2 233
Subscribers
No data24 hours
-157 days
-5030 days
Posts Archive
2 233
ዛሬ ነሀሴ 27 የዓለሙ መድህን የቸሩ መድሀኒዓለም ወርሃዊ መታሰቢያ ነው። እንኳን አደረሰን አደረሳቹ🙏
"እርሱም ኃጢአት አላደረገም ተንኰልም በአፉ አልተገኘበትም፤ ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም መከራንም ሲቀበል አልዛተም፤ ነገር ግን በጽድቅ ለሚፈርደው ራሱን አሳልፎ ሰጠ። ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ። " 1ኛ ጴጥ 2 : 22-25
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ በቀራንዮ አደባባይ የተሰቀልከው ለሰው ልጅ ደህንነት እንደመሆኑ መጠን ስለ እናትህ ስለ ድንግል ብለህ ምሬሃለሁ ይቅር ብዬሃለሁ በለኝ። ከአንተ በቀር ቸር ይቅር ባይ የለምና። (መልክአ መደኃኔ ዓለም)
2 233
ዛሬ ነሀሴ 26 የፃድቁ አባታችን የአቡነ ሃብተ ማርያም የፅንሰት በዓል ነው። እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ🙏
ፃድቁ አባታቸው ቅዱስ ፍሬ ቡሩክ እናታቸው ቅድስት ዮስቴና ሲሆኑ በእግዚአብሔር ሕግ የጸኑ ደጋግ ክርስቲያኖች ነበሩ፣ ጻዲቁ ነሐሴ 26 ተፀንሰው ፣ ግንቦት 26 በሰሜን ሸዋ የራውዕይ በሚባል ቦታ ተወለዱ፡፡ እናታቸው በበረሃ ሳለች ጻዲቁ ለዓለም ሁሉ የሚተርፍ ታላቅ ሰው እንደሚሆኑ ትንቢት ተነግሮለታል።
በልጅነታቸው ጀምሮ «እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ» የሚለውን ጸሎት አዘውትረው ይፀልዩ ነበር፡፡ በድንግልና ለመኖር በመወሰናቸው ከአባት አገራቸው ተሰደው አባ ሳሙኤል ዘደብረ ዓባይ ዘንድ 12 ዓመት አገልግለዋል፤ ኋላም ከአቡነ መለልኬዴቅ እጅ ምንኩስናን ተቀብለዋል፡፡
በሳምንት አንድ ጊዜ ቅጠል ብቻ እየተመገቡ፣ 40 እና 80 ቀን እየጾሙ እጅግ ጽኑ ተጋድሎ አድርገዋል። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም መጽሐፍትን ሲያነቡ ተገልጦላቸው ብዙ ፀጋና ታላቅ ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡
አቡነ ተክለ ሃይማኖት ህዝባቸውን ከአምስት መቅሰፍታት (መብረቅ፣ ቸነፈር፣ ረሃብ፣ ወረርሽኝ እና የእሳት ቃጠሎ) ለመታደግ ሲሉ ጻዲቁ በደብረ ሊባኖስ እንዲቀበሩላቸው ጠይቀው ፈቃድ አግኝተዋል።
ጻዲቁ አቡነ ሀብተ ማርያም በደብረ ሊባኖስ ተጋድሎአቸውን ፈጽመው ኅዳር 26 ቀን ከዚህ ዓለም በሰላም ዐርፈዋል፡፡
የጻድቁ በረከትና ረድኤት ከሁላችን ጋር ይሁን! አሜን🙏
2 233
ዛሬ ነሀሴ 25 የታላቁ ሰማዕት የቅዱስ መርቆሬዎስ ወርሃዊ መታሰቢያ ነው። እንኳን አደረሰን አደረሳቹ🙏
በ፪ኛው (2ኛው) ክፍለ ዘመን ሮም ውስጥ ከአረማዊ ቤተሰብ የተወለደው ቅዱስ መርቆሬዎስ፣ የቀድሞ ስሙ "ፒሉፓዴር" ነበር። የአባቱ ስም አሮስ የእናቱም ስም ሲዲሮስ ነበር። አባቱ በዱር ለአደን ሳለ በአራዊት ሊበላ ሲል በመለኮታዊ ጥበቃ ዳነ ከእርሱ ሚወለድ መልካም ፍሬ አለና።
በኋላ ቤተሰቡ በሙሉ ወደ ክርስትና ተመለሱ። የክርስትና ስምንም አገኙ አባቱ ኖህ፣ እናቱም ታቦት፣ ልጃቸውም መርቆሬዎስ ተባለ ትርጉምም የአብ ወዳጅ አንድም የክርስቶስ አገልጋልይ ማለት ነው። መርቆሬዎስ በወጣትነቱ የሮም ወታደር ሆነ፤ በሰውነቱ ጥንካሬና በውጊያ ብቃቱም በንጉሥ ዳክዮስ ዘንድ እጅግ ተወደደ።
