en
Feedback
Mereb Media መረብ ሚዲያ

Mereb Media መረብ ሚዲያ

Open in Telegram

Welcome to our Channel, Mereb Media - መረብ ሚዲያ We provide daily reliable and trusted information. መረጃ ለማድረስ፦ @MerebMereb

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Mereb Media መረብ ሚዲያ

Channel Mereb Media መረብ ሚዲያ (@merebmedia24) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 20 716 subscribers, ranking 11 335 in the News & Media category and 1 623 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 20 716 subscribers.

According to the latest data from 14 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -115 over the last 30 days and by -12 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 23.97%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 17.17% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 968 views. Within the first day, a publication typically gains 3 558 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 34.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Welcome to our Channel, Mereb Media - መረብ ሚዲያ We provide daily reliable and trusted information. መረጃ ለማድረስ፦ @MerebMereb

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 15 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

20 716
Subscribers
-1224 hours
-1627 days
-11530 days
Posts Archive
ምኒልክ ዕዝ በወሰደው የስቦ ማስከዳት እርምጃ በብልፅግና መከላከያ ሠራዊት ውስጥ አመራርና  አባል የሆኑ ወታደሮችን ከነ ሙሉ ትጥቃቸው መቀበሉን አስትወቀ! መነሻቸውን ከላስታ ወረዳ ብልባላ ከተማ እና ከዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን አዚላ ያደረጉ ሁለት የመከላከያ አመራሮችና ሁለት መሠረታዊ ወታደሮች በድምሩ አራት የአገዛዙ ሰራዊት አባላት አገዛዙን በመቃወም ሰኔ 08 ቀን 2018 ዓ/ም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር 30ኛ ክፍለ ጦር ቃኝዎችን ተቀላቅለዋል። የተቀላቀሉ አባላትም:- 1. ሃምሳ አለቃ መኩሪያው አባትይሁን ከ38ኛ ክፍለ ጦር መሐንዲስ 2. አስር አለቃ ይረፍ ደምሴ ከ38ኛ ክፍለ ጦር መሐንዲስ 3. ናትናኤል አቤል የሻለቃ ኦርዲናንስ 4. መሰረታዊ ወታደር ደረጀ አሸናፊ ሲሆኑ    👉 አንድ ጥቁር ስናይፐር    👉 ሦስት ጥቁር ክላሽ    👉 አንድ ሀይተር መገናኛ    👉 ሦስት የስናይፐር ካዝና    👉 አራት የደረትና የወገብ ትጥቅ    👉 420 የክላሽ ተተኳሽ    👉 56 የስናይፐር ተተኳሽ    👉 ስምንት የእጅ ቦምብ በመያዝ ተቀላቅለዋል። የመከላከያ አባላቱም ፋኖን ሲቀላቀሉ የ30ኛ ክፍለ ጦር ፋኖ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ደማቅ አቀባበል ያደረጉላቸው ሲሆን በተደረገላቸው አቀባበልም ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል። አባላቱ አያይዘውም የብልፅግና መንግስት ሃገራችን ኢትዮጵያን ወደ መቀመቅ እየከተታት መሆኑን ዘግይተን ብንረዳውም አሁንም አልረፈደምና የአማራን ህዝብ ለመካስ ብሎም ኢትዮጵያን ከመፍረስ ለማዳን ከፋኖ ጎን ሆነን የስርዓቱን ግብዓተ መሬት እናፋጥናለን ሲሉ ቃላቸውን ሰጥተዋል። በአንድ ወር ጊዜ ውስጥም በአውደ ውጊያ ከተማረከው ውጭ ሦስት ጥቁር ስናይፐር፣ ከ20 በላይ ጥቁር ክላሽና ሌሎች ትጥቆች ከመከላከያ በመውጣት ወደ 30ኛ ክፍለ ጦር ካዝና ገቢ ሆኗል ሲል የ303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል ። የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

