮችን አያከፍርም 🔎አመላካች የሰሪን ምንዳ ያገኛልና ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩልን ╚════◈◉◈════╝

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 10 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

11 990
Subscribers
-724 hours
+97 days
-830 days
Posts Archive
የዳሩል ሒጅረተይን ኢስላማዊ ትምህርትና ልማት ድርጅት ምስረታ እና ሪፖርት ▶️ https://youtu.be/t61f4jJNovk?si=wHuqakVUeXmNR92M

በሰባተኛው ክፍለ ዘመን ሁለተኛ አጋማሽ ተወልደው በስምንተኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ሩብ ዓመት የሞቱት ኢብኑ ተይሚያህ፥ የቁርዓንና የሱና እንዲሁም የሰሃቦች ንግግር ባንዲራ ስር ተመሽገው ፣ የተጅሲም
በሰባተኛው ክፍለ ዘመን ሁለተኛ አጋማሽ ተወልደው በስምንተኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ሩብ ዓመት የሞቱት ኢብኑ ተይሚያህ፥ የቁርዓንና የሱና እንዲሁም የሰሃቦች  ንግግር ባንዲራ ስር ተመሽገው ፣  የተጅሲምን (ለአላህ አካል አለው የማለትን አስተሳሰብ) ባንዲራ ከተሸከሙትና ለእርሱም ከታገሉት መካከል አንዱ ነበሩ ። ሙጀሲማዎች ኢማም ፈኽሩዲን አር-ራዚ በእነሱና በሸይኾቻቸው መዝሃብ ላይ ካሳረፏቸው ተከታታይና ብርቱ ምቶች የተነሳ ኢብኑ ተይሚያህ እስኪመጡ  ድረስ መነሳት አቅቷቸው ነበር ፤ እርሳቸው (አላህ ይዘንላቸውና) አከርካሪያቸውን ሰብረውና ለቀደሙትም ሆነ ለኋለኞቹ መሳቂያ አድርገው እንጂ አልተዋቸውም ነበር። ኢማም አር-ራዚ በክርክሮችና በጽሑፎቻቸው ላይ በእነሱ ላይ በጣም ጠንካራ ነበሩ ፤ እንዲያውም አንዳንዶቹ ከእኚህ ኢማም ከሚገጥማቸው አስፈሪ ነገር የተነሳ በሰዎች ፊት ያለቅሱ ነበር። ይህ ታላቅ ኢማም ካዘጋጇቸው እጅግ ጠንካራ መጽሐፍት መካከል “ተዕሲስ አት-ተቅዲስ ” ብለው የሰየሙት መጽሐፍ ይገኝበታል፤ በእሱም ውስጥ የእነሱን መዝሃቦች (አስተሳሰቦች) በሙሉ  ጠቅሰው በሁሉም መላምቶች ላይ ምላሽ ሰጥተውባቸዋል፤ ይህም መጽሐፍ አላህ ታላቁን ኢማም ታላቅ ምንዳ እንዲከፍልበት የምንለምንበት መልካም ስራ ሆኖ አልፏል። ኢብኑ ተይሚያህ የባልደረቦቻቸውን (ሙጀሲማዎችን ) ተጨባጭ ሁኔታ በተመለከቱ ጊዜና  የኢማም አር-ራዚ ተፅዕኖ በተጅሲም መዝሃብ ላይ ያለውን ብርታት ሲያስተውሉ ፣እንዲሁም  ኢማም አር-ራዚ ትተዋቸው የሄዱት መጽሐፍት በአሁኑ ጊዜ በባልደረቦቻቸው እጅ ያሉና የሙሸቢሃዎችንና (አላህን ከፍጡራን ጋር የሚያመሳስሉትን) የሙጀሲማዎችን መዝሃብ የሚያፈርሱባቸው መዶሻዎች መሆናቸውን በተረዱ ጊዜ በዋነኝነት በአብዛኞቹ መጽሐፎቻቸው ውስጥ በኢማም አር-ራዚ ላይ፣ እንዲሁም ከቀደሙትም ሆነ ከኋለኞቹ የኢማም አር-ራዚ ባልደረቦች በሆኑት በሌሎቹም ሁሉ ላይ ምላሽ ለመስጠት ቁርጠኝነታቸውን አጠናከሩ ። በዚህም ምክንያት በአብዛኞቹ መጽሐፎቻቸው ውስጥ የኢማም አርራዚን ስም በቀጥታ በመጥቀስ ወይም በእርሳቸው  መዝሃብ (አስተሳሰብ) እና አካሄድ ላይ በተደጋጋሚ ምላሽ ሲሰጡ  ታያቸዋለህ። ኢማም አር-ራዚ በሙጀሲማዎች ላይ ምላሽ ለመስጠትና የሃሳባቸውን ውድቀት ለማብራራት “አሳስ አት-ተቅዲስ” የተሰኘ ልዩ መጽሐፍ አዘጋጅተው ስለነበር ፣ ኢብኑ ተይሚያህ ትኩረታቸውን በዚህ መጽሐፍ ላይ አደረጉ ፤ በ“አሳስ አት-ተቅዲስ ” ላይ ምላሽ በመስጠት የሚታወቀውን ዝነኛ መጽሐፋቸውን ጻፉ ። ኢብኑ ተይሚያህ የተጅሲምን መዝሃብ ለመደገፍ በርካታ መጽሐፍትንና መልእክቶችን የጻፉ ሲሆን ፥ ሃሳቦቻቸውንም በመጽሐፎቻቸውና በፈትዋዎቻቸው  መካከል በተኑ ። ይህን መዝሃብ ለመደገፍና ለመከላከልም ምንም አይነት ጥረት ከማድረግ ወደኋላ አላሉም ።" -- ዶ/ር ሰዒድ ፎዳህ፥ « አል-ካሺፍ አስ-ሰጊር ዓን ዓቃኢድ ኢብኒ  ተይሚያህ»

