Berbir Mereja / በርብር መረጃ
Open in Telegram
Welcome back to our channel, where we bring you the latest updates and news from around the world.
Show more5 280
Subscribers
-824 hours
-57 days
-6630 days
Posts Archive
ኢራን በሆርሙዝ ሰርጥ የሰላም ስምምነቱን በመጣስ በድሮን ጥቃት ፈፅማለች ሲሉ ትራምፕ ገለፁ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትላንት ይፋ እንዳደረጉት፣ የኢራን ጦር ኃይሎች በስትራቴጂካዊቷ የሆርሙዝ ሰርጥ በሚያልፉ የንግድ መርከቦች ላይ ቢያንስ 4 የአጥፊ ድሮን ጥቃቶችን ሰንዝረዋል።
ከእነዚህም መካከል አንዱ የካሚካዜ ድሮን የአንድን የጭነት መርከብ ወለል መምታቱንና ጉዳት ማድረሱን ገልጸዋል።
ትራምፕ በፅሁፋቸው “ይህ የሰላም ስምምነቱን በግልፅ የጣሰ ሞኝነት ነው” ሲሉ ድርጊቱን አውግዘዋል።
አሜሪካ ቀሪዎቹን ሦስት ድሮኖች መትታ የጣለች ሲሆን፣ ጥቃት የደረሰባት መርከብ ግን ጉዞዋን ቀጥላለች።
@berbirmereja
@berbirmereja
#NewsAlert ‼️
ለህውሃት ተጨማሪ ማስጠንቀቂያ‼️ የአሜሪካ ኤምባሲ የሰላም ሂደቱን በሚያደናቅፉ አካላት ላይ ማስጠንቀቂያ ሰጠ‼️
የአሜሪካ ኤምባሲ ዛሬ ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ፣ በትግራይ ክልል የሰላም ሂደቱን የሚያደናቅፉ አካላት ከአፍሪካ ህብረት የውይይት ጥረት ጋር በአስቸኳይ እንዲተባበሩና የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንዲያደርጉ አሳሰበ።
ይህ መግለጫ የወጣው አሜሪካ “አክራሪ” ባላቸው የህወሓት አባላት ላይ የቪዛ ገደብ በጣለች በሳምንቱ ሲሆን፣ ህወሓት በበኩሉ የፕሪቶሪያው ስምምነት መፍረሱን በተደጋጋሚ ሲገልጽ መቆየቱ ይታወሳል።
@berbirmereja
@berbirmereja
ጥይት ወደውጪ መላክ ተጀመረ‼️
ኢትዮጵያ ለጎረቤቶቿ ጥይት በመሸጥ የውጪ ምንዛሬ እየተገኘ መሆኑ ተዘገበ።
ከወራት በፊት በአገር ውስጥ ጥይት ማምረት መጀመሩን ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ገልፀው ነበር፡፡ መከላከያ ሰራዊት ትናንት ባጋራው መረጃ በአገር ውስጥ የሚመረተው ጥይት የውጪ ምንዛሬ እያስገኘ መሆኑን ገልጧል፡፡
‹‹ኢትዮጵያ በያዘችው የለውጥ ጉዞ የጸጥታ መዋቅሯን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማደራጀት እና ወታደራዊ ቁሶችን በሀገር ውስጥ የማምረት አቅምን ለመገንባት የሚያስችል ታሪካዊ እርምጃ ወስዳለች›› የሚለው ሰራዊቱ፤ ይህ አካሄድ ሀገሪቱ በወታደራዊ አቅም ረገድ የነበራትን የውጭ ጥገኝነት በመቀነስ የራሷን የጸጥታ ፍላጎት በራሷ አቅም የምትፈታበትን አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል ብሏል።
