Berbir Mereja / በርብር መረጃ
Open in Telegram
Welcome back to our channel, where we bring you the latest updates and news from around the world.
Show more5 275
Subscribers
-824 hours
-57 days
-6630 days
Posts Archive
አዲሱ የመረጃ ነጻነት አዋጅ እስከ 5 ዓመት እስራት የሚያስቀጡ ቅጣቶችን አካቶ ጸደቀ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው ስብሰባ የመረጃ ነጻነት አዋጅ ቁጥር 1427/2018ን መርምሮ አጽድቋል።
🏢 የግል ድርጅቶች መረጃ የመስጠት ግዴታ አለባቸው
ቀደም ሲል መረጃ መጠየቅ የሚቻለው ከመንግሥት አካላት ብቻ የነበረ ሲሆን በአዲሱ ማሻሻያ ግን ማንኛውም ሰው " በግል ድርጅቶች ይዞታ ሥር የሚገኝ መረጃን " ጭምር መጠየቅና ማግኘት እንዲችል ተደርጎ ሕጉ ሰፍቷል።
💵 ለጋዜጠኞች ነፃ መረጃ ፤ ለሌሎች ጠያቂዎች የማባዣ ክፍያ
መገናኛ ብዙኃን (ጋዜጠኞች) መረጃን ለሕዝብ ተደራሽ ለማድረግ የሚሠሩ በመሆናቸው ያለምንም ክፍያ መረጃ የማግኘት መብታቸው የተጠበቀ ሲሆን ሌሎች መረጃ ጠያቂዎች ግን ሰነዶችን ለመገልበጥ (ፎቶ ኮፒ) የሚያስፈልገውን የማባዣ ወጪ ብቻ እንዲከፍሉ ተደንግጓል።
🏗 የመንግሥት ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ግልጽነት
ማንኛውም የመንግሥት አካል የሚተገብረውን ፕሮጀክት ፍሬ ነገር ብቻ ሳይሆን፣ የፕሮጀክቱን ዝርዝር አፈጻጸም፣ ተጠቃሚዎችን እና ያስገኘውን ውጤት መረጃ ለጠቅላላው ሕዝብ በተለያዩ የማሰራጫ ዘዴዎች ይፋ የማድረግ ግዴታ ተጥሎበታል።
🔍 የአካል ጉዳተኞች መብት
የመንግሥትም ሆነ የሕዝብ ተቋማት ለአካል ጉዳተኞች ሊነበብ፣ ሊታይ ወይም ሊደመጥ በሚችል አግባብ መረጃን ተደራሽ የማድረግ ምክንያታዊ እርምጃ የመውሰድ ግዴታ አለባቸው።
⚠️ እስከ 5 ዓመት እስራትና የገንዘብ ቅጣት የሚያስቀጡ ጥፋቶች
🔴 እስከ 5 ዓመት እስራት ወይም 100,000 ብር ቅጣት ፦
• መረጃን ለመከልከል በማሰብ ሆን ብሎ ሰነድን ያጠፋ፣ ያበላሸ፣ የቀየረ፣ የደለዘ ወይም የደበቀ የሥራ ኃላፊ።
• ሙስናን፣ ሕገ-ወጥ አሠራርን ወይም የሥራ ብቃት ጉድለትን ለመሸፈን መረጃን በሚስጥር የያዘ አካል።
• የግለሰብን ወይም የድርጅትን ስም (ቅሌት) ለመሸፈን መረጃን ደብቆ የያዘ ኃላፊ።
🟠 እስከ 3 ዓመት እስራት ወይም ከ25,000 እስከ 100,000 ብር ቅጣት ፦
• ሆን ብሎ የተሳሳተ ወይም ትክክለኛ ያልሆነ መረጃ ለጠያቂ የሰጠ ኃላፊ ወይም ሠራተኛ።
• ሚስጥር መሆኑን እያወቀ የመከላከያ እና የሀገር ደህንነት መረጃን አሳልፎ የሰጠ አካል።
• በአዋጁ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ለመረጃ ጠያቂዎች ከአንድ ጊዜ በላይ በተደጋጋሚ ምላሽ ያልሰጠ (ሲጠየቅ ችላ ያለ)።
🟡 እስከ 1 ዓመት እስራት ወይም ከ25,000 እስከ 50,000 ብር ቅጣት ፦
• የመረጃ ጥያቄን ወይም በቃል የቀረበን ጥያቄ በቅጽ ላይ ለመሙላት ፈቃደኛ ያልሆነና ግልባጩን የከለከለ።
• እያወቀ ለተቋሙ ማሳወቂያ ሐሰተኛ ወይም የተዛባ መረጃ የሰጠ ሠራተኛ።
• መረጃን አትሞ የማውጣት ግዴታን ያላከበረ ኃላፊ።
ምንጭ፦ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
@berbirmereja
@berbirmereja
ጄኔራል ባጫ ደበሌ የአፍሪካ ህብረት የህወሓትን እርምጃ እንዲያወግዝ ጠየቁ