photo content
+2

አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር በሚያስተዳድራቸው 5 ወረዳ ትምህርት ቤቶች 6ኛ ክፍል ፈተና በዚህ መልኩ አስጀምሯል። ፈተናው ከመጀመሩ በፊት የነበሩ የቅድመ ዝግጅ
+5
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር በሚያስተዳድራቸው 5 ወረዳ ትምህርት  ቤቶች  6ኛ ክፍል ፈተና በዚህ መልኩ አስጀምሯል። ፈተናው ከመጀመሩ በፊት የነበሩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችም በፋኖ ፀጥታ አስከባሪነትና አስተባባሪነት ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቁ ሲሆን፡ ከዛሬ ሰኔ 08/2018 ዓ/ም ጀምሮ ፈተናው ኮሩ በሚያስተዳድራቸው በሁሉም የፈተና ጣቢያዎች መሰጠት ተጀምሯል። የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

photo content
+3

photo content
+2

የአማራ ህዝብ የትጥቅ ትግል ያለበትን ወቅታዊ ሁኔታ እና በቀበሌ የህዝብ አስተዳደር ስራዎችን ላይ ሰፊ ውይይት ተካሄደ! በእነማይ ወረዳ ዘብች/እየሱስ ቀበሌ ከሚገኙ የማህበረሰብ ክፍል በአማራ ህዝብ
+4
የአማራ ህዝብ የትጥቅ ትግል ያለበትን ወቅታዊ ሁኔታ እና በቀበሌ የህዝብ አስተዳደር ስራዎችን ላይ ሰፊ ውይይት ተካሄደ! በእነማይ ወረዳ ዘብች/እየሱስ ቀበሌ ከሚገኙ የማህበረሰብ ክፍል በአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ወቅታዊ ሁኔታዎች እና በህዝብ አስተዳደር ስራዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል። በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር እና የእነማይ ወረዳ ጊዜያዊ መንግስት አመራሮች በመሩት የስብሰባ መድርክ ስለ አማራ ህዝብ የህልውና ትግል ያለበት ወቅታዊ ሁኔታ ሰፊ ግንዛቤ በመስጠት በቀበሌ ፍትህ አሰጣጥ፣ የቀበሌ መልካም አስተዳደር ፀጥታ፣ ህገወጥ የኦል መሬት ማስከበር፣ የፋይናስ እና ሎጀስቲክ አሰባሰብ በተመለከተ በሰፊው በመወያየት ለቀበሌ ጊዜያዊ መንግስት አቅጣጫ ተሰጥቷል።  በውይይት መድረኩ የተገኙት ማህበረሰብ እንደተናገሩት የአብይ አህመድ አምባ ገነን አገዛዝ በአማራ ህዝብ ላይ ከፍተኛ የሆነ በደል እና ጭቆና እያደረሰ ቢገኝም ይህንን አምባ ገነን ስረዓት ለመገርሰስ መስዋትነት እየከፈለ የሚገኘው የአማራ ፋኖ ጎን እንደሆኑ ተናግረዋል። ምንጭ፦ በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት ክፍል! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