የሮም መንግሥት ከበርባሮች ጋር በገጠመው አስፈሪ ጦርነት ወቅት፣ መርቆሬዎስና ወታደሮቹ ሊሸነፉ ተቃርበው ነበር። በዚያን ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል በታላቅ ብርሃን ተገልጦ የሚነድ ሰይፍ ሰጠውና እንዲህ አለው፦
"መርቆሬዎስ ሆይ! አትፍራ፤ በዚህ ሰይፍ ጠላቶችህን ድል ታደርጋለህ። ካሸነፍክ በኋላ ግን አምላክህን እንዳትረሳ።" መርቆሬዎስም በሁለቱ ሰይፎች (በምድራዊውና ከመልአኩ በተቀበለው) ጠላቶቹን ድል አድርጎ ተመለሰ። የሁለት ሰይፎች አባት(ባለቤት) ሚባለውም ለዚ ነው።
ንጉሥ ዳክዮስ ከድሉ በኋላ ለጣዖታቱ መሥዋዕት እንዲያቀርብ መርቆሬዎስን ባዘዘው ጊዜ፣ ቅዱስ መርቆሬዎስ ፈቃደኛ አልሆነም። "እኔ የክርስቶስ ባሪያ ነኝ እንጂ የጣዖት አምላኪ አይደለሁም" በማለት ክብሩንና ማዕረጉን በሙሉ ጥሎ ክርስትናውን መሰከረ። ንጉሡም እጅግ ተቆጥቶ በሰይፍ እንዲቀላ እስከታዘዘበት ጊዜ ድረስ በተለያዩ አስፈሪና ፅኑ ስቃዮች እንዲያልፍ አደረገው። ሰማዕቱ ግን በመልአኩ እርዳታ እየዳነ ጽናቱን አሳየ።
በመጨረሻም ቅዱስ መርቆሬዎስ ሕዳር ፳፭ (25) ቀን በሰማዕትነት ዐረፈ። ቅዱስ መርቆሬዎስ በሰማዕትነት ካረፈ በኋላ በ፬ኛው (4ኛው) ክፍለ ዘመን የነገሠው ንጉሥ ኡልያኖስ ክርስትናን ክዶ ወደ ጣዖት አምልኮ በመመለስ በክርስቲያኖች ላይ ታላቅ መከራ አውጆ ነበር።
በዚያን ጊዜ ቅዱስ ባስልዮስ እና ቅዱስ ጎርጎሪዮስ የቤተክርስቲያን መሪዎች ነበሩ። ኡልያኖስ ወደ ፋርስ ጦርነት ከመሄዱ በፊት ቅዱስ ባስልዮስን፦ "ከጦርነት ስመለስ የከተማዋን ክርስቲያኖች በሙሉ እፈጃለሁ፣ ቤተክርስቲያንንም አጠፋለሁ" በማለት ዛተባቸው።
ቅዱስ ባስልዮስና አማኞች በጾምና በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ጮኹ። ቅዱስ ባስልዮስ በቤተክርስቲያን ውስጥ ሆኖ ሲጸልይ፣ በግድግዳው ላይ ተሥሎ የነበረውን የቅዱስ መርቆሬዎስን ስዕል ይመለከት ነበር። ድንገት ግን የቅዱስ መርቆሬዎስ ስዕል ከመቀመጫው ጠፋ፤ የያዘው ሰይፍም በቦታው አልነበረም።
በዚያው ሰዓት ቅዱስ መርቆሬዎስ በጦር ሜዳ ላይ የነበረውን ንጉሥ ኡልያኖስን በጦር ወግቶ ገደለው ።በቤተክርስቲያን ውስጥ ሲጸልይ የነበረው ቅዱስ ባስልዮስ ከጥቂት ጊዜ በኋላ የቅዱስ መርቆሬዎስ ስዕል ወደ ቦታው ተመልሶ ተመለከተ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ በስዕሉ ላይ ያለው የቅዱስ መርቆሬዎስ ሰይፍ በደም ተለውሶ ነበር።
ታላቁ ሰማዕት ቤተክርስቲያንን ከጠላቶችዋ የታደገና ክርስትና እንዲቀጥል ያደረገ ታላቅ ባለውለታ ነው። ዛሬም ድረስ በቃል ኪዳኑ የሚማጸኑትን ሁሉ ከፈተና የሚጠብቅ ኃያል ሰማዕት ነው።
የታላቁ ሰማዕት የቅዱስ መርቆሬዎስ ምልጃና ጥበቃ ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን🙏
2 233
+2
ዛሬ ነሀሴ 24 የፃድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት፣የእናታችን የቅድስት ክርስቶስ ሰምራ እንዲሁም የሐዋርያው የቅዱስ ቶማስ ዓመታዊ የእረፍት በዓል ነው። እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን🙏
ከቅዱሳኑ ረድኤት፣ በረከት ያሳትፈን!
