Prosperity Party A.A - ብልፅግና
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Prosperity Party A.A - ብልፅግና 的分析概览
频道 Prosperity Party A.A - ብልፅግና (@prosperityaddis) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 175 名订阅者,在 政治 类别中位列第 4 082,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 575 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 175 名订阅者。
根据 30 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -1 943,过去 24 小时变化为 -162,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 6.39%。内容发布后 24 小时内通常能获得 4.71% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 842 次浏览,首日通常累积 620 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት”
凭借高频更新(最新数据采集于 31 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 政治 类别中的关键影响点。
13 175
订阅者
-16224 小时
-3427 天
-1 94330 天
帖子存档
ለምድራችን በረከት፣ ለዘላቂ ዕድገታችን አስተማማኝ መሰረት! አረንጓዴ አሻራ ለትውልዱ ተስፋን የምንተክልበት ታሪካዊ ሁነት!
ፓርቲያችን ያስቀመጠው በሀገራዊ አቅም ላይ መሰረትን ያደረገ የዘላቂ ዕድገት አቅጣጫ እውን እንዲሆን የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ፋይዳው ብዙ ነው፡፡ የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም የሀገራችንን የደን ሽፋን በከፍተኛ ደረጃ በመጨመር፣ የደን መመናመንን በመግታት ለመጪው ትውልድ የለመለመች ኢትዮጵያን ለማሻገር ወሳኝ ነው፡፡
የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን አሉታዊ ተፅዕኖ ለመቀነስ ቁልፍ ሚና የሚጫወተው የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም የአፈር መሸርሸርን በመከላከል ለምርታማነት ጉልህ ሚና ይጫወታል፡፡
የከርሰ ምድር ውሃ እንዲሞላ በማድረግ የውሃ ምንጮች እንዳይደርቁም ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረክታል፡፡ አረንጓዴ አሻራ የተለያዩ እንስሳትና እፅዋት እንዲሁም አዕዋፋት እንዳይጠፉና ወደ ሌሎች ሀገራትም እንዳይሰደዱ ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ለብዝሀ ህይወት መጠበቅም ዋስትና ይሰጣል፡፡
የዝናብ ስርጭትን በማስተካከል ድርቅና እሱን ተከትሎ የሚመጣውን የምርታማነት ችግር ለማስወገድም አረንጓዴ አሻራ ሚናው ላቅ ያለ ነው፡፡
የደን ውጤቶች የበርካታ ሀገራት ኢንዱስትሪዎችም የጀርባ አጥንት መሆናቸው ይታወቃል፡፡ ኢትዮጵያም የአየር ንብረቷን ከማረጋገጥ ባሻገር ለተለያዩ የፈርኒቸር ምርቶች አስተማማኝ ግብዓት እንዲኖራት ስለሚያስችል ኢንዱስትሪውን ይበልጥ ያነቃቃል፡፡
የክቡር ጠ/ሚ ዐብይ አህመድ ኢኒሸቲቭ የሆነው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብራችን ለምግብነት የሚያገለግሉ የተለያዩ አትክልትና ፍራፍሬዎች እንዲተከሉ በማድረግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለሚደረገው ርብርብም ተጨማሪ አቅም ፈጥሯል፡፡
