Berbir Mereja / በርብር መረጃ
前往频道在 Telegram
Welcome back to our channel, where we bring you the latest updates and news from around the world.
显示更多5 284
订阅者
+324 小时
-17 天
-7130 天
帖子存档
ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት ይፋ ተደረገ።
ተፈታኞች የመውጫ ፈተና ውጤታቸውን በ https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት መመልከት ይችላሉ።
መጀመሪያ የተቀመጠውን ሊንክ ይጫኑ በመቀጠል 'Exit Examination' ላይ 'View Results' የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤት መመልከት ይቻላል።
እናበለን ወይም ወዲያ ተደርሶ ወይም ባለበት ወይም ወይን ዘርሑኝን በብዙ እድርጎት! 🚀💰🔥
የስራ እድል እና ሥራ ማስታወቂያዎች! 🔥 እንዴት 10000 ተወካዮች ላይ የመጣችን ዜና እና ፈለግ ያውቅ!
- ዋጋ የማስታወቂያ ነቀርሳት
- ሊቀመንበር እንዳሉት ለመግባባት አስፈላጊ ተቋማት ⏳
- የተመጣጣኝ እና ወደ ሥራ ዕድል መምጣት!
ዙርያ ተዋዕቃ! 👉 የመደብ ንግድ አሁን ያስተዋወቁ! 🔥 ገጹን ይጎብኙ
#ad 📢 InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
“1 ቀን ያህል ፈቃድ ያለው ነገር አለ?
እኔ የገና አውቅልኝ፣ 00 ብር እንዴት ነው?
መረዳት የምትፈልጉት አሁን አልቅሱ
#ad 📢 InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች.
ተወዳጅ ሀይለኛ ተከታታይ ድራማ ክርክር ላይ ለ ወር 30 መዋቅር ነበር ፈሬ ከመውጣት እባክህ አትን! 💙 የድራማው ዝርዝር እንደ ፈላጊ የተሳነ ኡር. ይቀጥሉ! 👉 Join
#ad 📢 InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
አርቲስት ካሙዙ ካሳ በየካ ክፍለ ከተማ በከፍተኛ ድምፅ ማሸነፉን አስታወቀ
በየካ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲን ወክሎ ለምርጫ የቀረበው ታዋቂው አርቲስት ካሙዙ ካሳ፣ ከአካባቢው ነዋሪዎች ከፍተኛ ድምፅ በማግኘት ማሸነፉን በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል። አርቲስቱ የምርጫውን ውጤት ተከትሎ ለነዋሪዎችና ለመራጮች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፈ ሲሆን፣ ለተደረገለት ድጋፍም ጥልቅ ምስጋናውን አቅርቧል።
"እንደ ብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ ድምፅ ማግኘታችንና በአካባቢው ማሸነፋችን ታላቅ ድል ነው" ሲል የገለጸው አርቲስት ካሙዙ፣ ይህ ውጤት የህዝብ ድል መሆኑን በመጥቀስ፣ "ኢትዮጵያ አሸንፋለች" የሚል መልዕክት በድል አድራጊነት ስሜት አስተላልፏል።
@berbirmereja
@berbirmereja
"ይህ ፈቃድ የስምምነቱ አንድ አካል ነው" - ባሰንት
የአሜሪካ ገንዘብ ቢሮ ኢራን ለ60 ቀናት ነዳጅ ለዓለም ገበያ እንደምታቀርብ ገለጸ።
የቢሮው ኃላፊ ስኮት ባሰንት "ዋሽንግተን ለኢራን ጊዚያዊ የ60 ቀን ፈቃድ ሰጥታለች" ሲሉ ተናግረዋል።
"ነዳጅ ማውጣት፣ ማስተላለፍ እና መሸጥ የሚያስችል ሂደት ተፈጥሮላታል" በማለት ገልጸዋል። ባሰንት "ይህ ፈቃድ የስምምነቱ አንድ አካል ነው" ብለዋል።
