en
Feedback
Mereb Media መረብ ሚዲያ

Mereb Media መረብ ሚዲያ

Open in Telegram

Welcome to our Channel, Mereb Media - መረብ ሚዲያ We provide daily reliable and trusted information. መረጃ ለማድረስ፦ @MerebMereb

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Mereb Media መረብ ሚዲያ

Channel Mereb Media መረብ ሚዲያ (@merebmedia24) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 20 692 subscribers, ranking 11 335 in the News & Media category and 1 623 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 20 692 subscribers.

According to the latest data from 14 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -115 over the last 30 days and by -12 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 23.97%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 17.17% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 968 views. Within the first day, a publication typically gains 3 558 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 34.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Welcome to our Channel, Mereb Media - መረብ ሚዲያ We provide daily reliable and trusted information. መረጃ ለማድረስ፦ @MerebMereb

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 15 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

20 692
Subscribers
-1224 hours
-1627 days
-11530 days
Posts Archive
#ሰበር- ካምፑና ፖሊስ ጣቢያው ወደመ! #ፋኖ የከባድ መሣሪያ ጥቃት ጀመረ! #ቁስለኛ ወታደሮች ደሴ ገቡ! https://youtu.be/lPlPqrDpiH8?si=X6cw88xv3ycnfgH3

የዛሬ ሰኔ 08/2018 ዓ/ም እለታዊ የግንባር ተጋድሎዎችንና ሌሎች መረጃዎችን ተከታተሉ👉https://youtu.be/lPlPqrDpiH8?si=X6cw88xv3ycnfgH3

ፋኖ በተቆጣጠራቸው ቀጠናዎች ሕዝባዊ የሥልጣን መዋቅርን እያጠናከረ መሆኑን አስታወቀ! በእነማይ እና በእነብሴ ሳርምድር ወረዳዎች ከማሕበረሰቡ ጋር ጥልቅ ውይይቶች መካሄዱም ተነግሯል። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የብልፅግናን አምባገነን መዋቅር ሙሉ በሙሉ ባፈረሰባቸውና ነጻ ባወጣቸው ቀጠናዎች፣ ከሕዝቡ ጋር የሚያደርጋቸውን ሁለንተናዊ ውይይቶችና የጊዜያዊ መንግስት ምስረታ ሥራዎችን አጠናክሮ ቀጥሏል። በእነማይ እና በእነብሴ ሳርምድር ወረዳዎች የተካሄዱት ሰፋፊ ሕዝባዊ መድረኮች የትግሉን ወቅታዊ አሸናፊነት ያበሰሩ ሲሆን፤ ማኅበረሰቡም ከአምባገነኑ የአብይ አህመድ ሥርዓት ይልቅ በፋኖ ሕዝባዊ መስተዳድር ላይ ያለውን