fa
Feedback
Mereb Media መረብ ሚዲያ

Mereb Media መረብ ሚዲያ

رفتن به کانال در Telegram

Welcome to our Channel, Mereb Media - መረብ ሚዲያ We provide daily reliable and trusted information. መረጃ ለማድረስ፦ @MerebMereb

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Mereb Media መረብ ሚዲያ

کانال Mereb Media መረብ ሚዲያ (@merebmedia24) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 20 004 مشترک است و جایگاه 11 677 را در دسته اخبار و رسانه‌ها و رتبه 1 697 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 20 004 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 30 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -381 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -7 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 19.15% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.74% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 832 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 3 351 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 23 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Welcome to our Channel, Mereb Media - መረብ ሚዲያ We provide daily reliable and trusted information. መረጃ ለማድረስ፦ @MerebMereb

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 31 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانه‌ها تبدیل کرده‌اند.

20 004
مشترکین
-724 ساعت
+127 روز
-38130 روز
آرشیو پست ها
#ውሳኟ ከተማ ተያዘች/ 78 ጦር አለቀ! #19 ክላሽ ተገኘ/ ሆስፒታሉ በቁስለኛ ሞላ! #5 ከተሞች በቁጥጥር ስር ዋሉ! https://www.youtube.com/watch?v=V_wfxFoGSMghttps://www.youtube.com/watch?v=V_wfxFoGSMg

105ኛ ንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር ጥልቅ ግምገማ ካካሄደ በኋላ የኮር ስያሜና አዳዲስ የአመራር ምደባ አደረገ! በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር በስሩ የሚገኙ የክፍለ ጦር አመራሮችን
+1
105ኛ ንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር ጥልቅ ግምገማ ካካሄደ በኋላ የኮር ስያሜና አዳዲስ የአመራር ምደባ አደረገ! በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር በስሩ የሚገኙ የክፍለ ጦር አመራሮችን ጨምሮ ለተከታታይ አምስት ቀናት የድርጅቱ እና የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ውጤታማ ጥልቅ ግምገማና የተሳካ ሪፎርም ማካሄዱን በሕዝብ ግንኙነት ክፍሉ በኩል ለመረብ ሚዲያ በላከው መረጃ አስታውቋል። ከግምገማ መድረኩ በኋላ፡ የቀድሞው የ105ኛ ኮር የኮሩን የወትሮው ስያሜን ጨምሮ የአመራር ምደባውን በማስተካከል የተለያዩ  ኃላፊነኖችን ሰጥቷል። ኮሩ ከዛሬ ሃምሌ 24/2018 ዓ/ም ጀምሮ ከ105ኛ ወደ 15ኛ ኮር የስያሜ ለውጥ ያደረገ ሲሆን፡ የሰብሳቢነቱን ሚና በአርበኛ እንድሪስ ይማም ተክቷል። መረበኞች ነን መረጃ አጥማጆች! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

እየገቡ ነው! / ጥብቅ ትዕዛዝ ተላልፏል! ፋኖ በየከተሞች በሚገባበት ወቅት በሕዝቡ ላይ ምንም አይነት የሰብአዊና የንብረት ጉዳት እንዳይደርስ ልዩ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት የሚያዝ መመሪያ ተላለፈ። ፋኖ ወደ ትላልቅ ከተሞች ሲገባ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ ነው መመሪያው የሚያትተው። ፋኖ መንግሥት የመሆን አቅሙን ማሳየት ያለበት ሕዝብን በኃላፊነት ሲመራ እንደሆነ የገለፁት የአፋብን ምኒልክ ዕዝ ሰብሳቢ ፊታውራሪ ድርሣን ብርሃኔ፡ ታጋዮች ወደ ከተሞች በሚገቡበት ወቅት ከበቀልና ከንብረት ወረሳ በመታቀብ የዜጎችን ሰላምና ደኅንነት በጥብቅ እንዲጠብቁ የሚያስገነዝብ ወታደራዊና ፖለቲካዊ መመሪያ አስተላልፈዋል። ሙሉ መረጃውን በዚህ ተመልከቱ👉https://www.youtube.com/watch?v=V_wfxFoGSMghttps://www.youtube.com/watch?v=V_wfxFoGSMg

አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነዉ ኮር በአገዛዙ ወታደር ላይ የማያዳግም እርምጃ በመዉሰድ ድልን ተቀዳጁ! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አፋብን ወሎ ቤተ -አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነዉ ኮር  በአገዛዙ ወታደር ላይ የማያዳግም እርምጃ በመዉሰድ ድልን ተቀዳጁ! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አፋብን ወሎ ቤተ -አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር አካል የሆነው 14ኛ (ጀኔራል ሃይሉ ከበደ) ክፍለ ጦር በዋግህምራ ዞን ጋዝጊብላ ወረዳ  09 ቀበሌ ላልኪው የ አፓርታይዱ አብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ  ወታደር ላይ በተሰላና በታቀደ የተጠናከረ ሽምቅ ውጊያ እና ተስቦ በመግባት ከተኛበት ምሽግ ላይ የማያዳግም እርምጃ በመውሰድ ከፍተኛ ድል ተቀዳጅተዋል። የሽምቅ ውጊው ሐምሌ 23ለ24  ሃሙስ ለአርብ  ከሌሊቱ 6:00 ሰዓት እስከ ንጋት 11:00 ሰዓት የተጠናከረ ሲሆን ልዩ ቦታው ገበያው ሰፈር ወይም በተለምዶ ጊወርጊስ ትኩ ተብሎ ከሚጠራው ተራራ ላይ መሽጎ የነበረውን የጥላት ሃይል በሽምቅ ከማጥቃት ሙሉ በሙሉ ምሽጉን በማስለቀቅ በአገዛዙ ላይ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ አድርሰውበታል ። በተጠናከረው የሽምቅ ውጊያ ከ17በላይ የጥላት ሃይል ሲደመሰስ 4 ምርኮኛ፣9ጥቁር ክላሽ ፣1500 የብሬን ተተኳሽ፣725 የክላሽ ተተኴሽ ፣2 ኤፍዋን የእጅ ቦንብ ፣አንድ የወገብና አንድ የደረት ትጥቅ ተማርኳል ሲል የ303ኛ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መረጃውን አድርሷል። ምንጭ፦በአፋብን ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

በምሥራቅ ወለጋ በተደረገ ውጊያ ፋኖ 78 የአገዛዙን ወታደሮችን ሙትና ቁስለኛ በማድረግ አንጸባራቂ ድል መቀዳጀቱን አስታወቀ! በምሥራቅ ወለጋ ጊዳ ኪረሙ ወረዳ በነበረው አውደ ውጊያ የጎላ ወታደራዊ ስ
በምሥራቅ ወለጋ በተደረገ ውጊያ ፋኖ 78 የአገዛዙን ወታደሮችን ሙትና ቁስለኛ በማድረግ አንጸባራቂ ድል መቀዳጀቱን አስታወቀ! በምሥራቅ ወለጋ ጊዳ ኪረሙ ወረዳ በነበረው አውደ ውጊያ የጎላ ወታደራዊ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያላትን ቆፍቆፌ ከተማን የተቆጣጠሩት አርበኞቹ፡ አዲስ ዓለም ከተማን ጨምሮ በወረዳው ቦቃ፣ ነጭሎ እና ወዴሳ ዲማ የተባሉ ሦስት ቀበሌዎችን በቁጥጥራቸው ስር ማዋላቸው ተሰምቷል። ሙሉ መረጃውን በዚህ ተመልከቱ👉https://www.youtube.com/watch?v=V_wfxFoGSMghttps://www.youtube.com/watch?v=V_wfxFoGSMg