ኢራን እና አሜሪካ በስዊዘርላንድ በነበራቸው ድርድር በመጭዎቹ 60 ቀናት ውስጥ ዘላቂ የሰላም ስምምነት እንዲፈጸም የሚሰራ ከፍተኛ ኮሚቴ ተዋቅሯል። #thenewregion
"ኮሚቴው በ60 ቀን ውስጥ የመጨረሻ ስምምነት ላይ ለመድረስ የሚያስችል ፍኖተ ካርታ ላይ ተስማምቷል" - አሸማጋዮቹ
የኢራንና አሜሪካ አሸማጋዮች የሆኑት ኳታርና ፓኪስታን በጋራ ባወጡት መግለጫ የድርድር ሒደቱን የሚከታተል የፖለቲካ ኮሚቴ እና በሊባኖስ ጦርነት የሚያስቆም ቡድን መመስረቱን አሳውቀዋል።
"ከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ኮሚቴ በ60 ቀናት ውስጥ የመጨረሻ ስምምነት ላይ ለመድረስ የሚያስችል ፍኖተ ካርታ ላይ ተስማምቷል" ብለዋል።
የመጀመሪያውን ቀን የድርድር ነጥቦች ሲገልጹ፦
-ሉስርኔ በተባለ ሐይቅ የተካሄደው ድርድር አወንታዊ እና ገንቢ ድባብ ታይቶበታል፣
-ከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ኮሚቴ ድርድሩን በዋናነት የሚከታተል ይሆናል። ዋነኛ ተደራዳሪዎች የደረሱበትን ለኮሚቴው ያስታውቃሉ።
-ኮሚቴው ግጭትን ለማስቆም ከተቋቋመው ቡድን ጋር በመሆን የኒውክሌር፣ የማዕቀብ እና የመግባቢያ ሰነዱ አተገባበርን ይከታተላል።
-በስምምነቱ አንቀጽ 5 መሠረት የሆርሙዝ ወሽመጥን ለማስከፈትና በተደራዳሪዎች መካከል አለመግባባት እንዳይኖር የንግግር መስመር ክፍት ይሆናል።
-ግጭትን ለማስቆም የተቋቋመው ቡድን በሊባኖስ ድርድር እንዲደረግ እና ወታደራዊ ግጭት እንዲቆም ያደርጋል ብለዋል። #Bbc
@berbirmereja
@berbirmereja
ብልጽግና ፓርቲ ቀጣይ በሚኖረው የስልጣን ዘመን ብልሹ አሰራርን በቆራጥነት እከላከላለሁ አለ
በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ከፍተኛ ድምጽ ማግኘቱን ያረጋገጠው ገዢው ብልጽግና ፓርቲ በቀጣይ የስልጣን ዘመኑ ሌብነትን እና ብልሹ አሰራርን በቆራጥነት ለመከላከል እሰራለሁ ብሏል።
ፓርቲው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ያደረገውን ውጤት ተከትሎ ባወጣው መግለጫ በምርጫው ሂደት የተሳተፉ አካላትን አመስግኗል።
የህዝብ ተወካየሸች ምክር ቤት ካሉት 486 መቀመጫዎች 438ቱን ማሸነፉን ያረጋገጠው ፓርቲው በቀጣይ ሰላምንና ፀጥታን ማስፈን ላይ ሰራለሁ ብሏል።
በተለይም የኑሮ ውድነትን ለማቅለልና የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ እንዲሁም በተቋማት የቢሮክራሲ ሰንሰለተን መበጠስ ላይ እንደሚያተኩር ገልጿል።
በተጨማሪም በመገባደድ ላይ የሚገኘው የሀገራዊ ምክክር ሂደት የታለመለትን ዓላማ እንዲያሳካ በሚገባ እንደሚደግፍ አስታውቋል።
@berbirmereja
@berbirmereja
በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ሆቴሎች የኤሌክትሪክ መኪና ኃይል መሙያ ጣቢያ እንዲኖራቸው እየተሰራ ነዉ
በአዲስ አበባ ከተማ በሚቀጥሉት 10 ዓመታት 1ሺህ 176 የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ መሙያ ማዕከላት እንደሚያስፈልጉ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ገልጿል።አሁን ላይ በከተማዋ የሚገኙት ፈጣን የኃይል መሙያ ጣቢያዎች ከ200 እንደማይበልጡ የገለፀው ሚኒስቴሩ ይህንን ክፍተት ለመሙላት ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል።
