ገድለ ቅዱሳን
Ir al canal en Telegram
@Gedelat ለተለያዩ አስተያየት እና ጥቆማ ማድረስ ከፈለጉ በአድራሻችን ቢያደርሱን ይደርሰናል፡፡ በአድራሻችን ✍ @Mnfesawi_bot
Mostrar más6 494
Suscriptores
-524 horas
+37 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
6 494
🕊 💖 🕊
[ 🕊 ድምፀ ተዋሕዶ 🕊 ]
🍒 🍒
[ ሕይወት የሚገኝባቸው የቅድስት ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቶች በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በድምፅ ይቀርባሉ። ]
[ ሳምንታዊ መርሐ-ግብር ]
🩵 † 🩵
[ ❝ የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው ! ❞ ]
[ ክፍል ሃያ ሰባት ]
💛 ድንቅ ትምህርት 💛
[ በመምህራችን ቀሲስ ኅብረት የሺጥላ ]
🍒 🍒
❝ የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ፥ ከመከራም ሥጋት ያርፋል። ❞ [ ምሳ.፩፥፴፫ ]
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
👇
6 494
🕊 💖 🕊
[ 🕊 ድምፀ ተዋሕዶ 🕊 ]
🍒 🍒
[ ሕይወት የሚገኝባቸው የቅድስት ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቶች በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በድምፅ ይቀርባሉ። ]
[ ሳምንታዊ መርሐ-ግብር ]
🩵 † 🩵
[ ❝ የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው ! ❞ ]
[ ክፍል ሃያ ሰባት ]
💛 ድንቅ ትምህርት 💛
[ በመምህራችን ቀሲስ ኅብረት የሺጥላ ]
🍒 🍒
❝ የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ፥ ከመከራም ሥጋት ያርፋል። ❞ [ ምሳ.፩፥፴፫ ]
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
👇
6 494
🕊 💖 🕊
💛 ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ 💛
🕊
❝ ሰላም ለያዕቆብ ኤጲስ ቆጶስ ዘሀገረ ሥሩግ ወምህሮሁ ሕግ፡፡ ❞
[ ትምህርቱ ሕግና የሥሩግ ሀገር ኤጲስ ቆጶስ ለኾነ ለያዕቆብ ሰላምታ ይገባል። ] [ ተአምኆ ቅዱሳን ]
🩵 † 🩵
የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ የተሰጠውና የመንፈስ ቅዱስ እንዚራ በመባል የሚጠራው ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ በእጅጉ አስደናቂ የኾኑ የቅዱሳት መጻሕፍት ትርጓሜዎችን ፣ ጥልቅ ምስጢር ያላቸው የሃይማኖት ትምህርቶችን ጽፏል ፤ ከእነዚኽ መኻከል በግጥም መልክ የተዘጋጁ ሰባት መቶ ስሳ ሦስት ድርሳናትን ጽፏል ፤ ዳግመኛም ሰባ ሦስት ደብዳቤዎችን ፤ ስምንት የበዓላት ድርሳናትን ፤ ኹለት የቅዱሳን ታሪኮችን ፤ ፍሬ ቅዳሴን ፤ የጥምቀት መዝሙራትን ጽፏል፡፡