ሀገራችን በተለይም በቀንድ ከብት ከቀዳሚዎቹ ተርታ የምትሰለፍ በመሆኗ የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራማችን በእንስሳት መኖ ላይ የሚያጋጥመውን ሰፋ ያለ ችግር ለማቃለልም የማይተካ ሚና ያበረክታል፡፡
ኢትዮጵያ ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመሳሰሉ ግድቦችን እየገነባች የታዳሽ ሀይል አቅርቦቷን በእጅጉ እያስፋፋች በመሆኑ ታላላቅ ግድቦቻችን የተመጣጠነ ውሀ እንዲኖራቸው በማድረጉ በኩልም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር አስተማማኝ ዋስትና ነው፡፡
ለመዲናችን አዲስ አበበባ አንፀባራቂ ዕድገት ጉልህ ሚና እያበረከተ ለሚገኘው የቱሪዝን ዘርፍም መርሀ ግብሩ ትልቅ አቅም መፍጠሩን መገንዘብ ይቻላል፡፡
ሀገር አቀፍ የህዝብ ተሳትፎን በማሳደግ ህዝባችን በወንድማማችነት እና በእህትማማችነት ስሜት ለጋራ ልማት በአብሮነት እንዲነሳ በማድረግ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ማህበራዊ መስተጋብርን ከፍ አድርጓል፡፡
ተዘርዝረው ከማያልቁ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳዎቹ ባሻገር በዲፕሎማሲው መስክም የኢትዮጵያን ተፅዕኖ ፈጣሪነት አሳድጓል፡፡ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት መዛባት መኖሩን በማስረዳት መተባበር እንደሚገባ ከመጠየቅ ወጥታ አንገቷን ቀና አድርጋ መሞገት የምትችልበትን ተጨባጭ ድል አስመዝግባለች፡፡ ሚሊዮኖችን በማሳተፍ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን መትከል የቻለችው ኢትዮጵያ ለምድራችን ልምላሜ፣ ለመጪው ትውልድ ብሩህ ተስፋ በታሪክ ሲዘከር የሚኖር አሻራዋን እያሳረፈች ትገኛለች፡፡
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት
#aa_prosperity
ለሀገራችን ልምላሜ! ለከተማችን ውበት! አረንጓዴ አሻራ የአብሮነታችን ድምቀት!
በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም 4 ቀናት ብቻ ቀሩት!
ጎረቤት ሀገራትን እና ሌሎችንም የሚያረሰርሱ ድንበር ተሻጋሪ ወንዞች እያሏት የተጠማች፣ ለም አፈር እያላት ተመፅዋች፣ ሆና የኖረችውን የሀገራችንን ታሪካዊ ስብራቶች እየጠገኑ ከሚገኙ ውጤታማ እርምጃዎች አንዱ ነው፤ አረንጓዴ አሻራ፡፡
የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ(ዶ/ር) የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሸቲቭ መተግበር ከጀመረበት 2011 ዓ.ም ጀምሮ የህዝባችን ችግኝ የመትከል ብቻም ሳይሆን ችግኞችን የመንከባከብ ባህል በእጅጉ ተሻሽሏል፡፡ በተጨባጭም የሀገራችን የደን ሀብት ከመራቆት ወደ ማንሰራራት ተሸጋግሯል፡፡
ለሀገራዊ ዓላማ በአብሮነት መሰባሰቢያ፣ ወንድማማችነትን እና እህትማማችነትን ማጥበቂያ፣ የጋራ ብሩህ ነገን መገንቢያ የሆነው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የህዝባችንን አብሮነት አጠናክሯል፡፡
የሀገርን ጉዳይ ከግል እና ከቡድን ፍላጎቶች በማስቀደም ብዝሀ ማንነቶች፣ ብዝሀ ሀሳቦች በአንድነት የሚስተጋቡበት በመሆኑ ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታም ምቹ መደላድል የሚፈጥር ነው፡፡
የምንተክላት እያንዳንዷ ችግኝ የነገ ልምላሜያችን፣ የነገ ጥላችን እንዲሁም የነገ ውበታችን ናት፡፡ ተፍጥሮ በብዙ መልኩ አሟልታ ሰጥታናለች፡፡ በአግባቡ መያዝ ስላልቻልን ድርቅን ለመሳሰሉ ተፈጥሯዊ አደጋዎች በእጅጉ ተጋልጠን ቆይተናል፡፡ አረንጓዴ አሻራ ኢትዮጵያን ከነበረችበት ከፍተኛ የመራቆት ደረጃ በማውጣት ለዓለም የአየር ንብረት መጠበቅ ተምሳሌት ያደረገ ተግባራዊ እርምጃ ነው፡፡