በዚህ ረገድ መንግሥት ድሮን ቴክኖሎጂን በሀገር ውስጥ የማልማት እና የመገጣጠም ሥራን በስፋት እየተገበረ ይገኛል። የድሮን ማዕከላት መቋቋም እና በሥራ ላይ መዋል የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የአየር ክልሉን በአስተማማኝ ሁኔታ በመቆጣጠር እና የጸጥታ ስጋቶችን በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በታገዘ መንገድ ፈጣን ምላሽ እንዲሰጥ አስችሎታል ብሏል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪዎች ለቀላል እና ለከባድ የጦር መሣሪያዎች የሚያስፈልጉ ጥይቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት መጀመራቸው ሌላው ትልቅ ስኬት ነው ያለም ሲሆን፤ ‹‹ይህም በድንገተኛ የጸጥታ ተግዳሮቶች ጊዜ የጦር መሣሪያ እና ጥይት አቅርቦት እጥረት እንዳያጋጥም ዋስትና ከመስጠቱም በላይ፣ ለውጭ ግዥ ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ለማዳን አግዟል፤ ከዚያም አልፎ ሀገር ውስጥ የተመረተውን ጥይት ወደ ጎረቤት ሀገራት በመላክ የውጭ ምንዛሬ ማስገኘት ተጀምሯል›› በማለት አብራርቷል፡፡
#አንዳፍታ
@berbirmereja
@berbi
ብሪክስ ሀገራት ያቋቋሙት የልማት ባንክን፤ ኢትዮጵያ በአባልነት እንድትቀላቀል የሚያስችላት የማጽደቂያ ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተመራ።
ረቂቅ አዋጁ በፓርላማ ጸድቆ ለባንኩ የገዢዎች ቦርድ ሲገባ፤ ኢትዮጵያ ከደቡብ አፍሪካ፣ ግብጽ እና አልጄሪያ በመቀጠል አራተኛዋ አፍሪካዊት የልማት ባንኩ አባል አገር ትሆናለች።ዋና መስሪያ ቤቱን በቻይና ሻንጋይ ከተማ ያደረገው የብሪክስ የልማት ባንክ፤ “ኒው ዴቬሎፕመንት ባንክ” በሚል ስያሜ የሚጠራ ነው።
ይህንን ባንክ ኢትዮጵያ በአባልነት መቀላቀሏ “ለሀገራዊ የልማት ፋይናንስ፣ ለመሰረተ ልማት ድጋፍ እና ለማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት አማራጭ የገንዘብ ምንጮችን ለማግኘት” ያስችላታል ተብሎ እንደታመነበት የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።በቀድሞዋ የብራዚል ፕሬዝዳንት ዲልማ ሮዜፍ የሚመራው “ኒው ዴቬሎፕመንት ባንክ” ባንክ፤ “ታዳጊ ሀገራት ለሚያከናውኗቸው የመሰረተ ልማት እና የዘላቂ ልማት ዕቅዶች” የሚውል ገንዘብ ለማሰባሰብ የተቋቋመ ነው።
በ100 ቢሊዮን ዶላር የተፈቀደ እና በ52.7 ቢሊዮን ዶላር የተከፈለ ካፒታል የተቋቋመው ይኸው ባንክ፤ ከሻንጋይ በተጨማሪ በብራዚሏ ሳኦ ፖሎ እና በህንድ ጉጅራት ከተሞች ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች አሉት።
ብራዚል፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ቻይና እና ደቡብ አፍሪካ የባንኩ መስራች አባላት ሲሆኑ፤ ባንግላዴሽ፣ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች፣ ግብጽ፣ አልጄሪያ እና ኡዝቤኪስታን ባለፉት አምስት ዓመታት ባንኩን በአባልነት ተቀላቅለዋል።የ“ኒው ዴቬሎፕመንት ባንክ” የገዢዎች ቦርድ ኢትዮጵያን በዕጩ አባልነት የተቀበለው በጥቅምት 2015 ዓ.ም. ነበር።
Via Ethiopia Insider
@berbirmereja