ሜ/ጀኔራል ውባንተ አባተ ኮር ጉና ክፍለ ጦር  በተንቀሳቀሰው ቀጠና የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ማጠቃለያ ፈተናዎችን ማስጀመራቸው ታወቀ! የክፍለጦሩ አርበኞች የፀጥታውን ሁኔታ በበላይነት በማስጠበቅ የፈተና ቁሳቁሶች ስርጭትንእንዲሁም የመምህራንና የተማሪዎችን ደህንነት ከመጠበቀ አኳያ በአስተማኝኝ ሁኔታ እየሰሩ መሆናቸው ተነግሯል። 1ኛ፦ የፈተና ቁሳቁስ ስርጭትና የፀጥታ ጥበቃ በአፋብን በላይ ዘለቀ ዕዝ ሜ/ጄነራል ውብአንተ አባተ ኮር ስር የምትገኘው ጉና ክፍለ ጦር  በምትንቀሳቀስበት ቀጠና የሚገኙ የፈተና ጣቢያዎች ሙሉ ቁሳቁስ በክፍለጦሯል አርበኞች ሙሉ እጀባና ጥበቃ ተደርጎላቸው ያለምንም ፀጥታ ችግር በየጣቢያው ተሰራጭተዋል። ፈተና ከመጀመሩ በፊት የነበሩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችም ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቁ መቆየታቸው እና ፋኖ  ትምህርት እንዲጀመር መፍቀዱም የሚታወስ ነው። 2ኛ፦ የፋኖ ፣የተማሪዎች፣ የወላጆችና የመምህራን ቅንጅት በታሪክ አጋጣሚ ለየት የሚያደርገው የዘንድሮው የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ያለምንም "ህፀፅ" እንዲጀመር በየ ቀጠናው ያለው ጀግናው ፋኖ የአንበሳውን ድርሻ አበርክቷል። ይህ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው ፋኖ ከተማሪዎች፣ ከወላጆች እና ከመምህራን ጋራ ባለፉት ተከታታይ ወራቶች በተካሄዱ ውይይቶች በመሆኑ፣ ተማሪዎች በስነ- ልቦና ሳይሸበሩ፣ በትምህርት ገበታቸው ላይ ብቻ ትኩረት አድርገው ውጤታማ እንዲሆኑ እና ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ጉና ክፍለ ጦር አይተኬ ሚና ነበራት። በአጠቃላይ በአሁኑ ሰዓት የታላቋ ጉና ክፍለ ጦር በፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ መምህር አርበኛ አማረ እንደግ እየተመራ ሁሉም ስራ አስፈፃሜ ፣በስሯ ያሉት ከአምስት ብርጌዶች እና የወረዳ ጊዜያው የፋኖ መንግስት የተውጣጣ ግብር ሃይል የስራ ስምሪት በመስጠት ፈተናዎች በሰላምና በመረጋጋት እየተሰጡ የሚገኝ ሲሆን፣ ይህም የፀጥታና ክትትል ስራ ፈተናው ሙሉ በሙሉ እስኪጠናቀቅ ደረስ የሚቆይ ሲሆን ፣ በተፈጠረላቸው አስተማማኝ ሰላም ምክንያት ተማሪዎች አቅማቸውን እንዲያሳዩ ትልቅ በር ከፍቷል። ምንጭ፦ በአፋብን በላይ ዕዝ ሜ/ጀኔራል ውብአንተ አባተ ኮር ጉና ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ክፍል! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

photo content
+1

ይህ አዲሱ የመረብ ሚዲያ የፌስቡክ ገፅ ነው።ተቀላቀሉን! https://www.facebook.com/profile.php?id=61590677702737

በአሜሪካን ሀገር የፔንሴሌቪያ ምክር ቤት ለአድዋ ድል በሰጠው ታሪካዊ እውቅና ላይ የተሰጠ ምስጋና እና የአቋም መግለጫ! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedi
+3
በአሜሪካን ሀገር የፔንሴሌቪያ ምክር ቤት ለአድዋ ድል በሰጠው ታሪካዊ እውቅና ላይ የተሰጠ ምስጋና እና የአቋም መግለጫ! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