በጥቂት ዓመታት ውስጥ 48 ቢሊዮን ችግኞችን መትከል እራሱን የቻለ የገዘፈ ታሪክ ነው፤ ከ4 ቀናት በኋላ የምናካሂደው በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ደግሞ አይበገሬነታችንን ጭምር ለዓለም የምናሳይበት ታሪካዊ ሁነት ነው፡፡
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት
#aa_prosperity
የአንድ እቅድ አንድ ሪፖርት ስርአት በመዘርጋት እና በማጠናከር የፓርቲውን አሰራር ዲጂታላይዝ በማድረግና ዲጂታል ብልፅግና ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ስራዎች ተከናውነዋል ።አምባሳደር ሀሰን አብዱልቃድር
የብልፅግና ፓርቲ የስትራቴጂ ሥራ አመራርና የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ የ2018 ዓመታዊ የእቅድ አፈፃፀም እና የ2019 እቅድ ላይ የተዘጋጀ መድረክ በሐረር ከተማ እያካሄደ ይገኛል ።
በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽሕፈት ቤት በሚኒስትር ማዕረግ የስትራቴጂ ሥራ አመራርና የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ ኃላፊ አምባሳደር ሀሰን አብዱልቃድር በመክፈቻ መድረኩ ላይ እንደተናገሩት በተለይ የ2018 አፈጻጸም ለመገምገም እና በአመቱ የነበሩትን ጥንካሬዎች እንዲሁም ክፍተቶች በመሙላት ለ2019 የሚደረግ የዝግጅት የውይይት መድረክ እንደሚሆን አንስተዋል ።
ምንም እንኳን ዘርፉ በጣም ጥቂት ዓመት ዕድሜ ያለው ቢሆንም በአንድ ዓመት ውስጥ ዘርፈ ብዙ ስራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል።
በ2018 በጀት ዓመት በተለይም ከአንድ ዕቅድ፣ ከአንድ ሪፖርት እና የምዘና ስርዓቱን ከማዘመን አንጻር የተጀመሩ አበረታች ስራዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል ።
በዚህ የጋራ መድረክ አንዱ ከአንዱ የሚማማርበት፣ ልምድና ተሞክሮ የሚለዋወጥበት፣ የተሻለ አፈጻጸም ያላቸው ክልሎች ተሞክሯቸውን የሚያካፍሉበት መድረክ ስለሆነ የተሻለ ስራ አጠናክሮ ለመቀጠል ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው አስረድተዋል።
ይህንን የቴክኖሎጂ ማዘመን ስራ እንዲሁም አጠቃላይ የፓርቲ ስራዎችን ወደ ሲስተም እና ወደ ዲጂታል ምዝገባ ለማዛወር በሚደረገው ሂደት ውስጥ በዚህ ዓመት የተሰሩ ስራዎች እንደሚገመገም እና ቀጣይ አቅጣጫዎችን የሚቀመጥ መሆኑን አብራርተዋል።
በተጨማሪም ይህ መድረክ በነገው ዕለት በተለይ ከአንድ ዕቅድ፣ ከአንድ ሪፖርት እና ከዲጂታል ምዝገባ ጋር ተያይዞ ልምድና ብቃት ባላቸው የስራ ኃላፊዎች ስልጠና እንደሚኖር ጠቁመዋል ።
የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ በበኩላቸው ይህ መድረክ መዘጋጀቱ በዋናነት ኢትዮጵያ ለማየት ለማወቅ እና አብሮነትን ለማጠናከር ያለመ መሆኑን ጠቁመዋል።
ስራዎች ከመገምገም ባሻገር ሌሎች ለተያዙ የውህደትና ብዝሃነት በተለይ የነበሩትን የፖለቲካ ስብራቶች ከመጠገን አንጻር እንደዚህ ዓይነት መድረኮች በየቦታቸው መዘጋጀት አብሮነታችንን፣ ወንድማማችነታችንን እና እህትማማችነታችንን ወደ ተሻለ ደረጃ እንደሚያሻግር አክለዋል።
ፖለቲካችንን ወደ ስታንዳርድ የማምጣት ስራ ለመስራት ፓርቲዉ ዝግጅቶች አድርጎ ወደ ትግበራ መግባቱን አንስተው ይህንን በጥልቀት በመወያየት፣ ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የተሻለ፣ ከፍ ወደ አለ ደረጃ የሚያሻግር ሰፊ ውይይት እንደሚደረግ ጠቁመዋል ።