@berbirmereja
#Update
በኮንጎ በኢቦላ ወረርሽኝ የሟቾች ቁጥር 300 ደረሰ
የኢቦላ ወረርሽኝ በኮንጎ መቀስቀሱ በይፋ ከታወጀበት ከሚያዝያ 15/2026 ጀምሮ 304 ሰዎች መሞታቸውንና 1155 ሰዎች መጠቃታቸውን የሀገሪቱ የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ሚኒስቴሩ ገልጿል። ከ150 በላይ ሰዎች ከበሽታው ማገገማቸው ተመላክቷል።
የአፍሪካ በሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ማዕከል (Africa CDC) በበኩሉ ወረርሽኙን ለመግታት 1.4 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋል ብሏል።
በምሥራቅ ኮንጎ ቡንድቡግዮ ግዛት የተቀሰቀሰው የኢቦላ ወረርሽኝ በአሁኑ ወቅት ኢቱሪ፣ ኖርዝ ኪቩ ሳውዝ ኪቩን ጨምሮ በ34 የሀገሪቱ ግዛቶች መስፋፋቱ ተመላክቷል። #yenisafaq
@berbirmereja
@berbirmereja
የሪፖርት መረጃ ይዘው! እስቲ ይቆዩ፤ ሉሉ የመንግሥት ታሪክ ወደ ጎን መግባት ከፈለጉ፣ አዲስ ፕሮጀክት ተመልቷል! 🎬💔
- የሱልጣን አላዲን ጥላቻ አስተያየት ተገነባ
- የመሐመድ ቦዝዳግ አዲስ ፕሮጀክት እንደሚሠራ
- ይህ ፊልም ወደ ታሪኩ ይመለሳል
- ማህበረሰብ ላይ ጥይት እና ቅንጣት ይታወቃል
ይህን ውሳኔ አወሰነ ወይም ተምረት እንጂ አይፈልጋም! 👉 ቀይር ለሀይል
#ad 📢 InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች.
እዚህ ተወሽአዋይ እንዳለው… ነገር ግን ወደ ምዕራብ ውስጥ ከምንዛሬው የሚለው ነገር ብዙ ግራ! 🥼💪 በመጀመሪያ ዓይነት ኖር የማቀናበሪያዎች በዚህ ላይ ዕድል ላይ ነው!
- የምርመራ ተመዝጋቢ ይዘዋል
- በዚህ መንገድ ይጀምሩ ወይም ወደ ውይይት ይሂዱ
- ይህ አገልግሎት ለመረጃ ነው
👉 ተመልክት በዚህ ተጠቃሚ ዕድል 🧪🔍
#ad 📢 InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች.
በሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ በአንድ የጭነት መርከብ ላይ ጥቃት ተሰነዘረ
በሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ በኦማን የባሕር ዳርቻ አቅራቢያ «ኤቨር ላቭሊ» የተሰኘች የሲንጋፖር የጭነት መርከብ ማንነቱ ባልታወቀ ተወንጫፊ ሚሳኤል ተመትታለች። በጥቃቱ በመርከቧ ላይ ጉዳት ቢደርስም የሰው ሕይወት እንዳልጠፋ የብሪታንያ የባሕር ላይ ንግድ ደህንነት ተቋም (UKMTO) አስታውቋል።
ጥቃቱ የተፈጸመው አሜሪካና ኢራን ጦርነቱን ለማቆም የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመው ቀጠናው ለተወሰኑ ቀናት ረግቶ በቆየበት ወቅት ነው። በአሁኑ ወቅት ኢራን በባህረ ሰላጤው በሚያልፉ መርከቦች ላይ የትራንዚት ክፍያ ለመጣል በመፈለጓ ከአሜሪካ ጠንካራ ተቃውሞ እየገጠማት ይገኛል።
@berbirmereja
@berbirmereja
በትግራይ ክልል አከራካሪው የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ አዋጅ በአስቸኳይ ተግባራዊ እንዲሆን ታዘዘ!
