uz
Feedback
ሱፊይ አሕለሱና ወልጀመዐህ

ሱፊይ አሕለሱና ወልጀመዐህ

Kanalga Telegram’da o‘tish

╔════◈◉◈════╗                      أهل السنة والجماعة             ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⚪️አህለሱና ወልጀመዓህ ስንል የሰለፎችንና የኸለፎችን የግንዛቤ ዘይቤ የሚከተሉ ማለት ነው። 🔴ይህ መንገድ ሌሎች የኢስላም አስተሳሰብ ተከታዮችን አያከፍርም 🔎አመላካች የሰሪን ምንዳ ያገኛልና ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩልን ╚════◈◉◈════╝

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ሱፊይ አሕለሱና ወልጀመዐህ analitikasi

ሱፊይ አሕለሱና ወልጀመዐህ (@sufiyahlesuna) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 11 999 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 7 567-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 801-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 11 999 obunachiga ega bo‘ldi.

07 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -4 ga, so‘nggi 24 soatda esa 3 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 15.24% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 7.49% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 1 829 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 899 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 33 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
╔════◈◉◈════╗                      أهل السنة والجماعة             ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⚪️አህለሱና ወልጀመዓህ ስንል የሰለፎችንና የኸለፎችን የግንዛቤ ዘይቤ የሚከተሉ ማለት ነው። 🔴ይህ መንገድ ሌሎች የኢስላም አስተሳሰብ ተከታዮችን አያከፍርም 🔎አመላካች የሰሪን ምንዳ ያገኛልና ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩልን ╚════◈◉◈════╝

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 08 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

11 999
Obunachilar
+324 soatlar
+257 kunlar
-430 kunlar
Postlar arxiv
ኢማም ኢብኑ ሐጀር አል-ሀይተሚ ረሂመሁሏሁ እንዲህ ይላሉ ፦ « በሸሪዓ መሪዎች (ኡለሞች) ዘንድ የተረጋገጠውና የፀናው መመሪያ እንደሚከተለው ነው ፦ ከተለመደው ሥርዓት ውጪ የሆነ ድንቅ ነገር (ተአም
ኢማም ኢብኑ ሐጀር አል-ሀይተሚ ረሂመሁሏሁ እንዲህ ይላሉ ፦ « በሸሪዓ መሪዎች (ኡለሞች) ዘንድ የተረጋገጠውና የፀናው መመሪያ እንደሚከተለው ነው ፦ ከተለመደው ሥርዓት ውጪ የሆነ ድንቅ ነገር (ተአምር) የታየበት ሰው ፤ ሁኔታዎቹ ፣ አካሄዱና ሕይወቱ ከሸሪዓው መሠረቶች (ኡሱል) እና ዝርዝር ሕጎች (ፉሩዕ) ጋር የሚገጥሙና የሚስማሙ ከሆነ ፣ ያ ድንቅ ነገር " ከራማህ" ይባላል። ካልሆነ ግን ያ ነገር "ኢስቲድራጅ" (ማታለያ) ነው፤ ባለቤቱም ወይ በፈተና ላይ ያለ ሰው ነው ወይም ደግሞ "ዚንዲቅ" (ከሃዲ/መናፍቅ) ነው። በዚህም ምክንያት ነው አል-ጁነይድ እንዲህ ያሉት፦ "አንድ ሰው በውሃ ላይ ሲራመድ ወይም በአየር ላይ ሲበር ብታዩት እንኳ፤ በታዘዙና በተከለከሉ (በሸሪዓ) ሕጎች ዘንድ ያለውን አቋምና ሁኔታ እስክታዩ ድረስ በእሱ እንዳትታለሉ ።"» ከፍ አርሪዐእ