በከተማ አስተዳደሩ የህንፃ አዋጅ ወይንም ደንብ መሰረት የትኛውም አልሚ ተቋም ኃይል መሙያ ማዕከል የሚተክል መሆኑን ካላመላከተ ፍቃድ እንደማያገኝ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዲኤታ አቶ በርኦ ሀሰን ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።አሁን ላይ ሆቴሎች የምድር ቤታቸውን ለዚህ አገልግሎት እንዲያውሉ እየተደረገ ነዉ።
ሆቴሎች በተለይም ደግሞ ባለ ኮከብ ሆቴሎች ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የቻርጂንግ መሙያ ማዕከላት እንዲኖራቸው አቅጣጫ ተቀምጦ እየተሰራ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ጨምረው ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል ።ከሆቴሎች ፣ከአዲስ አበባ ቱሪዝምና ሆቴል ቢሮ እንዲሁም ከቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት ይህ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገልጿል።
እንደዚሁም ከኢትዮ ቴሌኮም ፣ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፣ከግል ተቋማት ፣ከአልሚዎችና ከከተማ መስተዳድሩ ጋር በመሆን ይህን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል፡፡
@berbirmereja
@berbirmereja
+3
ለጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡ የውጭ ሀገር ዜጎችን በመያዣነት በመጠቀም ከ15 ሚሊየን ብር በላይ የጠየቁ ሦስት ፓኪስታናውያን በቁጥጥር ስር ዋሉ።
የፓኪስታን ዜግነት ያላቸው ዝሻን ካሊድ፣ ፍርዝ መሃመድ እና መሀመድ ጀናይድ የተባሉ ተጠርጣሪዎች የወንጀል ድርጊቱን የፈጸሙት ሰኔ 4 እና ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ/ም በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 9 ጎሮ አትሌቶች መንደር ነው።
ተጠርጣሪዎቹ በተከራዩት የመኖሪያ ቤት ውስጥ የህንድና የባንግላዴሽ ዜግነት ያላቸውን ግለሰቦች በመያዣነት በመጠቀም የግል ተበዳዮችን በገመድ በማሰርና በፕላስተር በማፈን ከ15 እስከ 30 ሚሊየን ብር በመጠየቅ ጥቃት አድርሰውባቸዋል።
ተጠርጣሪዎቹ በዚህ ብቻ ሳያበቁ ሰኔ 11ቀን 2018 ዓ/ም ወደ ኢትዮጵያ ለጉብኝት የገቡ 4 የህንድ ዜጎችን በማሰርና በመደብደብ ከ15 እስከ 25 ሺህ የህንድ ሩፒ አስልኩ በማለት ድብደባ ሲፈጽሙባቸው እንደነበር የግል ተበዳዮች ለፖሊስ ቃላቸውን ሰጥተዋል።
የወንጀሉ መፈጸም መረጃ የደረሠው የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ ተገቢውን የፍርድ ቤት መያዣና የመበርበሪያ ትዕዛዝ በማውጣት ባከናወነው ኦፕሬሽን ተጠርጣሪዎቹን ለወንጀል ድርጊት ሲጠቀሙበት ከነበረው ቢላዋ፣ ገመድና ፕላስተር እንዲሁም ከተለያዩ የውጭ ሀገር ገንዘቦች ጋር በቁጥጥር ስር ውለዋል።
የአካባቢው ነዋሪዎች ተጠርጣሪዎቹ እንዲያዙ መረጃ በመስጠት ላደረጉት ቀና ትብብር ምስጋናውን ያቀረበው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አጠራጣሪ ጉዳዮች ሲያጋጥሙም ለፖሊስ መረጃ መስጠት እንደሚገባም መልዕክቱን አስተላልፏል።