ውዱዕ ከሚያጠፉ ተግባራቶች መካከል ሁለት ለአቅመ አዳም የደረሱ ባዕድ የሆኑ የወንድና የሴት ሰውነት ያለ ግርዶሽ መነካካት አንዱ ነው ።

ኢማም ኢብኑ ሐጀር አል-ሀይተሚ ረሂመሁሏሁ እንዲህ ይላሉ ፦ « በሸሪዓ መሪዎች (ኡለሞች) ዘንድ የተረጋገጠውና የፀናው መመሪያ እንደሚከተለው ነው ፦ ከተለመደው ሥርዓት ውጪ የሆነ ድንቅ ነገር (ተአም
ኢማም ኢብኑ ሐጀር አል-ሀይተሚ ረሂመሁሏሁ እንዲህ ይላሉ ፦ « በሸሪዓ መሪዎች (ኡለሞች) ዘንድ የተረጋገጠውና የፀናው መመሪያ እንደሚከተለው ነው ፦ ከተለመደው ሥርዓት ውጪ የሆነ ድንቅ ነገር (ተአምር) የታየበት ሰው ፤ ሁኔታዎቹ ፣ አካሄዱና ሕይወቱ ከሸሪዓው መሠረቶች (ኡሱል) እና ዝርዝር ሕጎች (ፉሩዕ) ጋር የሚገጥሙና የሚስማሙ ከሆነ ፣ ያ ድንቅ ነገር " ከራማህ" ይባላል። ካልሆነ ግን ያ ነገር "ኢስቲድራጅ" (ማታለያ) ነው፤ ባለቤቱም ወይ በፈተና ላይ ያለ ሰው ነው ወይም ደግሞ "ዚንዲቅ" (ከሃዲ/መናፍቅ) ነው። በዚህም ምክንያት ነው አል-ጁነይድ እንዲህ ያሉት፦ "አንድ ሰው በውሃ ላይ ሲራመድ ወይም በአየር ላይ ሲበር ብታዩት እንኳ፤ በታዘዙና በተከለከሉ (በሸሪዓ) ሕጎች ዘንድ ያለውን አቋምና ሁኔታ እስክታዩ ድረስ በእሱ እንዳትታለሉ ።"» ከፍ አርሪዐእ