በቅርቡ ጊዜያዊ አስተዳደሩን በማፍረስ ወደ ፕሬዝዳንትነት የተመለሱት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፣ አሳሳቢ የተባለ አዋጅ በመላ ክልሉ ማወጃቸው ይታወሳል። ይህንኑ አዋጅ መመልከታቸውን የገለጹት በናይሮቢ የኢትዮጵያ አምባሳደር ጄኔራል ባጫ ደበሌ፤ “የክተት አዋጅ እና የግዳጅ ምልመላ” በሚል ርዕስ ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ የአዋጁ ዋነኛ ዓላማ ሕዝቡን ለጠቅላላ ጦርነት መቀስቀስ እንደሆነ አመልክተዋል።
ከዚህ ጦርነት ቀስቃሽ እንቅስቃሴ በስተጀርባ የራስን ጦር እንደገና ማጠናከር እና ታጣቂዎችን እንደ "ቅጥረኛ ተዋጊ" ወደ ጎረቤት ሀገር ሱዳን ግጭት መላክ የሚሉ ግቦች እንዳሉ የገለጹት ጄኔራል ባጫ፤ የአፍሪካ ህብረት ይህን የህወሓት ድርጊት በአደባባይ እንዲያወግዝ ጠይቀዋል።
በተጨማሪም ህብረቱ ይህ አዋጅ በአስቸኳይ እንዲሰረዝ፣ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት የተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲመለስና የፖለቲካ ሂደቶች እንዲቀጥሉ ግፊት እንዲያደርግ አምባሳደሩ አሳስበዋል። ሊፈጠር የሚችለውን አላስፈላጊ ቀውስ ለመከላከልም የአፍሪካ ህብረት አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ አቅርበዋል።
@berbirmereja
@berbirmereja
#ችሎት
የበረከት ወርቁ (በረከት ገበሬዋ) የክስ ሂደት በሌለችበት እንዲታይ ተወሰነ።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት "በገበያ ላይ የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት አድርገዋል" የተባሉ የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር(ዲባራ ፉፋ) እና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር (አቶ ሹምአለም ብርሃኔ) ጨምሮ የከባድ ሙስና ወንጀል ክስ የተመሰረተባቸው ግለሰቦች ጉዳይ እየተመለከተ መሆኑ ይታወቃል።
ተጠርጣሪዎቹ ከመመሪያ ውጪ የነዳጅ ግዥና አከፋፋይነት ፈቃድ በመስጠት፣ በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ሊትር ናፍጣ በኮንትሮባንድ እንዲሸጥ በማመቻቸት እና ከጅቡቲ የሚመጣ ድጎማ የተደረገበትን ነዳጅ ከቁጥጥር ውጪ በማድረግ ወንጀል የተከሰሱ 13 ተከሳሾች ውስጥ የ 4 ተከሳሾች እና የአንድ የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ክስ እንዲቋረጥ በመደረጉ ክሳቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ተከሳሾች ቁጥር 9 ሆኗል።
ከእዚህ ቀደም በነበረው የችሎት ውሎ ከ1ኛ እስከ 10 ኛ ተከሳሾቹ የተከሰሱበት የክስ መዝገበ ከ 10 ኛ እስከ 13ኛ ተከሳሾች ከተከሰሱበት ክስ ተሻሽሎና ተለይቶ እንዲቀርብ እና ለበረከት ወርቁ(በረከት ገበሬዋ) የጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግ ችሎቱ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር።
በረከት ወርቁ ሰኔ 8/2018 በታተመው የአዲስ ዘመን እና Jun 18/2026 በታተመው Ethiopian Herald ጋዜጣ ጥሪ ቢደረግላትም በችሎቱ አልተገኘችም።
