Mereb Media መረብ ሚዲያ
前往频道在 Telegram
Welcome to our Channel, Mereb Media - መረብ ሚዲያ We provide daily reliable and trusted information. መረጃ ለማድረስ፦ @MerebMereb
显示更多📈 Telegram 频道 Mereb Media መረብ ሚዲያ 的分析概览
频道 Mereb Media መረብ ሚዲያ (@merebmedia24) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 20 003 名订阅者,在 新闻与媒体 类别中位列第 11 670,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 701 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 20 003 名订阅者。
根据 31 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -369,过去 24 小时变化为 -9,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 19.58%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.77% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 917 次浏览,首日通常累积 3 354 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 24。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Welcome to our Channel, Mereb Media - መረብ ሚዲያ We provide daily reliable and trusted information. መረጃ ለማድረስ፦ @MerebMereb”
凭借高频更新(最新数据采集于 01 八月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 新闻与媒体 类别中的关键影响点。
20 003
订阅者
-924 小时
-77 天
-36930 天
帖子存档
20 003
በአፋብን ወለጋ ቢዛሞ ቀጠና አይሻ ሰይድ ዕዝ ይበልጣል መኮነን አዲስ አለም ክ/ጦር ባደረገው የተጠና ኦፕሬሽን በኪረሙ ወረዳ ስር ቦቃ፣ ነጭሎ፣ ወዴሳ ዲማ የተባሉ ሦስት ቀበሌዎችን ጨምሮ ሃሮ አዲስ አለም ከተማን መቆጣጠሩን አስታወቀ።
ትናንት ሃምሌ 23/2018 ዓ/ም በተካሄደው በዚህ አውደ ውጊያ፡ የብልፅግና መከላከያ ሠራዊት ከክልሉ ጥምር ኃይል በጋራ ሆኖ የተሰለፈ ቢሆንም ከወደ ፋኖ የተሰነዘረበትን ጥቃት መቋቋም አቅቶ ተሽመድምዷል።
በዚህ ተጋድሎ 36 የጠላት ወታደሮች ሲገደሉ፡ 42 ወታደሮች ደግሞ ሲቆስሉ በድምሩ 78 የአገዛዙ ወታደሮችን ከስምሪት ውጭ ማድረግ ተችሏል።
በተጋድሎው፡ ጀግኖቹ የይበልጣል መኮነን አዲስ አለም ክ/ጦር አርበኞች ጠላትን አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት አዲስ አለም ከተማን ጨምሮ በጊዳ ኪረሙ ወረዳ ስር ቦቃ፣ ነጭሎ፣ ወዴሳ ዲማ የተባሉ ሦስት ቀበሌዎችን በቁጥጥራቸው ስር አስገብተዋል።
በተያያዘ!
ከሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አቤ ዶንጎሮ ወረዳ መነሻውን ያደረገ የጠላት ጦር ወደ ምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ ኪረሙ ወረዳ እገዛ ለማረግ እየተንቀሳቀሰ እንዳለ በአይሻ ሰይድ ዕዝ ስር የጌጤ ግርማ መብረቁ ክ/ጦር አርበኞች መንደር 21 ቀበሌ ልዩ ቦታው አንገር መድሃኒያለም ላይ በፈፀሙት የደፈጣ ጥቃት፡ በርካታ የጠላት ወታደሮች ሙትና ቁስለኛ ሲደረጉ፡ ጠላት የእንቅስቃሴ እቅዱ መክኖበት ብትንትኑ ወጥቷል።
በተመሣሣይ ከይበልጣል መኮነን አዲስ አለም ክ/ጦር እና ከአንገር ጉትን ክ/ጦር የተወጣጡ አሃዶች በቅንጅት በወሰዱት እርምጃ በርካታ የጠላትን ጦር ደምስሰው በኪረሙ ወረዳ የጎላ ወታደራዊ ጠቀሜታ ያላት ቆፍቆፌ ከተማን በቁጥጥራቸው ስር አስገብተዋል።
በዚህ ስፍራ ከመደምሰስ የተረፈው የጠላት ኃይል ሙትና ቁስለኛውን እያዝረከረከ የጊዳ አያና ወረዳ መቀመጫ ወደሆነችው ጊዳ ከተማ ፈርጥጧል።
ከወደፋኖ የተወሰደበትን እርምጃ መቋቋም ያልቻለው የአገዛዙ ሰራዊት እንደለመደው ንፁኋንን ኢላማ ያደረገ የከባድ መሳሪያ ድብደባ በማድረግ ወደሳ ዳማ በተባለ ቀበሌ ላይ የ13፣ የ15ና የ16 ዓመት ታዳጊ ልጆችን በአሰቃቂ ሁኔታ መግደሉ ነው የተሰማው።
መረበኞች ነን መረጃ አጥማጆች!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
20 003
በጊዳ ኪረሙ ወረዳ በተደረገ ውጊያ የጎላ ወታደራዊ ጠቀሜታ ያላት ቆፍቆፌና አከባቢዋ በፋኖ ቁጥጥር ስር ዋለ!