نصيحة سيدنا الشيخ محمد #الشعراوي لسيدي #الحبيب_عمر بن حفيظ 🥹💚🌿

ሱፊዮችና ትግሎቻቸው ============== 💎 በ1940ዎቹ እና በ1950ዎቹ ውስጥ ከመንግሥት ጋር የመጋጨት ባህሪ የነበረው የቲጃኒያ (Tijaniyyah) ጠሪቃ እንቅስቃሴ ጀመረ ፤ በዚህም ቲጃኒዎ
ሱፊዮችና ትግሎቻቸው ============== 💎 በ1940ዎቹ እና በ1950ዎቹ ውስጥ ከመንግሥት ጋር የመጋጨት ባህሪ የነበረው የቲጃኒያ (Tijaniyyah) ጠሪቃ እንቅስቃሴ ጀመረ ፤ በዚህም ቲጃኒዎች የ"ከማል አታቱርክ"ን ሐውልቶች ሰባበሩ። በ1950 ዓ.ም የሕግ ባለሙያ እና ነጋዴ የነበረው መሪያቸው " ሸይኽ ከማል ፒላቮግሉ" ተይዞ የአሥር ዓመት እስራት ተፈረደበት። ✅ በየካቲት 1954 ዓ.ም የከማሊስት ባለሥልጣናት በማርዲን አሥራ ሰባት የነቅሻባንዲያ ጠሪቃ ሸይኾችን አሰሩ። እንዲሁም በሰኔ 1950 ዓ.ም የሜቭሌቪ (Mevlevi) ጠሪቃ ሸይኽን ፣ እና በመጋቢት 1951 ዓ.ም የቃዲሪያ (Qadiriyya) ጠሪቃ ሸይኽን ለፍርድ ያቀረቡ ሲሆን፥ ከቤክታሺያ ጠሪቃ የተወሰኑ ሰዎችን አሰሩ ።

✍ መለያየት ወደ ጥላቻና ቂም መለወጥ የለበትም الطَّلَاقُ مَرَّتَانِ ۖ فَإِمْسَاكٌ بِمَعْرُوفٍ أَوْ تَسْرِيحٌ بِإِحْسَانٍ ۗ « ፍች ሁለት ጊዜ ነው፤ (ከዚህ በኋላ) በመልካም መያዝ ወይም በበጎ አኳኋን ማሰናበት ነው »። አልበቀራህ

«በዚህ በውሸትና በማጭበርበር በተሞላው አለም ውስጥ ለጠፋው የዚህ ዘመን ሰው ፣ ከራሱ ጋር ብቻውን መሆን በጣም አስፈላጊ ነገር ነው.. እሱ ለእርሱ የደህንነት መስመር እና የመዳኛ ጀልባ ነው ።»
«በዚህ በውሸትና በማጭበርበር በተሞላው አለም ውስጥ ለጠፋው የዚህ ዘመን ሰው ፣ ከራሱ ጋር ብቻውን መሆን በጣም አስፈላጊ ነገር ነው.. እሱ ለእርሱ የደህንነት መስመር እና የመዳኛ ጀልባ ነው ።»