በአምሃራ ሳይንት በለጩማ ግንባር በጠላት ከፍተኛ አመራሮች ላይ አስደናቂ የደፈጣ ጥቃት ተፈጸመ! ​በመካነ ሰላም ከተማ ለቀናት የሴራ ስብሰባ ሲያካሂዱ የነበሩት የአገዛዙ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች፣
በአምሃራ ሳይንት በለጩማ ግንባር በጠላት ከፍተኛ አመራሮች ላይ  አስደናቂ የደፈጣ ጥቃት ተፈጸመ! ​በመካነ ሰላም ከተማ ለቀናት የሴራ ስብሰባ ሲያካሂዱ የነበሩት የአገዛዙ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች፣ ወደ አምሃራ ሳይንት ወረዳ ለመግባት ሲሞክሩ በንሥሮች በተደገሰላቸው ጥብቅ ደፈጣ ክፉኛ ተመትተዋል። የአገዛዙ የጦር አመራሮች በመካነ ሰላም የነበራቸውን የግምገማ ስብሰባ ጨርሰው፣ የተለመደ የጥፋት ተልዕኮአቸውን ለመፈጸም በከፍተኛ መኪናዎች ታጅበው እየተንቀሳቀሱ በነበረበት ቅፅበት ጀግኖቹ  "በለጩማ" በተባለው ስልታዊ ቦታ ላይ መንገዱን ዘግተው በመጠባበቅ፣ ጠላት ጨርሶ ባልገመተው ሁኔታ መብረቃዊ የደፈጣ ጥቃት  ዶግ አመድ አድርገዉታል። ደፈጣዉም በጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ ስር በ105ኛ ኮር የ71ኛ ክፍለ ጦር አናብስቶች ሲሆን የተሰራዉ  በጥቃቱም የጠላት ዋና ዋና ወታደራዊ መሪዎች ጭምር ሙት እና ቁስለኛ ሁነዋል።  በጀግኖቹ ክንድ የደረሰባቸውን ከባድ ጉዳት መቋቋም ያልቻለው የጠላት ጦር፣ አመራሮቹን ለማዳን በከፍተኛ መደናገጥ ውስጥ ሆኖ ሲያነሳ የዋለ ሲሆን  ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው የጦር መኮንኖች በአስቸኳይ ወደ ደሴ  ሆስፒታል በሪፈር የተሸኙ ሲሆን ቀሪወቹ  በአምሃራ ሳይንት ወረዳ በሚገኘው አጅባር ሆስፒታል ገብተዋል። በጉዳቱ የተደናገጠዉ ስርዓት ሽንፈቱን ለመደበቅ ከትናንት ምሽት ጀምሮ በአጅባር ሆስፒታል ዙሪያ ጥብቅ ወታደራዊ ከበባ ያደረገ ሲሆን  የቆሰሉት አመራሮች ማህበረሰቡ እንዳያያቸዉ  በሚል ስጋት፣ ከሕክምና ባለሙያዎች ውጭ ማንም ሲቪል ታካሚ ወደ ሆስፒታሉ ግቢ እንዳይገባ ሙሉ በሙሉ እስካሁን ድረስ አግደው ይገኛሉ። ምንጭ፦ የምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን  መምሪያ! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24

photo content

ከደብረ ማርቆስ ወደ ስናን ሬሽን ለማቀበል በተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ላይ 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ስናን አባ ጅሜ ሻለቃ ባደረገው ማጥቃት 20 የአረመኔው ሰራዊት ሲደመሰሱ 12 የሚደርሱ ከባድ ቁ
+1
ከደብረ ማርቆስ ወደ ስናን ሬሽን ለማቀበል በተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ላይ 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ስናን አባ ጅሜ ሻለቃ ባደረገው ማጥቃት 20 የአረመኔው ሰራዊት ሲደመሰሱ 12 የሚደርሱ ከባድ ቁስለኛ ሁነው 3 ክላሽ ፣ 1050 ጥይት ተማርኳል። የአረመኔው ሰራዊት የ6ኛ ዕዝ 602ኛ ኮር 75ኛ ክ/ጦር ከደብረ ማርቆስ ተነስቶ ወደ ስናን ረዕቡ ገበያ ሬሽን ለማቀበል እየተንቀሳቀሰ ባለበት 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ስናን አባ ጅሜ ሻለቃ ባደረገው ማጥቃት 20 የጠላት ወታደሮች ሲደመሰሱ 12 የሚደርሱት ቁስለኛ ሁነዋል። በተፈፀመው ፈጣን ጥቃት የጠላት መስመራዊ መኮንኖች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን ፻ አለቃ ታሪኩ በቀለ ባቲሳ የሻለቃ አዛዥ ይገኝበታል። ጠላት በአልጠበቀው ስዓት በተከፈተበት ተኩስ አስክሬን ሳያነሳ ፈርጥጦ 3 ክላሽ፣ 1050 ጥይት ትጥቆችና ወታደራዊ ቦርሳዎች ተማርኳል። ምንጭ፦ በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

