en
Feedback
ወጣቶች ገነት ቅ/አ እና 1ኛ ደረጃ ት/ት ቤት

ወጣቶች ገነት ቅ/አ እና 1ኛ ደረጃ ት/ት ቤት

Open in Telegram
234
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
የወጣቶች ገነት ቅ/አንደኛና አንደኛ ደረጃ ት/ቤት በ20/01/2016 ዓ.ም ከተማሪ ወላጆች ጋር ጥልቅ ውይይት አካሄደ።በውይይቱ የ2016 የተለያዩ ዕቅዶች ማለትም የወተመህ፣የት/ቤት መሻሻል፣የመልካም አስተዳደር፣የት/ቤት መሪ ዕቅድ እንዲሁም ስለአዲሡ የተማሪዎች የስነምግባር መመሪያ፣የ2016 ሰላማዊ የመማር ማስተማር ተግባር፣የማጠናከሪያ ት/ት እና 1ኛ ሩብ አመት ሪፖርት ከት/ት ለትውልድ ንቅናቄ፣የልማት ክፍያ እንዲሁም ተማሪ ቅበላ አንፃር የት/ቤቱ ር/ምህር የሆኑት አቶ መሀመድ ኢሳ አቅርበዋል።በማከተልም የተለያዩ ሀሳቦች፣አስተያየቶችና ጥያቄዎች ከተነሡ በኋላ የት/ቤቱ ምክትል ርዕሳነ መምህራን፣ኬጂ አስተባባሪ መምህርት እና በት/ቤቱ ር/መምህር ገንቢ ሀሳቦችና ምላሾች በመስጠት ውይይቱ በጥሩ ተግባቦት ተጠናቋል።

በአዲስ አበባ ሌቦች ሊሰርቋቹህ ሲያስቡ  ከሚጠቀሙት ዘዴዎች መካከል:- 👇           👇              👇 ✔ሞተር  እና ሳይክል ወደ እርሶ ሲጠጋ ይጠንቀቁ  ስንቱ  ስልኩን ተበልቷልና። ✔የማያውቆት ሰው ፀያፍ ስድብ ይሰድቦታል።  ለመጣላት ሲጋበዙ ገላጋይ መስለው   የተሳዳቢው ተባባሪ ሌቦች ኪሶትን  ያጥቦታል። ✔ ታክሲ ውስጥ ሆን ብለው የታመመ  ወይም ነፍሰ ጡር የሚመስል ሰው  አስቀምጠው መስኮት እንዲከፍቱ በጥድፊያ   ይጠይቆታል ። እርሶም መስኮቱን ሲከፍቱ ወይም ቦታ ለመቀየር ሲያስቡ ኪሶት ይገባሉ። ✔ የታክሲ ረዳት በመመስል "የት ኖት " ብለው በሚያልፉበት መንገድ ይጠይቆታል።  እርሶ ወደጠሩት ቦታ  እንደሚሄዱ በማስመሰል ታክሲ ካስገቦት በኋላ  ዘርፈው ደብድበው ያወርዶታል። ✔ አውቀው በታክሲ ትርፍ  እንዲጫኑ ካደረጉ በኋላ "  ትራፊክ መጣ፣ውረድ  ፣ውረጂ " በማለት አዋክበው አውርደው  በመሀል ገንዘቦትን ወይም ሞባይል  ስልኮትን ይሰርቆወታል። ✔ አሁን አሁንማ  ማር ፣ቅቤ ተልኮለት ነው  በማለት  እቤት ሰተት ብለው ገብተው  የላከኝን ሰው ልንገረው ስልኮትን አውሱኝ በማለት ያልተሰማቸው በማስመሰል ሹልክ ብለው ያመልጣሉ። ✔ መንገድ ላይ  አጣዳፊ ካልሆነ   ስልክ ባያወሩ ይመረጣል። መንታፊው በዝቷልና። ✔ ሎተሪ ደረሰኝ  ብሎ ወይም የማያውቁት ሰው መንገድ ላይ  እያወሮት ሲሄድ  ይጠንቀቁ። ምንጭ👉ፊደል ፖስት