የዓመት ሰው ይበለን አሜን🙏
2 233
ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ! አንተን በመታመን ለጠራህ ሁሉ ፈጥነህ ስትደርስለት ከዓውሎ ነፋስ ይልቅ በተፋጠነ ሩጫ ነው። ጊዮርጊስ ሆይ! የዘወትር ጸሎቴንና የቃሌንም የልመና ጩኸት ትቀበል ዘንድ ለይቅርታና ለምህረት ፈጥነህ ወደ እኔ ቅረብ። 🙏
(መልክአ ቅዱስ ጊዮርጊስ)
2 233
ዛሬ ነሀሴ 22 የሊቀ መላዕክት የቅዱስ ዑራኤል ወርሃዊ መታሰቢያ ነው። እንኳን አደረሰን አደረሳቹ🙏
የእግዚአብሔር ህዝብ በባቢሎን ምርኮ በነበሩበት ዘመን ነቢዩ ዕዝራ (ዕዝራ ሱቱኤል) ስለ ቅድስት ከተማ ጽዮን መፈራረስ፣ ስለ ወገኖቹ መሰደድና መገፋት፣ ከሁሉም በላይ ደግሞ በጦርነቱ ወቅት የእግዚአብሔር ህግ የተጻፈባቸው ቅዱሳት መጻሕፍት በመቃጠላቸው ልቡ በሀዘን ተሰበረ።
ዕዝራ "ህጉ ከጠፋ ህዝቡ እንዴት ይመራል? ትውልዱስ እንዴት ፈጣሪውን ያውቃል?" ብሎ በመጨነቅ ወደ ምድረ ራፌድ ወጣ። በዚያም መሪር ዕንባን እያፈሰሰ፣ ስለ ወገኖቹና ስለ መጻሕፍቱ መጥፋት እያለቀሰ 40 ቀንና 40 ሌሊት በጾምና በጸሎት ተቀመጠ።
ዕዝራ ጾሙንና ጸሎቱን በፈጸመ ጊዜ፣ ልዑል እግዚአብሔር ምስጢር ገላጭ የሆነውን ታላቁን መልአክ ቅዱስ ዑራኤልን ወደ እርሱ ላከው። ቅዱስ ዑራኤልም በእጁ "የእሳት ጽዋ" ይዞ ከሰማይ ወረደ።
መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ዕዝራን እንዲህ አለው፦ "አፍህን ክፈት፣ ይህንንም የጥበብ ጽዋ ጠጣ"። ዕዝራም አፉን ከፈተ፤ ያን የእሳት ጽዋም ጠጣው። እዝራ ሱቱኤል 13: 38
ያን ጊዜ የዕዝራ ልቡና እንደ ብርሃን በራ! የተሰወረ ምስጢር ተገለጠለት። የጠፉትና የተቃጠሉት መጻሕፍት ሁሉ በቃሉ ተቀረጹለት(ተገለጡለት)።
ከዚያ በኋላ ዕዝራ አምስት ጸሐፊዎችን አዘጋጅቶ፣ ቅዱስ ዑራኤል የገለጠለትን ምስጢርና ትምህርት በ40 ቀናት ውስጥ መጻሕፍትን በቃሉ እየነገራቸው መልሰው እንዲጽፉ አደረገ። በዚህም ምክንያት ዕዝራ "ዳግማዊ ሙሴ" ተብሎ ተጠራ።
የቅዱስ ዑራኤል ተራዳኢነትና የነቢዩ ዕዝራ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን! ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ዑራኤል ጥበቡን፣ እውቀቱንና ምስጢሩን ለሁላችንም ይግለጥልን አሜን🙏
2 233
ዛሬ ነሀሴ 21 የእናታችን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ወርሃዊ መታሰቢያ ነው። እንኳን አደረሰን አደረሳቹ🙏
ድንግል ሆይ ስለዚህ እንወድሻለን፤ ከፍ ከፍም እናደርግሻለን እውነተኛ የጽድቅ መብልንና እውነተኛ የህይወት መጠጥን ወልደሽልናልና። (ቅዳሴ ማርያም)
