Mereb Media መረብ ሚዲያ
前往频道在 Telegram
Welcome to our Channel, Mereb Media - መረብ ሚዲያ We provide daily reliable and trusted information. መረጃ ለማድረስ፦ @MerebMereb
显示更多📈 Telegram 频道 Mereb Media መረብ ሚዲያ 的分析概览
频道 Mereb Media መረብ ሚዲያ (@merebmedia24) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 20 716 名订阅者,在 新闻与媒体 类别中位列第 11 335,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 623 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 20 716 名订阅者。
根据 14 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -115,过去 24 小时变化为 -12,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 23.97%。内容发布后 24 小时内通常能获得 17.17% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 968 次浏览,首日通常累积 3 558 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 34。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Welcome to our Channel, Mereb Media - መረብ ሚዲያ We provide daily reliable and trusted information. መረጃ ለማድረስ፦ @MerebMereb”
凭借高频更新(最新数据采集于 15 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 新闻与媒体 类别中的关键影响点。
20 716
订阅者
-1224 小时
-1627 天
-11530 天
帖子存档
20 724
ይህ አዲሱ የመረብ ሚዲያ የፌስቡክ ገፅ ነው።ተቀላቀሉን!
https://www.facebook.com/profile.php?id=61590677702737
20 724
+3
በአሜሪካን ሀገር የፔንሴሌቪያ ምክር ቤት ለአድዋ ድል በሰጠው ታሪካዊ እውቅና ላይ የተሰጠ ምስጋና እና የአቋም መግለጫ!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
20 724
በአምሃራ ሳይንት በለጩማ ግንባር በጠላት ከፍተኛ አመራሮች ላይ አስደናቂ የደፈጣ ጥቃት ተፈጸመ!
በመካነ ሰላም ከተማ ለቀናት የሴራ ስብሰባ ሲያካሂዱ የነበሩት የአገዛዙ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች፣ ወደ አምሃራ ሳይንት ወረዳ ለመግባት ሲሞክሩ በንሥሮች በተደገሰላቸው ጥብቅ ደፈጣ ክፉኛ ተመትተዋል።
የአገዛዙ የጦር አመራሮች በመካነ ሰላም የነበራቸውን የግምገማ ስብሰባ ጨርሰው፣ የተለመደ የጥፋት ተልዕኮአቸውን ለመፈጸም በከፍተኛ መኪናዎች ታጅበው እየተንቀሳቀሱ በነበረበት ቅፅበት ጀግኖቹ "በለጩማ" በተባለው ስልታዊ ቦታ ላይ መንገዱን ዘግተው በመጠባበቅ፣ ጠላት ጨርሶ ባልገመተው ሁኔታ መብረቃዊ የደፈጣ ጥቃት ዶግ አመድ አድርገዉታል።
ደፈጣዉም በጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ ስር በ105ኛ ኮር የ71ኛ ክፍለ ጦር አናብስቶች ሲሆን የተሰራዉ በጥቃቱም የጠላት ዋና ዋና ወታደራዊ መሪዎች ጭምር ሙት እና ቁስለኛ ሁነዋል።