ሙሉ አመኔታና አጋርነት በተግባር እያሳየ ይገኛል። በእነማይ ወረዳ ዘብች/እየሱስ ቀበሌ ከሚገኙ የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች ጋር በህልውና ትግሉ ወቅታዊ ሁኔታዎች እና በሕዝብ አስተዳደር ሥራዎች ላይ ሰፊና ፍሬያማ ውይይት ተካሂዷል። በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክፍለ ጦር እና በእነማይ ወረዳ ጊዜያዊ መንግስት አመራሮች በጋራ በመሩት የዚህ ስብሰባ መድረክ ላይ፦ ስለ አማራ ሕዝብ የህልውና ትግል አሁናዊ አሸናፊነትና ቁመና ሰፊ ግንዛቤ ተሰጥቷል። በቀበሌው ደረጃ ስላለው የፍትህ አሰጣጥ፣ ስለ መልካም አስተዳደርና ፀጥታ ጥበቃ፣ ስለ ሕገ-ወጥ የደንና መሬት ወረራ መከላከል እንዲሁም ስለ ፋይናንስ እና ሎጅስቲክስ አሰባሰብ ሂደቶች በሰፊው በውይይቱ ተሰቅሷል። ለቀበሌው ጊዜያዊ መንግስት የሥራ መሪዎች ትግሉንና ሕዝቡን በቅንነት ማገልገል የሚችሉበት ቀጣይ አቅጣጫ ተቀምጧል። በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት ነዋሪዎች እንደተናገሩት፣ "የአብይ አህመድ አምባገነን አገዛዝ በአማራ ሕዝብ ላይ ከፍተኛ የሆነ የዘር ማጥፋት፣ በደል እና ጭቆና እያደረሰ ቢገኝም፣ ይህንን አረመኔያዊ ሥርዓት ለመገርሰስና ክብራችንን ለመመለስ መስዋዕትነት እየከፈለ ከሚገኘው ከጀግናው የአማራ ፋኖ ጎን በሙሉ አቅማችን እንቆማለን" በማለት ፅኑ አቋማቸውን ገልጸዋል። በተመሳሳይ ዜና፣ በእነብሴ ሳርምድር ወረዳ ከዞባር ይቋንዳ ቀበሌ ነዋሪዎች ጋር የተጀመረው ሕዝባዊ ውይይት ተጠናክሮ ቀጥሏል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የፋኖ የፖለቲካና ወታደራዊ አመራሮች የትግሉን አሁናዊ ስትራቴጂካዊ ከፍታና የድርጅቱን እምቅ አቅም ለሕዝቡ አስረድተዋል። ፋኖ በአሁኑ ወቅት ከጠላት የብልፅግና ቡድን በተሻለ ሁኔታ የላቀ ዲፕሎማሲያዊ ቅቡልነትን በዓለም መድረክ ላይ በመፍጠሩ፣ ቀጠናዊና ዓለም አቀፋዊ ተቀባይነቱ በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩንና በርካታ አጋር ኃይሎችን ማፍራት መቻሉን ገልጸዋል። ይህም የብልፅግናን ዕድሜ አሳጥሮ በአጭር ጊዜ ታሪካዊ ድልን ለመቀዳጀት ትልቅ ዕድል መፍጠሩ ተብራርቷል። በማኅበረሰቡ በኩል በቀበሌው ውስጥ እያገለገሉ ባሉ ጊዜያዊ አመራሮች ላይ ሰፊና ገንቢ አስተያየቶች የተሰጡ ሲሆን፣ አመራሮቹም ለተነሱት ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ሰጥተዋል። በሕዝቡ አስተያየት መሠረት ግንባታና ማስተካከያ የሚያስፈልጋቸውን ክፍተቶች በመለየት፣ በቀጣይ በጥያቄዎቹ መሠረት የአመራር ማስተካከያ ሥራዎችን ለመሥራት የሚያስችል መመሪያና የሥራ አቅጣጫ ተሰጥቷል። የአማራ ሕዝብ የትግሉ ዋና ባለቤት በመሆኑ፣ የፋኖ አመራሮች በየጊዜው በየቀበሌው በመገኘት የማኅበረሰቡን አንገብጋቢ ችግሮች እያወያዩ የመለየትና አስቸኳይ መፍትሄዎችን የመስጠት ሂደቱን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ በአፅንኦት አስታውቀዋል። ይህ የፋኖ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትና የመንግስትነት ተግባር፣ ወራሪው የብልፅግና ጦር ዳግም ወደ ቀጠናው እንዳይመለስ ሕዝባዊ ግንቡን ይበልጥ ያጠነከረ መሆኑ ተመልክቷል። የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