ከ200 በላይ ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉበት የብስክሌት ሻምፒዮና ውድድር በአዲስ አበባ ከተማ ሊካሄድ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ብስክሌት ፌዴሬሽን ከጆርካ ኢቨንት ጋር በመተባበር የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብስክሌት ሻምፒዮናን ከሰኔ 17 እስከ ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በአዲስ አበባ ከተማ ለማካሄድ መዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡
ውድድሩ በካናዳ ሞንትርያል ሊካሄድ የታቀደውን የዓለም ብስክሌት ሻምፒዮና ውድድር ኢትዮጵያን የሚወክሉ ተወዳዳሪዎችን ለመምረጥ ዋና መድረክ መሆኑ ተገልጿል። ከመላው ሀገሪቱ እንዲሁም ከተለያዩ የአውሮፓ ክለቦች የተውጣጡ ከ200በላይ ተወዳዳሪዎች በውድድሩ ላይ እንደሚሳተፉ የኢትዮጵያ ብስክሌት ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት እና የአፍሪካ ብስክሌት ኮንፌደሬሽን እና ስራ አስፈፃሚ አቶ ወንድሙ ሀይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
ውድድሩ በወጣቶችና በአዋቂዎች ሁለቱም ፆታዎች መካከል የሚደረግ ሲሆን ታይም ትራያል እና ሮድ ሬስ በተባሉ ዘርፎች ይካሄዳል።
የዘንድሮ የሀገር ውስጥ ሻምፒዮና በዓለም አቀፍ የብስክሌት ፌዴሬሽን ወደ ዩ-ሲ-አይ ለሚዘጋጀውና ከ201 ሀገራት ምርጥ ተወዳዳሪዎች ለሚሳተፉበት የዓለም ሻምፒዮና ዋና የመምረጫ መድረክ በመሆኑ ከፍተኛ ሀገራዊ ፋይዳ አለው ተብሏል፡፡
ኮዬ ቡልቡላ እና አዲሱ ገበያን ጨምሮ በሦስት ቦታዎች የሚካሄደውይህ የሳይክል ውድድር 131 ኪሎ ሜትር ርቀት ያለው ሲሆን ከቤተመንግስት እስከ ቦሌ ባለው ክልል ውስጥ ይካሄዳል። በውጭ ሀገራት ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ተወዳዳሪዎችን ጨምሮ ከ13 በላይ ኢትዮጵያዊን በውድድሩ ይሳተፋሉ።
ባለፉት ዓመታት በዚህ በብሄራዊ ሻምፒዮና የተገኙ ውጤቶች ተወዳዳሪዎችን ወደ ዓለም አቀፍ ክለቦች እንዲቀላቀሉ እድል መፍጠሩ ተጠቅሷል።
በቀድሞ ዓመታት አንዳንድ አትሌቶች በጀርመን እና በቻይና ፕሮፌሽናል ክለቦች መቀላቀላቸው
ለሆርሙዝ የባህር ዳርቻ ቀውስ ተጠያቂው ትራምፕ ናቸዉ ስትል ጀርመን ተናገረች
የጀርመን መከላከያ ሚንስትር ቦሪስ ፒስቶሪየስ በሆርሙዝ ስትራተጂያዊ የባህር ዳርቻ ዙሪያ ለተፈጠረው ችግር የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን ተጠያቂ አድርገዋል።በመጨረሻም ትራምፕ "ቀዉሱን ወደ ሆርሙዝ ባህር ገፉት ግን እንደገና ከቀዉሱ ለመውጣት ፍላጎት አለን" ሲሉ ፒስቶሪየስ ለህዝብ ብሮድካስቲንግ ኤአርዲ ተናግረዋል።
ነገር ግን በባህሩ ዳርቻ ላይ ለሚደረገው የመርከብ ደህንነት ለመጠበቅ ለጀርመን ወታደራዊ ተልእኮ ከሚያስፈልጉት ቅድመ ሁኔታዎች ውስጥ አንዱ የጎረቤት ሀገራት የኢራን እና የኦማን ስምምነት ነው ሲሉም አክለዋል።የጀርመን መንግስት የሆርሙዝ ባህርን በነፃነት ማለፍ አስፈላጊ መሆኑን ደጋግሞ አሳስቧል።