ከሰሜኑ ጦርነት በፊት ከምርጫ ቦርድ እውቅና ውጭ በተካሄደ ምርጫ ተቋቁሞ የነበረውና በቅርቡ ወደ ሥራ የተመለሠው የትግራይ ክልል ምክር ቤት፣ ያጸደቀው የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ አዋጅ በአስቸኳይ ተግባራዊ እንዲሆን ትዕዛዝ አስተላልፏል። የምክር ቤቱ አፈጉባኤ ምኅረት ሃጎስ ለክልሉ ፍትሕ ቢሮ ሰኔ 17 ቀን በጻፉት ደብዳቤ፤ አዋጁ በክልሉ ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ እስኪወጣ ድረስ የክልሉ የፍትሕ አካላት፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና ፖሊስ ኮሚሽን በጊዜያዊነት በሕጉ እየሠሩበት እንዲቆዩ አዘዋል። ይህ አዋጅ በዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል የሚመራውና በቅርቡ የተቋቋመው ማዕከላዊ የጸጥታ ዕዝ በበላይነት ያስፈጽመዋል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅት ሂውማን ራይትስ ዎች (Human Rights Watch) የትግራይ ባለሥልጣናት ይህንን የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ አዋጅ “በዝባዥ” ሲል መኮነኑና በአስቸኳይ እንዲያነሱት ሰሞኑን በይፋ መጠየቁ ይታወሳል። ይሁን እንጂ የክልሉ ምክር ቤት ዓለም አቀፍ ግፊቶችን ወደ ጎን በመተው አዋጁ በፍጥነት መሬት ላይ እንዲወርድ ማዘዙ በክልሉና በአጠቃላይ በሀገሪቱ የሰላም ሂደት ላይ አዳዲስ ውጥረቶችንና ጥያቄዎችን እያስነሳ ይገኛል።
@berbirmereja
@berbirmereja
ደቡብ አፍሪካ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ከኢምባሲው የተሰጠ አስቸኳይ የጥንቃቄ ማሳሰቢያ
በደቡብ አፍሪካ በስደተኞች ላይ ጥቃቶች ሊፈጸሙ የሚችሉባቸው አዝማሚያዎች በመታየታቸው፣ በፕሪቶሪያ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በሀገሪቱ ለሚኖሩ ዜጎች አስቸኳይ የጥንቃቄ ማሳሰቢያ አስተላልፏል።
ኤምባሲው የዜጎችን ሁኔታ በቅርብ እየተከታተለና ከደቡብ አፍሪካ መንግስት ጋር አስፈላጊውን ግንኙነት እያደረገ ይገኛል።
ምንም እንኳን የደቡብ አፍሪካ መንግስት ጥቃቶችን ለመከላከልና የጸጥታ ማስከበር ተግባሩን ለማጠናከር ቃል ቢገባም፣ አሁንም የስጋት ምልክቶች በመኖራቸው ዜጎች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ተጠይቋል።
በመሆኑም በመላው ደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴያቸውን በጥንቃቄ እንዲያከናውኑ፣ ከአካባቢው የመንግስት አካላትና የኮሚኒቲ አደረጃጀቶች ጋር የቅርብ ግንኙነት በመፍጠር መረጃዎችን እንዲለዋወጡና ራሳቸውን ከደህንነት ስጋቶች እንዲጠብቁ ኤምባሲው አሳስቧል።
@berbirmereja
@berbirmereja
የቢል ጌትስ ድብቅ የፍቅር ህይወት እና የኤፕስታይን ማስፈራሪያ በአሜሪካ ኮንግረስ ተጋለጠ
