en
Feedback
ገድለ ቅዱሳን

ገድለ ቅዱሳን

Open in Telegram

@Gedelat ለተለያዩ አስተያየት እና ጥቆማ ማድረስ ከፈለጉ በአድራሻችን ቢያደርሱን ይደርሰናል፡፡ በአድራሻችን ✍ @Mnfesawi_bot

Show more
6 509
Subscribers
-124 hours
-77 days
-2530 days
Posts Archive
photo content
+3

🌼 ከዚህም በኋላ መጽሩስ መኰንን ከአማካሪዎቹ ጋር ተማከረ እንዲህም አላቸው "ስሙ ፋሲለደስ ስለሚባል ስለዚህ ሰው ምን ላድርግ እርሱን ያላሠቃየሁበት የሥቃይ መሣሪያ ምንም የቀረ የለም ከሐሳቡም አልተመለሰም" እነርሱም እንዲህ ብለው መከሩት "ራሱን በሰይፍ ቆርጠህ ከእርሱ ተገላገል እነሆ የዚች አገር ሰዎች በእርሱ ምክንያት አልቀዋልና"። 🌼 በዚያንም ጊዜ የቅዱስ ፋሲለደስን ራስ በሰይፍ እንዲቆርጡ መኰንኑ አዘዘና ቆረጡት የድል አክሊልን ተቀበለ ንቆ ሰለ ተዋት ምድራዊት መንግሥት ፈንታም ሰማያዊት መንግሥት አገኘ። ከሥጋውም ድንቆች የሆኑ ታላላቅ ተአምራት ተገለጡ ከእርሱም ጋር ሰማዕት ሁነው የሞቱ ሁሉም ቊጥራቸው ሃያ ሦስት ሺህ ሰባት መቶ ዘጠና ሦስት ሆነ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕቱ ቅዱስ ፋሲለደስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                              ✝ ✝ ✝ 🌼 #ቅዱስ_ቆርኔሌዎስ፦ ይህም ቅዱስ የጭፍራ አለቃ የሆነ ትሩፋቱና ገድሉም ያማረ ጻድቅ፤ በቅዱሳን አባቶቻችን ሐዋርያት ዘመን እግዚብሔርን ያገለገለ ነው። 🌼 የእግዚአብሔር መልአክም ተገልጦለት ሐዋርያ ጴጥሮስን ይጠሩት ዘንድ ሰዎችን እንዲልክ ጴጥሮስም ወደርሱ እንዲመጣ ሊሠራው የሚገባውን ከእርሱ ከጴጥሮስ እንዲሰማ አዘዘው። 🌼 ጴጥሮስም ወደርሱ በደረሰ ጊዜ የእግዚአብሔርን ቃል አስተማረው ለርሱና ከእርሱ ጋር ላሉት ሁሉ ከሁሉ ቤተሰቡ ጋር አምኖ ተጠመቀ። ከዚህ በኋላ ጴጥሮስ ለእስክንድርያ አገር ቅስና ሾመው ወደርሷ በደረሰ ጊዜ የጣዖታትን አምልኮ ተመልታ አገኛትና አስተማራቸው ብዙዎችንም ወደቀናች ሃይማኖት መልሶ አጠመቃቸው መኰንኑ ድሜጥሮስም አምኖ ከወገኖቹ ጋር በእርሱ እጅ ተጠመቀ። 🌼 የኑሮውን ዘመንና ሐዋርያዊ ተጋድሎውን አድርሶ በሰላም አረፈ እርሱም ከአሕዛብ አስቀድሞ ያመነ የመጀመሪያ አማኒ ነው።                              ✝ ✝ ✝ 🌼 #ቅድስት_ታዖድራ፦ ይችንም ቅድስት ሌላ ሰው አስገድዶ ከባሏ ወስዶ ከባሏ ጋር ያላትን አንድነት አበላሸ ያን ጊዜም ታላቅ ኀዘን በማዘን ተጸጸተች መሪር ልቅሶንም አለቀሰች የወንዶችንም ልብስ ለብሳ ወንድ መሰላ ከእስክንድርያ በሥውር ወጣች ስሟንም ቴዎድሮስ ብላ ሰየመችና ወደ ወንዶች ገዳም ገባች የምንኲስና ልብስንና የመላእክትን አስኬማ ለበሰች። የሚያዩዋት ሁሉ እርሷ እንደ ጃንደረባ የሆነች ወንድ ትመስላቸው ነበር እርሷ ግን በረኃብ፣ በጽምዕ ሌሊት በመትጋት ቀን በመቆም ጸንታ በመጋደል ላይ ታገሠች እንዲህም በመጋደል ተጠምዳ ብዙ ዘመን ኖረች። 🌼 በዚያም ወራት እንዲህ ሆነ አንድ ሰው ከአንዲት ብላቴና ጋር አመነዘረ እርሷም ፀንሳ ወንድ ልጅን ወለደች ወላጆቿም "ድንግልናሽን ያጠፋው ማነው" ብለው ጠየቋት እርሷም "በገዳም ውስጥ የሚኖር አባ ቴዎድሮስ እርሱ ደፍሮኝ ከእርሱ ፀነስኩ" ብላ በዚች ቅድስት ታኦድራ ላይ በሐሰት ተናገረች። 🌼 ወላጆቿም በሰሙ ጊዜ እጅግ አዘኑ ሕፃኑንም ወደዚያ ገዳም አበ ምኔት ወሰዱት እንዲህም አሉት "ይህ ሕፃን የልጅህ የመነኵሴው የቴዎድሮስ ልጅ ነው"። ያን ጊዜም አበ ምኔቱ ይቺን ቅድስት ታኦድራን ጠራትና እንዲህ አላት "ይህን ክፉ ሥራ ለምን ሠራህ በመነኰሳቱም ሁሉ ላይ ኀፍረትንና ጒስቁልናን አመጣህ" እርሷ ሴት መሆኗን አላወቀምና እርሷም አባቴ ሆይ "በድያለሁና ይቅር በለኝ" አለችው። 🌼 አበ ምኔቱም ተቆጥቶ ከገዳሙ አስወጥቶ አባረራት በበረሀ ውስጥ ሰባት ዓመት ኖረች ያም ሕፃን ከእርሷ ጋር ሁኖ ከሰይጣናት በሚመጡባት በብዙ መከራዎች ብዙ መከራዎች ላይ ታገሠች ብዙ ሥቃያትንም ፈጽሞ አሠቃዩዋት። 