نصيحة سيدنا الشيخ محمد #الشعراوي لسيدي #الحبيب_عمر بن حفيظ 🥹💚🌿

ሱፊዮችና ትግሎቻቸው ============== 💎 በ1940ዎቹ እና በ1950ዎቹ ውስጥ ከመንግሥት ጋር የመጋጨት ባህሪ የነበረው የቲጃኒያ (Tijaniyyah) ጠሪቃ እንቅስቃሴ ጀመረ ፤ በዚህም ቲጃኒዎ
ሱፊዮችና ትግሎቻቸው ============== 💎 በ1940ዎቹ እና በ1950ዎቹ ውስጥ ከመንግሥት ጋር የመጋጨት ባህሪ የነበረው የቲጃኒያ (Tijaniyyah) ጠሪቃ እንቅስቃሴ ጀመረ ፤ በዚህም ቲጃኒዎች የ"ከማል አታቱርክ"ን ሐውልቶች ሰባበሩ። በ1950 ዓ.ም የሕግ ባለሙያ እና ነጋዴ የነበረው መሪያቸው " ሸይኽ ከማል ፒላቮግሉ" ተይዞ የአሥር ዓመት እስራት ተፈረደበት። ✅ በየካቲት 1954 ዓ.ም የከማሊስት ባለሥልጣናት በማርዲን አሥራ ሰባት የነቅሻባንዲያ ጠሪቃ ሸይኾችን አሰሩ። እንዲሁም በሰኔ 1950 ዓ.ም የሜቭሌቪ (Mevlevi) ጠሪቃ ሸይኽን ፣ እና በመጋቢት 1951 ዓ.ም የቃዲሪያ (Qadiriyya) ጠሪቃ ሸይኽን ለፍርድ ያቀረቡ ሲሆን፥ ከቤክታሺያ ጠሪቃ የተወሰኑ ሰዎችን አሰሩ ።

✍ መለያየት ወደ ጥላቻና ቂም መለወጥ የለበትም الطَّلَاقُ مَرَّتَانِ ۖ فَإِمْسَاكٌ بِمَعْرُوفٍ أَوْ تَسْرِيحٌ بِإِحْسَانٍ ۗ « ፍች ሁለት ጊዜ ነው፤ (ከዚህ በኋላ) በመልካም መያዝ ወይም በበጎ አኳኋን ማሰናበት ነው »። አልበቀራህ

«በዚህ በውሸትና በማጭበርበር በተሞላው አለም ውስጥ ለጠፋው የዚህ ዘመን ሰው ፣ ከራሱ ጋር ብቻውን መሆን በጣም አስፈላጊ ነገር ነው.. እሱ ለእርሱ የደህንነት መስመር እና የመዳኛ ጀልባ ነው ።»
«በዚህ በውሸትና በማጭበርበር በተሞላው አለም ውስጥ ለጠፋው የዚህ ዘመን ሰው ፣ ከራሱ ጋር ብቻውን መሆን በጣም አስፈላጊ ነገር ነው.. እሱ ለእርሱ የደህንነት መስመር እና የመዳኛ ጀልባ ነው ።»

አዲሱን የመጅሊስ ሕገ ደንብ ስመለከት በተለይ አንቀጽ 14 ትኩረቴን ሳበው። ሆኖም እስካሁን ድረስ በዚህ ሕገ ደንብ ውስጥ ስለ ምርጫው ግልጽ የሆነ አሠራርና ሂደት አልተቀመጠም። በሌላ በኩል የሰለፍያ
አዲሱን የመጅሊስ ሕገ ደንብ ስመለከት በተለይ አንቀጽ 14 ትኩረቴን ሳበው። ሆኖም እስካሁን ድረስ በዚህ ሕገ ደንብ ውስጥ ስለ ምርጫው ግልጽ የሆነ አሠራርና ሂደት አልተቀመጠም። በሌላ በኩል የሰለፍያ ቡድን ለምርጫው ዝግጅት መጀመሩን አውቃለሁ። በተቃራኒው ደግሞ የሱፍያው ወገን መስጂዶችና መድረሳዎች ከመቀነስ ይልቅ የተጨመሩ ይመስላሉ። ይህም ብዙዎችን ተስፋ እንዲቆርጡ አድርጓል። አንዳንዶች "ምን አገባኝ?" ሲሉ፣ ሌሎች ደግሞ "ሞራላችን ዝቅ ብሏል" በማለት ይናገራሉ። የምንዘነጋው ግን አንድ ነገር አለ። እኛ እንደ ሱፍዮች የምናደርገው ትግል ነስርን ለማስገኘት አይደለም። እኛ የምንለፋው የአላህ ባሮች ስለሆንንና ዲናችንን መጠበቅ ግዴታችን ስለሆነ ነው። በዚህ ጥረት ነስር ቢመጣም ባይመጣም፣ የእኛ ድርሻ መልፋትና መታገል ነው። ነስር ግን የአላህ ነው። ስለዚህ አውራዶቻችንን እንጀምር፤ የተቋረጡ የዒልም መድረኮችን እናጠናክር፤ ልባችንን ከመኽሉቅ አስወግደን በአላህ ላይ እናስቀምጥ። ያኔ ነስሩ በአላህ ፈቃድ ይመጣል። እስቲ እያንዳንዳችን ራሳችንን እንመርምር። በሕይወታችን ከሰላት በኋላ ዱዓ፣ በፈጅር ሰላት ቅኑት፣ በሐሙስ ምሽት ቤተሰብን በልዩ ሁኔታ ማስደሰት፣ ተንቢህን ማንበብ፣ ደላኢሉል ኸይራትን ማንበብና መሰል መልካም ተግባራት በሕይወታችን አሉ? ወይስ ጠፍተዋል? በእርግጥ መጀመሪያ መቀየር ያለብን እኛ ነን። ወደ አላህ በእውነት ስንመለስ አላህ ነስሩን ያወርዳል። አላህ መልካም ሠሪዎችን ፈጽሞ አያጣ ወይም ምንዳቸውን አያሳጣም፦ ﴿إِنَّ اللَّهَ لَا يُضِيعُ أَجْرَ الْمُحْسِنِينَ﴾። ስለዚህ መልካም ሠሪዎች እንሁን፤ ከሐሜት፣ ከሒስድና ከመለያየት እንራቅ። ስለ ምርጫው ወሳኝ ጉዳዮች በቀጣይ ጽሑፍ እመለሳለሁ። ጠብቁኝ።