የማይክሮሶፍት መስራችና ቢሊየነሩ ቢል ጌትስ፣ ከባለቤታቸው ሜሊንዳ ጌትስ ጋር ሳይፋቱ በፊት ከሁለት ሩሲያውያን ሴቶች ጋር የነበራቸውን ግንኙነት ለአሜሪካ ኮንግረስ በሰጡት ዝግ የምስክርነት ቃለ-ጉባኤ ማመናቸውን ይፋ የሆነ ይፋዊ ሰነድ አጋለጠ።
በሰነዱ መሰረት፣ ጌትስ ከታዋቂው ወንጀለኛ ጄፍሪ ኤፕስታይን መዝገብ ጋር በተያያዘ በቀረበላቸው ጥያቄ ላይ ሁለቱም ሴቶች ህጋዊ እድሜ ላይ የነበሩ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
የመጀመሪያዋ ሴት በካርታ ጨዋታ (Bridge) ውድድር ላይ ያገኟት ሚላ አንቶኖቫ ስትሆን፣ ሁለተኛዋ ደግሞ ካሪማ ኒግማቱሊና የተባለች የኑክሌር ሳይንቲስት መሆኗ ታውቋል።
ጄፍሪ ኤፕስታይን ይህንን ሚስጥር ካወቀ በኋላ፣ ከቢል ጌትስ ጋር የነበረውን ግንኙነት እንደገና ለማደስና ማይክሮሶፍት ፈንድ እንዲያደርግለት ለማስፈራሪያነት ሊጠቀምበት እንደሞከረ በምስክርነቱ ላይ ተገልጿል።
ይህ መረጃ በቢል ጌትስ የግል ህይወት እና በኤፕስታይን መካከል በነበረው ግንኙነት ዙሪያ አዳዲስ ጥያቄዎችንና ከፍተኛ መነጋገሪያን አስነስቷል።
@berbirmereja
@berbirmereja
“1 ቀን ያህል ፈቃድ ያለው ነገር አለ?
እኔ የገና አውቅልኝ፣ 00 ብር እንዴት ነው?
መረዳት የምትፈልጉት አሁን አልቅሱ
#ad 📢 InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች.
አዲሱ የመረጃ ነጻነት አዋጅ እስከ 5 ዓመት እስራት የሚያስቀጡ ቅጣቶችን አካቶ ጸደቀ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው ስብሰባ የመረጃ ነጻነት አዋጅ ቁጥር 1427/2018ን መርምሮ አጽድቋል።
🏢 የግል ድርጅቶች መረጃ የመስጠት ግዴታ አለባቸው
ቀደም ሲል መረጃ መጠየቅ የሚቻለው ከመንግሥት አካላት ብቻ የነበረ ሲሆን በአዲሱ ማሻሻያ ግን ማንኛውም ሰው " በግል ድርጅቶች ይዞታ ሥር የሚገኝ መረጃን " ጭምር መጠየቅና ማግኘት እንዲችል ተደርጎ ሕጉ ሰፍቷል።
💵 ለጋዜጠኞች ነፃ መረጃ ፤ ለሌሎች ጠያቂዎች የማባዣ ክፍያ
መገናኛ ብዙኃን (ጋዜጠኞች) መረጃን ለሕዝብ ተደራሽ ለማድረግ የሚሠሩ በመሆናቸው ያለምንም ክፍያ መረጃ የማግኘት መብታቸው የተጠበቀ ሲሆን ሌሎች መረጃ ጠያቂዎች ግን ሰነዶችን ለመገልበጥ (ፎቶ ኮፒ) የሚያስፈልገውን የማባዣ ወጪ ብቻ እንዲከፍሉ ተደንግጓል።
🏗 የመንግሥት ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ግልጽነት
ማንኛውም የመንግሥት አካል የሚተገብረውን ፕሮጀክት ፍሬ ነገር ብቻ ሳይሆን፣ የፕሮጀክቱን ዝርዝር አፈጻጸም፣ ተጠቃሚዎችን እና ያስገኘውን ውጤት መረጃ ለጠቅላላው ሕዝብ በተለያዩ የማሰራጫ ዘዴዎች ይፋ የማድረግ ግዴታ ተጥሎበታል።
🔍 የአካል ጉዳተኞች መብት
የመንግሥትም ሆነ የሕዝብ ተቋማት ለአካል ጉዳተኞች ሊነበብ፣ ሊታይ ወይም ሊደመጥ በሚችል አግባብ መረጃን ተደራሽ የማድረግ ምክንያታዊ እርምጃ የመውሰድ ግዴታ አለባቸው።