የአሜሪካዋ ጆርጂያ እና ፔንሲልቪኒያ ግዛቶች ለአፍሪካውያን የነጻነት ተምሳሌት ለሆነው ታላቁ የአድዋ ድል በይፋ እውቅና በመስጠት መጋቢት 2 (ማርች 2) "የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን" ሆኖ እንዲከበር ታሪካዊ ውሳኔ አሳለፉ። ይህንን ዓለም አቀፋዊ እውቅና ተከትሎ፣ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) በውጭ ጉዳይ ቢሮው በኩል የምስጋና እና የአቋም መግለጫ ያወጣ ሲሆን፤ የጀግኖች አባቶቻችንን ታሪክ በማጉደፍ አገራችንን እያፈረሰ ያለውን አምባገነኑንና ፀረ-ሕዝብ የሆነውን ሥርዓት በፋኖ ክንድ ታግሎ ለመጣል ቃሉን አድሷል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የጥቁር ህዝቦች የነጻነት፣ የሉዓላዊነትና የክብር ተምሳሌት የሆነው የአድዋ ድል በአሜሪካ የፖለቲካ መድረክ ትልቅ ስፍራ አግኝቷል። የጆርጂያ ግዛት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በቅርቡ ባሳለፉት ታሪካዊ ውሳኔ፣ ማርች 2 (የካቲት 23) በግዛቲቱ ውስጥ "የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን" ሆኖ በይፋ እንዲከበር በሙሉ ድምፅ አፅድቀዋል። ይህ የውሳኔ ሃሳብ የአድዋ ድልን 130ኛ ዓመት መታሰቢያ ታሳቢ በማድረግ የቀረበና የጸደቀ ታሪካዊ ሰነድ ነው። የጆርጂያ ግዛት ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ ይህንን ታሪካዊ ሰነድ አስመልክተው በሰጡት ምስክርነት፣ የታላቋን ኢትዮጵያ መሪዎች ከፍ አድርገው አወድሰዋል። "ኢትዮጵያዊው ንጉሥ ዳግማዊ ምኒልክ እና ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ ብጡል በአመራር ሰጪነት አገራቸውን ከቅኝ ገዥ ተቀራማቾች አስጥለዋል" በማለት የነገስታቱን አኩሪ የታሪክ አሰሪነት አጉልተው ገልጸዋል። ውሳኔው የቅኝ ግዛትን ሥርዓትና አውሮፓውያን በአፍሪካ ላይ የነበራቸውን የበላይነት በተግባር የሰበረውን ይህንን ድል ከማወደስ ባሻገር፣ በጆርጂያ ለሚኖሩ በርካታ የኢትዮጵያ ተወላጆችና ዳያስፖራ አባላት ላበረከቱት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ባህላዊ እድገት እውቅና የሰጠ መሆኑ ተገልጿል። በተመሳሳይ የፔንሲልቪኒያ ግዛት ምክር ቤት እ.ኤ.አ. ጁን 3፣ 2026 በሰፊ ድምፅ ባሳለፈው ውሳኔ በህግ ደረጃ (HR 441)፣ ማርች 2ን "የአድዋ የድል ቀን" (Adwa Victory Day) ብሎ በይፋ አውጇል። ይህንን ታሪካዊና ዓለም አቀፍ እውቅና ተከትሎ፣ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ በውጭ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊው በብሩክ ስለሺ በኩል ጠንካራ የምስጋና እና የትግል የአቋም መግለጫ አውጥቷል። ንቅናቄው በመግለጫው እንዳሰፈረው፦ ዓለም የነፃነት ቀን ሲያከብር እኛ የድል ቀን እንድናከብር ላደረጉን፣ በደማቸው ከአእምሮ በላይ በሆነ ጀግንነት ታላቅ ድል ላጎናፀፉን ለዳግማዊ አፄ ምኒልክ እና ለእቴጌ ጣይቱ ብጡል ዘላለማዊ ክብርና ምስጋና ይግባቸው ብሏል። የፔንሲልቪኒያ እና የጆርጂያ ምክር ቤቶች ይህንን ታሪካዊ ቀን በይፋ ማወጃቸው ለታሪክ ፍትህ፣ ለዓለም አቀፍ የነፃነት ትግል፣ ለእኩልነትና ለሉዓላዊነት ክብር የሚሰጥ እጅግ ጠቃሚ እርምጃ መሆኑን አፋብን ገልጿል። አፋብን የትናንቱን የአድዋ ድል አኩሪ ታሪክ ዛሬ ሀገሪቱን ከዘወረው አፋኝ ሥርዓት ጋር በማነፃፀር አምባገነኑን መንግስት አጥብቆ ወቅሷል። "ትናንት በሰንደቅ ዓላማችን ስር ተሰልፈው፣ ክብሯንና ሉዓላዊነቷን ያስከበሩ ጀግኖች እና ‘ክተት’ ተብሎ በአድዋ ተራሮች ላይ የዘመተው ሕዝባችን በደምና በአጥንቱ ሀገር አቁሞልናል፤ ይሁን እንጂ ዛሬ ሀገራችን በገጠማት ፀረ-ሕዝብ እና አምባገነናዊ ሥርዓት ምክንያት የሰው ልጅ ነፃነትና ክብር እየተረገጠ ይገኛል" ሲል አስታውቋል። ይህንን ወቅታዊ በደልና ጭቆና ለመቀልበስ ድርጅቱ (አፋብን) በቁርጠኝነትና በቆራጥነት እየታገለ እንደሚገኝ አረጋግጧል። አክሎም፡ "ሰብአዊነትን፣ ክብርንና ነፃነትን ለሕዝባችን ለማስፈን እንዲሁም በአባቶቻችን ደምና አጥንት የቆመችው ሀገራችን አንድነቷ ተጠብቆ እና ተከብራ እንድትኖር የበኩላችንን ታሪካዊ ኃላፊነት እንወጣለን"* ሲል ቃሉን አድሷል። በመጨረሻም መግለጫው፣ ይህ ታሪካዊ እውቅና እንዲሰጥ ለሰሩ የሕግ አውጪዎች፣ ድጋፍ ላደረጉ የማኅበረሰብ አባላት እና የአድዋ ታሪክ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሻገረ እንዲቀጥል ለደከሙ ወገኖች ሁሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናውን አቅርቧል። የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

