880
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-2630 days
Posts Archive
Repost from N/a
በቀን 28/06/2017ዓም
በጨፌ ትምህርት ቤት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ114ኛ ጊዜ እና በሀገር ደረጃ ለ49ኛ ጊዜ የሚከበረውን የሴቶች ቀን (March 8) በደማቅ ሁኔታ ተከብረ። በዓሉ ፈጣን እና ቀልጣፋነት ያለው አገልግሎት በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል በሚል መሪ ቃል የሚከበር ነው።
በፕሮግራሙ ላይ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 አስተዳደር የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ጽ/ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ ውቢት ጌቱ, የትምህርት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ታደለ ዱሬሳ, የሴቶች እና ህፃናት ጽ/ቤት ባለሙያ እና የትምህርት ቤቱ የተለያዬ አደረጃቶች ተገኝተዋል። በትምህርት ቤቱ የስርዓተ ፆታ ክበብ አባላት አማካኝነት የተለያዩ አዝናኝ እና ትምህርት ሰጪ ፕሮግራሞች ተላልፈዋል።