🕊 💛 🕊
ከትምህርቱ ፦
❝ ክርስቶስ ወደ ጥምቀቱ መጣ በመጠመቂያው ውሃ ውስጥ አዳም በኃጢአት ምክንያት ተገፍፎት የነበረውን የጸጋ ልብስ አኖረ ... ስለዚህም አንድ ሰው ሲጠመቅ ያን በዛፎች መካከል ከእርሱ ተገፎ የነበረውን የጸጋ ልብስ ዳግም ይለብሰዋል፡፡ ❞
❝ ድንግል በምስጢር የተመላ ታቦትን ኾና ትኖራለች ፣ የካህናት ወገኖችም ደስ ይላቸዋል ፣ ያከብሯታልም። ❞
ምልጃውና ጸሎቱ አይለየን::
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
6 494
🕊 💖 ▬▬ † ▬▬ 💖 🕊
[ 🕊 መዝሙረ ተዋሕዶ 🕊 ]
[ ሳምንታዊ መርሐ-ግብር ]
🕊 💖 🕊
በስመ አብ ፡ ወወልድ ፡ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
ኦርቶዶክሳዊ መዝሙር ንጹሕና የተቀደሰ ነው ፥ ለእግዚአብሔር ምስጋናና ልመና የሚቀርብበት ፣ ይቅርታና ምሕረት የሚጠየቅበት ፣ ሰውን ሳይሆን እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት የሚዘጋጅ ንጹሕ መስዋዕት ነው ፥ በአበው ጸሎት ይዘጋጃል ፥ ከስጋዊና ከደማዊ ሀሳብ የራቀ ነው ፥ ልቦናን ወደ ንስሐ ይጠራል ፥ ከኃጢአትና ከክፉ ሥራ የመለየት ኃይል አለው ፥ ክፉ መንፈስን ከሰው ልብ ያርቃል ፥ መረጋጋትን ልቦናን ዘልቆ የሚሰማ ውስጣዊ ሰላምን ይሰጣል ፥ በአሚነ ሥላሴ ያጸናል ፥ የክርስቶስን የባህርይ አምላክነትና መሐሪነት ይመሰክራል ፥ የእመቤታችንን ፍቅር በልቦና ያሳድራል ፥ በእናትነቷና በምልጃዋ እንድንታመን ያደርጋል ፥ በቅዱሳን ጸሎትና በቃል ኪዳናቸው ያጸናናል ፥ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ያስተምረናል ፥ ፈሪሐ እግዚአብሔርንና ፍቅረ እግዚአብሔርን ያጎናጽፈናል፡፡
🕊 💖 🕊
ተወዳጆችሆይ ፦ በተቀደሰ ሰማያዊ ያሬዳዊ ዜማ ነብሳችንን እናስጊጣት፡፡ ከደጋጎቹ አባቶቻችን ጋር ከዓለም ርኩሰት በተለየ የተቀደሰ ዝማሬ አምላካችን እግዚአብሔርን እናመሥግን፡፡ ለስጋዊ ጆሮዎች ከሚመች ከረከሰ የተሃድሶ የኑፋቄ እርሾ ልቦናችንን እንጠብቅ፡፡ ገንዘብን ስለመውደድ ከሆነ ከሥጋዊ ሥራ ፈጽሞ እንለይ፡፡
†††
✟ 𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y ✟
🕊 💖 🕊
6 494
🕊
[ † እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ ሐናንያ እና ለሰማዕቱ ቅዱስ ቶማስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