⚠️ እስከ 5 ዓመት እስራትና የገንዘብ ቅጣት የሚያስቀጡ ጥፋቶች
🔴 እስከ 5 ዓመት እስራት ወይም 100,000 ብር ቅጣት ፦
• መረጃን ለመከልከል በማሰብ ሆን ብሎ ሰነድን ያጠፋ፣ ያበላሸ፣ የቀየረ፣ የደለዘ ወይም የደበቀ የሥራ ኃላፊ።
• ሙስናን፣ ሕገ-ወጥ አሠራርን ወይም የሥራ ብቃት ጉድለትን ለመሸፈን መረጃን በሚስጥር የያዘ አካል።
• የግለሰብን ወይም የድርጅትን ስም (ቅሌት) ለመሸፈን መረጃን ደብቆ የያዘ ኃላፊ።
🟠 እስከ 3 ዓመት እስራት ወይም ከ25,000 እስከ 100,000 ብር ቅጣት ፦
• ሆን ብሎ የተሳሳተ ወይም ትክክለኛ ያልሆነ መረጃ ለጠያቂ የሰጠ ኃላፊ ወይም ሠራተኛ።
• ሚስጥር መሆኑን እያወቀ የመከላከያ እና የሀገር ደህንነት መረጃን አሳልፎ የሰጠ አካል።
• በአዋጁ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ለመረጃ ጠያቂዎች ከአንድ ጊዜ በላይ በተደጋጋሚ ምላሽ ያልሰጠ (ሲጠየቅ ችላ ያለ)።
🟡 እስከ 1 ዓመት እስራት ወይም ከ25,000 እስከ 50,000 ብር ቅጣት ፦
• የመረጃ ጥያቄን ወይም በቃል የቀረበን ጥያቄ በቅጽ ላይ ለመሙላት ፈቃደኛ ያልሆነና ግልባጩን የከለከለ።
• እያወቀ ለተቋሙ ማሳወቂያ ሐሰተኛ ወይም የተዛባ መረጃ የሰጠ ሠራተኛ።
• መረጃን አትሞ የማውጣት ግዴታን ያላከበረ ኃላፊ።
ምንጭ፦ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
@berbirmereja
@berbirmereja
ጄኔራል ባጫ ደበሌ የአፍሪካ ህብረት የህወሓትን እርምጃ እንዲያወግዝ ጠየቁ
በቅርቡ ጊዜያዊ አስተዳደሩን በማፍረስ ወደ ፕሬዝዳንትነት የተመለሱት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፣ አሳሳቢ የተባለ አዋጅ በመላ ክልሉ ማወጃቸው ይታወሳል። ይህንኑ አዋጅ መመልከታቸውን የገለጹት በናይሮቢ የኢትዮጵያ አምባሳደር ጄኔራል ባጫ ደበሌ፤ “የክተት አዋጅ እና የግዳጅ ምልመላ” በሚል ርዕስ ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ የአዋጁ ዋነኛ ዓላማ ሕዝቡን ለጠቅላላ ጦርነት መቀስቀስ እንደሆነ አመልክተዋል።
ከዚህ ጦርነት ቀስቃሽ እንቅስቃሴ በስተጀርባ የራስን ጦር እንደገና ማጠናከር እና ታጣቂዎችን እንደ "ቅጥረኛ ተዋጊ" ወደ ጎረቤት ሀገር ሱዳን ግጭት መላክ የሚሉ ግቦች እንዳሉ የገለጹት ጄኔራል ባጫ፤ የአፍሪካ ህብረት ይህን የህወሓት ድርጊት በአደባባይ እንዲያወግዝ ጠይቀዋል።
በተጨማሪም ህብረቱ ይህ አዋጅ በአስቸኳይ እንዲሰረዝ፣ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት የተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲመለስና የፖለቲካ ሂደቶች እንዲቀጥሉ ግፊት እንዲያደርግ አምባሳደሩ አሳስበዋል። ሊፈጠር የሚችለውን አላስፈላጊ ቀውስ ለመከላከልም የአፍሪካ ህብረት አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ አቅርበዋል።