በአፋብን ወለጋ ቢዛሞ ቀጠና የአይሻ ሰይድ ዕዝ አርበኞች በቅንጅት በወሰዱት እርምጃ በርካታ የጠላትን ጦር ደምስሰው በኪረሙ ወረዳ የጎላ ወታደራዊ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያላት ቆፍቆፌ ከተማን በቁጥጥራቸው ስር አስገብተዋል።
በዚህ ስፍራ ከመደምሰስ የተረፈው የጠላት ኃይል ሙትና ቁስለኛውን እያዝረከረከ የጊዳ አያና ወረዳ መቀመጫ ወደሆነችው ጊዳ ከተማ ፈርጥጧል።
ሙሉ መረጃውን በዚህ ተመልከቱ👉https://www.youtube.com/watch?v=V_wfxFoGSMghttps://www.youtube.com/watch?v=V_wfxFoGSMg
20 003
#ውሳኟ ከተማ ተያዘች/ 78 ጦር አለቀ!
#19 ክላሽ ተገኘ/ ሆስፒታሉ በቁስለኛ ሞላ!
#5 ከተሞች በቁጥጥር ስር ዋሉ!
https://www.youtube.com/watch?v=V_wfxFoGSMghttps://www.youtube.com/watch?v=V_wfxFoGSMg
20 003
+1
105ኛ ንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር ጥልቅ ግምገማ ካካሄደ በኋላ የኮር ስያሜና አዳዲስ የአመራር ምደባ አደረገ!
በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር በስሩ የሚገኙ የክፍለ ጦር አመራሮችን ጨምሮ ለተከታታይ አምስት ቀናት የድርጅቱ እና የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ውጤታማ ጥልቅ ግምገማና የተሳካ ሪፎርም ማካሄዱን በሕዝብ ግንኙነት ክፍሉ በኩል ለመረብ ሚዲያ በላከው መረጃ አስታውቋል።
ከግምገማ መድረኩ በኋላ፡ የቀድሞው የ105ኛ ኮር የኮሩን የወትሮው ስያሜን ጨምሮ የአመራር ምደባውን በማስተካከል የተለያዩ ኃላፊነኖችን ሰጥቷል።
ኮሩ ከዛሬ ሃምሌ 24/2018 ዓ/ም ጀምሮ ከ105ኛ ወደ 15ኛ ኮር የስያሜ ለውጥ ያደረገ ሲሆን፡ የሰብሳቢነቱን ሚና በአርበኛ እንድሪስ ይማም ተክቷል።
መረበኞች ነን መረጃ አጥማጆች!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
20 003
እየገቡ ነው! / ጥብቅ ትዕዛዝ ተላልፏል!