🕊 † ቅዱስ ሐናንያ ሐዋርያ † 🕊
† ሐናንያ ቁጥሩ ከ፸፪ ቱ አርድእት ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ስማቸው ተመዝግቦ ከተቀመጠልን ከጥቂቶቹ ዋነኛው ነው:: ከነገደ እሥራኤል ተወልዶ : በሕገ ኦሪት አድጐ : ከወጣትነት ዕድሜው ትንሽ እልፍ ሲል ጌታችን ወንጌልን ማስተማር ጀምሯልና ጠራው:: እርሱም በበጐ ፈቃድ ተከትሎታልና ከ፸፪ ቱ አርድእት ደመረው::
ለ፫ ዓመታት ከጌታ እግር ተምሮ : ከዕለተ ስቅለት በፊት ሀብተ ፈውስም ተሰጥቶት ነበር:: ምክንያቱም ቅዱስ ሉቃስ እንደ ጻፈልን ሰብዐው አርድእት "ጌታ ሆይ! አጋንንት በስምህ ተገዙልን" ማለታቸውን አስቀምጦልናል:: [ሉቃ.፲፥፲፯] ቅዱስ ሐናንያ በበዓለ ዕርገት ተባርኮ በ፶ ኛው ቀንም መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ለስብከተ ወንጌል ወጥቷል::
በሚያስተምር ጊዜ የሶርያዋን ደማስቆን ማዕከል አድርጐ ነበር:: በሁዋላም አበው ሐዋርያት የዚህች ከተማ የመጀመሪያው ዻዻስ አድርገው ሹመውታል:: ጌታ ባረገ በ፰ ኛው ዓመት ክርስቲያኖችን ያሰቃይ የነበረው ሳውል [የሁዋላው ቅዱስ ዻውሎስ] ወደ ደማስቆ የተጉዋዘው ክርስቲያኖችን በተለይም ቅዱስ ሐናንያን ለማሠር ነበር::
ለእግዚአብሔር ምርጥ ዕቃ ይሆን ዘንድ መብረቅ ዐይኑን አጠፋው:: ወዲያውም ጌታችን ሳውልን ወደ ሐናንያ እንዲሔድ ነገረው:: ከ፫ ቀናት በሁዋላ ጌታችን ለሐናንያ ተገልጦ አነጋግሮታል::
ሳውል [ዻውሎስ] ወደ ሐናንያ የደረሰው በመሪ ነበር:: ፪ ቱ እንደተገናኙ ቅዱስ ሐናንያ ሳውልን አስተማረው : ፈወሰው : አጠመቀው : በጐ መንገድንም መራው:: በዚህ ምክንያት ቅዱሱ ሐዋርያ የቅዱስ ዻውሎስ የንስሃ አባቱ ይሰኛል:: [ሐዋ.፱፥፩-፲፱]
ከዚህ በሁዋላ ቅዱስ ሐናንያ ለብዙ ዓመታት በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ወንጌልን አስተማረ:: መከራንም ተቀበለ:: በመጨረሻም በዚህ ቀን ክፉዎች ከብዙ ስቃይ በሁዋላ በድንጋይ ወግረው ገድለውታል::
🕊 † ቅዱስ ቶማስ ዘሰንደላት † 🕊
† በ፫ ኛው መቶ ክ/ዘመን ከነበሩ ሰማዕታት አንዱ የሆነው ቅዱስ ቶማስ ወደ ሰማዕትነት ሕይወት የገባው በ፲፩ ዓመቱ በመላእክት መሪነት ነው:: ገና ወደ ምስክርነት አደባባይ እንደ ቀረበ መኮንኑ "ክርስቶስን ካድና ልሹምህ" ቢለው ሕጻኑ ቅዱስ ቶማስ ተቆጥቶ : "አንተ ሰነፍ መኮንን" ብሎ ገስጾ : በጐችን ይመልስባት በነበረችው ጅራፍ ገርፎታል:: ይሔም በዘመኑ የመጨረሻው የድፍረት ደረጃ ነበር::
† በዚህም ምክንያት በሕጻን ገላው ላይ የተቀበለው መከራ ሊናገሩት ይከብዳል::
¤ ግርፋት
¤ እሳት
¤ አራዊት በእርሱ ላይ አልፈዋል::