@berbirmereja
@berbirmereja
#ችሎት
የበረከት ወርቁ (በረከት ገበሬዋ) የክስ ሂደት በሌለችበት እንዲታይ ተወሰነ።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት "በገበያ ላይ የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት አድርገዋል" የተባሉ የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር(ዲባራ ፉፋ) እና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር (አቶ ሹምአለም ብርሃኔ) ጨምሮ የከባድ ሙስና ወንጀል ክስ የተመሰረተባቸው ግለሰቦች ጉዳይ እየተመለከተ መሆኑ ይታወቃል።
ተጠርጣሪዎቹ ከመመሪያ ውጪ የነዳጅ ግዥና አከፋፋይነት ፈቃድ በመስጠት፣ በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ሊትር ናፍጣ በኮንትሮባንድ እንዲሸጥ በማመቻቸት እና ከጅቡቲ የሚመጣ ድጎማ የተደረገበትን ነዳጅ ከቁጥጥር ውጪ በማድረግ ወንጀል የተከሰሱ 13 ተከሳሾች ውስጥ የ 4 ተከሳሾች እና የአንድ የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ክስ እንዲቋረጥ በመደረጉ ክሳቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ተከሳሾች ቁጥር 9 ሆኗል።
ከእዚህ ቀደም በነበረው የችሎት ውሎ ከ1ኛ እስከ 10 ኛ ተከሳሾቹ የተከሰሱበት የክስ መዝገበ ከ 10 ኛ እስከ 13ኛ ተከሳሾች ከተከሰሱበት ክስ ተሻሽሎና ተለይቶ እንዲቀርብ እና ለበረከት ወርቁ(በረከት ገበሬዋ) የጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግ ችሎቱ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር።
በረከት ወርቁ ሰኔ 8/2018 በታተመው የአዲስ ዘመን እና Jun 18/2026 በታተመው Ethiopian Herald ጋዜጣ ጥሪ ቢደረግላትም በችሎቱ አልተገኘችም።
በመሆኑም ከእዚህ ቀደም በነበረው የክስ መዝገብ በሰባተኛ ተከሳሽነት በተሻሻለው የክስ መዝገብ ደግሞ በ 5 ኛ ተከሳሽነት የተቀመጠችው በረከት ወርቁ የክስ ሂደት በሌለችበት እንዲካሄድ ተወስኗል።
አቃቢ ህግ ክሱን ለይቶ እና አሻሽሎ በሁለት መዝገብ ያደራጀው ሲሆን በተሻሻለው ክስ መሰረት በመጀመሪያው የክስ መዝገብ እነ ዲባራ ፉፋን ጨምሮ 6 ተከሳሾች በሁለተኛው የክስ መዝገብ እስምአለም ምህረቱን ጨምሮ ሦስት ተከሳሾች ይገኛሉ።
በገበያ ላይ ነዳጅ እጥረት እንዲከሰት በማድረግና ሥልጣንን ያለአግባብ በመገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል በድምሩ ከ 30 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት በመንግስት ላይ በማድረስ በሚል ክስ ጉዳያቸውን እየተከታተሉ የሚገኙት ተከሳሾች የክስ ሂደት በተለዋጭ ቀጠሮ በሌላ ችሎት እንዲታይ ተወስኗል።