አሳዛኝ ዜና! የአርበኛ ዝናቡ ልንገረው ቤተሰቦች መኖሪያ ቤት በፈረስ ቤት ከተማ ተቃጠለ! የአማራ ህዝብን በመጨፍጨፍ፣ ሀብትና ንብረቱን ማውደም የዘወትር መገለጫው የሆነውና ተስፋ የቆረጠው የአገዛዙ ቅጥረኛ ሰራዊት፣ የአርበኛ ዝናቡ ልንገረው ወላጆችን መኖሪያ ቤት በፈረስ ቤት ከተማ ማቃጠሉ ታውቋል። በራሱ ህዝብ ላይ ታንክ፣መድፍና አየር ኃይል አሰማርቶ ንፁሃንን የሚጨፈጭፈው፣ የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ፣ መሀመድ ተሰማ ለምዕራብ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ እድሚያለም ለሚባል ቅጥረኛ ግለሰብ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት መኖሪያ ቤቱ መቃጠሉን ከመረጃ ምንጮቻችን ለማወቅ ተችሏል። በቃጠሎው የደጋ ዳሞት ወረዳ፣ የአገዛዙ ቅጥረኛ ካድሬዎችና የሚሊሻ አባላት እንደተሳተፉ የዓይን እማኞች ገልጸዋል። በቤቱ ውስጥ ይገኙ የነበሩ ቁሳቁሶችን ጨምሮ ሌሎች ጠቃሚ ንብረቶች በእሳቱ መውደማቸው ታውቋል። በፈረስ ቤት ከተማ፣ ቀበሌ 02 ይገኝ የነበረው ይህ መኖሪያ ቤት፣ የአርበኛው ወላጆች ኑሯቸውን መስርተው፣ማኀበራዊ ህይዎታቸውን ይመሩበት እንደነበረ ተገልጿል። ላለፉት 3 አመታት በተለያዩ የአማራ ቀጠናዎች ከፋኖ ጋራ ፊት ለፊት ተዋግቶ ማሸንፍ ያልቻለው አገዛዙ፣ የበቀል ዱላውን የሚያሳርፈው ንጹሃን ዜጎችን በመገድልና ሀብት ንብረታቸውን በማውደም እንደሆነ ይታወቃል። በአርበኛ ዝናቡ ልንገረው ወላጆች ቤት የደረሰው ቃጠሎ የዚህ አንድ አካል ነው። ከውጊያ ቀጠና ውጭ የሚገኙ የሰላማዊ ዜጎችን ሀብትና ንብረት ማውደም፣ በዓለም አቀፉ የጄኔቫ የጦር ስምምነት( Geneva War Convention) መሰረት በጦር ወንጀልነት ሊያስጠይቅ የሚችል መሆኑንን በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የህግ ባለሙያዎች ገልጸዋል። ቃጠሎውን አስመልክቶ፣ ፈረስ ቤት ከተማን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች በስልክና በአካል ያነጋገርናቸው ሰላማዊ ዘጌጎች ድርጊቱን በጥብቅ አውግዘውታል። አንድ አገር እመራለሁ ከሚል አካል ፍፁም የማይጠበቅ "ወራዳ ተግባር" ሲሉ ኮንነው፣ አገዛዙ ምን ያህል የመንግስትነት ቁመናው እንዳጣና ተስፋ እንደቆረጠ ማሳያ ነው ሲሉ ጨምረው ገልጸዋል። አገዛዙ በጎንደር፣ በወሎ፣ በሸዋና በጎጃም ላለፉት 3 ዓመታት የተለያዩ የፋኖ ቤተሰቦችን ሀብት ንብረት ሲያወድሙ እንደቆዩ ይታወቃል። ምንጭ፦በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

photo content
+3

#ውሳኟ ከተማ ተያዘች/ 78 ጦር አለቀ! #19 ክላሽ ተገኘ/ ሆስፒታሉ በቁስለኛ ሞላ! #5 ከተሞች በቁጥጥር ስር ዋሉ! https://www.youtube.com/watch?v=V_wfxFoGSMghttps://www.youtube.com/watch?v=V_wfxFoGSMg