በሸሪዐ ፍቁድ (ሙባህ) የሆነ ነገር ሁሉ አይተገበርም !! ======= ጨዋና ክብራቸውን የሚጠብቁ ሰዎች (አህሉል ሙሩአህ ) ሌሎች የሚያደርጉትን ነገር ከመፈጸም ይቆጠባሉ ፤ ሷሊሆች ደግሞ የተወደዱ (መንዱብ) ነገሮችን ይመርጣሉ ፣ የተፈቀደን (ሙባህ) ነገር እንኳ ቢፈጽሙ ደረጃውን ከፍ በሚያደርግ መልካም ኒያ ነው የሚፈፅሙት ። ብዙሀኑ ህዝብ ደግሞ ከተፈቀዱት ነገሮች መካከል ከባህላቸውና ከልማዳቸው ጋር የሚስማማውን ይመርጣሉ ፤ በዚህ ሁሉ ላይ ምንም ችግር የለም! የፈቂህ ሚና ግን የዚህን ፍቁድ ተግባር ፍርድ ለማውጣት ማስረጃን መከተል ነው ፤ አንድን ነገር "የተፈቀደ (ሙባህ)" ነው ብሎ መፍረድ ማለት ማዘዝ ፣ ማበረታታት ወይም ማህበረሰቡ በባህል የማይቀበለውን ነገር እንዲያደርግ መገፋፋት ማለት አይደለም። ስለዚህ በእንደዚህ ባሉ ጉዳዮች ላይ ተቃውሞ ማሳየት በህግጋት ደረጃዎች መካከል አለመለየትን ፣ እንዲሁም በፈቂህና በሙፍቲ ፣ በሙጅተሂድና በዋኢዝ (መካሪ)፣ እና በዕውቀት (ዒልም) እና በዳዕዋ መካከል ያለውን ልዩነት አለመረዳትን ያሳያል!

የክረምት ኮርስ የሚሰጡ የዒልም አይነቶች ✍️ለመመዝገብ 0903030703 🌐 https://t.me/DarulHijreteinIslamicOrg

من تصوف ولم يتفقه فقد تزندق « ሸሪዐን ሳይማር ተሰውፍ ውስጥ የገባ በርግጥ ሙናፊቅ ሆኗል » ✍ ከወሀቢያነት ወጥተው " ሱፊ ፕሮማክስ ነን " ብለው ፌስቡኩን ያጨናነቁ ልጆች አሁን ደግሞ ሺዐ ሆነው አረፉት ፥ ባይገርማችሁ አሁን ላይ የሀበሻን ሺዐዎች የሚያንቀሳቅሰው ሰውዬ ራሱ በተመሳሳይ ሂደት ነው ያለፈው ( ወሀቢ ከዚያም ሱፊ ከዚያም ሺዐ) ጌትዬ ኺታማችንን አደራ