ፋኖ በየከተሞች በሚገባበት ወቅት በሕዝቡ ላይ ምንም አይነት የሰብአዊና የንብረት ጉዳት እንዳይደርስ ልዩ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት የሚያዝ መመሪያ ተላለፈ።
ፋኖ ወደ ትላልቅ ከተሞች ሲገባ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ ነው መመሪያው የሚያትተው።
ፋኖ መንግሥት የመሆን አቅሙን ማሳየት ያለበት ሕዝብን በኃላፊነት ሲመራ እንደሆነ የገለፁት የአፋብን ምኒልክ ዕዝ ሰብሳቢ ፊታውራሪ ድርሣን ብርሃኔ፡ ታጋዮች ወደ ከተሞች በሚገቡበት ወቅት ከበቀልና ከንብረት ወረሳ በመታቀብ የዜጎችን ሰላምና ደኅንነት በጥብቅ እንዲጠብቁ የሚያስገነዝብ ወታደራዊና ፖለቲካዊ መመሪያ አስተላልፈዋል።
ሙሉ መረጃውን በዚህ ተመልከቱ👉https://www.youtube.com/watch?v=V_wfxFoGSMghttps://www.youtube.com/watch?v=V_wfxFoGSMg
20 003
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነዉ ኮር በአገዛዙ ወታደር ላይ የማያዳግም እርምጃ በመዉሰድ ድልን ተቀዳጁ!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አፋብን ወሎ ቤተ -አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር አካል የሆነው 14ኛ (ጀኔራል ሃይሉ ከበደ) ክፍለ ጦር በዋግህምራ ዞን ጋዝጊብላ ወረዳ 09 ቀበሌ ላልኪው የ አፓርታይዱ አብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ ወታደር ላይ በተሰላና በታቀደ የተጠናከረ ሽምቅ ውጊያ እና ተስቦ በመግባት ከተኛበት ምሽግ ላይ የማያዳግም እርምጃ በመውሰድ ከፍተኛ ድል ተቀዳጅተዋል።
የሽምቅ ውጊው ሐምሌ 23ለ24 ሃሙስ ለአርብ ከሌሊቱ 6:00 ሰዓት እስከ ንጋት 11:00 ሰዓት የተጠናከረ ሲሆን ልዩ ቦታው ገበያው ሰፈር ወይም በተለምዶ ጊወርጊስ ትኩ ተብሎ ከሚጠራው ተራራ ላይ መሽጎ የነበረውን የጥላት ሃይል በሽምቅ ከማጥቃት ሙሉ በሙሉ ምሽጉን በማስለቀቅ በአገዛዙ ላይ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ አድርሰውበታል ።
በተጠናከረው የሽምቅ ውጊያ ከ17በላይ የጥላት ሃይል ሲደመሰስ 4 ምርኮኛ፣9ጥቁር ክላሽ ፣1500 የብሬን ተተኳሽ፣725 የክላሽ ተተኴሽ ፣2 ኤፍዋን የእጅ ቦንብ ፣አንድ የወገብና አንድ የደረት ትጥቅ ተማርኳል ሲል የ303ኛ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መረጃውን አድርሷል።
ምንጭ፦በአፋብን ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
20 003
በምሥራቅ ወለጋ በተደረገ ውጊያ ፋኖ 78 የአገዛዙን ወታደሮችን ሙትና ቁስለኛ በማድረግ አንጸባራቂ ድል መቀዳጀቱን አስታወቀ!
በምሥራቅ ወለጋ ጊዳ ኪረሙ ወረዳ በነበረው አውደ ውጊያ የጎላ ወታደራዊ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያላትን ቆፍቆፌ ከተማን የተቆጣጠሩት አርበኞቹ፡ አዲስ ዓለም ከተማን ጨምሮ በወረዳው ቦቃ፣ ነጭሎ እና ወዴሳ ዲማ የተባሉ ሦስት ቀበሌዎችን በቁጥጥራቸው ስር ማዋላቸው ተሰምቷል።
ሙሉ መረጃውን በዚህ ተመልከቱ👉https://www.youtube.com/watch?v=V_wfxFoGSMghttps://www.youtube.com/watch?v=V_wfxFoGSMg
20 003
አሳዛኝ ዜና!