ሰበር!....ዛሬም ተደገመ! በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር ስር የአረንዛው ጎንቻ ሬጅመንት አርበኞች በግንደወይን ከተማ አቅራቢያ ትግዳር እና እነሴ ቆል ተብለው በሚጠሩ አከባቢዎች
ሰበር!....ዛሬም ተደገመ! በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር ስር የአረንዛው ጎንቻ ሬጅመንት አርበኞች በግንደወይን ከተማ አቅራቢያ ትግዳር እና እነሴ ቆል ተብለው በሚጠሩ አከባቢዎች ላይ ሰፍሮ የነበረውን የጠላት ብልፅግና ወታደራዊ ኃይል ሙሉ ለመሉ በመደምሰስ አኩሪ ገድል መፈፀማቸው ድርጅቱ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያው በኩል አስታውቋል። በዝርዝር እንመለስበታለን። መረበኞች ነን መረጃ አጥማጆች! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

#70 ጦር ሲያልቅ 79 ክላሽ ተያዘ! #ከተማዋን ሰንጥቀው ገቡ/አዛዡ ተመታ! #አዲስ ዲሽቃና ብሬይ ተይዟል! https://youtu.be/nzjVo20Uw1k?si=wJeqGuVoElagQqij

የብልፅግናው አገዛዝ በገዳማትና በአብያተክርስቲያና ላይ እየፈፀመ ያለውን የድሮን ጥቃትና በጥቃቱ እየተገደሉ ያሉ ንፁኋኖችን ተከትሎ ከባድ ውግዘት ከየአቅጣጫው እየተሰነዘረበት ይገኛል። የዓለም አብያተ
የብልፅግናው አገዛዝ በገዳማትና በአብያተክርስቲያና ላይ እየፈፀመ ያለውን የድሮን ጥቃትና በጥቃቱ እየተገደሉ ያሉ ንፁኋኖችን ተከትሎ ከባድ ውግዘት ከየአቅጣጫው እየተሰነዘረበት ይገኛል። የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል በአማራ ክልል በሲቪሎችና በአምልኮ ቦታዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች "እጅግ የሚረብሹና ፈጽሞ ተቀባይነት የሌላቸው ናቸው" ሲል በጽኑ አውግዞ፡ በጥቃቶቹ ላይ አስቸኳይና ገለልተኛ ምርመራ እንዲደረግ ጥሪ አቅርቧል። ሙሉ መረጃውን ተመልከቱ👉https://www.youtube.com/watch?v=FlrMZiFurLM

በእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ሰኞ ገበያ ንዑስ ወረዳ እና ዲቦ ከተማ ተከማችቶ በነበረ የአገዛዙ ኃይል ላይ በተከፈተ ድንገተኛ ጥቃት የሻለቃ አዛዦችና የፖሊስ ኃላፊዎችን ጨምሮ ከ70 በላይ የአገዛዙ ወታ
+1
በእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ሰኞ ገበያ ንዑስ ወረዳ እና ዲቦ ከተማ ተከማችቶ በነበረ የአገዛዙ ኃይል ላይ በተከፈተ ድንገተኛ ጥቃት የሻለቃ አዛዦችና የፖሊስ ኃላፊዎችን ጨምሮ ከ70 በላይ የአገዛዙ ወታደሮች መደምሰሳቸው ታወቀ! በተጋድሎው አንድ አይሱዙ FSR መኪና ከነሙሉ ሎጀስቲክስ፣ አንድ ዶሽቃ፣ ሁለት ብሬን፣ 79 ክላሽንኮቭና አምስት መገናኛ ራዲዮዎች በፋኖ ቁጥጥር ስር ውለዋል። ሙሉ መረጃውን ተመልከቱ👉https://youtu.be/nzjVo20Uw1k?si=wJeqGuVoElagQqij

#70 ጦር ሲያልቅ 79 ክላሽ ተያዘ! #ከተማዋን ሰንጥቀው ገቡ/አዛዡ ተመታ! #አዲስ ዲሽቃና ብሬይ ተይዟል! https://youtu.be/nzjVo20Uw1k?si=wJeqGuVoElagQqij