photo content

የሰኔ 08/2017 ዓ/ም ክቡር ሰማዕቱ ሃምሳ አለቃ አደም አሊ (አባ ናደው) በአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 71ኛ እና 33ተኛ ክፍለ ጦር ሰራዊት ታስቦ ውሏል:: ክብርና ዘላለማዊ
+6
የሰኔ 08/2017 ዓ/ም ክቡር ሰማዕቱ ሃምሳ አለቃ አደም አሊ (አባ ናደው) በአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 71ኛ እና 33ተኛ ክፍለ ጦር ሰራዊት ታስቦ ውሏል:: ክብርና ዘላለማዊ ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት!! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

#ሰበር- ካምፑና ፖሊስ ጣቢያው ወደመ! #ፋኖ የከባድ መሣሪያ ጥቃት ጀመረ! #ቁስለኛ ወታደሮች ደሴ ገቡ! https://youtu.be/lPlPqrDpiH8?si=X6cw88xv3ycnfgH3

በፋኖ አስተማማኝ ጥበቃና አስተዳደር የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ማጠቃለያ ፈተና በሰላም መጀመሩ ተገለፀ! የብልፅግና መዋቅር በፈረሰባቸው ቀጠናዎች የፋኖ መንግስት የትምህርት ሂደቱን በበላይነት እያስፈጸመ መሆኑ ታውቋል። በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ በተቆጣጠራቸውና በበላይነት በሚያስተዳድራቸው ቀጠናዎች፣ ዛሬ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም መጀመር የነበረበት የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ማጠቃለያ ፈተና ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም መጀመሩ ተነግሯል። የፋኖ አርበኞች የፈተና ቁሳቁስ ስርጭትን፣ የተማሪዎችንና የመምህራንን ደህንነት በበላይነት እያስጠበቁ እንደሚገኙ የተገለጸ ሲሆን፤ ይህም ፋኖ ለአንገብጋቢው የትውልድ ግንባታና ትምህርት የሰጠውን የላቀ ትኩረትና የመንግስትነቱን እምቅ አቅም ያሳየበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሆኗል። በአፋብን በላይ ዘለቀ ዕዝ ሜጀር ጀኔራል ውብአንተ አባተ ኮር ስር የምትገኘው ታላቋ ጉና ክፍለ ጦር በምትንቀሳቀስበት ቀጠና፣ የፈተና ጣቢያዎች ሙሉ ቁሳቁስ በክፍለ ጦሩ አርበኞች ሙሉ እጀባና ጥበቃ ተደርጎላቸው ያለምንም የፀጥታ ችግር በየጣቢያው ተሰራጭተዋል። ፋኖ ቀደም ሲል በትምህርት ገበታ ላይ የነበረውን እገዳ አንስቶ ትምህርት እንዲጀመር መፍቀዱ የሚታወስ ሲሆን፤ ፈተናው ከመጀመሩ በፊት የነበሩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችም ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው መቆየታቸው ተነግሯል። ይህ የዘንድሮው የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ያለምንም እንከን እንዲጀመር ጀግናው ፋኖ የአንበሳውን ድርሻ አበርክቷል። ስኬቱ ሊመዘገብ የቻለው ፋኖ ከተማሪዎች፣ ከወላጆች እና ከመምህራን ጋራ ባለፉት ተከታታይ ወራቶች ባካሄዳቸው ውጤታማ ውይይቶች መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ተማሪዎች በስነ-ልቦና ሳይሸበሩ፣ በትምህርት ገበታቸው ላይ ብቻ ትኩረት አድርገው ውጤታማ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ረገድ አይተኬ ሚና በመጫዎቹ ነውት ተብሏል። በአሁኑ ሰዓት በሜጀር ጄነራል ውብአንተ አባተ ኮር ጉና ክፍለ ጦር የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ መምህር አርበኛ አማረ እንደግ እየተመራ፤ ሁሉም ስራ አስፈፃሚ፣ በስሯ ያሉት ከአምስት ብርጌዶች እና የወረዳው የፋኖ ጊዜያዊ መንግስት የተውጣጣ ግብረ ኃይል የስራ ስምሪት በመስጠት ፈተናው በሰላም እየተሰጠ ይገኛል። ይህ የፀጥታና የክትትል ስራ ፈተናው ሙሉ በሙሉ እስኪጠናቀቅ ድረስ የሚቀጥል ሲሆን፣ በተፈጠረላቸው አስተማማኝ ሰላም ምክንያት ተማሪዎች አቅማቸውን እንዲያሳዩ ትልቅ በር ተከፍቶላቸዋል። በተመሳሳይ ዜና፣ በአፋብን ጎንደር በላይ ዕዝ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር በሚያስተዳድራቸው 5 ወረዳዎች በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የ6ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተናን በይፋ አስጀምሯል። ፈተናው ከመጀመሩ በፊት የነበሩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በሙሉ በፋኖ ፀጥታ አስከባሪነትና አስተባባሪነት ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቁ ሲሆን፤ ከዛሬ ሰኔ 08/2018 ዓ/ም ጀምሮ ኮሩ በሚያስተዳድራቸው በሁሉም የፈተና ጣቢያዎች ፈተናው በተሳካ ሁኔታ እየተሰጠ እንደሚገኝ ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያረጋግጣል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የብልፅግና መንግስት የጸጥታ መዋቅር በፈረሰባቸው በእነዚህ ሰፊ ቀጠናዎች፣ የፋኖ ጊዜያዊ መስተዳድሮች ማህበራዊ አገልግሎቶችን በተለይም የትምህርት ሂደቱን ያለ ምንም መስተጓጎል ማስቀጠላቸው፤ ህዝቡ በፋኖ መዋቅር ላይ ያለውን አመኔታ ይበልጥ እንዳጠናከረው የመረብ ሚዲያ የግንባር ጋዜጠኞች ለማረጋገጥ ችለዋል። መረበኞች ነን መረጃ አጥማጆች! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

በምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር 12ኛ ክፍለጦር 6ኛ ሻለቃ ቃኝ በሰዋ ሜዳ በአገዛዙ ላይ የማያዳግም እርምጃ ወሰዱ። ጀብደኛው የ102ኛ ኮር 12ኛ ክፍለጦር የሰራዊት አባላት ዛሬ ሰኔ 8/2018ዓ/ም በሰ
በምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር 12ኛ ክፍለጦር 6ኛ ሻለቃ ቃኝ በሰዋ ሜዳ በአገዛዙ ላይ የማያዳግም እርምጃ ወሰዱ። ጀብደኛው የ102ኛ ኮር 12ኛ ክፍለጦር የሰራዊት አባላት ዛሬ ሰኔ 8/2018ዓ/ም በሰሜን ወሎ ዞን በጉባላፍቶ ወረዳ ከወልዲያ ከተማ በቅርብ ርቀት ልዩ ስሙ ሰዋ ሜዳ በተባለ አካባቢ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ የደፈጣ ጥቃት ፈፀሙ ። ጥቃቱን የፈፀሙት የ12ኛ ክፍለጦር  የሰራዊት አባላት ወልዲያ ከተማ መነሻውን በማድረግ የአገዛዙን የሰራዊት እሬሽን በመጫን ወደ ሰዋ ሜዳ ቀበሌ  በመጓዝ ላይ በነበረ ኮንቦይ ላይ በወሰዱት ማጥቃት 8 የመከላከያ ሰራዊት ሲገደሉ 15 የሚሆኑት ደግሞ ወልዲያ ሆስፒታል መግባታቸውን የውስጥ መረጃዎቻችን ገልፀውልናል። ጨፍጫፊውና እብሪተኛው የብልፅግና አገዛዝ በመላው አማራ ህዝብ በደረሰበት የፖለቲካ ኪሳራ ከፍተኛ ውዝግብ ላይ መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም ለሴቴና ህፃናት እንድሁም ከተማ ለሚኖሩ አዛውንት ሲቪሊያን የማይጨነቀውና በደረሰበት ምት የተወዛገበው አገዛዙ  አንድ የ9 አመት ልጅና አንድ አዛውንት ሽማግሌ በሁለት ንፁሀን ላይ ነፃ እርምጃ በመውሰድ በግፍ መሩሰኑ ታውቋል። ምንጭ፦በአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

#ሰበር- ካምፑና ፖሊስ ጣቢያው ወደመ! #ፋኖ የከባድ መሣሪያ ጥቃት ጀመረ! #ቁስለኛ ወታደሮች ደሴ ገቡ! https://youtu.be/lPlPqrDpiH8?si=X6cw88xv3ycnfgH3