ድንግል ሆይ የእግዚአብሄር ማደሪያ ንጹህ አዳራሽ ነሽ ጠላቶቼ ያቺ የሚመካባት እመቤቱ ወዴት አለች ብለው እንዳይዘባበቱብኝ። እኔን ባሪያሽን ለሀዘን ለትካዜ አሳልፈሽ አትስጪኝ። (መልክአ ማርያም)
2 233
ወር በገባ በ20 የታዛዡና የትሁቱ አባታችን የቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር ወርሃዊ መታሰቢያ ነው። እንኳን አደረሰን አደረሳቹ🙏
"ሐፂር" ማለት በግዕዝ "አጭር" ማለት ሲሆን፣ ጻድቁ በቁመታቸው አጭር ቢሆኑም በመንፈሳዊ ቁመናቸው ግን ሰማይ የደረሱ ታላቅ አባት ናቸው።
ዮሐንስ ሐፂር ገና በ18 ዓመታቸው የዓለምን ግርግር ትተው ወደ እስቄጥስ ገዳም ገቡ። በዚያም በአባ ባይሞይ እጅ እየተመሩ የመንፈሳዊ ህይወትን መሠረት መማር ጀመሩ። አባታችን ገና ከጅምሩ የታወቁት በጾምና በጸሎት ብቻ ሳይሆን፣ ለቃለ አበው ባላቸው ፍጹም "መታዘዝ" ነበር።
መምህራቸው አባ ባይሞይ የዮሐንስን ትሕትናና መታዘዝ ለዓለም ለማሳየት አንድ ፈተና አቀረቡላቸው። አንድ የደረቀ እንጨት ሰጧቸውና እንዲህ አሏቸው፦ "ይህን ደረቅ እንጨት ትከለውና ውኃ እያጠጣህ አብቅለው፤ ፍሬ እስኪያፈራም ተንከባከበው።"
ማንኛውም ሰው በምክንያት "ደረቅ እንጨት እንዴት ይበቅላል?" ብሎ ሊጠራጠር ይችላል። ዮሐንስ ግን ምንም ጥያቄ አላነሱም። "እሺ አባቴ" ብለው ተቀበሉ። ለሦስት ዓመታት ሙሉ፣ ውሃ ከሚገኝበት ሩቅ ቦታ በቀን ሁለት ጊዜ እየተመላለሱ ያንን የደረቀ እንጨት አጠጡት።
ከሦስት ዓመት በኋላ ያ ደረቅ እንጨት በተአምር ለመለመ! ታላቅ ዛፍ ሆኖ አብቦና አፍርቶ ጣፋጭ ፍሬ ሰጠ። አባ ባይሞይም ፍሬውን ለሌሎች ቅዱሳን እያደሉ እንዲህ አሉ፦ "የታዛዡንና የትሑቱን ሰው ፍሬ እንሆ ቅመሱ!" ዛሬም ድረስ በግብፅ በገዳመ አስቄጥስ ውስጥ ያ ዛፍ "የመታዘዝ ዛፍ" (Tree of Obedience) ተብሎ እንደ ቆመ ይነገራል።
አቡነ ዮሐንስ በትሕትናቸውና በተጋድሎአቸው እጅግ ከፍ ስላሉ፣ መለኮታዊ ሚስጥር ተገለጠላቸው። ቀና ቢሉ "ሥሉስ ቅዱስን" በግርማ መንግሥታቸው ይመለከታሉ፤ ዝቅ ቢሉ ደግሞ ኃጥአን የሚቀጡበትን "እንጦሮጦስን" ያያሉ። ጌታችንም ስለ ታዛዥነታቸው በገሃድ እየተገለጠ ያነጋግራቸው ነበር።
የታላቁ አባት የቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር በረከታቸው ይደርብን። የደረቀውን ህይወታችንና የከሰመው ተስፋችንን ያለምልሙልን አሜን🙏
2 233
ዛሬ ነሀሴ 19 የገናናው መልአክ የሊቀ መላዕክት የቅዱስ ገብርኤል ወርሃዊ መታሰቢያ ነው። እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ!