የአርበኛ ዝናቡ ልንገረው ቤተሰቦች መኖሪያ ቤት በፈረስ ቤት ከተማ ተቃጠለ!
የአማራ ህዝብን በመጨፍጨፍ፣ ሀብትና ንብረቱን ማውደም የዘወትር መገለጫው የሆነውና ተስፋ የቆረጠው የአገዛዙ ቅጥረኛ ሰራዊት፣ የአርበኛ ዝናቡ ልንገረው ወላጆችን መኖሪያ ቤት በፈረስ ቤት ከተማ ማቃጠሉ ታውቋል።
በራሱ ህዝብ ላይ ታንክ፣መድፍና አየር ኃይል አሰማርቶ ንፁሃንን የሚጨፈጭፈው፣ የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ፣ መሀመድ ተሰማ ለምዕራብ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ እድሚያለም ለሚባል ቅጥረኛ ግለሰብ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት መኖሪያ ቤቱ መቃጠሉን ከመረጃ ምንጮቻችን ለማወቅ ተችሏል።
በቃጠሎው የደጋ ዳሞት ወረዳ፣ የአገዛዙ ቅጥረኛ ካድሬዎችና የሚሊሻ አባላት እንደተሳተፉ የዓይን እማኞች ገልጸዋል። በቤቱ ውስጥ ይገኙ የነበሩ ቁሳቁሶችን ጨምሮ ሌሎች ጠቃሚ ንብረቶች በእሳቱ መውደማቸው ታውቋል።
በፈረስ ቤት ከተማ፣ ቀበሌ 02 ይገኝ የነበረው ይህ መኖሪያ ቤት፣ የአርበኛው ወላጆች ኑሯቸውን መስርተው፣ማኀበራዊ ህይዎታቸውን ይመሩበት እንደነበረ ተገልጿል።
ላለፉት 3 አመታት በተለያዩ የአማራ ቀጠናዎች ከፋኖ ጋራ ፊት ለፊት ተዋግቶ ማሸንፍ ያልቻለው አገዛዙ፣ የበቀል ዱላውን የሚያሳርፈው ንጹሃን ዜጎችን በመገድልና ሀብት ንብረታቸውን በማውደም እንደሆነ ይታወቃል። በአርበኛ ዝናቡ ልንገረው ወላጆች ቤት የደረሰው ቃጠሎ የዚህ አንድ አካል ነው።
ከውጊያ ቀጠና ውጭ የሚገኙ የሰላማዊ ዜጎችን ሀብትና ንብረት ማውደም፣ በዓለም አቀፉ የጄኔቫ የጦር ስምምነት( Geneva War Convention) መሰረት በጦር ወንጀልነት ሊያስጠይቅ የሚችል መሆኑንን በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የህግ ባለሙያዎች ገልጸዋል።
ቃጠሎውን አስመልክቶ፣ ፈረስ ቤት ከተማን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች በስልክና በአካል ያነጋገርናቸው ሰላማዊ ዘጌጎች ድርጊቱን በጥብቅ አውግዘውታል። አንድ አገር እመራለሁ ከሚል አካል ፍፁም የማይጠበቅ "ወራዳ ተግባር" ሲሉ ኮንነው፣ አገዛዙ ምን ያህል የመንግስትነት ቁመናው እንዳጣና ተስፋ እንደቆረጠ ማሳያ ነው ሲሉ ጨምረው ገልጸዋል።
አገዛዙ በጎንደር፣ በወሎ፣ በሸዋና በጎጃም ላለፉት 3 ዓመታት የተለያዩ የፋኖ ቤተሰቦችን ሀብት ንብረት ሲያወድሙ እንደቆዩ ይታወቃል።
ምንጭ፦በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
20 003
#ውሳኟ ከተማ ተያዘች/ 78 ጦር አለቀ!