አዲሱን የመጅሊስ ሕገ ደንብ ስመለከት በተለይ አንቀጽ 14 ትኩረቴን ሳበው። ሆኖም እስካሁን ድረስ በዚህ ሕገ ደንብ ውስጥ ስለ ምርጫው ግልጽ የሆነ አሠራርና ሂደት አልተቀመጠም። በሌላ በኩል የሰለፍያ
አዲሱን የመጅሊስ ሕገ ደንብ ስመለከት በተለይ አንቀጽ 14 ትኩረቴን ሳበው። ሆኖም እስካሁን ድረስ በዚህ ሕገ ደንብ ውስጥ ስለ ምርጫው ግልጽ የሆነ አሠራርና ሂደት አልተቀመጠም። በሌላ በኩል የሰለፍያ ቡድን ለምርጫው ዝግጅት መጀመሩን አውቃለሁ። በተቃራኒው ደግሞ የሱፍያው ወገን መስጂዶችና መድረሳዎች ከመቀነስ ይልቅ የተጨመሩ ይመስላሉ። ይህም ብዙዎችን ተስፋ እንዲቆርጡ አድርጓል። አንዳንዶች "ምን አገባኝ?" ሲሉ፣ ሌሎች ደግሞ "ሞራላችን ዝቅ ብሏል" በማለት ይናገራሉ። የምንዘነጋው ግን አንድ ነገር አለ። እኛ እንደ ሱፍዮች የምናደርገው ትግል ነስርን ለማስገኘት አይደለም። እኛ የምንለፋው የአላህ ባሮች ስለሆንንና ዲናችንን መጠበቅ ግዴታችን ስለሆነ ነው። በዚህ ጥረት ነስር ቢመጣም ባይመጣም፣ የእኛ ድርሻ መልፋትና መታገል ነው። ነስር ግን የአላህ ነው። ስለዚህ አውራዶቻችንን እንጀምር፤ የተቋረጡ የዒልም መድረኮችን እናጠናክር፤ ልባችንን ከመኽሉቅ አስወግደን በአላህ ላይ እናስቀምጥ። ያኔ ነስሩ በአላህ ፈቃድ ይመጣል። እስቲ እያንዳንዳችን ራሳችንን እንመርምር። በሕይወታችን ከሰላት በኋላ ዱዓ፣ በፈጅር ሰላት ቅኑት፣ በሐሙስ ምሽት ቤተሰብን በልዩ ሁኔታ ማስደሰት፣ ተንቢህን ማንበብ፣ ደላኢሉል ኸይራትን ማንበብና መሰል መልካም ተግባራት በሕይወታችን አሉ? ወይስ ጠፍተዋል? በእርግጥ መጀመሪያ መቀየር ያለብን እኛ ነን። ወደ አላህ በእውነት ስንመለስ አላህ ነስሩን ያወርዳል። አላህ መልካም ሠሪዎችን ፈጽሞ አያጣ ወይም ምንዳቸውን አያሳጣም፦ ﴿إِنَّ اللَّهَ لَا يُضِيعُ أَجْرَ الْمُحْسِنِينَ﴾። ስለዚህ መልካም ሠሪዎች እንሁን፤ ከሐሜት፣ ከሒስድና ከመለያየት እንራቅ። ስለ ምርጫው ወሳኝ ጉዳዮች በቀጣይ ጽሑፍ እመለሳለሁ። ጠብቁኝ።

በሸሪዐ ፍቁድ (ሙባህ) የሆነ ነገር ሁሉ አይተገበርም !! ======= ጨዋና ክብራቸውን የሚጠብቁ ሰዎች (አህሉል ሙሩአህ ) ሌሎች የሚያደርጉትን ነገር ከመፈጸም ይቆጠባሉ ፤ ሷሊሆች ደግሞ የተወደዱ (መንዱብ) ነገሮችን ይመርጣሉ ፣ የተፈቀደን (ሙባህ) ነገር እንኳ ቢፈጽሙ ደረጃውን ከፍ በሚያደርግ መልካም ኒያ ነው የሚፈፅሙት ። ብዙሀኑ ህዝብ ደግሞ ከተፈቀዱት ነገሮች መካከል ከባህላቸውና ከልማዳቸው ጋር የሚስማማውን ይመርጣሉ ፤ በዚህ ሁሉ ላይ ምንም ችግር የለም! የፈቂህ ሚና ግን የዚህን ፍቁድ ተግባር ፍርድ ለማውጣት ማስረጃን መከተል ነው ፤ አንድን ነገር "የተፈቀደ (ሙባህ)" ነው ብሎ መፍረድ ማለት ማዘዝ ፣ ማበረታታት ወይም ማህበረሰቡ በባህል የማይቀበለውን ነገር እንዲያደርግ መገፋፋት ማለት አይደለም። ስለዚህ በእንደዚህ ባሉ ጉዳዮች ላይ ተቃውሞ ማሳየት በህግጋት ደረጃዎች መካከል አለመለየትን ፣ እንዲሁም በፈቂህና በሙፍቲ ፣ በሙጅተሂድና በዋኢዝ (መካሪ)፣ እና በዕውቀት (ዒልም) እና በዳዕዋ መካከል ያለውን ልዩነት አለመረዳትን ያሳያል!