አካሉ ተቆራርጧል:: አንድ ጊዜም "ለጣዖታችሁ እንድሰግድ አምጡት" ብሏቸው ልክ ከፊቱ ሲደርሱ ወደ ጌታ ቢጸልይ መሬት ተከፍታ ውጣቸዋለች:: እሱን ያሰቃየው የነበረውን መኮንንም ከደዌው አድኖ ከነ ሠራዊቱ አሳምኖታል:: ሕጻኑን ቅዱስ ቶማስን ግን ያላመኑ አረማውያን በዚህች ቀን አንገቱን ሰይፈውት በሰማዕትነት ወደ ወደደው ክርስቶስ ሔዷል::
† አምላከ ቅዱሳን ከሐዋርያው በረከት : ከሰማዕቱም ምልጃ አይለየን::
🕊 † ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ † 🕊
በቤተ ክርስቲያን ታሪክ በደራሲነታቸው: በወንጌል አገልግሎታቸውና በቅድስናቸው ከተመሠከረላቸው ዐበይት ሊቃውንት አንዱ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ነው::
ሊቁ የተወለደው መጋቢት ፳፯ ቀን በ፬፻፴፫ ዓ/ም ሲሆን ሃገሩ ሶርያ ነው:: ወላጆቹ ክርስቲያኖች ለዚያውም አባቱ ሊቀ ካህናት ነበር:: ቅዱስ ያዕቆብ ገና በልጅነቱ ጀምሮ ጸጋ እግዚአብሔር የጠራው ነውና በብዙ ነገሩ የተለየ ነበር::
አንድ ቀን በዕለተ ሰንበት ገና በ፫ ዓመቱ እናቱ አቅፋ ወደ ቤተ መቅደስ ወሰደችው:: ምዕመናን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ሲቀበሉ ሕጻኑ ያዕቆብም ይቆርብ ዘንድ ቀረበ:: ሊቀ ዻዻሱ ደሙን በዕርፈ መስቀል ሊያቀብለው ሲል መልአኩ መጥቶ "በጽዋው ጋተው" አለው:: የጌታን ደም በጽዋ ቢጠጣ ምስጢር ተገለጸለትና "አንሰ እፈርሕ ሠለስተ ግብራተ-እኔስ ፫ ነገሮች ያስፈሩኛል" ሲል አሰምቶ ተናገረ::
ዻዻሱና ሕዝቡ ወደ ሕጻኑ ያዕቆብ ቀርበው "ምን ምን?" አሉት:: እርሱም :-
፩. ነፍሴ ከሥጋየ ስትለይ
፪. ቅድመ እግዚአብሔር ለፍርድ ስቀርብ
፫. ከፈጣሪየ የፍርድ ቃል ሲወጣ" አላቸው::
ያን ጊዜ ሕዝቡና ሊቀ ዻዻሳቱ "እግዚአብሔር በዚሕ ሕጻን አድሮ ዘለፈን" እያሉ ለንስሃ በቅተዋል::
ቅዱስ ያዕቆብ ፯ ዓመት ሲሞላው ይማር ብለው ወደ ጉባዔ አስገቡት:: በ፭ ዓመታት ብሉይ ከሐዲስ ጠንቅቆ በ፲፪ ዓመቱ ሊቅ ሆኗል:: በዚህ ወቅት የነበሩ ታላላቅ ሊቃነ ዻዻሳት ወደ እርሱ ተሰበብስበው "እንግዳ ድርሰት ድረስልን: አዲስ ምሥጢር ንገረን" አሉት:: እርሱ ግን ሲቻለው ስለ ትሕትና "አልችልም" አላቸው::
"እንግዲያውስ ትንቢተ ሕዝቅኤልን ተርጉምልን" ቢሉት ባጭር ታጥቆ አመሥጥሮላቸው ተደስተዋል:: ፈጣሪንም አመስግነዋል:: ቅዱስ ያዕቆብ ከዚህ በሁዋላ ወደ ገዳም ገብቶ ትሕርምተ አበውን: ዕጸበ ገዳምን: ሕይወተ ቅዱሳንን በተግባር ተምሯል:: በድንግልናው ጸንቶ: ጾምና ጸሎትን እያዘወተረ ኑሯል:: በፈቃደ እግዚአብሔር የሥሩግ [በኤፍራጥስና ጤግሮስ ወንዞች መካከል የምትገኝ የሶርያ ግዛት ናት] ኤዺስ ቆዾስ ሆኖ ተሹሟል:: በዘመኑም:-
፩. የ፬፻፶፩ ን የኬልቄዶን ጉባኤ አውግዟል
፪. ብዙ መናፍቃንን ተከራክሮ ምላሽ አሳጥቷል