በዓሉ የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የጤና እና የመረዳዳት እንዲሆን እመኛለሁ፡፡ አመሰግናለሁ! ዘላለም ሙላቱ ደሙ (ዶ/ር) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ! You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ... TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/ Website: - aaceb.gov.et Email;- aacaebc@gmail.com Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/

ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለመውሊድ በዓል አደረሳችሁ! (አዲስ አበባ 15/1/2016 ዓ.ም) የመውሊድ በዓል ሲከበር ፍቅርን ለአለም ያስተማሩትን የነብዩ መሐመድ የፍቅርና የአብሮነት
ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለመውሊድ በዓል አደረሳችሁ! (አዲስ አበባ 15/1/2016 ዓ.ም) የመውሊድ በዓል ሲከበር ፍቅርን ለአለም ያስተማሩትን የነብዩ መሐመድ የፍቅርና የአብሮነት አስተምሮትን በተግባር በማሳየት የተቸገሩ ወገኖቻችንን በመርዳት ፣ በመተባርና አብሮ በመብላት ሊሆን ይገባል፡፡ ከዚህም ጎን ለጎን በከተማ አስተዳደሩ የተጀመረው የ2016 የትምህርት ዘመን የትምህርት ልማት ስራ ውጤታማ እንዲሆን የሚጠበቅብንን ሁሉ በማድረግና እጅ ለእጅ ተያይዘን ለላቀ አፈጻጸም በመትጋትም ጭምር መሆን ይኖርበታል፡፡ በዚህ ስራ ውስጥ ደግም የተማሪዎች ፣ የመምህራን ፣ የትምህርት ባለሙያዎችና አመራሮች ፣ የከተማችን ማህበረሰብ እና የትምህርት ስራውን የምትደግፉ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆናችሁ ተቋማት ሚናችሁ የጎላ ነው፡፡ ከዚህ ቀደም ካስመዘገብናቸው አፈጻጸሞች በመነሳት በያዝነው የትምህርት ዘመንም በቅንጅታዊ አስራር በትምህርት ተደራሽነት ፣ ፍትሀዊነት ፣ ጥራት እና ሰላማዊ መማር ማስተማር መረጋገጥ ላይ ያለቀ አፈጻጸም እንደሚኖረን ምንም ጥርጥር የለኝም፡፡ በድጋሜ ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለመውሊድ በዓል አደረሳችሁ!

ጉዳዩ፦ ውጤት ማሳወቅን ይመለከታል 👉በ2015ዓ.ም የ6ኛ ክፍለ ከተማ አቀፍ ፈተና ሳይፈተኑ ከክልል እና ከሀገር ውጪ በመሸኛ የመጡ ተማሪዎች ወደ 7ኛ ክፍል ለማለፍ ከቢሮ ፈተና ተዘጋጅቶ እንዲፈተኑ
+2