በመሆኑም ከእዚህ ቀደም በነበረው የክስ መዝገብ በሰባተኛ ተከሳሽነት በተሻሻለው የክስ መዝገብ ደግሞ በ 5 ኛ ተከሳሽነት የተቀመጠችው በረከት ወርቁ የክስ ሂደት በሌለችበት እንዲካሄድ ተወስኗል።
አቃቢ ህግ ክሱን ለይቶ እና አሻሽሎ በሁለት መዝገብ ያደራጀው ሲሆን በተሻሻለው ክስ መሰረት በመጀመሪያው የክስ መዝገብ እነ ዲባራ ፉፋን ጨምሮ 6 ተከሳሾች በሁለተኛው የክስ መዝገብ እስምአለም ምህረቱን ጨምሮ ሦስት ተከሳሾች ይገኛሉ።
በገበያ ላይ ነዳጅ እጥረት እንዲከሰት በማድረግና ሥልጣንን ያለአግባብ በመገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል በድምሩ ከ 30 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት በመንግስት ላይ በማድረስ በሚል ክስ ጉዳያቸውን እየተከታተሉ የሚገኙት ተከሳሾች የክስ ሂደት በተለዋጭ ቀጠሮ በሌላ ችሎት እንዲታይ ተወስኗል።
መዝገቡ በሌላ ችሎት እንዲታይ ተመርቶ የነበረ ቢሆንም ሳይታይ በመቅረቱ ተለዋጭ ቀጠሮው ቀን በዛሬው የችሎት ውሎ ሳይወሰን ቀርቷል።
መንግሥት ድጎማ ያደረገበትን ነዳጅ ከጅቡቲ በመጫን 17.8 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ጉዳት በማድረስና በዋና ወንጀል አድራጊነት የመንግሥትን ሥራ በማይመች አኳኋን በመምራት ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ የተመሰረተባቸው ከ 11 እስከ 13 ኛ ያሉ ተከሳሾችን በሚመለከት ደግሞ ምስክሮችን የመስማት ሂደት በቀጠሮው መሰረት የሚቀጥል ይሆናል።
ፌዴራል ፖሊስ ይፈለጋሉ ካወጣባቸው እና እስካሁን በቁጥጥር ስር ያልዋሉትን ተከሳሾች ጌታቸው አሞኘ እና አቡሽ አየለን በሚመለከት ፖሊስ በአድራሻቸው ፈልጎ እንዳላገኛቸው ለችሎቱ የተገለጸ ሲሆን የጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግላቸው ታዟል።
የጌታቸው አሞኘ እና አቡሽ አየለ የጋዜጣ ጥሪ ለመጠባበቅ እና አቃቢ ህግ የሚያቀርባቸውን 24 ምስክሮችን የመስማት ሂደት ለማከናወን ከሐምሌ 21 እስከ 23/2018 ዓም ቀጠሮ ተሰጥቷል።
የቀድሞዋ ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተሾሙ‼️
የተመድ ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥ ሳህለወርቅ ዘውዴን በምእራብ አፍሪካና ሳህል ቢሮ (UNOWAS) የዋና ስትራቴጂያዊ ገምጋሚ አድርገው መድበዋል።
በቀጠናው ባላቸው ሰፊ ዲፕሎማሲያዊ ልምድ የተመረጡት ሳህለወርቅ፣ ገለልተኛ ስትራቴጂያዊ ግምገማ ለማካሄድ ኃላፊነታቸውን በዚህኛው ወር (ጁን) ማብቂያ ላይ በይፋ ይረከባሉ ተብሏል።
@berbirmereja
@berbirmereja
የቀድሞዋ ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተሾሙ‼️
የተመድ ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥ ሳህለወርቅ ዘውዴን በምእራብ አፍሪካና ሳህል ቢሮ (UNOWAS) የዋና ስትራቴጂያዊ ገምጋሚ አድርገው መድበዋል።
በቀጠናው ባላቸው ሰፊ ዲፕሎማሲያዊ ልምድ የተመረጡት ሳህለወርቅ፣ ገለልተኛ ስትራቴጂያዊ ግምገማ ለማካሄድ ኃላፊነታቸውን በዚህኛው ወር (ጁን) ማብቂያ ላይ በይፋ ይረከባሉ ተብሏል።
@berbirmereja
@berbirmereja
ክሪፕቶ አበባን በግስጋሴ መጨረሻ አጋጣጥ ይዟል!
