en
Feedback
Prosperity Party A.A - ብልፅግና

Prosperity Party A.A - ብልፅግና

Open in Telegram

የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Prosperity Party A.A - ብልፅግና

Channel Prosperity Party A.A - ብልፅግና (@prosperityaddis) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 14 456 subscribers, ranking 3 822 in the Politics category and 2 344 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 14 456 subscribers.

According to the latest data from 07 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -3 540 over the last 30 days and by -149 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 6.84%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 4.11% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 989 views. Within the first day, a publication typically gains 594 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Politics category.

14 456
Subscribers
-14924 hours
-6607 days
-3 54030 days
Posts Archive
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ማብራሪያ እና ምላሽ ይሰጣሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት (ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ማብራሪያ እና ምላሽ ይሰጣሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት (ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም) የመንግሥትን የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀርባሉ። በ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይም ከምክር ቤቱ አባላት ለሚነሡ ጥያቄዎች ማብራሪያ እና ምላሽ ይሰጣሉ። የጉባኤው ሙሉ ሂደትም ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች በቀጥታ ሥርጭት ለሕዝብ የሚተላለፍ ይሆናል። #aa_prosperity

መልካም ዘርን እየዘራን በጋራ እንተጋለን! በአብሮነት እንበለፅጋለን! በበጎነት የብዙዎች እምባ ታብሷል፤ በበጎነት የብዙዎች ተስፋ ለምልሟል፤ በበጎነት የብዙዎች ህመም ተፈውሷል፤ በበጎነት የብዙዎች ሀዘን ተወግዷል፤ በበጎነት የብዙዎች ደስታ ተመልሷል፡፡ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የህዝባችን መልካም እሴት ነው፡፡ ደስታንም ሀዘንንም የመጋራት የዳበረ ባህል ያለው ህዝባችን መተባበር፣ መረዳዳት፣ መተሳሰብ መለያው ነው፡፡ ያለው ለሌለው አካፍሎ በዓላትን በአብሮነት ማሳለፍ፣ የተቸገሩትን መርዳት፣ የደከሙትን ማበርታት የህዝባችን ነባር እሴት ነው፡፡ የህዝባችንን የበጎነት እሴቶች ተቋማዊ በማድረግ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ዓመቱን ሙሉ እንዲተገበር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጀመራቸው አበረታች ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶችን አስገኝተዋል፡፡ በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ በርካታ ትምህርት ቤቶች ተገንብተዋል ፣ የምገባ ማዕከላት ተገንብተዋል ፣ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ንቅናቄ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ጭምር ሰፍተውና ደረጃቸውን ጠብቀው ተሰርተዋል። እንኳንስ ማታ ቀንም ጭምር ለእንቅስቃሴ አስቸጋሪ በነበሩ ሰፈሮች ላይ በህብረተሰቡ የነቃ ተሳትፎ ቆሻሻን ያስወገዱ ፣ በውበት የደመቁ ፣ በመብራት ያሸበረቁ ሞዴል መንደሮች ተበራክተዋል። የቤት ልማት ፕሮግራም አካል በሆነውና በተለይም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን እምባ እያበሰ በሚገኘው የቤት ግንባታ መርሀ ግብርም የበጎ ፈቃደኞች አሻራ ጉልህ ነው። የከተማችን የደን ሽፋን ከነበረበት 2 ነጥብ 8 በመቶ ወደ 24 በመቶ ከፍ እንዲል በተገኘው አንፀባራቂ ድልም የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ውጤታማነት ደመቅ ብሎ ታይቷል። መስጠት አያጎልምና በጉልበታችን በገንዘባችን እና በእውቀታችን ዛሬ የምንዘራት መልካም ዘር የብዙዎችን ህይወት በመቀየር ለጋራ እድገታችን የጎላ ሚና እንደምታበረክት ልብ ማለት ይገባል፡፡ ብልፅግና ፓርቲ እየተገበረ የሚገኘው አሳታፊ፣ አካታች እና ሁሉን አቀፍ ልማት ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ፍትሀዊና ዘላቂ ተጠቃሚነት ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል፡፡ ልማት የሁሉንም ርብርብ እና ተሳትፎ ይጠይቃል፡፡ በተለያዩ አጋጣሚዎች ለተለያዩ ችግሮች የተጋለጡ ወገኖች በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተከናወኑ የሚገኙ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ተግባራት የልማት አቅሞቻችንን ያጎለብታሉ፤ ከተረጅነት ወደ አምራችነት የሚደረገውን ሽግግርም ያፋጥናሉ፡፡ በጎነትን በማጠናከር የብዙዎችን ተስፋ የምናለመልምበት መልካም የስራ ሳምንት ይሁንልን ! ይሁንላችሁ! መልካም የስራ ሳምንት !! በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት #aa_prosperity