መሀመድ ቢሆነኝ ኮር አስቴ ጎማ ተራራ ክ/ጦር በመኮይ ከተማ በሚገኙ የብልፅግና ኃይሎች ላይ መብረቃዊ ጥቃት አደረሰ! በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ በመሃመድ ቢሆነኝ ኮር ስር የሚንቀሳቀ
መሀመድ ቢሆነኝ ኮር አስቴ ጎማ ተራራ ክ/ጦር በመኮይ ከተማ በሚገኙ የብልፅግና ኃይሎች ላይ መብረቃዊ ጥቃት አደረሰ! በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ በመሃመድ ቢሆነኝ ኮር ስር የሚንቀሳቀሰው ጀግናው የአስቴጎማ ተራራ ክፍለጦር፣ በይፋት አውራጃ አንፆኪያ ገምዛ ወረዳ መኮይ ከተማ መደበቂያቸውን ባደረጉ የብልፅግና የካድሬ፣ የሚሊሻ፣ የፖሊስና የኮማንዶ ስብስቦች ላይ የተቀናጀ መብረቃዊ ጥቃት ተፈፀመ። ክፍለጦሩ በከተማዋ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ላይ ባደረገው የሚካናይዝድ ሞርተር ጥቃት፣ የፀረ-አማራው የብልፅግና ስብስብ አባላት የሆኑ 10 ታጣቂዎችን ድባቅ መምታት ችሏል። ከደረሰባቸው ከፍተኛ ጉዳት የተነሳም 4ቱ በአሁኑ ወቅት በደሴ ሪፈራል ሆስፒታል በጽኑ ሕክምና ላይ እንደሚገኙ ታውቋል። የብልፅግና አስተዳደር ላለፉት ሦስት ዓመታት ወደ ወታደራዊ ካምፕነት ቀይሮት በነበረው በመኮይ ከተማ የሙያና ቴክኒክ ማሰልጠኛ ኮሌጅ ውስጥ መሽጎ በነበረው የልዩ ዘመቻ አየር ወለድ ኮማንዶ ሰራዊት ላይም ወታደራዊ  ኢላማውን በጠበቀ መልኩ የሞርተር መብረቃዊ ጥቃት ተፈጽሟል። በዚህ ጥቃት ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ በርካታ የአገዛዙ ታጣቂዎች ላይ ከፍተኛ የአካልና የቁሳቁስ ጉዳት መድረሱ ተረጋግጧል። ምንጭ፦ በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