እንደ ነበርበት ትታወቅ የሚያውቅ እድል! 💫 የምንም ገበያ የእርዳታ ዕቅድ ትግባር እንዲታወስ እንደ ካርዶች ወይም የክሪፕቶ እድል መልእክት 📈 እንዳይረቁ እና ታች ማሳክ ይችላሉ፦
- የተለያዩ ገንዘብ መለያዎች
- አሳየሁ ዝርዝር እና መንበር አብሮ ችግኝ
- የእኛ ክሪፕቶ ሳቢን ይወድቃሉ!
ወደ ክሪፕቶ ወረቀት ተለዋዋጭ ይከታተሉ! 👉
ያለን ስለ እንፋልኝ ነልኮህ የመለያይ ዝይቅ! 💙
#ad 📢 InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
“1 ቀን ያህል ፈቃድ ያለው ነገር አለ?
እኔ የገና አውቅልኝ፣ 00 ብር እንዴት ነው?
መረዳት የምትፈልጉት አሁን አልቅሱ
#ad 📢 InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች.
እንዴት ነፃ ኢንተርኔት ሳይከፈል ለማግኘት ስልክዎን በፍጥነት ትችላለች? ነገር ግን ምንም አብዛኛውን ሰው አላወቀም የሚያሳየው መንገድ በዚህ ውስጥ ነው… ቀጥለው እዚህ ያነቡ 🇪🇹Ethio Free Internet
አሁን ጀምሩ እና ማዳን ትችላላችሁ!
#ad 📢 InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
ወደ ስራቸው እንዲመለሱ ተወሰነ‼️
የአማራ ክልል ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ጉባኤው በክልሉ በነበረው ግጭት በተለያየ ምክንያት ስራቸውን ለቀው ወደ ትጥቅ ትግል ገብተው ለነበሩ 2167 ሰራተኞች ወደ መደበኛ ስራቸው እንዲመለሱ ውሳኔ ማሳለፉን አሳውቋል።
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መስተዳደር ምክር ቤት በ6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት በ11ኛ መደበኛ ስብሰባው 738 መምህራን፣ 92 የገቢ ተቋማት ሰራተኞች፣ 1337 (115 በማንነት ምክንያት በፈጠረ ግጭት ተሰናብተው የነበሩ) ሲቪል ሰርቢስ ሰራተኞች በድምሩ 2167 ሰራተኞች ወደ መደበኛ ስራ መደባቸው እንዲመለሱ ወስኗል።
ምክር ቤቱ በውሳኔውም ከሚመደቡበት ቀን ጀምሮ የስራ መደባቸው የሚያስገኛቸውን ደሞዝ የሚያገኙ መሆናቸውን በግልፅ አመላክቷል።
@berbirmereja
@berbirmereja
እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ የድሮን ጥቃት ፈጸመች
አልጀዚራ እንደዘገበው፤ በአሜሪካ እና ኢራን ግፊት የተደረገውን የተኩስ አቁም ስምምነት በመጣስ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ ናባቲህ አካባቢ በፈጸመችው የድሮን ጥቃት የሁለት ሰዎች ሕይወት አልፏል። ጥቃቱ የተፈጸመው ግጭቱን ለማቆም በዋሽንግተን የሰላም ውይይት እየተካሄደ ባለበት ወቅት ነው።
የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ «በአሜሪካ በኩል ጥያቄ ቢቀርብ እንኳ ጦራችንን ከደቡብ ሊባኖስ አናስወጣም» ያሉ ሲሆን፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁም ሄዝቦላህን ለመከላከል በደቡብ ሊባኖስ ልዩ ቀጠና የመፍጠር ዓላማቸው ገና እንዳልተጠናቀቀ ገልጸዋል።
በአንጻሩ የሊባኖስ ፕሬዚዳንት ጆሴፍ አውን የእስራኤል ጦር ሲወጣ የሊባኖስን መደበኛ ጦር በደቡብ እንደሚያሰፍሩ አስታውቀዋል።
@berbirmereja
@berbirmereja
የሱዳን ጦር በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ የሚገኝ ቁልፍ ምሽግ ተቆጣጠረ‼️
የሱዳን መከላከያ ሠራዊት (SAF) በብሉ ናይል ክልል ከኢትዮጵያ ድንበር አንድ ኪሎ ሜትር ገደማ ርቀት ላይ የሚገኘውንና በጆሴፍ ቱካ በሚመራው የሱዳን ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ (SPLM-N) ይዞታ ሥር የነበረውን «አል-ባር» የተባለ ቁልፍ ወታደራዊ ምሽግ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታወቀ።