የክረምት ኮርስ የሚሰጡ የዒልም አይነቶች ✍️ለመመዝገብ 0903030703 🌐 https://t.me/DarulHijreteinIslamicOrg

من تصوف ولم يتفقه فقد تزندق « ሸሪዐን ሳይማር ተሰውፍ ውስጥ የገባ በርግጥ ሙናፊቅ ሆኗል » ✍ ከወሀቢያነት ወጥተው " ሱፊ ፕሮማክስ ነን " ብለው ፌስቡኩን ያጨናነቁ ልጆች አሁን ደግሞ ሺዐ ሆነው አረፉት ፥ ባይገርማችሁ አሁን ላይ የሀበሻን ሺዐዎች የሚያንቀሳቅሰው ሰውዬ ራሱ በተመሳሳይ ሂደት ነው ያለፈው ( ወሀቢ ከዚያም ሱፊ ከዚያም ሺዐ) ጌትዬ ኺታማችንን አደራ

እንዲህ አይነት ኪታቦችን ነው እንግዲህ ወሀቢዮች ባለ ብዙ ጥራዝ የሀዲስ ሸርሆችን ፅፈናል ብለው የሚጎርሩት

በታላቁ ሊቅ አል-ሀረሪ በተዘጋጀው የሱነን እብን ማጃህ ማብራሪያ (ሸርህ) ላይ ዳሰሳ ====================== ይህን ማብራሪያ ሁለት ጊዜ አንብቤዋለሁ ፤ እናም የመጽሐፉ ምንጮች ከ"ቱሕፈተ
በታላቁ ሊቅ አል-ሀረሪ በተዘጋጀው የሱነን እብን ማጃህ ማብራሪያ (ሸርህ) ላይ ዳሰሳ ====================== ይህን ማብራሪያ ሁለት ጊዜ አንብቤዋለሁ ፤ እናም የመጽሐፉ ምንጮች ከ"ቱሕፈተል አሕወዚ"፣ " ዓውኑል መዕቡድ " እና " ሐሺየቱ አስ-ሲንዲ" የማይዘልሉ ናቸው ወደሚል መደምደሚያ ደርሻለሁ። ከ"ፈትሑል ባሪ" የተጠቀሱት ጥቅሶች ሁሉ (ዋናው መጽሐፍ እያለም ቢሆን) ከሙባረክፉሪ እርሳቸው ደግሞ ከሸውካኒ ፤ እርሳቸው ደግሞ ከኢብኑ ሐጀር አድርገው የተቀዱ ናቸው ። ከሌሎች ታዋቂ መጻሕፍት የተደረጉ ጥቅሶችም እንዲሁ ናቸው። በዚህ ማብራሪያ ውስጥ ያለው ምርጥ ነገር ቢኖር የሐዲስ ዘጋቢዎችን የሕይወት ታሪክ ደጋግሞ ማቅረቡ ነው። የተተረጎመ

ተለቆዋል ተለቆዋል። አጃኢብ የሆነ ትምህርት ከሸህ መነል ከሪም https://youtu.be/4V1ajbc6J7Q?si=Xz0wL2riwKNQ7qiR
ተለቆዋል ተለቆዋል። አጃኢብ የሆነ ትምህርት ከሸህ መነል ከሪም https://youtu.be/4V1ajbc6J7Q?si=Xz0wL2riwKNQ7qiR

ሱፊይ አሕለሱና ወልጀመዐህ - Statistics & analytics of Telegram channel @sufiyahlesuna