በውይይቱ መድረክም የሁሉም ክልሎች አመታዊ አፈፃፀም ሪፖርተር እየቀረበ ሰፊ ውይይት እየተደረገ ይገኛል ።
#aa_prosperity
የግብርና ትራንስፎርሜሽን በኢትዮጵያ አይቀሬ መሆኑን የባሌ አርሶ አደሮች ስኬት በግልጽ ይመሰክራል- ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)
የብልፅግና ፓርቲ ህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ አመራሮች በባሌ ዞን ሲናና ወረዳ በክላስተር የለማ የስንዴ ማሳን የጎበኙ ሲሆን፣ የዘርፉ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በጉብኝቱ ወቅት "የግብርና ትራንስፎርሜሽን በኢትዮጵያ አይቀሬ መሆኑን የባሌ አርሶ አደሮች ስኬት በግልጽ ይመሰክራል" ብለዋል።
ይህ የባሌ ዞን የስንዴ ልማት ስኬት ብልፅግና ፓርቲ ለግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ ለገጠር መዋቅራዊ ሽግግር፣ ለሜካናይዜሽን እና ለኢንዱስትሪያላይዜሽን የሰጠውን ከፍተኛ ትኩረትና የፖሊሲ ፍሬ የሚያሳይ ትልቅ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትርጉም ያለው ክስተት ነው።
መንግሥት የግብርና መሣሪያዎች ከቀረጥ ነፃ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ያደረገው ውሳኔ በቀላሉ የሚታይ የግብር ማሻሻያ ሳይሆን፣ የግብርናውን ክፍለ-ኢኮኖሚ ከመሰረቱ ለመቀየር የተወሰደ ስትራቴጂካዊ የፖሊሲ እርምጃ ነው። በሲናና ወረዳ የአስተራረስ ዘዴው ከባህላዊ ወደ ዘመናዊ ተቀይሮ 74% በላይ በሜካናይዜሽን መሸፈኑ፣ የፓርቲው የልማት ፖሊሲዎች ከወረቀት ወጥተው የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት በተግባር ማሳደጋቸውን የሚያረጋግጥ ነው።
የግብርና ትራንስፎርሜሽን የመጨረሻ ግብ የምርት መጠን መጨመር ብቻ ሳይሆን የአርሶ አደሩን የአስተራረስ ባህልና የማህበራዊ-ኢኮኖሚ ግንኙነት ማዘመን ነው። አርሶ አደሮች በክላስተር ተደራጅተው በጋራ የሚያርሱበት፣ የሚወቅጡበት እና የሚሰበስቡበት አዲስ የስራ ባህል መፍጠራቸው የተበታተነውን ባህላዊ የገጠር ኢኮኖሚ ወደ ተደራጀና ዘመናዊ የምርት ኃይል ቀይሮታል።
በወረዳው የሚገኙ አርሶ አደሮች በራሳቸው አቅም ፋብሪካ ለመመሥረት በዝግጅት ላይ መሆናቸው፣ የብልፅግና ፓርቲን የኢንዱስትሪ ሽግግር ራዕይ መሬት ያወረደ ትልቅ ማሳያ ነው። አርሶ አደሩ በጥሬ ምርት አቅራቢነት ብቻ ሳይወሰን የምርት እሴት ጨማሪ እና ባለፋብሪካ የሚሆንበት መንገድ መከፈቱ፣ የገጠር ካፒታል ወደ ኢንዱስትሪ መዋዕለ-ነዋይ የመሸጋገሩ ትልቅ መዋቅራዊ እርምጃ ነው።
ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ እንደገለጹት፣ ይህንን የመሬት ላይ ስኬት ወደ ሙሉ ሀገራዊ ብልፅግና ለመቀየር ከአርሶ አደሩ ነባራዊ ሁኔታ ጋር የተጣጣመ ውጤታማ የኮሙኒኬሽን መንገድ መጠቀም ወሳኝ ነው። የህዝቡን ንቃተ-ህሊና የሚያሳድግ እና የልማት ባለቤትነቱን የሚያረጋግጥ የመረጃ ልውውጥ ማድረግ የትራንስፎርሜሽኑን ዘላቂነት ያረጋግጣል።
በአጠቃላይ፣ "ባሌ ኢትዮጵያን የመመገብ የተፈጥሮ ፀጋ ያለው አካባቢ ነው" የሚለው እውነት አሁን በቴክኖሎጂ፣ በፖሊሲ ድጋፍ እና በህዝብ ተሳትፎ ታግዞ የሀገሪቱን የምግብ ሉዓላዊነት የሚያረጋግጥ ትልቅ ኃይል ሆኗል። ይህም የብልፅግና ፓርቲ የኢኮኖሚ ፍልስፍና የሀገሪቱን የነገ ተስፋ በራስ አቅም የመገንባት አቅሙን በተግባር ያሳየበት ማረጋገጫ ነው።
800 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ደማቅ ታሪክ ለመፃፍ 5 ቀናት ብቻ ይቀሩናል!
በአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ባለፉት የለውጥ ዓመታት 48 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል የማይቻል የሚመስልን ታምር በተጨባጭ ማሳካት ተችሏል፡፡
በድርቅ እና በረሀብ የምትታወቀው ኢትዮጵያ አሁን ላይ የልምላሜ ቀንዲል ወደመሆን እየተሸጋገረች ትገኛለች፡፡ በየዓመቱ የተተከሉ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞች ‹‹በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ›› እንደሚባለው ዘርፈ ብዙ ጥቅሞችን እየሰጡ ይገኛሉ፡፡
የአየር ንብረትን ከመጠበቅ ባሻገር የቡና ኤክስፖርታችን በእጅጉ እንዲጨምር፣ የሌሎች ፍራፍሬዎች ምርታማነትም ከእጥፍ በላይ እንዲያድግ፣ በአጠቃላይ ለምግብ ሉዓላዊነት ለሚደረገው ርብርብ አረንጓዴ አሻራ የጎላ ሚና ማበርከት ጀምሯል፡፡
መርሀ ግብሩ የአፈር መሸርሸርን ቀንሷል፤ በመጥፋት አፋፍ ላይ የነበሩንት እና ጠፍተው የነበሩትን ወንዞች እና ሀይቆች ህልውና መታደጉንም የሀሮሚያን ሀይቅ መጥቀስ ይቻላል፡፡
የመዲናችን አዲስ አበባ የደን ሽፋን ከ2 ነጥብ 8 ወደ 24 በመቶ ከፍ ያለውም በዚሁ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ነው፡፡
በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ደማቅ ታሪክ ለመፃፍ እንዘጋጅ!
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት
#aa_prosperity
የብልፅግና ፓርቲ ህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ አመራሮች አረንጓዴ አሻራቸውን በመዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ቅጥር ቅቢ ውስጥ አኑረዋል።
የዘርፉ ከፍተኛ አመራሮች በዞኑ የተለያዩ የልማት ስራዎችንና የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን እየጎበኙ ይገኛሉ።
በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ተክለን ሌላ አዲስ ታሪክ ለመፃፍ 5 ቀናት ብቻ ቀርተዋል።
#aa_prosperity
አረንጓዴ አሻራ - ለጋራ መግባባት እና አገራዊ አንድነት !
ባለፉት ዓመታት በአገር አቀፍ ደረጃ በንቅናቄ ሲካሄድ የቆየው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን ከመትከል ባለፈ የአካባቢን ስነ ምህዳር በመጠበቅ፣ በስራ እድል ፈጠራ፣እንዲሁም ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡
በእነዚህ ዓመታት በርካታ ኢትዮጵያውን ያለ ልዩነት በንቅናቄ በማሳተፍ በሕዝቦች ዘንድ ለአብሮነትና ለአገራዊ መግባባት የራሱን ሚና ሲጫወት ቆይቷል፡፡ ይህ መርሃ ግብር ከተለያዩ አካባቢዎች ፣ ከተለያዩ ማንነትና አመለካከቶች ያላቸው ኢትዮጵያን በንቅናቄ ማሳተፍ መቻሉ ዜጎች ለአንድ ዓላማና ለአገራዊ እድገት እንዲሰለፍ በማድረግ መነቃቃትን ፈጥሯል፡፡