በብክለት ከመጥፋት ወደ ማንሰራራት ! የቀበና ወንዝ ታሪካዊ ኡደት ! አዲስ አበባን የከበቧት ተራሮች ፣ በዙሪያዋና በውስጧ የሚገኙ እፅዋት ፣ አዕዋፋት ፣ እንስሳት ፣ ወንዞች እንዲሁም ሌሎች የተፈጥሮ ሀብቶች ከተማዋን ለኑሮ ይበልጥ ተስማሚ የሚያደርጉ የፈጣሪ ገፀ በረከቶች ናቸው:: ሁሉም ዜጋ በባለቤትነት ሊንከባከባቸውና ሊጠብቃቸው የሚገቡ የተፈጥሮ ሀብቶቻችን ለነገው ትውልድ አርቆ ባለማሰብ ችግር ከፍተኛ ጉዳት ሲያስተናግዱ ቆይተዋል። ውስብስብ ችግሮችን ካስተናገዱ ፣ አስታዋሽ ካጡ ፣ ችላ ከተባሉ የከተማችን ፀጋዎች ውስጥ የከተማችን ወንዞች ተጠቃሽ ናቸው። እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ ወንዞችን የቆሻሻ መጣያ አድርጎ የመመልከት አስተሳሰብ በመዳበሩ የተለያዩ ቆሻሻዎችን ወንዝ ላይ የሚጥሉ ግለሰቦች ቁጥራቸው ቀላል አልነበረም፤ ህሊናቸውን ባይወቅሳቸው እንኳን የህግ ተጠያቂነት ያለ የማይመስላቸው አንዳንድ ደንታቢሶች ዛሬም ቢሆን መኖራቸውን በተለያየ አጋጣሚ መታዘብ ይቻላል። የቀበና ወንዝ ከሚመነጭበት ከእንጦጦ ተራራ ትንሽ ወረድ እንዳለ ጀምሮ ወንዙ በሚወርድባቸው በሁሉም አካባቢዎች ፌስታልን ጨምሮ የተለያዩ ደረቅ ቆሻሻዎች ተከምረው መመልከት የተለመደ ሆኖ ቆይቷል። የወንዙ ተፈጥሮ ለቆሻሻ መጣያነት የሆነ እስኪመስል ድረስ ወደ ቀበና ወንዝ የማይወረወር ቆሻሻ አልነበረም። የሰው ልጅ በዚህ ልክ ከተፈጥሮ ጋር በመጣላት ህልውናውን አደጋ ላይ ይጥላል እንዴ ? ያስባሉ አደገኛ ድርጊቶች ቀበናን ጨምሮ በሌሎችም የከተማችን ወንዞች ላይ ተፈፅመዋል ። የመፀዳጃ ቤት ቱቦን ከቀበና ወንዝ ጋር የሚያገናኙ ግለሰቦች ቁጥራቸው ቀላል አልነበረም፤ የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶች ተደራሽ ባልሆኑባቸው የታችኛው የከተማችን አካባቢዎች አሁንም ቢሆን መሰል ችግሮች አይኖሩም ብሎ በልበ ሙሉነት ለመናገር አያስደፍርም። መደባበቅ ሳያስፈልግ ታግለን ማስወገድ የሚገባን ይህ የአደባባይ ገመና አይደለም በዓለም ሶስተኛዋ የዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የትኛውንም ከተማ ስለማይመጥን ፈጥኖ መታረም የሚገባው አፀያፊ ተግባር ነው። የቀበና ወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት ጋር በተያያዘ የወንዙን ህልውና ለማስጠበቅ ከሚደረጉ ስራዎች በተጨማሪ አውቀውም ይሁን ሳያውቁ ውሀውን በሚበክሉ ግለሰቦች እንዲሁም ተቋማት ላይ ጠበቅ ያለ ተጠያቂነትን የሚያሰፍን የህግ ማዕቀፍም መተግበር ጀምሯል። ወደ ወንዞች የሚለቀቁ ፍሳሾች ሁሉ ተገቢው ማጣሪያ ከተደረገላቸው በኋላ እንዲቀላቀሉም የክትትልና የቁጥጥር ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ። ለራሳቸውም ፣ ለጎረቤቶቻቸውም እንዲሁም ለአካባቢያቸው