📌አላማው የድንበር አካባቢዎችን ከዓማፂያን ማጽዳት እና በፈጣን ድጋፍ ኃይል (RSF) እና በSPLM-N ጥምረት እጅ የምትገኘውን ስትራቴጂካዊ የድንበር ከተማ «ኩርሙክን» መልሶ መቆጣጠር ነው።
📌 ሠራዊቱ በሰሜን ዳርፉር የጠላት ድሮን መትቶ መጣሉን የገለጸ ሲሆን፤ አራተኛ ዓመቱን የያዘው የሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት በተለያዩ ግንባሮች በማገርሸቱ የሲቪሎች መፈናቀል እና የሰብአዊ ቀውሱ በከፍተኛ ሁኔታ እየባሰ መጥቷል።
@berbirmereja
@berbirmereja
ሴኔቱ በኢራን ላይ እርምጃ እንዳይወሰድ ወሰነ።
የአሜሪካ ሴኔት በኢራን ጉዳይ "ታሪካዊ" ያለውን ውሳኔ አሳልፏል።
የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት (Senate) ባደረገው ስብሰባ ረቂቁን 50 በ 48 ድምፅ አጽድቆታል።
ሴኔቱ በጉዳዩ ለመወሰን ጦርነቱ ከተቀሰቀሰበት የካቲት ወር ጀምሮ ዘጠኝ ጊዜ ቢሰበሰብም ውሳኔ ላይ መድረስ አልቻለም ነበር።
ውሳኔው ዶናልድ ትራምፕ በተናጠል እርምጃ ከመውሰድ እንዲቆጠቡ የሚያደርግ ነው። ይህም ፕሬዝዳንቱን ለሰላም ስምምነት ያስገድዳቸዋል። #associatedpress
@berbirmereja
@berbirmereja
IMF በኢራን ጦርነት ሳቢያ ለኢትዮጵያና ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ ሊያደርግ ነው።
የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በቅርቡ በነበረው የኢራን ጦርነት ምክንያት የተፈጠረውን የኤኮኖሚ ቀውስ ለመታደግ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለተወሰኑ የአፍሪቃ ሃገራት የሚሰጠውን የገንዘብ ድጋፍ ሊያሳድግ ነው።
ድጋፉን ከማሳደግ በተጨማሪ ገንዘቡን በፍጥነት ለማቅረብ ማቀዱ ተሰምቷል።
የድርጅቱ ቃል አቀባይ ጁሊ ኮዛክ እንዳሉት በድጋፉ ኢትዮጵያ፣ ጋምቢያ እና ቡርኪና ፋሶ ተጠቃሚ ሲሆኑ፣ በተጨማሪ ማላዊ አዲስ የፋይናንስ ድጋፍ እንድታገኝ ከተቋሙ ጋር የተፋጠነ ውይይት እያደረገች መሆኑን ጠቁመዋል።
የIMF የአፍሪካ ዳይሬክተር ዘይን ዘይዳን በዋሽንግተን በሰጡት መግለጫ፣ በመካከለኛው ምስራቅ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት የአፍሪካ ቀጠና "ከባድ ፈተና" ውስጥ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
አሁን የተኩስ አቁም ስምምነት ቢደረስም በጦርነቱ ምክንያት የተስተጓጎለው የባህረ ሰላጤው ሀገራት የኃይል እና የነዳጅ ምርት ወደ ቀድሞ ቦታው ለመመለስ ከ6 እስከ 7 ወራት ሊፈጅ እንደሚችል ጠቁመዋል።
የነዳጅ ምርት አቅርቦቱ መቋረጥ በአፍሪካ ሀገራት ላይ ከፍተኛ የነዳጅ እና የማዳበሪያ ዋጋ ንረትን አስከትሏል።
በተጨማሪ ሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔም የ25 ሚሊዮን ዶላር የትብብር መርሃግብር አካል የሆነውን 6.1 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ከስምምነት ደርሰዋል። #DW #AFP
@berbirmereja
@berbirmereja
#NationalDialogue🇪🇹
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሐምሌ 8/2018 ዓ/ም ለሚጀመረው ሀገራዊ ጉባዔ ለምክክር የቀረጻቸውን 8 አጀንዳዎች ይፋ አድርጓል።
ምክክር የሚደረግባቸው 8 የተመረጡ አጀንዳዎች የትኞቹ ናቸው ?