🌼 ከዚህም በኋላ ዳግመኛ ተቀብለው ወደ ገዳም አስገቡአት ጥቂት ቀንም ኖረች መልካም ተጋድሎዋንም ፈጽማ በሰላም አረፈች ነፍሷንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጥታ የዘላለም ሕይወትን አገኘች። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት ታኦድራ ጸሎት ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                             ✝ ✝ ✝ 🌼 #ሰማዕቷ_ቅድስት_በነፍዝዝ፦ የስሟ ትርጓሜ ጣፋጭ የሆነ ማለት ነው።  ይቺም ቅድስት በእድሜዋ ፈጽማ የሸመገለች ነበረች በፋርስ ንጉሥ በሳቦር ዘመንም መከራ ተቀበለች ከዘጠኝ መቶ ክርስቲያን ጋር ማርከው ወስደው አሠሩዋት የሠራዊቱም አለቃ ታላቅ ሥቃይን አሠቃይቶ ከዚያ በኋላ ራሷን በሰይፍ ቆረጠ። 🌼 ራሷንም ከአስቆረጣት በኋላ ከአንገቷ የፈሰሰው ደም እስከ ራቀ ድረስ ወደ ላይ ወጣ ከዚያ የተቀመጡ ጠላቶችም ኃይላቸው ደከመ። የፀሐይ ብርሃንም ጨለመ በዚያም ቦታ ደግሞ ጣፋጭ የሆነ መዐዛ ተመላ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት በነፍዝዝ ጸሎት ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                               ✝ ✝ ✝ 🌼#የእስና_አገር_ሰዎች_ሦስቱ_ቅዱሳን_ሰማዕታት #ገበሬዎች_ሱርስ_አጤኬዎስ_መስተሐድራ፦ አርያኖስም ከሀገሪቱ በስተደቡብ ምንም ሳያስቀር ወታደሮቹ እስከ ደከሙ ድረስ ሰይፋቸውንም ወደ አፎቱ መልሰው ነበር የአገር ሰዎችን ጨርሶ ገድሎ ሲመለስ እሊህ ሦስቱ ገበሬዎች ከዱር ሲመለሱ በከተማ መካከል በተገናኙት ጊዜ "እኛ ክርስቲያኖች ነን" ብለው በግልጥ ጮኹ አርያኖስም ሰምቶ ወታደሮቹን "እሊህን ገበሬዎች ትገድሏቸው ዘንድ ይገባል" አላቸው። 🌼 ወታደሮቹም "እኛ ደክመናል ሰይፎቻችንንም ወደ አፎታቸው አስገብተናል" አሉት እሊህ ቅዱሳንም ሰምተው "እነሆ መቆፈሪያዎች ከእኛ ጋራ አሉ" በእነርሱ ግደሉን አሉ ከዚያም አንገታቸውን በደንጊያ ላይ አድርገውላቸው ቆረጡአቸው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የመስከረም 11 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ 🌼 "#ሰላም_ለፋሲለደስ_እምነ ክሣዱ ዘአንጠብጠበ። ደመ ቀይሐ ወጸዓድዒደ ሐሊበ። ምስለ አዝማዲሁ ወሰብኡ እስመ ለሞት ተውህበ። በከመ ኮኖሙ ዲበ ምድር አበ። ዘበሰማያት ተሠይመ አቡሆሙ ካዕበ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የመስከረም 11።                          ✝ ✝ ✝ 🌼 #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ተንሥኡ ላዕሌየ ሰማዕተ ዐመፃ። ወዘኢየአመር ነበቡ ላዕሌየ። ፈደዩኒ እኪት ህየንተ ሠናይት"። መዝ 34፥3-4። የሚነበበው ወንጌል 16፥24-ፍ.ም።                            ✝ ✝ ✝ 🌼 #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወይርአዩ አሕዛብ በቅድመ አዕይንቲነ። በቀለ ደሞሙ ለአግብርቲከ ዘተክዕወ። ይባዕ ቅድሜከ ገዐሮሙ ለሙቁሓን"። መዝ 78፥10-11። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 12፥1-12፣ ያዕ 3፥1-13፣ የሐዋ ሥራ 10፥1-9። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 21፥12-21። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ፋሲለደስ የዕረፍት በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።                   @Teamihokidusan