እና ለከተማችን የማይጨነቁ ምግባረ ብልሹ ግለሰቦችን መንግስት በህግ አግባብ ተጠያቂ ማድረጉ እንደተጠበቀ ሆኖ መሰል ድርጊቶች ከከተማችን ነዋሪዎች የተሰወሩ ስላልሆኑ በማጋለጥና ተጠያቂ እንዲሆኑ በማድረግ ከተማችንን ከጉስቁልና ማውጣትና እንደ ስሟ አበባ ማድረግ ከሁላችንም ይጠበቃል። በቀበና ወንዝ ተፋሰስ ልማት ወንዙ የሚፈስበትን የማስተካከል ፣ ዘመናዊና ደረጃቸውን የጠበቁ ድልድዮችን የመገንባት ፣ ወንዙ በሚያልፍባቸውን አካባቢዎች የአረንጓዴ ማልማት ፣ ፍሳሾች ወደ ወንዙ እንዳይገቡ የፍሳሽ ማስወገጃ የመስራት ፣ ዘርፈ ብዙ ግልጋሎት የሚሰጡ መለስተኛ ግድቦችን የመገንባት ፣ ከወንዙ ራቅ ብሎ የሚገኙትን የከተማው አካባቢዎችም አስተሳስሮ የማልማት ስራዎች በተቀናጀና በተናበበ መልኩ ተከናውነዋል። የውሃ ላይ መዝናኛዎች፣ አንፊ ቲያትሮች ፣ ፕላዛዎች፣ ደርጃቸውን የጠበቁ ፣ ከማራኪ ተፈጥሯዊ ገፅታ ጋር የተሰናሰኑ የእግረኛና የሳይክል መንገዶች እና ሌሎችም ለአዋቂዎችም እና ለህፃናትም መዝናኛ የሚሆኑ ልማቶች የቀበና ወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት በረከቶች ናቸው። በአካባቢው የነበሩ ሀገር በቀል ፣ እድሜ ጠገብ ዛፎችን በጠበቀ መልኩ ለምግብነት ጭምር የሚውሉ የተለያዩ እፅዋት መተከላቸው ለከተማችን ልምላሜ ትልቅ አቅም ፈጥሯል። በነዋሪዎቻችን ቀናህ ትብብርና ተሳትፎ ፣ በራሳችን የጉልበት ሰራተኞች ፣ በራሳችን ኮንትራክተሮች ፣ በራሳችን መሀንዲሶች ፣ በራሳችን ባለሙያዎች ፣ ከከተማ እስከ ወረዳ በሚገኙ አመራሮች የቅርብ ክትትል በመፍጠንና በመፍጠር እውን የሆነው የቀበና ወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት የአዲስ አበባን ሁለንተናዊ ተምሳሌትነት አስፍቷል። ኮንሶን በእርከን ስራ ለዓለም ካስተዋወቁና ኢትዮጵያን ካኮሩ እናት አባቶቻቸው ጠንካራ የስራ ባህል የወረሱ የኮንሶ ወጣቶችም በቀበና ወንዝ ዳር ፕሮጀክት ጉልህ አሻራቸውን አሳርፈዋል። በአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራው ዓለም አቀፍ ዝናን ያተረፈውን የኮንሶዎችን የእጅ ጥበብ በከተማችንም ለማሳረፍ ምቹ ሁኔታ የፈጠረው የቀበና ወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት በአንድ በኩል የሁላችንም ቤት የሆነችውን አዲስ አበባን በጋራ ለመገንባት በሌላ በኩል ደግሞ የህዝብ ለህዝብ ትስስራችንንም ከማጠናከር አኳያም የላቀ ፋይዳ አበርክቷል። ቀበና እና አከባቢው ለነዋሪዎች የደህንነት ስጋት ፣ የጤና ጠንቅ የነበረበት ጊዜ አብቅቶ ፤ ሁሉም የከተማችን ነዋሪዎች እንዲሁም ቱሪስቶች የሚያዘወትሩት ተጨማሪ የቱሪስት መዳረሻ ወደ መሆን ተሸጋግሯል። በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ ፅ / ቤት #aa_prosperity

አዲስ አበባ፦ የሕዝብ አገልጋዮችን በማገልገል ሁለንተናዊ ብልፅግናን እየገነባች ያለች ከተማ! የአዲስ አበባ ከተማ ለውጥ በሕንፃዎች ግንባታና በመሠረተ ልማት መስፋፋት ብቻ የሚገለጥ አይደለም ፤ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል የልማቱ ፍትሀዊ ተቋዳሽ አድርጓል እንጂ። የፓርቲያችን አሻጋሪ እሳቤዎች በተግባር እየተተረጎሙ የሕዝባችንን ኑሮ በቀጥታ የሚለውጡ የተቀናጁ ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ ሰው ተኮር ልማቶች እውን ሆነዋል። በከተማችን በየዘርፉ ተግባራዊ እየሆኑ የሚገኙ ልማቶች የነዋሪዎቻችንን የኑሮ ደረጃ ያሻሻሉ ፣ የአሁኑን ብቻም ሳይሆን መጪውን ትውልድም ታሳቢ ያደረጉ ዘላቂና ሰው ተኮር ልማቶች ናቸው። በበርካታ አገልግሎት ሰጪ መንግሥታዊ ተቋማት ውስጥ ለሚሰሩ ሰራተኞችና ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ዜጎች እየቀረበ የሚገኘው የመኖሪያ ቤት አቅርቦትና የማኅበራዊ ድጋፍ ፕሮግራሞች የዚህ ቁርጠኝነት ተጨባጭ ማሳያዎች ናቸው። በትናንትናው ዕለት በከንቲባ አዳነች አቤቤ ይፋዊ የግንባታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር የተካሄደለት የአዲስ አበባ ከተማ የፖሊስ ሰራዊት የተቀናጀ የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ ፕሮጀክትም የከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ መንግሥታዊ ተቋማት ውስጥ ሆነው ሕዝባቸውን በታማኝነት የሚያገለግሉ ሰራተኞችን ለመደገፍ ያለውን የጸና ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ ነው። የሕዝብ አገልጋዮችን ለማብቃት እንዲሁም ህይወታቸውን ለማሻሻል አቅም በፈቀደ መጠን የሚደረገው ርብርብ የሕዝብ አገልጋይነትን ይበልጥ ለማጠናከርም ያግዛል። የአገልጋይነት ባህልን በማሳደግ ጠንካራ ተቋማትን መገንባት ለዘላቂ ሰላም፣ ለፍትሃዊ ልማት እና ለሁለንተናዊ ብልፅግና መረጋገጥ ቁልፉ ጉዳይ ነው። በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ጽ/ቤት #aa_prosperity