ቅዱስ ገብርኤል ከክፉ ሁሉ ይጠብቀን አሜን🙏
2 233
📌ነገሮችን ከማድረጋችን በፊት ቆም ብለን እሺ ከዚያስ ወዲያ ብለን ብንጠይቅ በህይወታችን ብዙ ነገር አይበላሹም። አድርገን ሳይሆን ከማድረጋችን በፊት ቀድመን እናስብ!
አሁን ምናደርገው መጨረሻው ምንድነው?
እኛን ይጠቅመናል ወይስ ይጎዳል?
ሰውንስ ይጠቅማል ወይስ ይጎዳል?
ፈጣሪንስ ያስደሰታል ወይስ ያሳዝናል?
ቆም ብለን እንጠይቅ?
መልካም ቀን🙏🙏
2 233
ጊዜው የይሁዳ ንጉሥ ሕዝቅያስ በኢየሩሳሌም የነገሠበት ወቅት ነበር። ያኔ ምድርን በኃያልነቱና በጭካኔው ያንቀጠቀጠው የፋርስና የአሦር ንጉሥ ሰናክሬም፣ እጅግ ግዙፍና አስፈሪ ሠራዊቱን አስከትሎ ወደ ኢየሩሳሌም መጣ። ቅጽሯን አጥብቆ ከበባት፤ ህዝቡንም በታላቅ ፍርሃት አወከው።
ሰናክሬም በጉልበቱና በሠራዊቱ ብዛት በመታበይ፣ ከንቱ በሆነ ትዕቢት ተሞላ። የሰማይና የምድር ፈጣሪ የሆነውን እግዚአብሔርን በመሳደብና በማንኳሰስ ወደ ንጉሡ ወደ ሕዝቅያስና ወደ ይሁዳ ሕዝብ እንዲህ የሚል መልእክት ላከ፦
"በእውኑ ከእጄ ሊያድናችሁ የሚችል አምላክ አለን? አትታለሉ!"
ንጉሡ ሕዝቅያስ ይህንን ዛቻና በፈጣሪው ላይ የተሰነዘረውን የስድብ ቃል በሰማ ጊዜ ልቡ በሐዘን ተሰበረ። ነገር ግን እንደ ሰናክሬም በጦርና በጋሻ ሳይሆን፣ እውነተኛው መሸሸጊያ በሆነው በፈጣሪው ተማመነ። ንጉሣዊ ልብሱን አውልቆ፣ የትሕትናና የንስሐ ምልክት የሆነውን ማቅ ለበሰ። ቀጥታም ወደ እግዚአብሔር ቤት (ቤተ መቅደስ) በመግባት በግምባሩ ተደፍቶ ሰገደ።
ሕዝቅያስ በዕንባና በታላቅ ልመና ወደ ሰማይ ጮኸ፦ "አምላክ ሆይ! አገራችንንና ቅድስት ከተማችንን ኢየሩሳሌምን ከዚህ ጨካኝ ጠላት እጅ አድን!" እያለ ማለደ።
እግዚአብሔር የሕዝቅያስን ትሕትና፣ የሕዝቡን ጭንቀትና እውነተኛ ጸሎት ሰማ። በዚያች በታላቅ የጭንቀት ሌሊት፣ ፈጣሪ የሰማይ ሠራዊት አለቃ የሆነውን፣ ታላቁን መልአክ ቅዱስ ሚካኤልን ወደ ሰናክሬም ሰፈር ሰደደው።
የብርሃን መልአክ ቅዱስ ሚካኤል እጅግ አስደናቂና አስፈሪ በሆነ መለኮታዊ ኃይል ወደ ሰናክሬም ሠራዊት መሃል ወረደ። በዚያች በአንድ ሌሊት ታላቅ ተአምር ተደረገ፤ የመልአኩ ሰይፍ በጠላት ሰፈር ላይ በተቃጣ ጊዜ፣ ከሰናክሬም ሠራዊት መካከል አሥራ ስምንት ዕልፍ ከአምስት ሺህ (185,000) የሚሆኑት ኃያላን ወታደሮች ሙሉ በሙሉ ወደቁ።
ታላቁ የይሁዳ ሕዝብና ቅድስት ከተማ ኢየሩሳሌም፣ አንድም ሰው ሳይሞትባቸውና ሳይደማባቸው፣ በሚያስደንቅ መለኮታዊ ጥበቃ ከጥፋት ዳኑ። ትዕቢተኛው ንጉሥ ሰናክሬምም በኃፍረትና በውርደት ተመትቶ ሸሸ።