🌼 "በስመ አብ ወወልደ  ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌼            🌼 #መስከረም ፲፩ (11) ቀን። 🌼 እንኳን #ለአንጾኪያ_ነገሥታት_አባታቸው፤ መካሪያቸው ለሆነ በዲዮቅልጥያኖስ ዘመን ለነበረው፤ ጌታችን ከሞት እያስነሣው በጽኑ ሥቃይና ተጋድሎ ሲጋደል ለኖረው ለታላቁ ሰማዕት #ለቅዱስ_ፋሲለደስ፣ #በቅዱሳን_አባቶቻችን_ሐዋርያት ዘመን እግዚአብሔርን ያገለገለ #የጭፍራ_አለቃ (፻አለቃ) ለሆነ ትሩፋቱና ገድሉም ላማረ ለጻድቁ ሰው #ለቅዱስ_ቆርኔሌዎስ ለዕረፍታቸው በዓል፣ ለእስክድርያ አገር በንጉሥ ዘይኑን ዘመን ለነበረች #ለቅድስት ታዖድራ ለዕረፍቷ በዓል እግዚአብሔር አምላክ ሰላም አደረሰን፡፡ በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ የስሟ ትርጓሜ ጣፋጭ ከሆነ ከከበረች #ከሰማዕቷ_ከቅድስት_በነፍዝዝ ከዕረፍት በዓል፣ #ስማቸው_ሱርስ_አጤኬዎስና_መስተሐድራ ከሚባሉ ሦስት ገበሬዎች ከእስና አገር ሰዎች በሰማዕትነት ከዐረፉ፣ #ከቅዱሳን_ከባስልዮስ ሰማዕትና #ከኢየሩሳሌም_ኤጲስቆጶስ_ከቴዎድሮስ ከሰማዕት አለቃ #ከቀውስጦስም ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                       ✝ ✝ ✝ 🌼 #ለአንጾኪያ_ነገሥታት_አባታቸውና_መካሪያቸው የሆነው #ሰማዕቱ_ቅዱስ_ፋሲለደስ፦ እርሱም ለሮም ንጉሥ የሠራዊት አለቃ ነው መንግሥቱም ሁለመናዋ በእርሱ ምክር የጸናች ናት። ብዙዎችም ወንዶችና ሴቶች የቤት ውልዶች አገልጋዮች አሉት። 🌼 ዝምድናውም እንዲህ ነው ስሙ ኑማርያኖስ የተባለ የሮም ንጉሥ ለቴዎድሮስ በናድሌዎስ እናቱ የሆነች የቅዱስ ፋሲለደስን እኅት አግብቶ ዮስጦስን፣ ገላውዴዎስን፣ አባዲርን ወለደችለት እሊህም ለቅዱስ ፋሲለደስ የእኅቱ ልጆች ናቸው። የቅዱስ ፋሲለደስም ሚስት ለቅዱስ ፊቅጦር እናት እኅት ናት ከእርሷም ስማቸው አውሳብዮስና መቃርስ የተባሉ ሁለት ልጆችን ወለደ። 🌼 በዚያም ወራት የቊዝና የፋርስ ሰዎች የሮምን ሰዎች ሊወጓቸው በላያቸው ተነሡ ያን ጊዜ የንጉሥ ልጅ ዮስጦስን የፋሲለደስ ልጅ አውሳብዮስን ከጦር ሠራዊቶቻቸው ጋር ለውጊያ ላኳቸው። ንጉሡ ኑማርዮስም ሌሎች ጠላቶች በተነሡበት በኩል ለጦርነት ሒዶ በውጊያው ውስጥ ሞተ የሮም መንግሥትም የሚጠብቃትና የሚመራት የሌላት ሆነች። 🌼 እንዲህም ሆነ በዚያ ወራት ስለ ጦርነት ለመደራጀት የሮም ሰዎች ከሀገሩ ሁሉ አርበኞች የሆኑ ሰዎችን ሰበሰቡ ከውስጣቸውም ከላይኛው ግብጽ ስሙ አግሪጳዳ የሚባል የፍየሎች እረኛ የሆነ አንድ ሰው አለ። እርሱንም መኳንንቱ ወስደው በመንግሥት ፈረሶች ላይ ባልደራስ አድርገው ሾሙት እርሱም በጠባዩና በሥራው ሁሉ ኃይለኛና ብርቱ ነበር። 🌼 ከንጉሥ ኑማርያኖስ ሴቶች ልጆች አንዲቱ ወደርሱ በመስኮት ተመለከተች ወደደችውም መልምላም ወስዳ አገባችው ስሙንም ዲዮቅልጥያኖስ ብላ ሰይማ አነገሠችው። ከጥቂት ቀኖችም በኋላ ሰማይና ምድርን የፈጠረ እግዚአብሔርን ትቶ ጣዖታትን አመለከ ቅዱስ ፋሲለደስም ሰምቶ እጅግ አዘነ የመንግሥትንም አገልግሎት ተወ። 🌼 ከዚህም በኋላ የንጉሥ ኑማርያኖስ ልጅ ዮስጦስና የፋሲለደስ ልጅ አውሳብዮስ ጠላቶቻቸውን ድል አድርገው የጠላቶቻቸውንም አገሮች አጥፍተው ደስ ብሏቸው ተመለሱ። ነገር ግን የነገሠው ዲዮቅልጥያኖስ የክብር ባለቤት ክርስቶስን ክዶ አምልኮ ጣዖትን አቁሞ አገኙት እጅግም አዘኑ ተቆጥተውም ተነሡ ሰይፎቻቸውን መዝዘው ዲዮቅልጥያኖስን ገድለው የንጉሥ ኑማርያኖስን ልጅ ዮስጦስን ሊያነግሡ ወደዱ ፋሲለደስም ከዚህ ሥራ ከለከላቸው። 🌼 ከዚህም በኋላ ቅዱስ ፋሲለደስ ዘመዶቹን፣ ሠራዊቱን፣ አገልጋዮቹንም ሁሉ ሰበሰባቸውና በክብር ባለቤት በክርስቶስ ስም ደሙን ሊያፈስ እንደፈለገ አስረዳቸው ሁሉም እንዲህ ብለው መለሱለት "አንተ በምትሞትበት ሞት እኛ ከአንተ ጋር እንሞታለን" በዚህም ምክር በአንድነት ተሰማሙ። 