እጅግ በጣም ሀቀኛና ጀግና፣ ታማኝና አማኝ፣ ፅኑና ከአላማው ዝንፍ የማይል፣ሩህሩህና ቸር፣ ፍትህ አዋቂና አስተዋይ መሪ እንዲሁም አልሞ ተኳሽ ነው ይሉታል አብረውት ከምሽግ ውሎው የሚያድሩ ጓዶቹ። ሳጅን አደም "አባ ናደው" የሚለውን ስያም ያገኘው የጎላሌውን ምሽግ በሰበሩበት ወቅት ነበር። መረብ ሚዲያ ከሁለት ዓመታት በፊት ስለ ጎላሌው ምሽግ መሰበር ዘግቦት የነበረውን መለስ ብለን እናስታውሳችሁ.... ወቅቱ ወርሃ መጋቢት 2016 ዓ/ም ነበር። በደቡብ ወሎ ዞን ወግዲ ወረዳ ጎረንጅ ቀጠና ልዩ ስሙ ጎላሌ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ። ከወግዲ ወረዳ ወደ ጎረንጅ ያቀናው የአገዛዙ ጥምር ጦር፣ በጎረንጅ ቀጠና እልህ አስጨራሽ ውጊያ ሲያካሂድ አርፍዶ ከሰዓት ከባድ ዶፍ ያዘለ ዝናብ መዝነብ በመጀመሩ ውጊያው ጋብ አለ። ዝናቡ አላቆመም ዶፍና ውሽንፍር የቀላቀለ ዝናብ እየዘነበ ነው። ጊዜው እየመሸ ነበር። ጀንበር ልግባ ልግባ እያለች በምትጣደፍበት በዚህ ቅጽበት አባ ናደው እስኪ በጎቼን ላሙቅ ብሎ ቦምብ በሽርጡ ቋጥሮ ከተቀመጠበት ብድግ አለ። ጓዶቹ ዝናቡ በረድ እስከሚል መታገስ እንዳለባቸው ደጋግመው ቢነግሩትም አሻፈፈኝ አለ። "ሰዓቷ የወንድ ልጅ ሰዓት ናት" ነበር አጅሬ ምላሹ። "አትከተሉኝ።ታሪክ ሰርቼ አስደምማችኋለሁ" ብሎ እግሮቹ በቅርብ ርቀት ወደ ሚገኘው የጠላት ምሽግ መራመድ ጀመሩ።ማምረሩን ያወቁ የተወሰኑ ጓዷቹ በቅርብ ርቀት ተከተሉት። ሳጅን አደም ያን ከባድ ዶፍና ውሽንፍር ዝናብ መሀል ለመሀል ሰንጥቆ የጠላት ምሽግ ላይ ሲደርስ በሽርጡ ታቅፎ ይዞት የነበረውን ቦምብ በግራ እጁ እያነሳ፡ ቀለበቱን በጥርሱ እየነቀለ አከታትሎ ይወረውር ጀመር። ቀን ላይ ሲዘንብ የዋለው ዝናብ ለብርድ የሰጣቸው የጥምር ጦር አባላት ሙቀት በሙቀት ሆኑ። ምሽጉ በዋይታ ተዋጠ። የድረሱልኝ ተማፅኖ የሚያቀርቡና የጣር ድምፅ  የሚያሰሙ የመከላከያና የአድማ ብተና እንዲሁም ሚሊሻ አባላት ስፍር ቁጥር አልነበራቸውም። ገሚሱ ጥሩ ባለሙያ እንደሰራችው ፍርፍር አካሉ ተቆራርሷል።ገሚሱ ደግሞ "ወይኔ እግሬ፡ ወይኔ እግሬ" ይላል። ገሚሱ ደግሞ "ማሎ፡ ማሎ፡ ሀደኮ፡ ሀደኮ" ይላል። ገሚሱ በዛ ዝናብ መሀል "ውሃ ስጡኝ? ውሃ ስጡኝ?" ይላል። አባ ናደው በሽርጡ ታቅፎ የያዘውን ቦምብ መወርወሩን አላቆመም። እየመረጠ ቦምቡ ወዳልነካው የምሽጉ ስፍራ ይወረውራል። ከሰማዩ ጉርምርምታ ጋር ተዳምሮ በቦምቡ ፍንዳታ ምድር ቃጤ ሆነች። ያሁሉ የወታደሩ ዋይታና የጣር ድምፅ ከግማሽ ሰዓት በኋላ ፀጥ እረጭ አለ።ሰማዩም ከነ ሳጅን አደም አሊ ጋር ምክር እንዳለው ሁሉ መስኮቱን ጥርቅም አድርጎ ዘጋ። ያ አስፈሪው የጎለሌ ምሽግ፣ መከላከያ ሰራዊቱ ለወራት ያህል በግሬደር ታግዞ የሰራው የጎላሌው የኮንክሪት ምሽግ በነሳጅን አደም አሊና በጓዶቹ ክንድ ተደረመሰ። በእለቱ በስፍራው የነበሩ ሰዎች በምሽጉ ውስጥ የሬሳ ክምር የሬሳ ነዶ ነው ያየነው ሲሉ የአይን ምስክርነታቸውን ሰተዋል። ከዚህን ዕለት ጀምሮ ሳጅን አደም አሊ አባ ናደው ተባለ።የለጋምቦው አንበሳ እና የገነቴ ጌጥ የሆነው አባ ናደው እጅግ በጣም ደፋር በዛው ልክ ደግሞ እሩህሩህ ነው ይሉታል የትግል አጋሮቹ። የጎላሌን ምሽግ ደርምሶ ታሪክ የሰራው አባ ናደው በጀግንነት እና በወታደራዊ ጥበቡ የተመሰከረለት ነው። ይህ ጀግና ሰኔ 08/2017 ዓ/ም ስለ አማራ ሕዝብ ሲል የክብር መስዋዕትነትን ከተቀበለ ዛሬ ድፍን አንድ ዓመት ሞልቶታል። ክብርና ዘላለማዊ ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት!! መረበኞች ነን መረጃ አጥማጆች! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

photo content

ፋኖ ከውጊያው ጎንለጎን በሚወስደው የስቦ ማስከዳት እርምጃ ውጤታማ ድል እያገኘ መሆኑ ታውቋል። ከክላሽ ጀምሮ ትጥቅ ደርበው ያነገቡ ወታደሮች ፋኖን ተቀላቅለዋል። አራት ጥቁር ክላሽና 600 የክላሽ ተ
+1
ፋኖ ከውጊያው ጎንለጎን በሚወስደው የስቦ ማስከዳት እርምጃ ውጤታማ ድል እያገኘ መሆኑ ታውቋል። ከክላሽ ጀምሮ ትጥቅ ደርበው ያነገቡ ወታደሮች ፋኖን ተቀላቅለዋል። አራት ጥቁር ክላሽና 600 የክላሽ ተተኳሽ እንዲሁም አራት ቦምብና ሌሎች ወታደራዊ ቁሣቁሶችን የያዙ ሁለት የብልፅግና መከላከያ ሰራዊት አባላት ዛሬ ሰኔ 08/2018 ዓ/ም በምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር አደም አሊ(አባናደው) ክፍለጦርን ተቀላቅለዋል። የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