በጀግኖቹ ክንድ የደረሰባቸውን ከባድ ጉዳት መቋቋም ያልቻለው የጠላት ጦር፣ አመራሮቹን ለማዳን በከፍተኛ መደናገጥ ውስጥ ሆኖ ሲያነሳ የዋለ ሲሆን ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው የጦር መኮንኖች በአስቸኳይ ወደ ደሴ ሆስፒታል በሪፈር የተሸኙ ሲሆን ቀሪወቹ በአምሃራ ሳይንት ወረዳ በሚገኘው አጅባር ሆስፒታል ገብተዋል።
በጉዳቱ የተደናገጠዉ ስርዓት ሽንፈቱን ለመደበቅ ከትናንት ምሽት ጀምሮ በአጅባር ሆስፒታል ዙሪያ ጥብቅ ወታደራዊ ከበባ ያደረገ ሲሆን የቆሰሉት አመራሮች ማህበረሰቡ እንዳያያቸዉ በሚል ስጋት፣ ከሕክምና ባለሙያዎች ውጭ ማንም ሲቪል ታካሚ ወደ ሆስፒታሉ ግቢ እንዳይገባ ሙሉ በሙሉ እስካሁን ድረስ አግደው ይገኛሉ። ምንጭ፦ የምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
20 724
+1
ከደብረ ማርቆስ ወደ ስናን ሬሽን ለማቀበል በተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ላይ 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ስናን አባ ጅሜ ሻለቃ ባደረገው ማጥቃት 20 የአረመኔው ሰራዊት ሲደመሰሱ 12 የሚደርሱ ከባድ ቁስለኛ ሁነው 3 ክላሽ ፣ 1050 ጥይት ተማርኳል።
የአረመኔው ሰራዊት የ6ኛ ዕዝ 602ኛ ኮር 75ኛ ክ/ጦር ከደብረ ማርቆስ ተነስቶ ወደ ስናን ረዕቡ ገበያ ሬሽን ለማቀበል እየተንቀሳቀሰ ባለበት 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ስናን አባ ጅሜ ሻለቃ ባደረገው ማጥቃት 20 የጠላት ወታደሮች ሲደመሰሱ 12 የሚደርሱት ቁስለኛ ሁነዋል።
በተፈፀመው ፈጣን ጥቃት የጠላት መስመራዊ መኮንኖች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን ፻ አለቃ ታሪኩ በቀለ ባቲሳ የሻለቃ አዛዥ ይገኝበታል።
ጠላት በአልጠበቀው ስዓት በተከፈተበት ተኩስ አስክሬን ሳያነሳ ፈርጥጦ 3 ክላሽ፣ 1050 ጥይት ትጥቆችና ወታደራዊ ቦርሳዎች ተማርኳል።
ምንጭ፦ በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
20 724
+1
ግፍን የተቃዎሙ የአገዛዙ ወታደሮች ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ከስምሪት ቀጠናቸው በመጥፋት ፋኖ በገፍ መቀላቀላቸውን ቀጥለዋል።
ወታደሮቹ፦
1, ስናይፐር እና ~ 220 የስናይፐር ተተኳሽ
2, ጥቁር ክላሽ ~ 220 የክላሽ ተተኳሽ
2, ቦምብ በመያዝ ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው በምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 33ኛ ክፍለጦርን ተቀላቅለዋል ሲል የክፍለጦሩ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል አስታውቋል።
ስቦ ማስከዳቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
20 724
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ምንጃርና ከረዩ አውራጃ ነበልባል ክፍለ ጦር ድል ተቀዳጀች
በአፋብን ሸዋ/ጠ/ግ/አሳምነው ዕዝ ከሠም ፪ኛ ኮር ነበልባል ክፍለ ጦር የብልፅግናውን ጥምር ጦር እንደ ቅጠል አረገፉት።
ሁለት የነበልባል ክፍለ ጦር ሻለቆች የተሳተፉበት ውጊያ ማለትም መብረቅ ሻለቃ እና መቶ አለቃ አበባው ሻለቃ ፋኖዎች በጥምረት ባደረጉት ገድል የብልፅግናውን ግብስብስ ሠራዊት በ06/10/2018 ከቀኑ 6:00 እስከ ማታ 9:45 ሰዓት በነበረው ፍልሚያ ፋኖዎቹ መብረቃዊ ክንዳቸውን በመሰንዘር እንደ እሳት ሲለበልቡት አምሽተዋል።