1) አጀንዳ ቁጥር 1 የሀገር ግንባታ ጉዳይ፣
2) አጀንዳ ቁጥር 2 የፖለቲካ ስርዓት፣ የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣
3) አጀንዳ ቁጥር 3 የፌዴራል ከተሞች፥ አዲስ አበባና ድሬዳዋ
4) አጀንዳ ቁጥር 4 የሃይማኖት ጉዳዮች፣
5) አጀንዳ ቁጥር 5 የተቋማት ግንባታ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣
6) አጀንዳ ቁጥር 6 ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች፣ የአርሶ አደሮች እና የአርብቶ አደሮች ጉዳይ፣
7) አጀንዳ ቁጥር 7 ሙስና እና መልካም አስተዳደር
8) አጀንዳ ቁጥር 8 ሰላም ግንባታ
አጀንዳዎቹ በተለያዩ ክልሎች ከ200 ሺሕ በላይ ሰዎችን በማመካከር የተገኙ መሆናቸውን የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
@berbirmereja
@berbirmereja
ብሄራዊ ባንክ ባካሄደው የ100 ሚ. ዶላር ጨረታ የዶላር ዋጋ ቀንሷል
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ በዛሬው ዕለት ባካሄደው የ100 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ላይ የብር ዋጋ መሻሻል ማሳየቱን አስታውቋል። በጨረታው ላይ 14 ባንኮች የተሳተፉ ሲሆን፣ የነበራቸው አጠቃላይ ፍላጎት ከ160 ሚሊዮን ዶላር በላይ ደርሶ ነበር። ይሁን እንጂ ማሸነፍ የቻሉት ዘጠኝ ባንኮች ብቻ ሲሆኑ፣ በዕለቱ አንድ ዶላር የተሸጠበት አማካይ እና ከፍተኛ ዋጋ 157 ብር ሆኖ ተመዝግቧል፤ ዝቅተኛው ዋጋ ደግሞ 152 ብር ደርሷል።
ይህ የዛሬው የጨረታ ውጤት ካለፈው ሳምንት ጋር ሲነፃፀር የዶላር ፍላጎትም ሆነ የምንዛሬ ዋጋ መቀነሱን ያሳያል። ባለፈው ሳምንት በተካሄደው ተመሳሳይ የ100 ሚሊዮን ዶላር ጨረታ ላይ የባንኮች ፍላጎት 236 ሚሊዮን ዶላር ደርሶ የነበረ ሲሆን፣ አንድ ዶላር የተጫረተበት ዋጋም 158 ብር እንደነበር ይታወሳል። ይህ የዋጋ መቀነስ የብርን የመግዛት አቅም ለማጠናከር ተስፋ ሰጪ ምልክት እንደሆነ ተነግሮለታል።
@berbirmereja
@berbirmereja
" የታጠቁ ሃይሎች በፈፀሙት ጥቃትና 1 ሚሊሻ ፣ 1 መደበኛ ፖሊስ፣ 1 የአድማ ብተና ፖሊስ መስዋዕት ሆነዋል " ሲሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የምስራቅ ጉራጌ ዞን ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ሙሰማ ጀማል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
" ታግተው የነበሩ 48 ዘጎች ሙሉ በሙሉ ተመልሰዋል " ሲሉም ገልጸዋል።
እንደ ፖሊስ አዛዡ ገለጻ፣ ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ/ም በዞኑ ሶዶ ወረዳ ሱተንና ጢያ መሃል ላይ በተለምዶ 'ቃሬ' ተብሎ በሚጠራው አከባቢ የታጠቁ ሃይሎች " ሸኔ " አንድ መለስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ እና 5L አነስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ አስቁመው ተሳፋሪዎችን የማገት እንቅስቃሴ አድርገዋል።