ግፍን የተቃዎሙ የአገዛዙ ወታደሮች ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ከስምሪት ቀጠናቸው በመጥፋት ፋኖ በገፍ መቀላቀላቸውን ቀጥለዋል። ወታደሮቹ፦ 1, ስናይፐር እና ~ 220 የስናይፐር ተተኳሽ 2, ጥቁር ክላሽ ~
+1
ግፍን የተቃዎሙ የአገዛዙ ወታደሮች ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ከስምሪት ቀጠናቸው በመጥፋት ፋኖ በገፍ መቀላቀላቸውን ቀጥለዋል። ወታደሮቹ፦ 1, ስናይፐር እና ~ 220 የስናይፐር ተተኳሽ 2, ጥቁር ክላሽ ~ 220 የክላሽ ተተኳሽ 2, ቦምብ  በመያዝ ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው በምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 33ኛ ክፍለጦርን ተቀላቅለዋል ሲል የክፍለጦሩ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል አስታውቋል። ስቦ ማስከዳቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ምንጃርና ከረዩ አውራጃ ነበልባል ክፍለ ጦር ድል ተቀዳጀች በአፋብን ሸዋ/ጠ/ግ/አሳምነው ዕዝ ከሠም ፪ኛ ኮር ነበልባል ክፍለ ጦር የብልፅግናውን ጥምር ጦር እንደ ቅጠል አረገፉት። ሁለት የነበልባል ክፍለ ጦር ሻለቆች የተሳተፉበት ውጊያ ማለትም  መብረቅ  ሻለቃ እና መቶ አለቃ አበባው ሻለቃ ፋኖዎች በጥምረት  ባደረጉት ገድል የብልፅግናውን  ግብስብስ  ሠራዊት በ06/10/2018 ከቀኑ 6:00 እስከ ማታ 9:45 ሰዓት በነበረው ፍልሚያ  ፋኖዎቹ  መብረቃዊ ክንዳቸውን በመሰንዘር እንደ እሳት ሲለበልቡት አምሽተዋል። መነሻውን ከባልጪ  አድርጎ  ወደ ኢራንቡቲ ቀበሌ ያቀናውን የሪፐፕሊካን ጥበቃ 5ኛ ክፍለጦር እና በስሩ በጥቅማጥቅም የሰበሰባቸውን ሆድ አደር ሚሊሾች  እንዲሁም አዲስ ተጨማሪ ሰራዊት በመያዝ ኢራንቡቲ ቀበሌን እቆጣጠራለሁ ብሎ በመንጋ ቢመጣም በአይበገሬዎቹ  ነበልባል ክፍለ ጦር  ሠራዊታችን ወደ መጣበት እዲመለስ አድርገውታል።     የሀይል ብልጫ የተወሰደበት የጠላት ሀይል  ከ15 በላይ እንደተገደለበት እና ቁጥሩ በውል  ያልታወቀ ቁስለኛ በአንቡላንስ ከአራት ጊዜ  በላይ ጭኖ እንዳመላለሰ እና የሞተበትን ሀይል በአካባቢው ማህበረሰብ በማስገደድ ለህክምና የምታመላልሰው አንቡላንስ ደርሳ እስክትደርስ 15ቱን እሬሳ እዲያቀብሉት ማስገደዱን  የውስጥ መረጃችን አሳውቆናል። ይህ በእንዲሕ እንዳለ የአፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ ዓፄ አምደ ጽዮን ኮር 7/70 ክፍለጦር  አንድ(1) የአገዛዙ ወታደር =>  አንድ(1) ዘመናዊ ስናይፐር መሳሪያ => አንድ(1) የደረት ትጥቅ =>  አራት(4) ካዝና በመያዝ ወደ ፋኖ ተቀላቅሏል። በሌላ የአውደ ውጊያ ቀጠና በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋት አውራጃ  አስገራሚ ጀብዶች ተሠርተዋል የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝ የዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ ፩ኛ ኮር  7/ለ70 ክፍለ ጦር ዛሬም እንደ ትላንቱ በጠላት ይዞታዎች ውስጥ ሰርገው በመግባት አስገራሚ ድሎችን ማስመዝገባቸውን ቀጥለውበታል። ​የክፍለ ጦሩ ልዩ የኦፕሬሽን ቃኝዎች የፋሺስት አብይ አህመድ ግብስብስ ሰራዊትን ወደ ሚንቀሳቀስበት ቦታ ሰርገው በመግባት የጠላትን እቅድ በማክሸፍ መብረቃዊ ጥቃቶችን ፈፅመዋል። ​የሰርጎ ገብ ውጊያ ስምሪቱ በቀን 05/10/2018 ዓ.ም ከለሊቱ 5:00 ሰዓት ላይ ከአጣዬ ተነስቶ ወደ በርግቢ አቅጣጫ እየገሰገሰ በነበረው የጠላት መከላከያ ሰራዊት ላይ የ7ለ70 ክፍለ ጦር ጀግኖች በ06/10/2018  በበርግቢ ቀበሌ እና በይምልዎ መካከል ላይ አድፍጠው በመጠበቅ ከባድ ድንገተኛ ጥቃት ፈፅመዋል። በዚህ እልህ አስጨራሽ የለሊት ውጊያ የጠላት ኃይል ድባቅ በመመታቱ ወደ መጣበት ተገዶ ለማፈግፈግ ተገዷል። በዚሕም ከጠላት ሀይል አራት(4) የተገደሉ ሲሆን የተቀሩት ደግሞ በጽኑ ቆስለው በሕክምና ላይ እንደሚገኙ የውስጥ መረጃዎቻችን ገልፀዋል። ​ ​ይህ የድል ጉዞ ሳይቋረጥ በማግስቱ በ07/09/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ላይ ከአጣዬ ከተማ ተነስቶ ወደ አላላ በመጓዝ ላይ በነበረው የሆድ አደር ሚሊሻ ኃይል ላይ ሌላ ስልታዊ ጥቃት ተፈጽሟል። የክፍለ ጦሩ የቁርጥ ቀን ልጆች አራዳ በር ላይ ቀድመው ሰርገው በመግባትና ምሽግ በመያዝ፣ በሚሊሻው ላይ የጀግንነት ክንዳቸውን አሳርፈዋል።​በዚህ እልህ አስጨራሽ ውጊያ እንድሪስ የተባለው የጠላት ሚሊሻ መሪ እስከ ግብረ አበሮቹ ሙሉ በሙሉ የተደመሰሰ ሲሆን፣ ካጋጠማቸው ከባድ ሽንፈት የተረፉት 3ቱ (ሦስቱ) ደግሞ በከባድ የመቁሰል አደጋ ምክንያት ሪፈር ተጽፎላቸው በሕይወትና በሞት መካከል ይገኛሉ ሲል መረጃዎቻችን ተናግረዋል። ምንጭ፦በአፋብን አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

photo content

#ከበላጎ ምሽግ እስከ ዋድላ ቋና! #ያልተነገረ ገድል፣ ያልተዘከረ ዋጋ! #እስከ መቃብር የታመኑ ጀግኖች! https://youtu.be/zj7iFTfiyYk?si=kD2dLnQs9WGRTwBO

#ያልተነገረ ገድል፣ ያልተዘከረ ዋጋ! ሙሉ ዝግጅቱን በዚህ ተከታተሉ👉https://youtu.be/zj7iFTfiyYk?si=kD2dLnQs9WGRTwBO