#19 ክላሽ ተገኘ/ ሆስፒታሉ በቁስለኛ ሞላ!
#5 ከተሞች በቁጥጥር ስር ዋሉ!
https://www.youtube.com/watch?v=V_wfxFoGSMghttps://www.youtube.com/watch?v=V_wfxFoGSMg
20 003
ሰበር!....ዛሬም ተደገመ!
በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር ስር የአረንዛው ጎንቻ ሬጅመንት አርበኞች በግንደወይን ከተማ አቅራቢያ ትግዳር እና እነሴ ቆል ተብለው በሚጠሩ አከባቢዎች ላይ ሰፍሮ የነበረውን የጠላት ብልፅግና ወታደራዊ ኃይል ሙሉ ለመሉ በመደምሰስ አኩሪ ገድል መፈፀማቸው ድርጅቱ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያው በኩል አስታውቋል።
በዝርዝር እንመለስበታለን።
መረበኞች ነን መረጃ አጥማጆች!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
20 003
#70 ጦር ሲያልቅ 79 ክላሽ ተያዘ!
#ከተማዋን ሰንጥቀው ገቡ/አዛዡ ተመታ!
#አዲስ ዲሽቃና ብሬይ ተይዟል!
https://youtu.be/nzjVo20Uw1k?si=wJeqGuVoElagQqij
20 003
የብልፅግናው አገዛዝ በገዳማትና በአብያተክርስቲያና ላይ እየፈፀመ ያለውን የድሮን ጥቃትና በጥቃቱ እየተገደሉ ያሉ ንፁኋኖችን ተከትሎ ከባድ ውግዘት ከየአቅጣጫው እየተሰነዘረበት ይገኛል።
የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል በአማራ ክልል በሲቪሎችና በአምልኮ ቦታዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች "እጅግ የሚረብሹና ፈጽሞ ተቀባይነት የሌላቸው ናቸው" ሲል በጽኑ አውግዞ፡ በጥቃቶቹ ላይ አስቸኳይና ገለልተኛ ምርመራ እንዲደረግ ጥሪ አቅርቧል።
ሙሉ መረጃውን ተመልከቱ👉https://www.youtube.com/watch?v=FlrMZiFurLM
20 003
+1
በእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ሰኞ ገበያ ንዑስ ወረዳ እና ዲቦ ከተማ ተከማችቶ በነበረ የአገዛዙ ኃይል ላይ በተከፈተ ድንገተኛ ጥቃት የሻለቃ አዛዦችና የፖሊስ ኃላፊዎችን ጨምሮ ከ70 በላይ የአገዛዙ ወታደሮች መደምሰሳቸው ታወቀ!
በተጋድሎው አንድ አይሱዙ FSR መኪና ከነሙሉ ሎጀስቲክስ፣ አንድ ዶሽቃ፣ ሁለት ብሬን፣ 79 ክላሽንኮቭና አምስት መገናኛ ራዲዮዎች በፋኖ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
ሙሉ መረጃውን ተመልከቱ👉https://youtu.be/nzjVo20Uw1k?si=wJeqGuVoElagQqij
20 003
#70 ጦር ሲያልቅ 79 ክላሽ ተያዘ!
#ከተማዋን ሰንጥቀው ገቡ/አዛዡ ተመታ!