በወቅቱ በአከባቢው የነበሩ ሚልሻዎች፣ መደበኛ እና የልዩ ሃይል ፖሊሶች ተሳፋሪዎችን ለመታደግ ባደረጉት የተኩስ ልውውጥ 20 ተሳፋሪዎችን ማስጣል መቻላቸውን ገልጸዋል።
28 የሚሆኑትን ቡድኑ ወደ አጎራባች የኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ስዶ ዳቺ ወረዳ ይዞ መሸሹን አመልክተዋል።
ተሳፋሪዎችን በማዳን ሂደት ውስጥ በነበረው የተኩስ ልውውጥ ፦
👉 1 ሚሊሻ
👉 1 መደበኛ ፖሊስ
👉 1 የአድማ ብተና አባል በድምሩ 3 የመንግስት የፀጥታ አካላት መስዋዕት መሆናቸውን ኮማንደር ሙሰማ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።
በማግስቱ ሰኔ 14/2018 ፀጥታ ሃይሉ ከኦሮሚያ ክልል ፀጥታ አካላት ጋር በመሆን በተደረገው የተኩስ ልውውጥ ታግተው ያደሩ 28 ተሳፋሪዎችን ማስለቀቅ መቻሉን አስረድተዋል።
" ለሕዝብ ሰላምና ደህንነት ሲሉ ከተሰውት ሶስቱ የፀጥታ አባላት በተጨማሪ 1 መደበኛ ፖሊስ እና 1 የክልሉ አድማ ብተና አባል በጥይት ተመተው ተርፈዋል " ብለዋል።
በነበረው ሁኔታ በውል ያልታወቀ ንብረት ከመዘረፉ ባለፈ በተሳፋሪዎች ላይ ምንም አይነት ጉዳት አለመድረሱንና ሁሉም ተሳፋሪዎች መለቀቃቸውን ተናግረዋል።
@berbirmereja
@berbirmereja
የኢትዮጵያና የሌሎች ምሥራቅ አፍሪካ አገራት ዜጎች ወደ ሊቢያ እንዳይገቡ ተከለከሉ
በሊቢያ የተወካዮች ምክር ቤት የተሰየመው መንግሥት የኢትዮጵያ፣ የሱዳን፣ የኤርትራ እና የሶማሊያ ዜጎች ወደ ሊቢያ ግዛት እንዳይገቡ አገደ።
ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም የወጣው ይህ አዲስ አዋጅ እገዳው በሁሉም የየብስ፣ የባሕር እና የአየር ወደቦች ላይ በአስቸኳይ ተፈጻሚ እንዲሆን ያዝዛል።
ይሁን እንጂ ዕገዳው በሊቢያ ዕውቅና ያላቸውን የዲፕሎማቲክ እና የቆንስላ ልዑካን አባላትንና ቤተሰቦቻቸውን አይመለከትም።
በተጨማሪም በትምህርት፣ በሕክምና እና በተዛማጅ የጤና ሙያዎች ላይ የተሰማሩ ባለሙያዎችን ከእገዳው ነፃ ያደረገ ሲሆን፣ ይህም ሊሆን የቻለው ከሚመለከታቸው አካላት ሕጋዊ የቅጥር ኮንትራት እና ይሁንታ ማግኘት ሲችሉ ብቻ እንደሆነ ተገልጿል።
የሊቢያ የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር ይሄንን መመሪያ በማንኛውም የወደብ መግቢያ ላይ ወዲያውኑ እንዲያስፈጽም የታዘዘ ሲሆን፣ ትዕዛዙን ተላልፈው በሚገኙ እና ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ በሌላቸው ዜጎች ላይ ከአገር ማባረርን ጨምሮ አስፈላጊው እርምጃ እንደሚወሰድ አስታውቋል።
via:- ሊቢያ የዜና ወኪል (LANA)
@berbirmereja
@berbirmereja
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