የውይይት ባህልን በማዳበር የፅንፈኝነት አስተሳሰብን እንስበር ! ለዘመናት ሲንከባለሉ የመጡ ችግሮቻችን በዳበረ የውይይት ባህል ፣ በስልጡን የፖለቲካ አካሄድ ዘላቂ መፍትሔ ያገኛሉ። ፅንፍና ፅንፍ ተራርቆ በመነቃቀፍም የሚባባስ እንጅ የሚፈታ ችግር ሊኖር አይችልም። በጠብ መንጃ አፈሙዝ የራስን ፍላጎት ለማሳካት የሚደረግ የድንቁርና አካሄድም ወደ ጥልቅ የችግር አዙሪት ውስጥ ከማስገባት ውጭ የሚፈይደው አንዳች ነገር እንደሌለ የመጣንበት ታሪክ ምስክር ነው። ብልፅግና ፓርቲ "ሰላምን በሰላማዊ መንገድ ብቻ " በሚል መርህ ትዕግስት በሚፈታተን እልህ ብርቱ ርብርብ እያደረገ የሚገኘውም የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ ጠንቅቆ በመረዳት ፣ ዘመኑንም በመዋጀት ነው፡፡ በኃይል ስልጣን ማግኘት ፣ ፍላጎትን ከሌሎች ላይ መጫን በአንድ ወቅት ተሳክቶ ሊሆን ይችላል ፤ ውጤቱ ግን ተያይዞ ጥፋት መሆኑ በተግባር ታይቷል። አሁን ላይ ባለው ነባራዊ ሁኔታ ደግሞ አይደለም ስልጣን በኃይል ማግኘት ለማሰብ የማይቻልበት ሁኔታ ተፈጥሯል። ህዝባችን በ7 ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለፅንፈኞች ዛቻ ጆሮ ባለመስጠት ከሌሊት እስከ ሌሊት በአይበገሬነት በመምረጥ ፣ ፍፁም ሰላማዊ፣ ነፃ ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ፍትሀዊ ምርጫ በማካሄድ ያስተላለፈው መልክት ዋና ማጠንጠኛም " በምርጫ ብቻ " የሚል ነው። ከህዝብ እና ከሀገር ጥቅም በሚፃረር መልኩ የግል እና የቡድን ጥቅምን ማሳደድ ለጊዜው ሊመስል ይሆናል እንጅ ውጤቱ የጋራ ጉብቁልና ነው። በድሀ ህዝብ መካከል የሚገኝ የግል እና የቡድን ክብር የለም። በተዋረደች እና እጆቿን ለልመና በዘረጋች ሀገር ውስጥ አንገቱን ቀና አድርጎ የሚሄድ ዜጋ አይኖርም። ለአካታችነት እና ለአሳታፊነት እንዲሁም ለፍትሀዊ ተጠቃሚነት ልዩ ትኩረት የሚሰጠው የመደመር ፍልስፍና ልዩነትን እያጠበበ አብሮነትን እያጠበቀ በጋራ የመምከር፣ በጋራ የመስራት ፣ በጋራ የማደግ ባህልን እየገነባ ይገኛል። መተሳሰቡ ፣ መከባበሩ ፣ መደማመጡ ካለ ኢትዮጵያ ለሌሎችም የሚትረፈረፉ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ፀጋዎች አሏት። ሁለንተናዊ ብልፅግናን የማረጋገጥ ርብርቡ አንዱን የሚጠቅም አንዱን የሚያገል እንዳልሆነ ከእስካሁኑ ሂደት ተረጋግጧል። ፅንፈኝነት የሰላም ፀር ነው። ፅንፈኝነት የዕድገት ፀር ነው። ለዚህ መድሀኒቱ ደግሞ ሚዛናዊነትን ተላብሶ በሰጥቶ መቀበል መርህ በጋራ መምከር ነው። ከፅንፈኝነት መራቅ እና ፅንፈኝነትን መታገል እንደተጠበቀ ሆኖ ዘላቂ መፍትሄ ለሆነው የውይይት ባህል መዳበር አሻራን ማሳረፍ ከሁላችንም ይጠበቃል ። በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት #aa_prosperity