መነሻውን ከባልጪ አድርጎ ወደ ኢራንቡቲ ቀበሌ ያቀናውን የሪፐፕሊካን ጥበቃ 5ኛ ክፍለጦር እና በስሩ በጥቅማጥቅም የሰበሰባቸውን ሆድ አደር ሚሊሾች እንዲሁም አዲስ ተጨማሪ ሰራዊት በመያዝ ኢራንቡቲ ቀበሌን እቆጣጠራለሁ ብሎ በመንጋ ቢመጣም በአይበገሬዎቹ ነበልባል ክፍለ ጦር ሠራዊታችን ወደ መጣበት እዲመለስ አድርገውታል።
የሀይል ብልጫ የተወሰደበት የጠላት ሀይል ከ15 በላይ እንደተገደለበት እና ቁጥሩ በውል ያልታወቀ ቁስለኛ በአንቡላንስ ከአራት ጊዜ በላይ ጭኖ እንዳመላለሰ እና የሞተበትን ሀይል በአካባቢው ማህበረሰብ በማስገደድ ለህክምና የምታመላልሰው አንቡላንስ ደርሳ እስክትደርስ 15ቱን እሬሳ እዲያቀብሉት ማስገደዱን የውስጥ መረጃችን አሳውቆናል።
ይህ በእንዲሕ እንዳለ የአፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ ዓፄ አምደ ጽዮን ኮር 7/70 ክፍለጦር አንድ(1) የአገዛዙ ወታደር
=> አንድ(1) ዘመናዊ ስናይፐር መሳሪያ
=> አንድ(1) የደረት ትጥቅ
=> አራት(4) ካዝና በመያዝ ወደ ፋኖ ተቀላቅሏል።
በሌላ የአውደ ውጊያ ቀጠና
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋት አውራጃ አስገራሚ ጀብዶች ተሠርተዋል
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝ የዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ ፩ኛ ኮር 7/ለ70 ክፍለ ጦር ዛሬም እንደ ትላንቱ በጠላት ይዞታዎች ውስጥ ሰርገው በመግባት አስገራሚ ድሎችን ማስመዝገባቸውን ቀጥለውበታል።
የክፍለ ጦሩ ልዩ የኦፕሬሽን ቃኝዎች የፋሺስት አብይ አህመድ ግብስብስ ሰራዊትን ወደ ሚንቀሳቀስበት ቦታ ሰርገው በመግባት የጠላትን እቅድ በማክሸፍ መብረቃዊ ጥቃቶችን ፈፅመዋል።
የሰርጎ ገብ ውጊያ ስምሪቱ በቀን 05/10/2018 ዓ.ም ከለሊቱ 5:00 ሰዓት ላይ ከአጣዬ ተነስቶ ወደ በርግቢ አቅጣጫ እየገሰገሰ በነበረው የጠላት መከላከያ ሰራዊት ላይ የ7ለ70 ክፍለ ጦር ጀግኖች በ06/10/2018 በበርግቢ ቀበሌ እና በይምልዎ መካከል ላይ አድፍጠው በመጠበቅ ከባድ ድንገተኛ ጥቃት ፈፅመዋል። በዚህ እልህ አስጨራሽ የለሊት ውጊያ የጠላት ኃይል ድባቅ በመመታቱ ወደ መጣበት ተገዶ ለማፈግፈግ ተገዷል። በዚሕም ከጠላት ሀይል አራት(4) የተገደሉ ሲሆን የተቀሩት ደግሞ በጽኑ ቆስለው በሕክምና ላይ እንደሚገኙ የውስጥ መረጃዎቻችን ገልፀዋል።
ይህ የድል ጉዞ ሳይቋረጥ በማግስቱ በ07/09/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ላይ ከአጣዬ ከተማ ተነስቶ ወደ አላላ በመጓዝ ላይ በነበረው የሆድ አደር ሚሊሻ ኃይል ላይ ሌላ ስልታዊ ጥቃት ተፈጽሟል። የክፍለ ጦሩ የቁርጥ ቀን ልጆች አራዳ በር ላይ ቀድመው ሰርገው በመግባትና ምሽግ በመያዝ፣ በሚሊሻው ላይ የጀግንነት ክንዳቸውን አሳርፈዋል።በዚህ እልህ አስጨራሽ ውጊያ እንድሪስ የተባለው የጠላት ሚሊሻ መሪ እስከ ግብረ አበሮቹ ሙሉ በሙሉ የተደመሰሰ ሲሆን፣ ካጋጠማቸው ከባድ ሽንፈት የተረፉት 3ቱ (ሦስቱ) ደግሞ በከባድ የመቁሰል አደጋ ምክንያት ሪፈር ተጽፎላቸው በሕይወትና በሞት መካከል ይገኛሉ ሲል መረጃዎቻችን ተናግረዋል።
ምንጭ፦በአፋብን አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
20 724
#ከበላጎ ምሽግ እስከ ዋድላ ቋና!
#ያልተነገረ ገድል፣ ያልተዘከረ ዋጋ!
#እስከ መቃብር የታመኑ ጀግኖች!
https://youtu.be/zj7iFTfiyYk?si=kD2dLnQs9WGRTwBO
20 724
#ያልተነገረ ገድል፣ ያልተዘከረ ዋጋ!