ጉዳዩ፦ ውጤት ማሳወቅን ይመለከታል 👉በ2015ዓ.ም የ6ኛ ክፍለ ከተማ አቀፍ ፈተና ሳይፈተኑ ከክልል እና ከሀገር ውጪ በመሸኛ የመጡ ተማሪዎች ወደ 7ኛ ክፍል ለማለፍ ከቢሮ ፈተና ተዘጋጅቶ እንዲፈተኑ ተደርጓል፤ 👉 በዚህም መሰረት ውጤታቸው 👉 ወደ 7ኛ ክፍል የሚያሳልፋቸው 7ኛ ክፍል እንዲገቡ 👉ወደ 7ኛ ከፍል የማያሳልፋቸው(ያላለፋ) ደግሞ 6ኛ ክፍል ገብተው እንዲማሩ እንድታደርጉ እናሳስባለን ፡፡ 👉በፈተናቸው ውጤት መሰረት ወደ 7ኛ ክፍል ሳይዛወሩ 7ኛ ክፍል ተመዝግበው የሚማሩ ተማሪዎች ትምህርታቸው ተቀባይነት የሌለው ሲሆን ለሚፈጠረውም ስህተት ያስተማረው ት/ቤት ሀላፊነቱን የሚወስዱ ይሆናል ፡፡ ማሳሰቢያ 👉ተፈትነው ውጤት ያልመጣላቸው ተማሪዎች ካሉ ሪፖርት ይደረግ

የመስማት ችግር (hearing problem) ሠው የተለያዩ የመግባቢያ መንገዶች አሉት ከነዚህም ውስጥ ዋነኛው በአፍና ጆሮ በሚደረግ መስተጋብር የመግባባት ክህሎት ነው። ማለትም ከአንደኛው ሠው ከአፍ የሚወጣውን ድምጽ ሌላኛው ሠው በጆሮው አድምጦ በአእምሮው አገናዝቦ መልእክት የመለዋወጥ ችሎታ ነው። ይህ ዋነኛው እና ተፈጥሯዊ የመግባባት መንገድ በተለያዬ ምክነያቶች ሊጎዳ ይችላል።ስለሆነም ሌሎች የመግባቢያ መንገዶችን በአጋዥነት ወይም በግድ ልንጠቀም እንችላለን። ይህ ከአፋ ወደ ጆሮ የሚደረግ የመግባባት ሒደት 1 መናገር ባለመቻል ማለትም ከሳንባ በቂ አየር ከማስወጣት ጀምሮ የድምጽ ክሮች እርግብግቢት ያለመፍጠር እንዲሁም የተፈጠረውን እርግብግቢት ወደ ድምጸት የሚቀይሩልን የከንፈር፣ የምላስ፣ የጥርስ፣ የላንቃ እንዲሁም በአፍንጫ የሚያልፈው አየር መመጣጠን ችግር በሚገጥማቸው ጊዜ የመግባባት ሒደቱ ችግር ያጋጥማል። 2 በጭንቅላት ውስጥ የሚፈጠሩ ህመሞች ፣ የደም መፍሠስ፣የአእምሮ እድገት ችግር ቃላቶችን የመረዳት ችሎታ እና ቃላቶችን ለማውጣት መቸገር ያስከትላል። 3 ሌላው እና በዋናነት የሚጠቀሠው  ጆሮ ላይ በሚፈጠሩ ችግሮች መስማት መቀነስ እና መግባባት አለመቻል ሲሆን ለዛሬ በሠፊው የምንመለከተውም ይሔን የመስማች ችግር በምን በምን ምክነያት እንደሚከሠትና መፍትሔዎችን ይሆናል ። ፨  በሀገራችን በቂ ጥናት የተደረገበት ዘርፍ ባይሆንም የመስማት ችግር ሁሉንም የእጅሜ ክልል የሚያጠቃ ፤ በቀላሉ ሊስተካከሉ ከሚችሉ እስከ ውስብስብ ህክምና የሚፈልጉ ብሎም ሌሎች የመግባቢያ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የሚያስገድዱ የህመም አይነቶች ሊያመጡት የሚችል ነው። እነዚህ የመስማት ችግር የሚያመጡ ህመሞች በተለያዩ የጆሮ ክፍሎች ከፍለን ለማየት ያክል     1 የውጨኛው የጆሮ ክፍል ፦ በኩክ መደፈን ፦ የተፈጥሮ  ወይም በእብጠት ወይም በኢንፌክሽን የውጨኛው ቱቦ መደፈን 2 የመሀከለኛው የጆሮ ክፍል      ፦ የጆሮ ታንቡር በኢንፌክሽን ወይም በምት መጎዳት ፦ የመሀከለኛዉ የጆሮ ክፍል በፈሳሽ መሞላት ፦ የመሀከለኛው የጆሮ ክፍል አጥንቶች ተንቀሳቃሽ አለመሆን ፦ በእብጠት መጠቃት 3 የውስጥ የጆሮ ክፍል ፦ የአፈጣጠር ችግር ፦ ለከፍተኛ ደምጽ መጋለጥ ፦ የተለያዬ መድሀኒቶች ተጎዳኝ ተጽኖ ፦ የመሀል የጆሮ ችግር የውስጠኛውን ማጥቃት ፦ከእድሜ ጋር ተያይዞ የሚመጣ መስማት መቀነስ ፦ ሌሎች ምክንያቶች የተወሠኑትን በዝርዝር ስናይ ሀ በኩክ ምክነያት መስማት መቀነስ ኩክ የሚመረተው በጆሮ ቱቦ ጸጉር ባለው የቆዳ ክፍል ሲሆን ተፈጥሯዊ ኢንፌክሽንን የመከላከል አቅም እና ራሱን የማስወገድ ባህሪ አለው። ይህን ከውስጥ ወደ ውጭ የመውጣት ሒደት ሊያዛቡ የሚችሉ (ኩክ ለማውጣት በምንሞክር ጊዜ ወደ ውስጥ መግፍት ) ኩክ እንዲጠራቀምና ችግር እንዲሆን ያደርጋሉ። በዚህ ጊዜ የመሥማት መቀነስ ፣ ጆሮ ላይ ድፍን የማድረግ ስሜት፣ እና የመውጋት ባህሪ ስለሚያመጣ በማጠብ ወይም የተለያዬ ማውጫወችን በመጠቀም ማስወገድ እና መስማትን በቀላሉ ማስተካከል ይቻላል። ለ. የጆሮ ታንቡር መጎዳት   ይህ ችግር ምን አልባትም በሀገራችን ከፍተኛውን የመሰማት ችግር የሚያመጣ እንደሆነ እገምታለሁ። የሚከሰተውም በመሀለኛው የጆሮ ክፍል በሚፈጠር የኢንፌክሽን ሒደት ሲሆን በመጀመሪያ  በኢንፌክሽኑ ምክነያት መሀለኛው የጆሮ ክፍል ላይ የሚጠራቀመው ፈሳሽ  የጆሮ ታንቡርን የመወጠር  እና የህመም ስሜት የመፍጠር ፣ትኩሳት እንዲሁም ህጻናት ላይ አብዝቶ ጆሯቸውን የመጎተት ባህሪ ያሳያሉ። ይህ የጆሮ ታንቡሩን የወጠረው ፈሳሽ በመጨረሻ የጆሮ ታንቡሩን በስቶ ወደ ውጭ መፍሠስ ይጀምራል ፤ በዚህ ጊዜ የህመም ስሜቱ መቀነስ ቢያሳይም ቀጣይነት ያለው ችግርና መስማት መቀነስን ስለሚያስከትል ህክምና እንዲያገኙ ማድረግ አስፈላጊ ነው ።   በህክምና ሒደቱ የጆሮ ታንቡር መቀደድ ከሌሎች ችግሮች ጋር መያያዙ ከታየ በሁዋላ እና የመሥማት ችግሩ በምን ያክል መጠን  እንደቀነሠ በማየት በቀዶ ጥገና ይስተካከላል ።    ሐ. የጆሮ አፈጣጠር ችግር በአፈጣጠር ችግር የሚከሠቱ የመሰማት ችግሮች በአብዛኛው አደገኛና ለህክምና አስቸጋሪ የሚባሉ ሲሆኑ፤ በብዛት መስማት የተሳናቸው ትምህርት ላይ ተጠቃሚ ሆነው የምናገኛቸው ወገኖችም በዚህ የአፈጣጠር ችግር ተጎጅዎች ናቸው። ይህ የአፈጣጠር ችግር ከጆሮ ቅጠል ከሚፈጠሩ እስከ ድምጹን የሚቀበሉ የነርቮች አለመፈጠር ሊሆን ይችላል። የዚህ ችግር መፍትሔዎች በሀገራችን በጅምር ላይ ያሉ ሲሆን በውጭ ከሚገጠሙ የመስማት ማገዣ፣ በአጥንት የሚቀበር ድምጽ ማስተላለፊያ፣ እንዲሁም በኮክሊያ (ዉሰጥ የጆሮ ክፍል) ላይ በሚገቡ ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ መስማትን ማሻሻል ይቻላል። ነገር ግን የነዚህ መሳሪያዎች ውድ መሆን ተጠቃሚ  የሆኑ ህሙማን ጥቂቶች ብቻ እንዲሆኑ አስገድዷቸዋል ።      