የዜጎችን አኗኗር ምቹ እና ዘመናዊ ማድረግ የኮሪደር ልማት መርሃ-ግብራችን ዋነኛ ግብ ነው። ‎ያየነው የአርባ ምንጭ ከተማ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት፤ ዘመናዊ የአስፋልት መንገድ እና መብራቶችን እና ዲጂታል ስክሪኖችን ያካተተ ሲሆን በተጠናቀቁት የኮሪደር ስራዎች ላይ አገልግሎቱ ተጀምሯል። ‎ ‎ጥራቱን የጠበቀ ዘመናዊ መሠረተ-ልማትን ከአረንጓዴ ልማት ጋር በማስተሳሰር የከተሞቻችንን ምቹነት የማረጋገጥ ስራችን ተጠናክሮ ይቀጥላል! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) #aa_prosperity

በጋራ እንመክራለን ! የጋራ እጣ ፈንታችንን በጋራ እንወስናለን ! ኢትዮጵያውያን ልዩነቶቻቸውን አክብረው፣ በብዝሀነት ተሰባጥረው ፣ በአብሮነት ተጋምደው የኖሩት በመካከላቸው ችግሮች ስላልነበሩ ሳይሆን ችግሮችን በራስ አቅም የመፍታት የቆየ የመቻቻል እና የመከባበር ባህል ስለነበራቸው ነው። መልካም መስተጋብርን የሚያጠብቁ ጥንታዊ እሴቶች ስለነበሯቸው የሚገጥሟቸውን ችግሮች በዛፍ ጥላ ስር ቁጭ ብለው እየመከሩ መፍትሄ ሲሰጡ ኖረዋል ፤ አሁንም ቢሆን ይህ መልካም እሴት ምን አልባትም ደብዝዞ ሊሆን ይችላል እንጅ አልጠፋም። ጥራዝ ነጠቅ የሆኑ የፅንፈኝነት አካሄዶች ፣ እኔ ብቻ ትክልል የሚል ግትርነት ፣ እኔ ያልሁት ካልሆነ የሚል ተቸካይነት የህዝባችን እሴቶች አይደሉም። ኋላቀር ፖለቲካ የወለዳቸው ፣ ነጠላ ትርክት ያጎመራቸው የፅንፈኝነት አካሄዶች ሀገራችንን እና ህዝባችንን በተደጋጋሚ ከባድ ዋጋ ሲያስከፍሉ ኖረዋል። ከዛም ከዚህም የሚታዩ የህዝብን ሰላም የሚያውኩ ፣ በብሔራዊ ጥቅም የሚቆምሩ ፣ ለባዕዳን ባደሩ ባንዳዎች የሚለኮሱ የጥፋት ድግሶች መነሻቸውም ሆነ መድረሻቸው ከሀገራዊ እሴቶች እንዲሁም ከዘመናዊ ስልጣኔ የተጣላ ኋላቀር የፖለቲካ ባህል ነው፡፡ ሲንከባለሉ ለመጡ ሀገራዊ ችግሮች የስልጡንነት መገለጫ በሆነው የጠረንጴዛ ዙሪያ ውይይት ዘላቂ መፍትሄ ለማበጀት ኢትዮጵያ ስትመክር ቆይታለች። ብሔራዊ ምክክሩ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ድምፅ ሲያሰባስብ ቆይቶ የኢትዮጵያን ብሩህ ነገ ወደሚፈነጥቅ አዲስ ምዕራፍ እየተሸጋገረ እንደሚገኝ ኮሚሽኑ አብስሯል። ኃምሌ 8 / 2018 ዓ.ም ከሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች ፣ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች የወከሉ ኢትዮጵያውያን በጅምር ላይ ያለውን የሀገረ መንግስት ግንባታ ጨምሮ በሌሎችም የጋራ እጣፈንታቸው ላይ በአብሮነት ይመክራሉ። በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት #aa_prosperity