ፒስቶሪየስ በሆርሙዝ ባህር ዳርቻ ለሚካሄደው የደህንነት ተልእኮ ከጀርመኑ ቡንዴስታግ ፓርላማ እዉቅና ይፈልጋል ብለዋል።ከበጋ ዕረፍት በፊት ፓርላማዉ ውሳኔ ያሳልፍ እንደሆነ ይጠበቃል፡፡ በአንድ በኩል በአሜሪካ እና በኢራን መካከል በስዊዘርላንድ የሚደረገው ድርድር ወደ የተረጋጋ የተኩስ አቁም ይመራ እንደሆነ ግልጽ አይደለም፡፡
@berbirmereja
@berbirmereja
#UK
" የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ማነቃቃት አልቻሉም ፤ በህዝብ ዘንድ ያላቸው ተቀባይነት በከፍተኛ ሁኔታ አሽቆልቁሏል ፤ በሹመት ላይም ከፍተኛ የሆነ ውዝግብ ፈጥረዋል " የተባለላቸው የብሪታንያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር ከሥልጣናቸው እንደሚለቁ አስታወቁ።
ሁለት ዓመት ስልጣን ላይ የቆዩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሱት በገዥው ሌበር ፓርቲ አባላትና በሚኒስትሮች ዘንድ ላለፉት ቀናት ከፍተኛ የፖለቲካ ጫና ሲደረግባቸው ከቆየ በኋላ ነው።
ባለፈው ሳምንት በተካሄደው የፓርላማ ማሟያ ምርጫ የፓርቲው ቁልፍ ተቀናቃኝ የሆኑት አንዲ በርንሃም ያገኙትን ወሳኝ ድል ተከትሎ ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጫናው የበረታባቸው።
አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የፓርቲው መሪ እስከ መጪው መስከረም ወር ፓርላማው ስራ ከመጀመሩ በፊት ተለይቶ የሚታወቅ ሲሆን እስከዚያው ድረስ ግን ስታርመር በኃላፊነታቸው ላይ እንደሚቆዩ ገልጸዋል።
የእሳቸው ከስልጣን መልቀቅ ብሪታንያ ባለፉት 10 ዓመታት ውስጥ ሰባተኛውን ጠቅላይ ሚኒስትር እንድታስተናግድ ያደርጋታል።
@berbirmereja
@berbirmereja
“አሁን 00 ብር ሳያከፍሉ ፈሪ ኢንተርኔት እና ክሪፕቶ ለማግኘት ጀመርኩ! ባለቤት በማይታመነው መንገድ የሚሰጥ ሴክሬት ያለ። የዛሬው አዳዲስ ሴብሲ መነሻ ለመሆን እዚህ ጠብቁ
#ad 📢 InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች.
“ኢራን ጦርነቱን አሸንፋለች!” 92 በመቶው እስራኤላዊያን
በቅርቡ የተደረገ አዲስ የሕዝብ አስተያየት ጥናት እንደሚያሳየው፣ አብዛኛው የእስራኤል ሕዝብ የጦርነቱን ውጤትና የተኩስ አቁም ስምምነቱን በጽኑ ተቃውሟል፦
📌92% እስራኤላውያን በጦርነቱ ኢራን የበላይነቱን እንዳገኘች ያምናሉ።
📌 72.5% የሚሆነው ሕዝብ የጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁን "ትልቅ ድል ተቀዳጅተናል" ንግግር ውድቅ አድርጓል። 87.8% የሚሆነው ደግሞ ሀገሪቱ ወታደራዊ ግቧን እንዳላሳካች ያምናል።
📌በዶናልድ ትራምፕ አደራዳሪነት የተደረሰውን የተኩስ አቁም ስምምነት አብዛኛው ሕዝብ ያልወደደው ሲሆን፣ 82.9% እስራኤላውያን የሀገሪቱ ደህንነት መዳከሙን ገልጸዋል።
📌 እንደ ሚኒስትር ቤን ግቪር ያሉ ቀኝ አክራሪ ፖለቲከኞች ጦርነቱ እንዲቀጥል እየገፋፉ ሲሆን፣ 48.2% ሕዝብ በሒዝቦላህ ላይ አዲስ ጥቃት እንዲከፈት ይደግፋል።
👉 ይህ የሕዝብ ቅሬታና የፖለቲካ ጫና የተፈጠረው፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ የሙስና ክስ ሂደት ወደ ማጠናቀቂያው በተቃረበበት እጅግ ፈታኝ ወቅት ላይ ነው።
@berbirmereja
@berbirmereja
አስተማሪ ታሪክ