🌼 ከዚህም በኋላ በንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ፊት ቁመው ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመኑ ከእርሳቸውም ግርማ የተነሣ ታላቅ ፍርሃትን ፈራ እነርሱ የመንግሥት ልጆች ናቸውና። 🌼 የቅዱስ ፊቅጦር አባት ኅርማኖስም ወደ ግብጽ አገር ይልካቸው ዘንድ በዚያም እንዲያሠቃዩዋቸው መከረው ሁሉንም እየአንዳንዳቸውን ለብቻቸው አድርጎ ላካቸው አባዲርንና እኀቱ ኢራኒን ወደ አንዲት አገር፣ አውሳብዮስንና ወንድሙ መቃርስን ወደሌላ ቦታ፣ ገላውዴዎስንም እንዲሁ አደረጉ። በናድሌዎስ ቴዎድሮስም እሼ በሚባል ዕንጨት ላይ በመቶ ሃምሳ ሦስት ችንካር ተቸንክሮ ገድሉን ፈጸመ። 🌼 ቅዱስ ፋሲለደስን ግን አምስት ከተማዎች ወዳሉበት ወደ አፍሪካ ምድር ወደ መኰንኑ ወደ መጽሩስ ላከው መጽሩስም በአየው ጊዜ መንግሥቱን ክብሩን ስለ ተወ እጅግ አደነቀ። ክብር ይግባውና ጌታችን ክርስቶስም መልአኩን ልኮ በመንፈስ ወደ ሰማይ አውጥቶ በብርሃን ያጌጠ መንፈሳዊ ማደሪያን አሳየው ነፍሱም እጅግ ደስ አላት ከዚህም በኋላ ወደነበረበት መለሰው። ባሮቹን ግን ነፃ ያወጣቸው አሉ የቀሩትም ከእርሱ ጋር የሰማዕትነት አክሊልን የተቀበሉ ሰባት ሺህ ሠላሳ ሦስት የሚሆኑ አሉ። 🌼 ቅዱስ ፋሲለደስንም ታላቅ ስቃይን አሰቃዩት በመንኰራኲርና በተሣሉ የብረት ዘንጎች ሥጋውን ሰነጣጥቀውት ሞተ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ያለ ጥፋት ከሞት አድኖ አስነሣው አሕዛብም ሁሉ ይህን ድንቅ ተአምር በአዩ ጊዜ አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አመኑ መኰንኑንም ረገሙት ጣዖቶቹንም ሰደቡ በእነርሱ ላይም ተቆጥቶ ራሶቻቸውን በሰይፍ ይቆርጧቸው ዘንድ ወታደሮቹን አዘዘ የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበሉ ቊጥራቸውም ዐሥራ አራት ሺህ ሰባት መቶ ወንዶች ሠላሳ ሰባት ሴቶች ናቸው። 🌼 ከዚህም በኋላ ቅዱስ ፋሲለደስን ሥጋው ሁሉ ቀልጦ እንደ ውኃ እስከሚሆን በብረት ምጣድ ውስጥ አበሰሉት መኰንኑም በተራራ ላይ ጥልቅ ጒድጓድ ቆፍረው በዚያ እንዲቀብሩት አዘዘ እንዲሁም አደረጉ። ያን ጊዜም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ፋሲለደስን ከሞት ደግሞ አስነሣው ወደ መኰንኑም መጥቶ እንዲህ ብሎ ጮኸ "መኰንን መጽሩስ ሆይ እፈር ከሀዲ ንጉሥህም የረከሱ ጣዖቶችህም ይፈሩ እነሆ ክብር ይግባውና ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ያለ ጉዳት ከሞት ጤነኛ አድርጎ አስነሥቶኛልና"። ሕዝቡም ይህን ተአምር በአዩ ጊዜ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምነው በሰማዕትነት ሞቱ ቁጥራቸውም ሁለት ሺህ ሦስት መቶ ሆነ። 🌼 ከዚህም በኋላ ቅዱስ ፋሲለደስን በውስጧ መጋዝ ካላት መንኰራኲር ላይ አውጥቶ ታላቅ ሥቃይን አሠቃየው ዳግመኛም በብረት ዐልጋ ላይ በሆዱ አስተኝተው ከበታቹ እሳትን አነደዱ ያን ጊዜም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጠለት ከዚያ ስቃይም ውስጥ አንስቶ ያለ ጉዳት ጤነኛ አደረገው እንዲህም ብሎ ቃል ኪዳን ሰጠው "ፋሲለደስ ሆይ ዕውቅ መታሰቢያህን ለሚያደርግ ሁሉ ወይም ለድኆች በስምህ ምጽዋትን ለሚሰጥ ወይም ለተራቈተ ልብስን ወይም በመታሰቢያህ ቀን ለቤተ ክርስቲያን መባ ለሚሰጥ በብዙም ቢሆን በጥቂት መታሰቢያህን ለሚያደርጉ ሁሉ እኔ በደላቸውን ሁሉ እተውላቸዋለሁ መኖሪያቸውንም በመንግሥተ ሰማያት ከአንተ ጋራ አደርጋለሁ"። ጌታችንም ይህን ካለው በኋላ በታላቅ ክብር ወደ ሰማያት ዐረገ ቅዱስ ፋሲለደስም በፍጹም ደስታ ደስ ተሰኘ።