የቅዱስ ሚካኤል ጥበቃ፣ ፈጣን አማላጅነትና ተራዳኢነት ከሁላችን ጋር ይሁን። አሜን🙏
2 233
ዛሬ ሐምሌ 8 የፃድቁ አባታችን የአቡነ ኪሮስ ዓመታዊ የእረፍት በዓል ነው። እንኳን አደረሳችሁ እንኳን አደረሰን🙏
️
አቡነ ኪሮስ ከሮም ነገስታት ወገን ሲሆኑ አባታቸ ንጉስ ዮናስ እናታቸው አንስራ ይባላሉ፡፡ ወላጆቹ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ደጋግ ቅዱሳን ነበሩና አቡነ ኪሮስ በታህሳስ 8 ተወለዱ፡፡ አቡነ ኪሮስ የመጀመሪያ ስሙ ዲላሶር ይባል ነበር፡፡ በኋላ አባቱ ከሞተ በኋላ ሀብቱን ከወንድሙ ተካፍሎ ለድሆች መጽውቶ ዓለምን ንቆ መንኖ ሄደ፡፡ ከአባ በቡነዳ ገዳም ገባ፡፡
በ17 ዓመቱ ሥርዓተ ምነኩስናን ተማረ፡፡ በአባ በቡነዳ እጅ መነኮሰ፡፡ ከዚህ በኋላ በጾም በጸሎት ተወስኖ ኖረ፡፡ስለ ዓለም መከራ ለ40 ዘመን ተኝተው ሲጸልዩ እላያቸው ላይ ሳር በቅሎባቸው ሳለ መላእክት መጥተው ተነስ ቢሉት አዳም የፍጡር ቃል ሰምቶ ወድቀዋል ጌታዬ ድምጹን ያሰማኝ አላቸው በኋላ ኪሩቤል አንስቶ ወስዶ ገነት አሳይተውት ጌታችንም ቃል ኪዳን ሰጣቸእ።
ቃል ኪዳናቸውም መካኖች ልጀ የሌላቸው ገድሉን አቅፈው ቢያለቅሱ ጸበሉን ቢጠጡ ስምህን ቢጠሩ፤ የመካኒቱን ማህጸን እከፍታለሁ፡፡ የሚሞትባቸውን እንዳይሞተባቸው አደርጋለሁ፡ በንጹ ገንዘቡ ቂምና በቀል ሳይዝ በህግ በስጋውና በደሙ የጸና ሰው በስምህም በተሠራው ቤተክርስቲያን ጧፍ ዘይት ያበራ መገበሪያ ያመጣውን ልጅ አሰጠዋለሁ፡፡ ብሎ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ ከዚም በኋላ በተወለዱ 270 ዓመታቸው ሐምሌ 8 አርፈዋል።
የፃድቁ አባታችን የአቡነ ኪሮስ ረድኤት፣ በረከታቸውና አማላጅነታቸው ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን🙏
2 233
ሐምሌ 7 በዚች ቀን ሥላሴ ያደረጉት ተአምር ይህ ነው፡፡
እግዚአብሔርን የሚፈራ ቸር ጻድቅ የሆነ ስሙ አብርሃም የተባለ ምድያም በሚባል አገር አንድ ሰው ይኖር ነበር የሚስቱም ስም ሳራ ይባላል፡፡ እነዚህ ቅዱሳን በሥላሴ ሕግ ተጠብቀው ስደተኛውን እንግዳውን እየተቀበሉ ያስተናግዱ ነበር፡፡ እንግዳ ሳይዙ ወይም ሣይኖር የሰናፍጭ ቅንጠት ሰንኳ ያህል ምግብ ምንም ምን አይቀምሱም ነበር፡፡
የበጎ ነገር ጠላት የሆነ ሰይጣንም ይህን በተመለከተ ጊዜ ከጭፍሮቹ አንዱን እንዲህ ሲል ላከው፡፡ እንግዶች ሁሉ ወደ አብርሃም ቤት እንዳሄዱ በምድያም ገዳና ተቀምጠህ ዕውነቱን በሐሰት ለውጠህ ተናገር፡፡ እንሆ ደምህ በመሬት ላይ እስኪወርድ ድረስ ራስክን በድንጋይ ፈጥፍጠው አለው፡፡