ተጠናክሮ በቀጠለው የብልፅግናው ሰራዊት ፍልሰት ዛሬም አሥር አለቃ ገለታ አብዲሳ የተባለው የ103ኛ ኮማንዶ ክፍለጦር ጋንታ መሪ አንድ ዘመናዊ ስናይፐር በመያዝ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው
+1
ተጠናክሮ በቀጠለው የብልፅግናው ሰራዊት ፍልሰት ዛሬም አሥር አለቃ ገለታ አብዲሳ የተባለው የ103ኛ ኮማንዶ ክፍለጦር ጋንታ መሪ አንድ ዘመናዊ ስናይፐር በመያዝ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር የ7ለ70 ክፍለጦርን መቀላቀሉን ኮሩ በላከው መረጃ አስታውቋል። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ያወጣውን የምህረት አዋጅ ተቀብሎ ከሁለት ወር በፊት ፋኖን በተቀላቀለው የትግል ጓደኛው አማካኝነት ስለ ፋኖ እውነተኛ ማንነት የተነገረው የኦሮሞ ብሔር ተወላጁ ፲አለቃ ገለታ አብዲሳ አንድ ዘመናዊ ስናይፐር ከ95 በላይ ተተኳሽ በመያዝ ከነ ሙሉ ትጥቁ ፋኖን ሲቀላቀል በአፄ አምደ ፅዮን ኮር 7ለ70 ክፍለ ጦር አመራሮች ስለተደረገት አቀባበል ላቅ ያለ ምስጋናውን ያቀረበ ሲሆን ወቅታዊ የአገዛዙ ሰራዊት ግዳጅን የመፈፀም አቅሙ እንደተዳከመና በሰራዊቱ ውስጥ ከፍተኛ የእርስ በእርስ መከፋፈል መፈጠሩን ገልጿል። ምንጭ፦በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

ምኒልክ ዕዝ በወሰደው የስቦ ማስከዳት እርምጃ በብልፅግና መከላከያ ሠራዊት ውስጥ አመራርና  አባል የሆኑ ወታደሮችን ከነ ሙሉ ትጥቃቸው መቀበሉን አስትወቀ! መነሻቸውን ከላስታ ወረዳ ብልባላ ከተማ እና ከዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን አዚላ ያደረጉ ሁለት የመከላከያ አመራሮችና ሁለት መሠረታዊ ወታደሮች በድምሩ አራት የአገዛዙ ሰራዊት አባላት አገዛዙን በመቃወም ሰኔ 08 ቀን 2018 ዓ/ም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር 30ኛ ክፍለ ጦር ቃኝዎችን ተቀላቅለዋል። የተቀላቀሉ አባላትም:- 1. ሃምሳ አለቃ መኩሪያው አባትይሁን ከ38ኛ ክፍለ ጦር መሐንዲስ 2. አስር አለቃ ይረፍ ደምሴ ከ38ኛ ክፍለ ጦር መሐንዲስ 3. ናትናኤል አቤል የሻለቃ ኦርዲናንስ 4. መሰረታዊ ወታደር ደረጀ አሸናፊ ሲሆኑ    👉 አንድ ጥቁር ስናይፐር    👉 ሦስት ጥቁር ክላሽ    👉 አንድ ሀይተር መገናኛ    👉 ሦስት የስናይፐር ካዝና    👉 አራት የደረትና የወገብ ትጥቅ    👉 420 የክላሽ ተተኳሽ    👉 56 የስናይፐር ተተኳሽ    👉 ስምንት የእጅ ቦምብ በመያዝ ተቀላቅለዋል። የመከላከያ አባላቱም ፋኖን ሲቀላቀሉ የ30ኛ ክፍለ ጦር ፋኖ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ደማቅ አቀባበል ያደረጉላቸው ሲሆን በተደረገላቸው አቀባበልም ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል። አባላቱ አያይዘውም የብልፅግና መንግስት ሃገራችን ኢትዮጵያን ወደ መቀመቅ እየከተታት መሆኑን ዘግይተን ብንረዳውም አሁንም አልረፈደምና የአማራን ህዝብ ለመካስ ብሎም ኢትዮጵያን ከመፍረስ ለማዳን ከፋኖ ጎን ሆነን የስርዓቱን ግብዓተ መሬት እናፋጥናለን ሲሉ ቃላቸውን ሰጥተዋል። በአንድ ወር ጊዜ ውስጥም በአውደ ውጊያ ከተማረከው ውጭ ሦስት ጥቁር ስናይፐር፣ ከ20 በላይ ጥቁር ክላሽና ሌሎች ትጥቆች ከመከላከያ በመውጣት ወደ 30ኛ ክፍለ ጦር ካዝና ገቢ ሆኗል ሲል የ303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል ። የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24