photo content

🌼 "በስመ አብ ወወልደ  ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌼            🌼 #መስከረም ፲፩ (11) ቀን። 🌼 እንኳን ለኢትዮጵያዊው ጻድቅ ለታላቁ አባት #ለአቡነ_አናንያ የዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                         ✝️ ✝️ ✝️ 🌼  #አቡነ_አናንያ የተባሉት ታላቅ ጻድቅ ከቤተ ኤዎስጣቴዎስ የተገኙ ሲሆን በዐፄ ይስሐቅና ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን የኖሩ ሲሆን ገድል ተጽፎላቸዋል፡፡ ( cf. Kinefe-Rigb, JES 13, vol.2, item no. 15) ገዳማቸው ኤርትራ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ገድልም ተጽፎላቸዋል፡፡ 🌼 ስለጻድቁ የተጻፈ ዝርዝር መረጃ ለጊዜው ባናገኝም ከገዳማቸው የተገኘው ማስታወሻ እንደሚናገረው ጻድቁ የተወለዱት ኤርትራ ሠራየ ውስጥ ልዩ ስሙ "ማይ ልሓም" በሚባል ቦታ ነው፡፡ ወላጆቻቸውም ፈሪሃ እግዚአብሔር የነበራቸው ደጋግ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ 🌼 የአቡነ አናንያ የምንኵስና ትውልዳቸው ከአቡነ ኤዎስጣቴዎስ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ አባ በኪሞስን ያመነኵሳሉ፣ አባ ኪሞስ አባ ጳውሎስን፣ አባ ጳውሎስ ደግሞ አቡነ አናንያን ያመነኵሳሉ፡፡ ጻድቁ በጾም ጸሎት በገዳማዊ ሕይወታቸው የጸኑ መንፈሳዊ ተጋዳይ ሲሆኑ ለፍጥረቱ ሁሉ የሚራሩ ሩኅሩኅ በመሆናቸው በዚህ ይታወቃሉ፡፡ 🌼 ጻድቁ አቡነ አናንያ አቡነ አናንያ በተወለዱበት ቦታ ላይ ታላቅ ገዳም ያላቸው ሲሆን የአባታቸው የአባ ጳውሎስና የእርሳቸው ዐፅም አንድ ላይ በገዳማቸው ውስጥ በክብር ዐርፎ ይገኛል፡፡ 🌼 ከመቃብራቸውም ብዙ አስገራሚ ተኣምራት ተገልጠው ታይተዋል፡፡ በገዳማቸው ያለው ፈዋሽ ጠበልም እስከአሁን ድረስ ብዙ ተኣምራት እያደረገ ይገኛል፡፡ የጻድቁ ዕረፍታቸው መስከረም 11 ነው፡፡ ከአቡነ አናንያ እግዚአብሔር ረድኤት በረከትን ያሳትፈን፣ በጸሎታቸው ይማረን!፡፡ 🌼 አቡነ አናንያ የሚባሉ ሌላም የሸዋ ተወላጅ ጻድቅ መኖራቸውን ሊቀ ብርሃናት መርቆሬዎስ አረጋ ጽፈዋል፡፡ ይኽም ጻድቅ የትውልድ ሀገራቸው ሸዋ ተጉለት ልዩ ስሙ በረከት መንደር አቡዬ ገዳም ተወለዱ፡፡ ይኽም ጻድቅ ዋልድባን ከመሠረቱት 800 ቀደምት አበው ቅዱሳን ውስጥ አንዱ ናቸው። ምንጭ፦ ከገድላት አንደበት።                    @Teamihokidusan