፫. በወንጌል አገልግሎት መልካም እረኝነቱን አሳይቷል
፬. ዛሬ የምንገለገልበትን መጽሐፈ ቅዳሴውን ጨምሮ በርካታ መንፈሳዊ ድርሰቶችን ደርሷል::
በመጨረሻም ከብዙ የተጋድሎና የቅድስና ዓመታት በሁዋላ በተወለደ በ፸፪ ዓመቱ በ፭፻፭ ዓ/ም በዚሕች ቀን አርፏል:: አንዳንድ ምንጮች ደግሞ ሰኔ ፳፯ ቀን እንዳረፈ ይናገራሉ:: ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ለቤተ ክርስቲያን የቁርጥ ቀን ተወዳጅ ልጇ ነውና በእጅጉ ታከብረዋለች::
አምላከ ቅዱሳን ከታላቁ ሊቅ በረከት ይክፈለን::
🕊
[ † ሰኔ ፳፯ [ 27 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ሐናንያ ሐዋርያ [ከ፸፪ ቱ አርድእት]
፪. ቅዱስ ቶማስ ሰማዕት [ዘሰንደላት]
፫. ቅዱስ አልዓዛር ነዳይ [በነዌ ደጅ የወደቀ : ቀጥሎ ደግሞ በአብርሃም እቅፍ ውስጥ የተገኘ ጻድቅ - ሉቃ.፲፮፥፲፱]
፬. ቅዱስ ማማስ
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. የጌታችንና አምላካችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በዓለ ስቅለት
፪. አቡነ መብዐ ፅዮን ጻድቅ
፫. ቅዱስ መቃርስ [የመነኮሳት ሁሉ አለቃ]
፬. ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ
፭. ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት
፮. ቅዱስ ቢፋሞን ጻድቅና ሰማዕት
፯. ማር ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት
† " በደማስቆም ሐናንያ የሚሉት አንድ ደቀ መዝሙር ነበረ:: ጌታም በራዕይ :- "ሐናንያ ሆይ!" አለው:: እርሱም "ጌታ ሆይ! እነሆኝ" አለ:: ጌታም :- ተነስተህ ቅን ወደ ሚባለው መንገድ ሒድ:: በይሁዳ ቤትም ሳውል የሚሉትን አንድ የጠርሴስ ሰው ፈልግ:: እነሆ እርሱ ይጸልያልና:: ሐናንያ የሚሉትም ሰው ገብቶ ደግሞ እንዲያይ እጁን ሲጭንበት አይቷል" አለው::" † [ሐዋ.፱፥፲-፲፰]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር
† ወለወላዲቱ ድንግል
† ወለመስቀሉ ክቡር
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬
💖 🕊 💖
6 494
🕊 🌺 🕊
🌹 [ 🕊 ድንግል ሆይ 🕊 ] 🌹
🕊 🌺 🕊
❝ ድንግል ሆይ የእግዚአብሔር ማደሪያ ንፁህ አዳራሽ ነሽና ፤ ጠላቶቼ ፦ ያቺ የሚመካባት እመቤቱ ወዴት አለች ብለው እንዳይዘባበቱብኝ እኔን ባሪያሽን ለሀዘን ለትካዜ አሳልፈሽ አትስጪኝ።
እመቤቴ ማርያም ሆይ የዚህን ዓለም ቅባት ዘይት ያይደለ የምስጋና ሽቶ መቀባት ለተገባው እራስሽም ሁለ ምስጋና ይገባል። ድንግል ሆይ በነፍሰ በሥጋ በውስጥ በአፍአ ንጽሕት ነሽና እኔን ሀጥኡን ባሪያሽን በቅዱስ ቁርባኑ ፍም ሁሉ ያነጻኝ ዘንድ ሰማያዊውን ሱራፊን ሁሉ እዘዥልኝ።