እንዲህ አይነት ኪታቦችን ነው እንግዲህ ወሀቢዮች ባለ ብዙ ጥራዝ የሀዲስ ሸርሆችን ፅፈናል ብለው የሚጎርሩት

በታላቁ ሊቅ አል-ሀረሪ በተዘጋጀው የሱነን እብን ማጃህ ማብራሪያ (ሸርህ) ላይ ዳሰሳ ====================== ይህን ማብራሪያ ሁለት ጊዜ አንብቤዋለሁ ፤ እናም የመጽሐፉ ምንጮች ከ"ቱሕፈተ
በታላቁ ሊቅ አል-ሀረሪ በተዘጋጀው የሱነን እብን ማጃህ ማብራሪያ (ሸርህ) ላይ ዳሰሳ ====================== ይህን ማብራሪያ ሁለት ጊዜ አንብቤዋለሁ ፤ እናም የመጽሐፉ ምንጮች ከ"ቱሕፈተል አሕወዚ"፣ " ዓውኑል መዕቡድ " እና " ሐሺየቱ አስ-ሲንዲ" የማይዘልሉ ናቸው ወደሚል መደምደሚያ ደርሻለሁ። ከ"ፈትሑል ባሪ" የተጠቀሱት ጥቅሶች ሁሉ (ዋናው መጽሐፍ እያለም ቢሆን) ከሙባረክፉሪ እርሳቸው ደግሞ ከሸውካኒ ፤ እርሳቸው ደግሞ ከኢብኑ ሐጀር አድርገው የተቀዱ ናቸው ። ከሌሎች ታዋቂ መጻሕፍት የተደረጉ ጥቅሶችም እንዲሁ ናቸው። በዚህ ማብራሪያ ውስጥ ያለው ምርጥ ነገር ቢኖር የሐዲስ ዘጋቢዎችን የሕይወት ታሪክ ደጋግሞ ማቅረቡ ነው። የተተረጎመ

ተለቆዋል ተለቆዋል። አጃኢብ የሆነ ትምህርት ከሸህ መነል ከሪም https://youtu.be/4V1ajbc6J7Q?si=Xz0wL2riwKNQ7qiR
ተለቆዋል ተለቆዋል። አጃኢብ የሆነ ትምህርት ከሸህ መነል ከሪም https://youtu.be/4V1ajbc6J7Q?si=Xz0wL2riwKNQ7qiR

ከሴቶች ሁሉ የላቀችዋ እናታችን ዓኢሻህ (ረ.ዐ) ============================ አል-ሐሰን እንዲህ ይላሉ፦ ነቢያት ሞትን በሚጠሉበት ጊዜ (ይህም ተፈጥሯዊና የሰው ልጅ ባህሪ የሆነ ጥላ
ከሴቶች ሁሉ የላቀችዋ እናታችን ዓኢሻህ (ረ.ዐ) ============================ አል-ሐሰን እንዲህ ይላሉ፦ ነቢያት ሞትን በሚጠሉበት ጊዜ (ይህም ተፈጥሯዊና የሰው ልጅ ባህሪ የሆነ ጥላቻ ብቻ ነው) አሏህ ከእርሱ ጋር በሚያደርጉት መገናኘት ፤ ከስጦታዎች በሚወዱት ነገር ሁሉ ሞትን ያገራላቸው ነበር። ይህም አንደኛው ነፍሱ ከጎኖቹ መካከል ስትወጣ ባየውና በተገለጸለት ነገር ተደስቶና ወዶ እስኪሆን ድረስ ነው ። 🔴 በኢማም አቡ ሐኒፋ «ሙስነድ» ውስጥ ደግሞ ከዓኢሻ (ረዲየላሁ ዐንሃ) እንደተወራው ነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፦ 🔴 « ጀነት ውስጥ የዓኢሻን መዳፍ ንጣት አይቻለሁና በእርግጥም (ሞት ) ለኔ ቀላል ተደርጎልኛል ።» 🔴 🔴 ኢብኑ ሰዕድና ሌሎችም ነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ማለታቸውን አስተላልፈዋል፦ « ሞቴ በእርሱ ምክንያት የቀለለልኝን ነገር በእርግጥ ጀነት ውስጥ አይቻለሁ ፤ ልክ መዳፏን [ማለትም የዓኢሻን] እየተመለከትኩ ይመስለኛል ።» 🔴በዚህም ምክንያት የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ዓኢሻን እጅግ በጣም አጥብቀው ይወዷት ነበር ፤ ከእርሷ መለየትንም መሸከም አይችሉም ነበር። ስለዚህም የሞት ፍርሃታቸውንና ሕመማቸውን ለማቅለል እርሷ ጀነት ውስጥ ተመስላ ታየቻቸው ። በእርግጥም ሞት የሚናፈቀው ከሚወዱት ጋር ለመገናኘት ሲባል ብቻ ነውና። ───────────────────────────