ሰይጣኑም ይህን ትእዛዝ ከተቀበለ በኃላ ወደ ምድያም ወረደና ደሙ በምድር ላይ እስኪፈስ ራሱን በድንጋይ ገምሶ በጎዳና ላይ ተቀመጠ፡፡ በጎዳና የሚያልፋ መንገደኞች ሰዎች ወደ እርሱ በደረሱ ጊዜ እናንት መንገደኞች ከወዴት መጥታችኋል ወዴትስ ትሄዳለችሁ ሲል ጠየቃቸው፡፡መንገደኞቹም እኛስ ወደ ደገኛው ወደ አብርሃም ቤት እንሄዳለን አሉት፡፡
በውኑ አብርሃም ደግነቱ በክፋት እንደተለወጠና ክፋ ሰው እንደሆነ አልሰማችሁምን፡፡እንሆ እንግዳ ከመጥላቱ የተነሳ ደሜ ከመሬት ላይ እንደ ውሃ እስኪፈስ ድረስ የፈተነከተኝን ራሴን መጥታችሁ ተመልከቱ ይልቁንስ በኔ የደረሰ እንዳይደርስባችሁ አትሂዱ አላቸው፡፡
እንግዶቹም ያ ቸርና መልካም ሰው የነበረ አብርሃም ምን ነክቶት ክፋ ሰው ሊሆነ ቻለ በማለት እርስ በራሳቸው ተወያዩ፡፡ ይህንንም ከተባባሉ በኃላ ተመልሰው ወደ ሀገራቸው ሄዱ፡፡
በዚችም ዕለት አብርሃም ከቤቱ ወጥቶ በጎዳና እንግዳ ፈልጉ አጣ፡፡ ከዚያም ወደ ቤቱ ተመልሶ ገባና ምንም ሳይቀምስ ተኛ፡፡
በማግስቱ አምስት ሰዎች ወደ አብርሃም ቤት ሲሄዱ ያ ተንኮለኛ ሰይጣን አገኛቸውና እንደቀድሞ እናንተ ሰዎች ወዴት ትሄዳላችሁ ሲል ጠየቃቸው እነሱም ወደ አብርሃም ቤት እንሄዳለን አሉት፡፡
ሰይጣን መልሶ ወንድሞቼ ሆይ አብርሃም ራሴን ፈንክቶኝ ከማህል ራሴ የሚወርደው ደሜን ተመልከቱ አላቸው፡፡ እንሆ አሁንም እንደኔ እንዳትሆኑ በሰላም ወደ ሀገራችሁ ተመለሱ አላቸው፡፡ በዚህን ጊዜ እነዚያ እንግዶች እርስ በራሳቸው አብርሃም ከሚገድለንስ ወደ ሀገራችን ብንመለስ ይሻላል ተባባሉ፡፡
ዳግመኛም እንደልማዱ ወደ ጎዳና ወጥቶ ፀሐይ እስኪ ጠልቅ ድረስ ሲጠብቅ ውሎ ምንም እንግዳ ሳይገኝ ቀረ፡፡ ከዚያም ወደቤት ተመልሶ ምንም ሳይቀምስ ተኝቶ አደረ፡፡ በሦስተኛውም ቀን አጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ የአብርሃም የልቡን ቆራጥነና የሰይጣንን ተንኮል ተመልክተው ወደ አብርሃም ቤት ሄዱ፡፡ በዚህ ጊዜ የሰይጣን ምክሩ ሁሉ ተሻረ ይዘውም ወደ መጨረሻይቱ የሲኦል ረግረግ ጣሉት፡፡ እሊህ ሥላሴም በእንግዳ ደንብ በአብርሃም በቤቱ ደጃፍ ተቀመጡ፡፡
አብርሃም በደጁ እንደተቀመጡ በተመለከቱ ጊዜ ወደ ቤቱ እሮጦ ገብቶ ለሚስቱ እንዲህ ሲል ነገራት፡፡ እኅቴ ሣራ ሆይ እንሆ የከበሩ አረጋውያን ሦስት እንግዶች መጥተዋልና፡፡