ቴወድሮስ እዝ 201ኛ ኮር፣ 74 ኛ ክፍለ ጦር ዓባይ ሸለቆ ሻለቃ አስደናቂ ጀብዱ ፈፅማለች። ዛሬ በቀን 22/11/2018 ዓ.ም ንጋት11:00 ሰዓት አካባቢ የአባይ ሸለቆ ተርቦች ሻለቃ መሪውን ከሙሉ ሀይሉ ጋር በመደምሰስ ዲሽቃ፣ ብሬንና በርካታ የነፍስ ወከፍ መሳሪያ በመማረክ እጅግ ድንቅ ስራ ሰርተዋል። በዚህ የአፋብን የወረዳው ጊዜያዊ መንግስት የፀጥታ ሀይልም ጭምር በተሳተፈበት ድንቅ ኦፕሬሽን በእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ሰኞ ገበያ ንዑስ ወረዳ እና ዲቦ ንዑስ ወረዳ ዲቦ ከተማ ተከማችቶ በነበረው የሚሊሻና አድማ በትን እንዲሁም ፖሊስ ላይ የሸለቆው አዳኞች ባልጠበቀው መልኩ ድንገተኛ ጥቃት በመፈፀም ሙትና ቁስለኛ አድርገውታል። በዚህም ሻለቃ መሪውን ጨምሮ 61አድማ ብተና ኃይል፣ 08 ፖሊሶች ሲገደሉ 50 አለቃ ታደሰ የተባለ የሚሊሻ ሀላፊን ጨምሮ በርካታ ሚሊሻ ወደ ላይኛው ተሸኝቷል። 08 ሚሊሻም ቆስሎ ሆስፒታል ገብቷል። 👉 በኦፕሬሽኑ የተገኙ ምርኮዎች:- 1) አንድ ዲሽቃ 2) ሁለት ብሬን 3) 79 ክላሽ 4) 05 መገናኛ ሬዲዮ 5) 02 የድሽቃ ሸንሸል 6) 05 ሳጥን የዲሽቃ ተተኳሽ 7) በርካታ የብሬንና የክላሽ 8) አንድ FSR መኪና ሙሉ ሎጀስቲክ እንደጫነ 👉 ከተገደሉት መካከል:- • ኢ/ር አስናቀ የፖሊስ ፅ/ቤት ኃላፊ፣ • ኢ/ር ወርቁ ------አድማ ብተና ሻለቃ አዛዥ፣ • ነጋሽ-----ድሽቃ ተኳሽ • ጀማል ኡመር ----አድማ ብተና ጋንታ መሪ • ኢንስፔክተር ውዱ -------የፖሊስ አመራር • ኢንስፔክተር ማሞ ----የፖሊስ አመራር ይገኙበታል። ምንጭ፦ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ! የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24 https://t.me/MerebMedia24

photo content
+3

የብልፅግናው አገዛዝ በገዳማትና በአብያተክርስቲያና ላይ እየፈፀመ ያለውን የድሮን ጥቃትና በጥቃቱ እየተገደሉ ያሉ ንፁኋኖችን ተከትሎ ከባድ ውግዘት ከየአቅጣጫው እየተሰነዘረበት ይገኛል። የዓለም አብያተ
የብልፅግናው አገዛዝ በገዳማትና በአብያተክርስቲያና ላይ እየፈፀመ ያለውን የድሮን ጥቃትና በጥቃቱ እየተገደሉ ያሉ ንፁኋኖችን ተከትሎ ከባድ ውግዘት ከየአቅጣጫው እየተሰነዘረበት ይገኛል። የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል በአማራ ክልል በሲቪሎችና በአምልኮ ቦታዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች "እጅግ የሚረብሹና ፈጽሞ ተቀባይነት የሌላቸው ናቸው" ሲል በጽኑ አውግዞ፡ በጥቃቶቹ ላይ አስቸኳይና ገለልተኛ ምርመራ እንዲደረግ ጥሪ አቅርቧል። ሙሉ መረጃውን ተመልከቱ👉https://www.youtube.com/watch?v=FlrMZiFurLM

በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር በመርጡለ ማርያም ሰኞ ገበያ ከድም ሰሳ አምልጠው መረዋ በረሃ የገቡ 14 የ ጠላ ት ሰራዊት አባላትን በአባይ ሸለቆ ሻለቃ ገቢ አድርጓቸዋል። ተጨማሪ
በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር በመርጡለ ማርያም ሰኞ ገበያ ከድም ሰሳ አምልጠው መረዋ በረሃ የገቡ 14 የ ጠላ ት ሰራዊት አባላትን በአባይ ሸለቆ ሻለቃ ገቢ አድርጓቸዋል። ተጨማሪ 13 ክላሽ እና 1 ብሬን ተማርኮ ገቢ ሁኗል። ሙሉ መረጃውን ተመልከቱ👉https://www.youtube.com/watch?v=FlrMZiFurLM

#ሰበር-ዲሽቃ እና ብሬን ተያዘ! #ፖሊስ ጣቢያው ተሰበረ/ታላቅ ድል! #ሙሉ ጦሩ አለቀ/ አዛዦቹ እጅ ሰጡ! https://www.youtube.com/watch?v=FlrMZiFurLM

በብልፅግና መከላከያ ሠራዊት ተቋም ውስጥ በታችኛው እርከን አመራርነት ደረጃ ላይ የነበሩ ሁለት የጦር መኮንኖች መገናኛ ራዲዮዎችንና ጥቁር ክላሽንኮቭ መሣሪያዎችን እንደያዙ ፋኖን መቀላቀላቸው ታወቀ።
በብልፅግና መከላከያ ሠራዊት ተቋም ውስጥ በታችኛው እርከን አመራርነት ደረጃ ላይ የነበሩ ሁለት የጦር መኮንኖች መገናኛ ራዲዮዎችንና ጥቁር ክላሽንኮቭ መሣሪያዎችን እንደያዙ ፋኖን መቀላቀላቸው ታወቀ። የብልፅግናው አገዛዝ ጀምበር እንዳዘቀዘቀችበት የተረዱና ይሄው አገዛዝ በሕዝብ ላይ የሚፈፅመውን ግፍና በደል የተቃዎሙ ወታደሮች ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ከስምሪት ቀጠናቸው በመጥፋት ወደ ፋኖ መጉረፋቸውን ቀጥለዋል። ሙሉ መረጃውን ተመልከቱ👉https://www.youtube.com/watch?v=FlrMZiFurLM

በጎጃም ቀጠና አባይ ሸለቆ አከባቢ በብልፅግና አገዛዝ ጦር ላይ በተከፈተ ድንገተኛና ፈጣን ማጥቃት በርካታ የሠራዊቱ አባላት መደምሰሳቸው ታወቀ። የቴዎድሮስ ዕዝ አርበኞች፡ የጠላት ጦር የተሰነዘረበትን
በጎጃም ቀጠና አባይ ሸለቆ አከባቢ በብልፅግና አገዛዝ ጦር ላይ በተከፈተ ድንገተኛና ፈጣን ማጥቃት በርካታ የሠራዊቱ አባላት መደምሰሳቸው ታወቀ። የቴዎድሮስ ዕዝ አርበኞች፡ የጠላት ጦር የተሰነዘረበትን ጥቃት እንዳይመክት ፈጣን ማጥቃት በመክፈት እንዲሁም ጠላት እንዳይሸሽ ደግሞ ዙሪያ ገባውን አስቀድሞ በመቆለፍ በወሰዱት በዚህ እርምጃ፡ አንድ ዶሽቃ ከነ ሙሉ ተተኳሽ ሳጥኑ፣ ብሬንና በርካታ የነፍስ ወከፍ መሣሪያዎችን ከነተተኳሾቻቸው እጅ ከፈንጅ ማርከው መታጠቃቸው ተሰምቷል። ሙሉ መረጃውን ተመልከቱ👉https://www.youtube.com/watch?v=FlrMZiFurLM