መ. ለከፍተኛ ድምፅ በመጋለጥ ከአየር ብክለት መካከል የሚካተተው ይህ የድምጽ ብክለት በአንድ ጊዜ በጣም ከፋተኛ ድምጽ በመሥማት ማለትም እንደ ተኩስ ፣ ፍንዳታ ድምጾች ወይም ለረጅም ጊዜ ከፍ ላለ ድምጽ ተጋላጭ በመሆን (የፍብሪካ ሠራተኞች ፣ ሙዚቃ ተጫዋቾች ፣ ምሽት ቤት ሠራተኞች ፣ሌሎችም) የሚከሠት ነው። ይህ ችግር የሚከሠተው በዋናነት  መሥማትን በሚቀበሉ ተንቀሳቃሽ ሴሎች ተጽኖ በመፍጠር ነው።    ይህን ችግር ለመከላከል ከፍተኛ የሆነ የድምጽ ብክለት መከላከል መመሪያ ሊተገበር ያስፈልጋል። እንደ ሀገር ይሔን ለማድረግ ደካማ ህግ እና ተቋሞች ቢኖሩም በግለሠብ ጀረጃ ጥንቃቄዎች ሊደረጉ ይገባል ።    ሠ. በመድሀኒት ምክንያት የሚመጡ ይህ ችግር መድሀኒት ከሚያዘው ባለሙያ ጋር ስለ መድሀኒት ተጎዳኝ ተጽኖ በመነጋገር በቀላሉ ማስወገድ ይቻላል። በተለይም ፦ ለሽንት ማሸኛ የሚወሠድ መድሀኒት (lasix) ፦ ለኢንፌክሽን የሚሠጡ aminoglycosides ፦ ለካንሰር ህመም የሚሠጥ cisplatin ፦ ለወባ በሽታ የሚሠጥ ክሎሮኪን ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግባቸው ያስፈልጋል። ረ. ከእድሜ ጋር የሚመጣ ሌሎች መስማት መቀነስ የሚያመጡ ችግሮች እንደሌሉ ከተረጋገጠ በሗላ እድሜያቸው በገፋ ሠወች ላይ የመስማት መቀነስ እና ጆሮ ውስጥ የሚፈጠር የሚጮህ ድምጽ ሊያጋጥም ይችላል ይሔም እንደማንኛውም ነርቭ መድከም ሊወሠድ ይችላል። በቀላል ምሳሌ ለማስረዳት ያህል ሬዲዮ ሲያረጅ ወይም ሲበላሽ ጥራቱ እንደሚቀንስ እና አላስፈላጊ ድምፅ እንደሚያወጣ ማለት ነው። የድምፅ ማገዣወች ይህን ችግር በተወሠነ መጠን ያስተካክላሉ። በአጠቃላይ የመስማት ችግር የሚፈጥረውን ዘርፈ ብዙ ጫና በመረዳት መከላከል ላይ እናተኩር። ዶ/ር አለማየሁ እሸት ከአንገት በላይ ስፔሻሊስት @HakimEthio

11/1/2016 ለአብዮት ቅድመ አንደኛ ደረጃ፣ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ / ቤት ከባድ እና ጥብቅ ጥንቃቄ መለእክት ለተማሪ ወላጆች በሙሉ ቀደም ሲል መስከረም 8/2016 ዓ.