እመቤቴ ማርያም ሆይ ብርሃነ መለኮት ፈጽሞ ለተዋሐደው ለራስሽ ፀዳል ሁሉ ሰላምታ ይገባል። ለፊትሽ ፀዳልም ሁሉ ምስጋና ይገባል። ከፀሐይ ከጨረቃ ከከዋክብት እጅግ አንጸባራቂ ነውና። እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ የመግቢያ መውጫዬን ጎዳና ጥረጊልኝ። በመዓልትና በሌሊትም ከሚያሸምቅ ማጅራት መቺ ሁሉ ጠብቂኝ። እርሱ የተንኮል ወጥመድ አጥምዶ ጉድጓድ ቆፍሮ ይጠብቀኛልና። ❞
[ መልክዐ ማርያም ]
🕊 🌺 🕊
6 494
🍒 🍒
🕊 ም ክ ረ ቅ ዱ ሳ ን 🕊
═══════════════
▷ ❝ የ ማ ያ ቋ ር ጥ ው ጊ ያ ! ❞
[ 💛 በሊቀ ዲያቆናት ሀቢብ ጊዮርጊስ 💛 ]
🕊 🍒 🕊
❝ በመጠን ኑሩ ንቁም ፥ ባላጋራችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ ይዞራልና ፤
በዓለም ያሉት ወንድሞቻችሁ ያን መከራ በሙሉ እንዲቀበሉ እያወቃችሁ በእምነት ጸንታችሁ ተቃወሙት። ❞ [ ፩ጴጥ.፭፥፰ ]
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
👇
6 494
🕊 † 🕊
[ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ]
🩵 🩵
[ አንድ ባሕርይ እንደሆነ እናምለን ! ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
❝ ሁሉን ይገዛ በሁሉ ይፈርድ ዘንድ በኋላ ዘመን ዳግመኛ በሥጋ ይመጣልና ፤ ለሁሉም እንደ ሥራው ይከፍለዋል ፥ በቀናች ሃይማኖት የጸኑትን ደስ ካሰኙት ከሰማዕታት ፤ ከነቢያት ከሐዋርያት ጋር ሁሉ በመንግሥተ ሰማያት በክብር ያኖረዋል ፤ ውዳሴ ከንቱን በመውደድ ከሃይማኖት የወጡትን ግን ከአይሁድና ከሕግ አፍራሾ ሁሉ ጋር በገሀነም በሥቃይ ያኖራቸዋል እሊህም ወደ ዘለዓለም ኵነኔ ይሔዳሉ። [ ማቴ.፳፭፥፴፩-፵፮ ፡ ግብ.ሐዋ.፩፥፲፩ ። መዝ. ፷፪ (፷፩)፥፲፪ ። ሮሜ.፪፥፮—፲ ]
በተራበ በተጠማ በታመመ በደከመ ጊዜ መለኮት ከትስብእት ተለየ ፤ መለኮትስ ተዋሕዶት ቢሆን ድንቅ ድንቅ ሥራ በሠራ ነበር እያሉ ባለማወቃቸው ክርስቶስን ሁለት አካል ሁለት ባሕርይ ነው የሚሉ አሉ። እንዲህ ከቀናች ከክርስቲያን ሃይማኖት የተለዩ ናቸው ።
እኛ ግን ባለመለየት አንድ አካል ፤ አንድ ባሕርይ እንደሆነ እናምለን ፤ ግን በፈቃዱ ሥጋውን መከራ እንዲቀበል አደረገ። ሰዎች የተዋሐደው ሥጋ ምትሐት ነው ፤ እውነተኛ ሥጋ አይደለም እንዳይሉ ፤ ስለዚህም እንዲታመም አደረገው። [ ኢሳ.፶፫፥፪-፬ ዮሐ.፲፥፲፰ ። ሉቃ.፳፬፥፲፱-፳፩ ] ❞
[ 🕊 ቅዱስ ቄርሎስ 🕊 ]
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