መዝገቡ በሌላ ችሎት እንዲታይ ተመርቶ የነበረ ቢሆንም ሳይታይ በመቅረቱ ተለዋጭ ቀጠሮው ቀን በዛሬው የችሎት ውሎ ሳይወሰን ቀርቷል።
መንግሥት ድጎማ ያደረገበትን ነዳጅ ከጅቡቲ በመጫን 17.8 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ጉዳት በማድረስና በዋና ወንጀል አድራጊነት የመንግሥትን ሥራ በማይመች አኳኋን በመምራት ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ የተመሰረተባቸው ከ 11 እስከ 13 ኛ ያሉ ተከሳሾችን በሚመለከት ደግሞ ምስክሮችን የመስማት ሂደት በቀጠሮው መሰረት የሚቀጥል ይሆናል።
ፌዴራል ፖሊስ ይፈለጋሉ ካወጣባቸው እና እስካሁን በቁጥጥር ስር ያልዋሉትን ተከሳሾች ጌታቸው አሞኘ እና አቡሽ አየለን በሚመለከት ፖሊስ በአድራሻቸው ፈልጎ እንዳላገኛቸው ለችሎቱ የተገለጸ ሲሆን የጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግላቸው ታዟል።
የጌታቸው አሞኘ እና አቡሽ አየለ የጋዜጣ ጥሪ ለመጠባበቅ እና አቃቢ ህግ የሚያቀርባቸውን 24 ምስክሮችን የመስማት ሂደት ለማከናወን ከሐምሌ 21 እስከ 23/2018 ዓም ቀጠሮ ተሰጥቷል።
የቀድሞዋ ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተሾሙ‼️
የተመድ ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥ ሳህለወርቅ ዘውዴን በምእራብ አፍሪካና ሳህል ቢሮ (UNOWAS) የዋና ስትራቴጂያዊ ገምጋሚ አድርገው መድበዋል።
በቀጠናው ባላቸው ሰፊ ዲፕሎማሲያዊ ልምድ የተመረጡት ሳህለወርቅ፣ ገለልተኛ ስትራቴጂያዊ ግምገማ ለማካሄድ ኃላፊነታቸውን በዚህኛው ወር (ጁን) ማብቂያ ላይ በይፋ ይረከባሉ ተብሏል።
@berbirmereja
@berbirmereja
የቀድሞዋ ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተሾሙ‼️
የተመድ ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥ ሳህለወርቅ ዘውዴን በምእራብ አፍሪካና ሳህል ቢሮ (UNOWAS) የዋና ስትራቴጂያዊ ገምጋሚ አድርገው መድበዋል።
በቀጠናው ባላቸው ሰፊ ዲፕሎማሲያዊ ልምድ የተመረጡት ሳህለወርቅ፣ ገለልተኛ ስትራቴጂያዊ ግምገማ ለማካሄድ ኃላፊነታቸውን በዚህኛው ወር (ጁን) ማብቂያ ላይ በይፋ ይረከባሉ ተብሏል።
@berbirmereja
@berbirmereja
ክሪፕቶ አበባን በግስጋሴ መጨረሻ አጋጣጥ ይዟል!
እንደ ነበርበት ትታወቅ የሚያውቅ እድል! 💫 የምንም ገበያ የእርዳታ ዕቅድ ትግባር እንዲታወስ እንደ ካርዶች ወይም የክሪፕቶ እድል መልእክት 📈 እንዳይረቁ እና ታች ማሳክ ይችላሉ፦
- የተለያዩ ገንዘብ መለያዎች
- አሳየሁ ዝርዝር እና መንበር አብሮ ችግኝ
- የእኛ ክሪፕቶ ሳቢን ይወድቃሉ!
ወደ ክሪፕቶ ወረቀት ተለዋዋጭ ይከታተሉ! 👉
ያለን ስለ እንፋልኝ ነልኮህ የመለያይ ዝይቅ! 💙
#ad 📢 InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