ቋሚ የዳሩል ሒጅረተይን አባል እንሁን ሁላችንም ፕሮሞሽን እናድርግ። በሐዲስ አመላካች የሰሪን ምንዳ ያገኛል። https://t.me/DarulHijreteinIslamicOrg

ጥያቄ፡- ✍ የነቢያት ተአምራት እና የአውሊያዎች ከራማዎች ነገ የሚሆነውን ነገር ማወቅን ያካተተ ሆኖ ሳለ ፤ አሏህ በቁርኣኑ « በሰማያትም ሆነ በምድር ካሉት ሁሉ አላህ ካልሆነ በቀር ሩቅን (الغي
ጥያቄ፡- ✍ የነቢያት ተአምራት እና የአውሊያዎች ከራማዎች ነገ የሚሆነውን ነገር ማወቅን ያካተተ ሆኖ ሳለ ፤ አሏህ በቁርኣኑ « በሰማያትም ሆነ በምድር ካሉት ሁሉ አላህ ካልሆነ በቀር ሩቅን (الغيب) የሚያውቅ የለም በላቸው » ማለቱ ፣ እንዲሁም ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) «ከአላህ በስተቀር ነገ የሚሆነውን የሚያውቅ የለም» ማለታቸውና  ይህንን የመሰሉ የቁርኣንና የሐዲሥ ጥቅሶች ትክክለኛ ግንዛቤያቸው  ምን ማለት ነው? መልስ፡- ✅ (ትክክለኛው ግንዛቤ) ፡- ያንን ነገር (ገይብን /ነገ የሚሆነውን) ያለ አንዳች ወይም ያለማንም እገዛ (በተናጠል )በራሱ ሙሉ በሙሉና ሁሉንም አጠቃላይ በሆነ እውቀት የሚያውቅ ከአሏህ በስተቀር ማንም የለም ማለት ነው። ተአምራት (ሙዕጂዛት) እና ካራማዎች ግን የተከሰቱት አላህ ለነቢያቱና ለአውሊያዎቹ ባሳወቃቸው (በገለጸላቸው) መንገድ እንጂ፣ እነሱ ራሳቸው በተናጠልና በራሳቸው ችሎታ ያወቁት አይደለም። ይህም ልክ እኛ ፀሐይ ስትወጣ ለስድስት ሰዓታት ወይም መሰል ያህል እንደምትቆይ ፣ ከዚያም ከእኩለ ሠማይ ዘንበል እንደምትል  (ዘዋል እንደምትሆን)፣ ከዚያም ያን ያህል ቆይታ እንደምትጠልቅ፣ ከዚያም እንደዚሁ ያን ያህል ሰዓት ቆይታ እንደገና እንደምትወጣ እንደምናውቀው ማለት ነው። በጨረቃም ሆነ በሌሎች ወደፊት እንደሚከሰቱ በሚታወቁ ነገሮች ላይ ያለው ንግግር ተመሳሳይ ነው። ይህ እኛ በራሳችን ያወቅነው የሩቅ እውቀት (ዒልሙል ገይብ) ሳይሆን ፣ አላህ ነገሮችን በለመድነው የተፈጥሮ ሥርዓት (ዓዳህ) እንዲጓዙ ስላደረገው ብቻ ያወቅነው እውቀት ነው። _______ (1) የኢማም አን-ነወዊ ፈትዋዎች «አል-መሳኢል አል-መንሡራህ» ገጽ 270። https://t.me/sufiyahlesuna