እንግዲህ አንቺ ፈጥነሽ እንጀራና ወጡን ጥሩውን ጠላና መልካሙን ጠጅ አዘጋጂ እኔም የወይፈን ፍሪዳ አርዳለሁ አላት፡፡ ሣራ ሚስቱም እሺ ጌታዬ እንዳልከኝ አደርጋለሁ አለች፡፡ ዳግመኛም ዕርጎውን ማሩን አንድ ታዘጋጅና ለእግራቸው መታጠቢያ ውሀ በምንቸት ታሞቅላቸው ዘንድ አዘዛት፡፡
ከዚህም በኃላ ለእያንዳቸው ለራሳቸው ሦስት ታላላቅ ዳቦ ትጋግር ዘንድ አዘዛት፡፡ አብርሃም ይህን ከተናገረ በኃላ ወይፈኑን አርዶ ሥጋውን በየብልቱ አወጣው፡፡
ከዚያም የታረደውን የወይፈንኑን ሥጋ በትከሻው ተሸክሞ ወደ ቤቱ ይዞ ከገባ በኃላ ለሚስቱ ሰጣትና እኔ እግራቸውን እስካጥብ ድረስ ይህን ሥጋ ቅባቱን በዛ አድርገሽ በጨውና በቅመም አጣፍጠሽ ስሪው አላት እሷም እሺ በጄ አለችው አብርሃምም ከቤቱ መድረክ በስተውጭ ሥላሴን ባገኛቸው ቦታ ላይ ልብሱን አነጠፈና ጌቶች እግራችሁን አጥባችሁ ዘንድ ወደ ወንድማችሁ ቤት ዝለቁ አላቸው፡፡
ከዚህ በኃላ ተነሥተው ወደ ድንኳን ወይም አዳራሽ ገቡና ባነጠፈላቸው ምንጣፍ ላይ ተቀመጡ፡፡ በዚህ ጊዜ የአብን እግር ማጠብ ጀመረና አብን ካጠበ በኋላ ወልድና መንፈስ ቅዱስም ታጥበው አገናቸው ያለመለየት አንድ ናቸውና፡፡ በዚህ ጊዜ ማዕዱን በገበታ ሠርቶ ወይኑንም በማድጋ ቀድቶ አቀረበላቸውና እስኪጠግቡ ድረስ በሉ ጠጡ፡፡
ማዕዱ ከተነሣ በኋላ ለእንግዶች እራት የታረደው ወይፈን በቤቱ በራፍ ፊት ለፊት ከውጭ በኩል ቆሞ አየው፡፡ አብርሃም ይህን ወይፈን ባየ ጊዜ ፈጽሞ ፈራ ተንቀጠቀጠ፡፡
በዚህ ጊዜ ሥላሴ አብርሃም ሆይ ሰይጣን እንደቀናብህ ጠንቅቀህ እወቅ እንግዳ በመጣልህ ጊዜ በብሩህ ልቡና እና በንቁ ኅሊና ሆነህ ተቀበለው፡፡ ነገር ግን እንግዳ ካልመጣ እራትህን በጊዜ ብላ መጠጥህንም ጠጣ እንጂ ጦምህን አትደር አሉት፡፡
ይህንንም ተናግረው እኒህ በአምሳልና በህልውና ትክክል የሆኑ ሥላሴ ወደ ሰማይ አረጉ፡፡ ይህም ሁሉ የሆነው ሐምሌ ሰባት ቀን ነው፡፡ የምድያም ሰዎች ስለዚህ ለምግብ ከተዘጋጀ በኃላ ሥላሴ ሰላስነሡት ወይፈን እንዲሁም በሥላሴ ዘንድ በተደረጉት ድንቅ ድንቅ ሥራዎች ሁሉ ፈጸመው ተደነቁ፡፡
ይቅርታቸው ሀብተ ረድኤታቸው በመላው ህዝበ ክርስቲያን ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን፡፡
(ሰይፈ ሥላሴ ዘእሁድ)
2 233
ሰላም ለቃልኪ፦ የተበተነ ልቡናን ለሚሰበስብ ቃልሽ ሰላምታ ይገባል፡፡ የኃጢአት ደዌን ለሚፈውሰው መድኃኒት ለሆነው እስትንፋስሽም ሰላምታ ይገባል፡፡ ተስፋ ለቆረጡት ተስፋ፣ ለደከሙትም መጽናኛ የሆንሽ ቅድስት አርሴማ ሆይ ጨለማው በማይገፋ እሳቱም በማይጠፋ በጭንቅ ቀን በታመነው ቃል ኪዳንሽ ፈጽመሽ አድኚኝ፡፡ 🙏
መልክአ ቅድስት አርሴማ