ኢትዮጵያ ትመክራለች! ትስማማለች ! ኢትዮጵያውያን ለህዝብ ክብር ፣ ለሀገር ልዕልና የህይወት መስዋዕነትነት እስከመክፈል የሚደርስ የወንድማማችነት ፣ የእህትማማችነት እንዲሁም የአብሮነት አኩሪ ታሪክ
ኢትዮጵያ ትመክራለች! ትስማማለች ! ኢትዮጵያውያን ለህዝብ ክብር ፣ ለሀገር ልዕልና የህይወት መስዋዕነትነት እስከመክፈል የሚደርስ የወንድማማችነት ፣ የእህትማማችነት እንዲሁም የአብሮነት አኩሪ ታሪክ አላቸው። የመተሳሰብ ፣ የመደማመጥ እንዲሁም የመከባበር ሀገራዊ እሴቶች እየተሸረሸሩ በመምጣታቸው ፣ የፅንፈኝነት አስተሳሰብ እንደ ሰደድ እሳት በመስፋፋቱ ሀገርንና ህዝብ አላስፈላጊ ዋጋ ሲከፍሉ ቆይተዋል። ፅንፈኝነት ሀገር የሚያደማበት ፣ ፅንፈኝነት ህዝብን አላስፈላጊ መስዋዕትነት የሚያስከፍልበት ጊዜ እንዲያበቃ ፓርቲያችን ብልፅግና አሻጋሪ እሳቤዎችን ነድፏል ፤ መንግስትም ህዝባችንን በማሳተፍ በቁርጠኝነት እየተገበረ ይገኛል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን አንግቦት የተነሳው ታላቅ ሀገራዊ ራዕይ እንዲሳካ ፓርቲያችን የድርሻውን ሲወጣ ቆይቷል። በቀጣይም የሚጠበቅበትን መወጣቱን አጠናክሮ ይቀጥላል። ኢትዮጵያ የምትመክርበት ፣ ኢትዮጵያ የምትከብርበት ፣ ኢትዮጵያ የምትደመጥበት ፣ ታሪካዊውና ብሩህ ተስፋ ፈንጣቂው ብሔራዊ ምክክር በድል እንዲቋጭ በየደረጃው የሚገኘው አመራር ፣ አባላት ፣ ደጋፊዎች ፣ ሁሉም የከተማችን ነዋሪዎች ታሪካዊ አሻራቸውን ማሳረፍ ይጠበቅባቸዋል፤ ይገባቸዋልም። በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት #aa_prosperity

የእንጦጦ - ቀበና የወንዝ ዳርቻ  ፕሮጀክት፦  የከተማችን አዲስ ድምቀት!! የእንጦጦ - ቀበና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት  የወንዝ ዳርቻ ልማት  ብቻ ሳይሆን፣  የብልፅግናን  እሳቤ በተግባር ያሳየ ታላቅ  ከተማ አቀፍ ብቻ ሳይሆን ሀገራዊ  ፕሮጀክት ነው! ፕሮጀክቱ  በአጠቃላይ 10.35 ኪሎ ሜትር ርዝመትና 87.6 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ይህ ግዙፍ ስራ፣ ከተማችንን ወደ ላቀ የውበትና የፅዳት ደረጃ ከማሸጋገሩ ባለፈ፣ በቀጥታ የነዋሪውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጠ ነው። ፕሮጀክቱ የወንዝ ዳርቻ ልማት ብቻ ሳይሆን፣ የከተማዋን ገጽታ የቀየሩ ዘመናዊ ግድቦችም የተገነቡበት ነው። በዚህም መነሻነት፦ 1 የከተማዋን ገፅታ የሚቀይር  ታላቅ ግድብ፣ 16  ውሃ ፍሰቱን የሚቆጣጠሩና ውበት የሚሰጡ አነስተኛ ግድቦች፣  3 ቼክ ዳሞች ፣ 20.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ጠንካራ የድጋፍ ግንብ/ግድግዳ ግንባታ አካባቢውን ከአደጋ የሚጠብቅ እና 3 ሰው ሰራሽ ፏፏቴዎች እና አስደናቂ የውሃ ምንጭ ግንባታዎች ተጠናቀው ለአገልግሎት ከፍት ሆነዋል፡፡ የብልፅግና ጉዟችን ማዕከሉ ሰው ነው!  ፕሮጀክቱ ወንዝን ከመጠበቅና ከመንከባከብ ባለፈ፤ የቱሪስትና የህዝብ መዝናኛ መስህብ በመሆን፣ በዙሪያው ለሚኖሩ በርካታ ነዋሪዎች ሰፊ የስራ እድል ፈጥሯል። በተጨማሪም ለህፃናት መጫወቻ፣ ለአዋቂዎች ማረፊያና ለአገልግሎት መስጫ የሚሆኑ በርካታ የህዝብ መጠቀሚያ ስፍራዎችን በውስጡ አካቶ ይዟል። ፕሮጀክቱ የሀገርን ከፍታና የዜጎችን የኑሮ ጥራት ማሻሻል እንደሚቻል ያሳየ ህያው ምስክር ነው!! በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