ታሪክ የሚነጋገር እና የዓለምን ምስጢሮች የሚያሳይ ቦታ ነው። እንደ አሳዛኝ ፍላጎት፣ አስደናቂ ዝርዝሮች፣ ታሪካዊ ግንዛቤ ትዕዛዝ ይፈልጋሉ? ተምሩ ታሪክን በቀላሉ፣ ግልጽ እና አስደናቂ መልኩ! 📜
አስተማሪነት, አሳዛኝ ትንታኔዎች, የማይረሳ ታሪክ ትናንትና። 🔍
ተጫወት 🌟
#ad 📢 InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
+1
"ሜሎኒ የጦር ሰፈሮችን እንድንጠቀም ፍቃደኛ አልሆነችም" - ትራምፕ
"እኔ ጠ/ሚ እስከሆንኩ ድረስ ሊጣስ አይችልም" - ሜሎኒ
መነሻውን በG7 የተነሱትን የጋራ ፎቶ ያደረገው የትራምፕ እና የሜሎኒ ውዝግብ ሌላ ቄማቸውን እስከ ማዘራዘር ደርሷል። የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ጋር ውዝግብ ውስጥ ገብተዋል።
ትራምፕ፦ "የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በቡድን ሰባት ጉባዔ ከእኔ ጋር ፎቶ ለመነሳት ደጋግማ ጠየቀችኝ።
ጣሊያንን ራሷን ለማስተዋወቅ እየተጠቀመችባት ነው፤ ጣሊያንን የምትወደውንና የምትጠብቀውን አሜሪካን አትደግፍም። ጣሊያን ኔቶን ጨምሮ አሜሪካ ኢራን የኑክሌር ጦር ባለቤት እንዳትሆን ላቀረብንላት ጥያቄ መልስ አልሰጠችም።
አሜሪካ ጣሊያንንና ኔቶን ለመጠበቅ በቢሊዮን ዶላር ብታወጣም ሜሎኒ የጦር ሰፈሮችን እንድንጠቀም ፍቃደኛ አልሆነችም። አሁን አሜሪካ የኢራንን ጦር ከመታ በኋላ ወዳጅ ለመሆን ሞከረች፤ አይሆንም" ብለዋል።
ሜሎኒ፦ "ፕሬዚዳንት ትራምፕ ይሄ በተደጋጋሚ የምታደርገው ስም የማጥፋት ጥቃት ትርጉም የለውም።
የእኔን እውቅና በተመለከተ የአንተ ጓደኛ መሆን በተወሰነ መልኩ ጥቅም የለውም፤ ካንተ ጋር ባለኝ ግንኙነትም የሚወሰን አይደለም። የእኔ እውቅና መሰረቱ የጣሊያንን ብሄራዊ ጥቅም ማስጠበቅ ነው፣ እናም ሁልጊዜ የማደርገው እሱን ነው።
አሜሪካ ጣሊያንን ጠይቃ ውድቅ የተደረገው ሀሳብን በተመለከተም ያደረኩት ከዚህ የመነጨ ነው፤ የወታደራዊ ሰፈር መጠቀም በፈጸምነው ስምምነት የሚተዳደር ነው፤ ይሄ ደግሞ እኔ ጠቅላይ ሚኒስትር እስከሆንኩ ድረስ ሊጣስ አይችልም።
በየትኛውም ሁኔታ የእኔ ስብዕና የአንተ ጉዳይ አይደለም፤ በራስህ ላይ አተኩር" ብለዋል። #abs
@berbirmereja
@berbirmereja
የነፃ ኢንተርኔት በአንደኛ መርገፍ ነው! መለያየት ስለ አንዳንድ ይህ ደንብ ነው? 😱💔 አንዳንድ ሰላማችሁን በተግባር የሚወስድ ኢንተርኔት መግኘት በደንብ አለባቹ! 🔥📱
💡 ያነሱ፦
- ከሁሉም ዝግግም መቀየሪያዎቹ ይዘው ፣ ከ፡ አርዕዕይ ኢንተርኔት ዝርዝር በድምፅ ይገኙ በዚህ መነሳቴ ገበሬ ሁለት አይነት ይኖሩ ይበል።
- ወደ አንድ ኢንተርኔት በዚህ የእውነት ቴሎ በቄላትን አድርጉ የሚይምረቱ ይምጣ፤ ውስተ መግዛት ይችሉ!
- የጥቅም ምርመራ እየሚስፉ ፣ በቀበሌ ነው፣ ከይከንቱ ወይንም ላቂ ምዕጌ!
🤗 የውስጥ መዋቅር ውሎ ይስከሩ በእንደዚህ በዋጋው የተወሰኑ ኢንተርኔት ያግኙ! 👉 በዚህ የእውነት
#ad 📢 InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
የለመኑ ዙፋን መዋቅር ከገንዘብ ገበያ መምርም ወይ የርቅ ማዕከላችን ስለ ቢተኮች ትዕዛዝ መረዳት ይቻላል።
ወደ ዚህ በገፅ ዙፋን የሚያስታወክ ወይም አግኙ መዋቅር አይልኩም።
ዛሬ ይወቁ! 👉 ይገናኙ
#ad 📢 InsideAds ነፃ ተመዝጋቢዎች
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