ሙሉ ዝግጅቱን በዚህ ተከታተሉ👉https://youtu.be/zj7iFTfiyYk?si=kD2dLnQs9WGRTwBO
20 724
#ከበላጎ ምሽግ እስከ ዋድላ ቋና!
#ያልተነገረ ገድል፣ ያልተዘከረ ዋጋ!
#እስከ መቃብር የታመኑ ጀግኖች!
https://youtu.be/zj7iFTfiyYk?si=kD2dLnQs9WGRTwBO
20 724
የድል ዜና ከደራ!
በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር በፍቃዱ በላይ ክፍለ ጦር የበረሀው ጀግኖች ትናንት ከማለዳ አንድ(1:00) ሰዓት ከ30 ደቂቃ ጀምረው እስከ ምሽቱ አንድ(1:00) ሰዓት ድረስ በተደረገ እልሕ አስጨራሽ ውጊያ በሰረርኩላ እና በቱቲ ከተሞች መሽጎ በነበረው የአገዛዙ ኃይል ላይ እንደ እሳት እያቃጠሉ ጠንካራ ምት አድርገውበታል። ሆኖም የሥርዓቱ ጅምላ ተጋላቢ ኃይል በመሬት ላይ ሊቀበለው የሚገባውን ታሪካዊ ቅጣት ከጀግኖቹ ክንድ ተመግቧል።
የበረሀው ትንታግ በፍቃዱ በላይ ክፍለጦር አንዲት እሳት የለበሰች ሻለቃ ወደ ሰረርኩላ ከተማ በረገጠችበት ቅጽበት በአገዛዙ ጥርቅም ኃይል ላይ የወሰደችው ፈጣንና መብረቃዊ የማጥቃት ስልት ጠላትን ሙሉ በሙሉ ግራ አጋብቶታል። ከዚሕም የተነሳ ጭንቅ ውስጥ የገባውና መውጫ ያጣው የአገዛዙ ኃይል ጫካ ውስጥ ያደራጀውን ዘራፊውን የ"ሸኔ" ስብስብ ለአጋዥነትና ለሕይወት ማዳኛ የጋበዘ ሲሆን የአናብስቶቹ ክንድ የማይነካ በመሆኑ ነገሩ እዳሠበው ሳይሳካ ቀርርቶበታል።
በመጨረሻም ጠላት የሚያስማርከውን አስማርኮ የጓዶቹን አስከሬን እንኳን ሳይሰበስብ ከተማዋን ጥሎ ወደ ጫካ ፈርጥጧል። ጀግኖቹ የሰረርኩላን ከተማ እስከ ምሽቱ ሁለት(2:00) ሰዓት ሙሉ በሙሉ በቁጥጥራቸው ስር አውለዋታል።
በሌላ በኩል በቱቲ ከተማ በተደረገው አውደ ውጊያ እጅ በአፍ የሚያስጭን ነበር። የቱቲ ከተማ በተናዳፊዎቹ ሻለቆች የባሩድ ጢስ ስትታጠን፣ ባሩዱም ሲቆላ በዋለበት በዚያ አስፈሪ ሰዓት ጠላት ምሽጉን በመነጠቁ ከተማዋን ጥሎ ለመውጣት ተገዷል። የወገን ኃይል ከተማዋን ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር ድላቸውን አጣጥመዋል።
ይሕ በእንዲሕ እንዳለ ጠላት በእውር ድንብርና በፍርሃት ተውጦ ዙ-23 እና ሞርተሮችን እያጮኸ ቢውልም በጀግኖቹ የቦታ ቁጥጥርና በማይበገረው የስነ-ልቦና የበላይነት ግንባሩን ተመትቶ እንደ ቅጠል ሲረግፍ አምሽቶ ፣ በዚህ ደማቅ አውደ ውጊያ የተረጋገጠውና በጀግኖቹ እጅ የገባው የምርኮ ዝርዝር እንደሚከተለው ይፋ ሆኗል፦
➾3 ከፋኖ ከድተው ወደ አገዛዙ ገብተው የነበሩ ባንዳዎች
➾1 የአገዛዙ ካድሬ
➾3 የሚሊሻ አባላት
➾የተማረከ ንብረት ዝርዝር ፦
➾8 ክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች
➾4 የወገብ ትጥቅ
➾1 የደረት ትጥቅ
➾6 የእጅ ቦንቦች እና... በርካታ ተተኳሽ ጥይቶች በጀግኖቹ እጅ ገቢ ተደርገዋል።
ምንጭ፦ በአፋብን አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
20 724
###
ከሳምንት በፊት ከፍተነው የነበረው የፌስቡክ ገፅ ላልተወሰኑ ቀናት ታግዷል።በአዲስ ገፅ መጥተናል።
መረበኞች ነን መረጃ አጥማጆች!