photo content

[ የእግዚአብሔር ሕግ - ፴፫ - ] .mp312.08 MB

🕊 💖 🕊 [ 🕊 ድምፀ ተዋሕዶ 🕊 ] 🍒 🍒 [ ሕይወት የሚገኝባቸው የቅድስት ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቶች በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በድምፅ ይቀርባሉ። ] [ ሳምንታዊ መርሐ-ግብር ]
🕊                        💖                       🕊           [  🕊  ድምፀ ተዋሕዶ   🕊  ]   🍒                                                    🍒 [  ሕይወት የሚገኝባቸው የቅድስት ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቶች በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በድምፅ ይቀርባሉ።  ]         [   ሳምንታዊ መርሐ-ግብር   ] 🩵                        †                         🩵 [  ❝ የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው ! ❞  ]             [    ክፍል ሠላሳ ሦስት   ]           💛   ድንቅ ትምህርት  💛 [ በመምህራችን ቀሲስ ኅብረት የሺጥላ ] 🍒                                                    🍒 ❝ የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ፥ ከመከራም ሥጋት ያርፋል። ❞ [ ምሳ.፩፥፴፫ ] ════════════════                            †††                ✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟ 🕊                        💖                       🕊                              👇

photo content
+1

[ ስንክሳር መስከረም - ፲ - ] .mp32.86 MB

🕊 † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን † [   † መስከረም ፲ [ 10 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት †  ] †   🕊  በዓለ ስዕለ አድኅኖ   🕊   † ይህች ቀን በቤተ ክርስቲያን ስለ ቅዱሳት ስዕላት የሚነገርባት ክብርት ቀን ናት:: 'ስዕለ አድኅኖ' ማለት 'እግዚአብሔር በረድኤት የሚገለጥበት: አንድም በቅዱሳኑ አማካኝነት ጸጋ የሚገኝበት: የሚያድን ስዕል' ማለት ነው:: ስለዚህ ነገር አንዳንዶቹ ሊነቅፉን ይፈልጋሉ:: እኛ ግን ከማን እንደ ተማርነው እናውቃለን:: ከመነሻው እኛ ስዕልን አናመልክም:: ይልቁኑ አምልኮን እንፈጽምበታለን እንጂ:: ስዕልን ለሰው ልጆች የሰጠ ራሱ ባለቤቱ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ ይመሠክራል:: እንዲያውም የመጀመሪያው ሰዐሊ ራሱ አምላካችን ነው:: አዳምን እንደ መልኩ: በምሳሌው ሲፈጥረው መላእክት የእግዚአብሔርን ምስል አዳም ላይ አይተዋልና:: [ዘፍ.፩፥፳፮] (1:26) ለሙሴም ስዕለ ኪሩብን እንዲስል ያዘዘ ራሱ ነው:: [ዘጸ.፳፭፥፳፪] (25:22) በዚያም ላይ ሆኖ ሙሴና አሮንን ሲነጋገራቸው ኑሯል:: በመቅደሰ ሰሎሞንም ተመሳሳይ ነገርን እናገኛለን:: [፪ዜና.፯፥፲፪] (7:12) , ፩ነገ.፱፥፩] (9:1) በሐዲስ ኪዳንም ጌታ ስዕለ ኪሩብ ያለበትን መቅደስ ቤቴ [ማቴ.፳፩፥፲፫] (21:13): የአባቴ ቤት [ዮሐ.፪፥፲፮] (2:16) ሲለው: በቅዱስ ሰውነቱ ሲመስለውም [ዮሐ.፪፥፳፩] (2:21) እንመለከታለን:: ቅዱስ ዻውሎስ ለገላትያ ሰዎች ስለ ስዕለ ስቅለት ሲያስታውሳቸው [ገላ.፫፥፩] (3:1): ቅዱስ ዮሐንስም በራዕዩ በደም የተረጨች ልብስ ብሎ ያላትን መተርጉማን ያትታሉ:: [ራዕይ.፲፱፥፲፫] (19:13) በትውፊት ትምሕርት ደግሞ የመጀመሪያው ስዕል በቅዱስ ሚካኤል ክንፍ ላይ የተሳለ ሲሆን ስዕሉም የእመቤታችን ነው:: "ሚካኤል በክነፊሁ ጾራ መንጦላዕተ ደመና ሠወራ" እንዳለ ቅዱስ ያሬድ:: በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአቃርዮስና ለቬሮኒካ ፲፪ [12] ዓመት ደም ይፈሳት ለነበረችው ሴት) መልክአ ገጹን ሠጥቷቸዋል:: ['ቬሮኒካ' በላቲን 'ቬሮን-ኢኮን' 'እውነተኛ መልክ' እንደ ማለት ነው] ቀጥሎም ዮሐንስ ወንጌላዊ ለጢባርዮስ ቄሣር ስዕለ ስቅለቱን ሲስልለት ቅዱስ ሉቃስ ደግም የእመቤታችን 'ምስለ ፍቁር ወልዳን' ስሏል:: ከዚያም ሲያያዝ ይሔው ከእኛ ደርሷል:: ነገር ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይ በከተሞች አካባቢ ቅርጾች በዝተዋልና ይሔ አላስፈላጊ መዋስ [ያውም ከመናፍቃን] ቢቀር መልካም ነው ባይ ነኝ:: ኋላ ቁጭ ብለው የሰቀሉትን ቁሞ ማውረድ ከባድ ነውና:: †   🕊   ጼዴንያ    🕊   † በዚህች ቀን ቅዱስ ሉቃስ የሳላትና ሥጋን የለበሰችው: ከፊቷም ወዝ የሚወጣትና ድውያንን የምታድነው የድንግል ማርያም ስዕለ አድኅኖ ወደ ጼዴንያ ከወዳጇ ከብጽዕት ማርታ ዘንድ ገብታለች:: ቅድስት ማርታ ሃብት ንብረቷን በአብርሃማዊ ተግባር [በምጽዋትና እንግዳን በመቀበል] ላይ ያዋለች ክብርት ሴት ናት:: ለእመ ብርሃን ካላት ፍቅር የተነሳ እንቅልፍ አልነበራትም:: ተግታ ታገለግላትም ነበር:: ስዕሏን እንዲያመጣላት የላከችው ኢትዮዽያዊው መነኩሴ አባ ቴዎድሮስ የስዕሏን ተአምራት ባየ ጊዜ ለራሱ ለመውሰድ ሞክሮ ነበር:: [እርሱ ምን ያድርግ! እኔም ብሆን ይህንኑ ነበር የማደርገው] ነገር ግን ከሁሉም በተሻለ የምትወዳት ቅድስት ማርታ ነበረችና በድንቅ ተአምር: በዚህች ቀን ወደ ጼዴንያ ገብታለች:: ቅድስት ማርታም ያለ ዕረፍት ስታገለግላት ኑራ ዐርፋለች:: ይህቺ ክብርት ስዕለ አድኅኖ የአሁን መገኛ 4 መረጃዎች አሉ:- ፩. ያለችው ኢትዮዽያ ውስጥ [ደብረ ዘመዳ በሚባል ገዳም] ነው:: የመጣችውም ከግማደ መስቀሉ ጋር ነው:: ፪. ያለችው በቀደመ ቦታዋ ነው:: ፫. የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት ወስደዋታል:: ፬. በፈጣሪ ጥበብ ተሰውራለች:: †   🕊  ልደታ ለማርያም  🕊   † በግብጽ ውስጥ ከሚገኙ ገዳማት በአንዱ: ማለትም በአስቄጥስ ደብረ አባ መቃርስ የእመቤታችንን ዜና ሕይወት የሚናገር ፩ [1] መጽሐፍ አለ:: መጽሐፉ እንደሚለው እመ ብርሃን ድንግል ማርያም የተጸነሰችው ታሕሳስ ፲፯ [17] ቀን ነው:: በዚህ ሒሳብ መሠረት ደግሞ እመ አምላክ የተወለደችው መስከረም 10 ቀን ነው:: ዓለማቀፍ ትውፊቱ ግን ነሐሴ ፯ [7] ተጸንሳ: ግንቦት ፩ [1] ቀን መወለዷን ያሳያል:: †  🕊 ተቀጸል ጽጌ / አጼ መስቀል  🕊  † 'ተቀጸል ጽጌ' ማለት 'መስቀል ሆይ! በአበባ አጊጥ' እንደ ማለት ሲሆን 'አጼ መስቀል' ደግሞ አጼ ገብረ መስቀልን: አንድም አፄ ዳዊት ቀዳማዊን ይመለከታል:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:- በሃገራችን ኢትዮዽያ የነገረ መስቀሉ ትምሕርት ከመጣ ጀምሮ መስቀል ይከበራል:: በአደበባባይ ግን እንዲከበር ያደረጉት የቅዱስ ካሌብ ልጅ አፄ ገብረ መስቀል ናቸው:: በወቅቱ ንጉሡ: ሠራዊቱ: ዻዻሱና ሕዝቡ በተገኙበት ቅዱስ ያሬድ "መስቀል መልዕልተ ኩሉ ነገር: ያድኅነነ እምጸር-መስቀል ከሁሉ ነገር በላይ ነው: ከጠላትም ያድነናል" እያለ ይዘምር ነበር:: የአበባ ጉንጉንም ለመስቀሉና ለንጉሡ ይቀርብ ነበር:: ከ፰፻ [800] ዓመታት በሁዋላም አፄ ዳዊት ግማደ መስቀሉን ባስመጡ ጊዜ መስከረም ቀን ተተክሎ ታላቅ በዓልም ሆኖ ተከብሯል:: †   🕊   ንግሥተ ሳባ    🕊   † ይሕቺ ደግ ኢትዮዽያዊት ከ፫ [3] ሺ ዘመናት በፊት የነበረች ደግ እናት ናት:: በሥጋዊ ደረጃ ከታንዛንያ እስከ የመን ያስተዳደረች ስመ ጥር ንግሥት ስትሆን በመንፈሳዊው ደረጃ ደግሞ እግዚአብሔር የቀባውን ሰው ፍለጋ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዛለች:: ከዚያውም አምልኮተ እግዚአብሔርን ከሥርዓተ ኦሪት ጋር አምጥታለች:: ድንግልናዋን ለታላቁ ንጉሥ ሰሎሞን ሰጥታ ምኒልክን ወልዳለች:: ይህቺ ንግሥት በጌታችን (በፈጣሪ) አንደበትም ተመስግናለች:: [ማቴ.፲፪፥፵፪] (12:42) በስምም "ሳባ: አዜብና ማክዳ ተብላ ትታወቃለች:: ዛሬ ዕለተ ዕረፍቷ ነው:: እመ ብርሃን ድንግል ማርያም ጣዕሟን ፍቅሯን: ጸጋ በረከቷን: ከስዕሏም ረድኤት ትክፈለን:: የቅዱሳኑም ክብር አይለየን:: 🕊 [  † መስከረም ፲ [ 10 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት   ] ፩. ቅድስት ድንግል እግዝእትነ ማርያም ፪. በዓለ ስዕለ አድኅኖ ፫. ቅዱስ እፀ መስቀል [ተቀጸል ጽጌ] ፬. ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ ፭. ቅድስት ማርታ ዘጼዴንያ ፮. ቅድስት ዮዲት ጥበበኛዋ ፯. ንግስተ ሳባ / ማክዳ / አዜብ ፰. ቅድስት መጥሮንያ ሰማዕት ፱. አፄ ዳዊት ንጉሥ ፲. ቅድስት አትናስያና ፫ [3] ልጆቿ [   †  ወርሐዊ በዓላት    ] ፩. ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ ፪. ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሜራ ፫. ቅዱስ  ያዕቆብ ሐዋርያ [ወልደ እልፍዮስ] ፬. ቅድስት እሌኒ ንግስት ፭. ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ " የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ! በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተስሎ ነበር:: ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው ? " [ገላ.፫፥፩] (3:1) † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖

[ ድምፀ ተዋሕዶ ] ጾመ ፍልሠታ ከመግባቱ አስቀድሞ ከቆመበት እነሆ ቀጥሏል።

photo content

[ የእግዚአብሔር ሕግ - ፴፪ - ] .mp311.39 MB

🕊 💖 🕊 [ 🕊 ድምፀ ተዋሕዶ 🕊 ] 🍒 🍒 [ ሕይወት የሚገኝባቸው የቅድስት ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቶች በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በድምፅ ይቀርባሉ። ] [ ሳምንታዊ መርሐ-ግብር ]
🕊                        💖                       🕊           [  🕊  ድምፀ ተዋሕዶ   🕊  ]   🍒                                                    🍒 [  ሕይወት የሚገኝባቸው የቅድስት ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቶች በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በድምፅ ይቀርባሉ።  ]         [   ሳምንታዊ መርሐ-ግብር   ] 🩵                        †                         🩵 [  ❝ የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው ! ❞  ]             [    ክፍል ሠላሳ ሁለት   ]           💛   ድንቅ ትምህርት  💛 [ በመምህራችን ቀሲስ ኅብረት የሺጥላ ] 🍒                                                    🍒 ❝ የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ፥ ከመከራም ሥጋት ያርፋል። ❞ [ ምሳ.፩፥፴፫ ] ════════════════                            †††                ✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟ 🕊                        💖                       🕊                              👇

photo content

+1
4 ያቺን የጥሪ ቀን.mp38.01 MB

🕊 💖 🕊 🩵 [ መዝሙረ ተዋሕዶ ] 🩵 🕊 💖 🕊 ኦርቶዶክሳዊ መዝሙር ንጹሕና የተቀደሰ ነው ፥ ለእግዚአብሔር ምስጋናና ልመና የሚቀርብበት ፣ ይቅርታና ምሕረት የሚጠየቅበት ፣ ሰውን ሳይሆን
🕊                        💖                        🕊   🩵       [   መዝሙረ ተዋሕዶ   ]        🩵 🕊                        💖                     🕊 ኦርቶዶክሳዊ መዝሙር ንጹሕና የተቀደሰ ነው ፥ ለእግዚአብሔር ምስጋናና ልመና የሚቀርብበት ፣ ይቅርታና ምሕረት የሚጠየቅበት ፣ ሰውን ሳይሆን እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት የሚዘጋጅ ንጹሕ መስዋዕት ነው ፥ በአበው ጸሎት ይዘጋጃል ፥ ከስጋዊና ከደማዊ ሀሳብ የራቀ ነው ፥ ልቦናን ወደ ንስሐ ይጠራል ፥ ከኃጢአትና ከክፉ ሥራ የመለየት ኃይል አለው ፥ ክፉ መንፈስን ከሰው ልብ ያርቃል ፥ መረጋጋትን ልቦናን ዘልቆ የሚሰማ ውስጣዊ ሰላምን ይሰጣል ፥ በአሚነ ሥላሴ ያጸናል ፥ የክርስቶስን የባህርይ አምላክነትና መሐሪነት ይመሰክራል ፥ የእመቤታችንን ፍቅር በልቦና ያሳድራል ፥ በእናትነቷና በምልጃዋ እንድንታመን ያደርጋል ፥ በቅዱሳን ጸሎትና በቃል ኪዳናቸው ያጸናናል ፥ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ያስተምረናል ፥ ፈሪሐ  እግዚአብሔርንና ያጎናጽፈናል፡፡ 🕊                        💖                      🕊 ተወዳጆችሆይ ፦ በተቀደሰ ሰማያዊ ያሬዳዊ ዜማ ነብሳችንን እናስጊጣት፡፡ ከደጋጎቹ አባቶቻችን ጋር ከዓለም ርኩሰት በተለየ የተቀደሰ ዝማሬ አምላካችን እግዚአብሔርን እናመሥግን፡፡ ለስጋዊ ጆሮዎች ከሚመች ከረከሰ የተሃድሶ የኑፋቄ እርሾ ልቦናችንን እንጠብቅ፡፡ ገንዘብን ስለመውደድ ከሆነ ከሥጋዊ ሥራ ፈጽሞ እንለይ፡፡ 🌸                                                  🌸                            †††                ✟ 𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y ✟ 🕊                        💖                        🕊

photo content

[ ስንክሳር መስከረም - ፱ - ] .mp37.42 MB