ም ለወላጆች መደረግ ስለሚገቡ ጥንቃቄዋች የአብዮት ትምህር ቤት ለወላጆች ማስገንዘቡ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ በስብሰባው ያልተገኙ አንዳንድ የተማሪ ወላጆች በዛሬው እለት የችግሩ ሰለባ ሆነዋል፡፡ ይህም ሁለት የትምህርት ቤታችን 6ኛ ክፍል ተማሪዎች በዛሬው እለት ከትምህርት ቤት ወደ ቤት በመጓዝ ላይ ሳሉ አንድ ማንነቱ ያልታወቀ ሌባ ልዩ ስሙ ለም ሄቴል በመንገድ ጠብቆ ህፃናቶችን በማታለል እኔ አድስ መምህራችሁ ነኝ፡፡ ስለሆነም አሁን ለተማሪዎች አድስ ኳስ ግዛላቸው ተብየ ልገዛላችሁ እየሄድኩ ነው፡፡ነገር ግን በችኮላ ስመጣ ቦርሳየን እና ስልኬን ትምህርት ቤት ረስቼ ስለመጣሁ እሮጥ ብላችሁ አምጡልኝ፡፡ ቦርሳችሁን ግን እዳያደክማችሁ እኔ ይዤ እጠብቃችኋለሁ፡፡ በማለት የተማሪዎችን አድስ ቦርሳ እድሁም የፅፈት መሳሪያ ደብተር እስኪብርቷቸውን አጭበርብሮ ወስዶባቸዋል፡፡ ስለሆነም ሁሉም የትምህርት ቤታችን ማህበረሰብ ከእደዚህ አይነት ማጭበርበር ከሚሰሩ ሰዎች ተማሪዎች ሰለባ እዳይሆኑ ተማሪዎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ከኛ በተጨማሪ በቤት እድታስገነዝቧቸው ስንል እናሳስባለን፡፡ ይህ መሞከሪያ ነው ከዚህ በበለጠ ህፃናት ተታለው ከማያቁት ሰው ጋር በምንም ተአምር እዳይሄዱ፣ እቃ መስጠትም ይሁን መቀበል እዳያደርጉ በታክሲም ይሁን በሌላ ትራንስፖርት እንሸኛችሁ ቢሏቸው አምነው ተከትለው እዳይሄዱ ሁሉም የተማሪ ወላጆች ለተማሪዎች በድግግሞሽ እድታስገነዝቡ እናሳስባለን፡፡ ይህ መለእክት በሁሉም ትምህርት ቤት የሚገኙ ተማሪ ወላጆች እድያስገነዝቡ ቢደረግ መልካም ነውና ሸር አድርጉ ለምታውቋቸው ሁሉ፡፡

Repost from Yeka Education
👉አማርኛ ቋንቋ ትምህርት በሩሲያ ሞስኮ ትምህርት ቤቶች መሰጠት ተጀምሯል። 👉የሩሲያው ዜና አግልግሎት ስፑቲኒክ እንደዘገበው አማርኛን ጨምሮ የአፍሪካ ቋንቋዎችን በሩሲያ ትምህርት ቤቶች መሰጠት ተጀ
+2
👉አማርኛ ቋንቋ ትምህርት በሩሲያ ሞስኮ ትምህርት ቤቶች መሰጠት ተጀምሯል። 👉የሩሲያው ዜና አግልግሎት ስፑቲኒክ እንደዘገበው አማርኛን ጨምሮ የአፍሪካ ቋንቋዎችን በሩሲያ ትምህርት ቤቶች መሰጠት ተጀምሯል። 👉የቋንቋዎቹ ትምህርት መጀመር በሩሲያ እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል የሚኖረውን ኢኮኖሚያዊ፣ ዲፕሎማሲያዊና በባሕላዊ መስኮች የነበሩ ትስስሮችን ይበለጥ ለማሳድግ ሚናው የጎላ መሆኑን የትምህርት ቤቶች ርዕሰ መምህራን ተናግረዋል። 👉አማርኛ ቋንቋን በሁለተኛ ቋንቋነት መማር የጀመሩ ተማሪዎች ለስፑቲኒክ እንደተናገሩት፣ ቋንቋውን ከማወቅ ባሻገር ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የህዝቡን ባህልና አኗኗር የማወቅ ጉጉት አሳድሮባቸዋል። 👉ሩሲያ በሞስኮ ትምህርት ቤቶች ከመስከረም ጀምሮ አማርኛ ቋንቋ ማስተማር እንደምትጀምር ባለፈው ዓመት ማስታወቋ ይታወሳል። via👉ኢዜአ