👉https://www.facebook.com/profile.php?id=61590677702737
20 724
#ከበላጎ ምሽግ እስከ ዋድላ ቋና!
#ያልተነገረ ገድል፣ ያልተዘከረ ዋጋ!
#እስከ መቃብር የታመኑ ጀግኖች!
https://youtu.be/zj7iFTfiyYk?si=kD2dLnQs9WGRTwBO
20 724
#ከበላጎ ምሽግ እስከ ዋድላ ቋና!
#ያልተነገረ ገድል፣ ያልተዘከረ ዋጋ!
#እስከ መቃብር የታመኑ ጀግኖች!
https://youtu.be/zj7iFTfiyYk?si=kD2dLnQs9WGRTwBO
20 724
እስከ መቃብር የታመኑ ጀግኖች!
የአማራን ሕዝብ ሕልውና አስጠብቆ እንደ ሕዝብ ለማቆምና ሕልውናውን አስከብሮ የመኖር መብቱን ለማረጋገጥ እንዲሁም እስካሁን ለተፈፀመበት ሁሉን አቀፍ ግፍና መከራ ፍትሕ ርትዕ ለማስፈን፣ ሃገርን ከውድመትና ከመፍረስ ለመታደግ በሚደረገው በዚህ ተጋድሎ፡ አያሌ አማራዎች አንድያ ነፍሳቸውን፣ ውድ አካላቸውን፣ አበባማው ዕድሜያቸውን፣ እንቁውን የጉልምስና ጊዜያቸውን እንዲሁም ሃብትና ንብረታቸውን ያለ ምንም ስስት ገብረዋል።
ስለ አማራ ሕዝብ ነፃ መውጣትና ሕልውና መረጋገጥ ሲሉ ውድ ሕይወታቸውን፣ ወጣትነታቸውንና አለም ኑሯቸውን መስዋዕት ካደረጉ ቆራጥ ጀግኖች መካከል የወልድያ ተወላጅ አርበኛ ደምስ ይመርና ጓዶቹ ናቸው።
ከዚህ ቀደም ሚዲያ ላይ ያልተለቀቁ የውጊያ ቪዲዮዎችን እና ሌሎች የግንባር ተንቀሳቃሽ ምስሎችን አካተን ክቡር ሰማዕቶቹን እንዘክራለን።
ከደቂቃዎች በኋላ ይጠብቁን!
###
ከሳምንት በፊት ከፍተነው የነበረው የፌስቡክ ገፅ ላልተወሰኑ ቀናት ታግዷል።በአዲስ ገፅ መጥተናል።
መረበኞች ነን መረጃ አጥማጆች!
👉https://www.facebook.com/profile.php?id=61590677702737
20 724
+1
በጠላት 75ኛ ክ/ጦር 5ኛ ሬጅመንት አባል የነበሩ ወታደር ዮሐንስ ሃምባሳ እና ወታደር ደቻሳ ደሪባ የተባሉ ሁለት ወታደሮች የብልፅግናውን አገዛዝ ስርዓት ተቃውመው ከነሙሉ ትጥቃቸው በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ስናን አባ ጅሜ ሻለቃን መቀላቀላቸውን የኮሩ ህዝብ ግንኙነት ክፍል አስታውቋል።
###
ከሳምንት በፊት ከፍተነው የነበረው የፌስቡክ ገፅ ላልተወሰኑ ቀናት ታግዷል።በአዲስ ገፅ መጥተናል።
መረበኞች ነን መረጃ አጥማጆች!
👉https://www.facebook.com/profile.php?id=61590677702737
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