#አዲስ ዲሽቃና ብሬይ ተይዟል!
https://youtu.be/nzjVo20Uw1k?si=wJeqGuVoElagQqij
20 003
ቴወድሮስ እዝ 201ኛ ኮር፣ 74 ኛ ክፍለ ጦር ዓባይ ሸለቆ ሻለቃ አስደናቂ ጀብዱ ፈፅማለች።
ዛሬ በቀን 22/11/2018 ዓ.ም ንጋት11:00 ሰዓት አካባቢ የአባይ ሸለቆ ተርቦች ሻለቃ መሪውን ከሙሉ ሀይሉ ጋር በመደምሰስ ዲሽቃ፣ ብሬንና በርካታ የነፍስ ወከፍ መሳሪያ በመማረክ እጅግ ድንቅ ስራ ሰርተዋል።
በዚህ የአፋብን የወረዳው ጊዜያዊ መንግስት የፀጥታ ሀይልም ጭምር በተሳተፈበት ድንቅ ኦፕሬሽን በእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ሰኞ ገበያ ንዑስ ወረዳ እና ዲቦ ንዑስ ወረዳ ዲቦ ከተማ ተከማችቶ በነበረው የሚሊሻና አድማ በትን እንዲሁም ፖሊስ ላይ የሸለቆው አዳኞች ባልጠበቀው መልኩ ድንገተኛ ጥቃት በመፈፀም ሙትና ቁስለኛ አድርገውታል።
በዚህም ሻለቃ መሪውን ጨምሮ 61አድማ ብተና ኃይል፣ 08 ፖሊሶች ሲገደሉ 50 አለቃ ታደሰ የተባለ የሚሊሻ ሀላፊን ጨምሮ በርካታ ሚሊሻ ወደ ላይኛው ተሸኝቷል። 08 ሚሊሻም ቆስሎ ሆስፒታል ገብቷል።
👉 በኦፕሬሽኑ የተገኙ ምርኮዎች:-
1) አንድ ዲሽቃ
2) ሁለት ብሬን
3) 79 ክላሽ
4) 05 መገናኛ ሬዲዮ
5) 02 የድሽቃ ሸንሸል
6) 05 ሳጥን የዲሽቃ ተተኳሽ
7) በርካታ የብሬንና የክላሽ
8) አንድ FSR መኪና ሙሉ ሎጀስቲክ እንደጫነ
👉 ከተገደሉት መካከል:-
• ኢ/ር አስናቀ የፖሊስ ፅ/ቤት ኃላፊ፣
• ኢ/ር ወርቁ ------አድማ ብተና ሻለቃ አዛዥ፣
• ነጋሽ-----ድሽቃ ተኳሽ
• ጀማል ኡመር ----አድማ ብተና ጋንታ መሪ
• ኢንስፔክተር ውዱ -------የፖሊስ አመራር
• ኢንስፔክተር ማሞ ----የፖሊስ አመራር ይገኙበታል።
ምንጭ፦ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
20 003
የብልፅግናው አገዛዝ በገዳማትና በአብያተክርስቲያና ላይ እየፈፀመ ያለውን የድሮን ጥቃትና በጥቃቱ እየተገደሉ ያሉ ንፁኋኖችን ተከትሎ ከባድ ውግዘት ከየአቅጣጫው እየተሰነዘረበት ይገኛል።
የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል በአማራ ክልል በሲቪሎችና በአምልኮ ቦታዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች "እጅግ የሚረብሹና ፈጽሞ ተቀባይነት የሌላቸው ናቸው" ሲል በጽኑ አውግዞ፡ በጥቃቶቹ ላይ አስቸኳይና ገለልተኛ ምርመራ እንዲደረግ ጥሪ አቅርቧል።
ሙሉ መረጃውን ተመልከቱ👉https://www.youtube.com/watch?v=FlrMZiFurLM
20 003
በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር በመርጡለ ማርያም ሰኞ ገበያ ከድም ሰሳ አምልጠው መረዋ በረሃ የገቡ 14 የ ጠላ ት ሰራዊት አባላትን በአባይ ሸለቆ ሻለቃ ገቢ አድርጓቸዋል።
ተጨማሪ 13 ክላሽ እና 1 ብሬን ተማርኮ ገቢ ሁኗል።
ሙሉ መረጃውን ተመልከቱ👉https://www.youtube.com/watch?v=FlrMZiFurLM