በተለይም ደግሞ የችግኝ ጉድጓድ አብሮ የመቆፈር፣ አብሮ የመትከል ሁኔታ በሕዝቦች ዘንድ ማሕበራዊ መስተጋብር በመፍጠር ለአገራዊ ጉዳዮችን በጋራ ለመወያየትና ለመመካከር ምቹ ሁኔታን የፈጠረ ነው፡፡
እርስ በእርስ የመወያየትና የመነጋገር ባህላችን እየጎለበተ እንዲሄድና ችግሮች የመፍታት ልምድ እንዲዳብር እድል የሚሰጥ ነው፡፡
ዓለም አቀፍ የአየር ንብት ለውጥ እያስከተ ያለውን ጉዳት ለመከላከል እንዲሁም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የአረንጓዴ አሻራን ቀጣይነት ባለው መልኩ ማከናወን እንደሚገባ በዜጎችን ዘንድ መግባባትና አዎንታዊ ትብብር መፍጠር የቻለ ኢንሸቲብ ነው፡፡
ዛሬ የሚተክለው ችግኝ ለነገ ትልውድ የሚተላለፍ ውርስ በመሆኑ ዜጎች የወደፊት የአገራቸውን መጻኢ እድል በጋራ ለመጠበቅና ለመንከባከብ የኃላፊነት ስሜት እንዲዳብር ያደርጋል፡፡ በዚህ ከእኔነት ይልቅ የእኛ የሚል አስተሳሰብን በማስተጋባት ነጋቸውን የተሻለ በማድረግ የአገር ባለቤትነት ስሜት እንዲዳብር ያድጋል፡፡
ኢትዮጵያውያን በአገራዊ ፕሮጀክቶቻችን በጋራ የመሳተፍ ባህል እየጎለበተ በሄደ ቁጥር የአገራዊ መግባባትና ውይይት መጠናከር መሠረት የሚጥል መሆኑ የአረንጓዴ አሻራ ማሳያ በመሆኑ በንቃት መሳተፍ ይገባል፡፡
#aa_prosperity
አዲስ አበባ እየተዋበች፤ የዜጎች ፍትሃዊ ተጠቃሚነትም እያረጋገጠች የብልፅግና ማሳያ ከተማ እየሆነች ነው!
ዛሬ አዲስ አበባ አሮጌውን ሸማዋን እያወለቀች፣ አዲስ ብርሃን፣ አዲስ ተስፋ እና አዲስ ውበት በመጎናፀፍ ላይ ናት።
ጎዳናዎቿ አረንጓዴን እየለበሱ፣ ህንጻዎቿ በዘመናዊ ዲዛይን እየተቀየሩ ከምንም በላይ ደግሞ ለነዋሪዎቿ ህይወት መቀየር፣ ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ላይ አትኩራለች።
የከተማችን የሰው ተኮር ልማት ስራዎች በአስከፊ ሁኔታ የሚኖሩትን ወገኖች አስታውሰው፤ ለህፃናቱም፥ ለአዋቂውም፥ ለድሃውም፥ ለሃብታሙም ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ የሚያደርጉ ናቸው ።
ከነዚህ ሰው ተኮር ተግባራት ውስጥ አንዱ ትናንት በቆጥ ላይ ፣ በቆሸሸ ጎጆዎች፣ መፀዳጃ ቤት በሌላቸው፣ ክረምት ሲገባ በሚያፈሱ ቤቶች በኑሮም በጤናም እጅግ እየተቸገሩ ይኖሩ የነበሩ አቅመ ደካሞች እና የሀገር ባለውለታዎች ክብር ያለው ኑሮ እንዲኖሩ የመኖሪያ ቤት ለማቅረብ የተሰራው አኩሪ ተግባር በትልቁ ከሚጠቀሱት ውስጥ ነው ።
በተስፋ ብርሃን ምገባ ማዕከላት አረጋውያን ፥ ማህበራዊ ችግር ያለባቸው የሃገር ባለውለታዎች በቀን አንድ ጊዜ እየተመገቡ ይገኛሉ። በተመሳሳይ በትምህርት ቤቶች ተማሪዎች ቁርስ እና ምሳ ይመገባሉ። በቀዳማይ ልጅነት ልማት ፕሮግራም እድሜአቸው እስከ ስድስት ዓመት የሆኑ ህፃናት እና አነስተኛ ገቢ ያላቸው ወላጆች ተጠቃሚ ሆነዋል።
ይህ ሁሉ ለቀጣይ ትውልድ የተሻለ ከተማ፣ ንጹህ አካባቢ እና ተስፋ የተሞላ ህይወት የማኖር ተግባር ነው።
አዲስ አበባ እየተዋበች ብቻ ሳይሆን፣ ዜጎቿንም እየቀየረች ያለች የብልፅግና ማሳያ ከተማ እየሆነች ነው!
#aa_prosperity
