fa
Feedback
Prosperity Party A.A - ብልፅግና

Prosperity Party A.A - ብልፅግና

رفتن به کانال در Telegram

የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Prosperity Party A.A - ብልፅግና

کانال Prosperity Party A.A - ብልፅግና (@prosperityaddis) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 120 مشترک است و جایگاه 3 613 را در دسته سیاست و رتبه 2 171 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 120 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 29 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -3 343 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -63 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 8.99% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 4.73% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 1 390 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 731 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 30 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته سیاست تبدیل کرده‌اند.

15 120
مشترکین
-6324 ساعت
-3757 روز
-3 34330 روز
آرشیو پست ها
የእንጦጦ - ቀበና የወንዝ ዳርቻ  ፕሮጀክት፦  የከተማችን አዲስ ድምቀት!! የእንጦጦ - ቀበና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት  የወንዝ ዳርቻ ልማት  ብቻ ሳይሆን፣  የብልፅግናን  እሳቤ በተግባር ያሳየ ታላቅ  ከተማ አቀፍ ብቻ ሳይሆን ሀገራዊ  ፕሮጀክት ነው! ፕሮጀክቱ  በአጠቃላይ 10.35 ኪሎ ሜትር ርዝመትና 87.6 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ይህ ግዙፍ ስራ፣ ከተማችንን ወደ ላቀ የውበትና የፅዳት ደረጃ ከማሸጋገሩ ባለፈ፣ በቀጥታ የነዋሪውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጠ ነው። ፕሮጀክቱ የወንዝ ዳርቻ ልማት ብቻ ሳይሆን፣ የከተማዋን ገጽታ የቀየሩ ዘመናዊ ግድቦችም የተገነቡበት ነው። በዚህም መነሻነት፦ 1 የከተማዋን ገፅታ የሚቀይር  ታላቅ ግድብ፣ 16  ውሃ ፍሰቱን የሚቆጣጠሩና ውበት የሚሰጡ አነስተኛ ግድቦች፣  3 ቼክ ዳሞች ፣ 20.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ጠንካራ የድጋፍ ግንብ/ግድግዳ ግንባታ አካባቢውን ከአደጋ የሚጠብቅ እና 3 ሰው ሰራሽ ፏፏቴዎች እና አስደናቂ የውሃ ምንጭ ግንባታዎች ተጠናቀው ለአገልግሎት ከፍት ሆነዋል፡፡ የብልፅግና ጉዟችን ማዕከሉ ሰው ነው!  ፕሮጀክቱ ወንዝን ከመጠበቅና ከመንከባከብ ባለፈ፤ የቱሪስትና የህዝብ መዝናኛ መስህብ በመሆን፣ በዙሪያው ለሚኖሩ በርካታ ነዋሪዎች ሰፊ የስራ እድል ፈጥሯል። በተጨማሪም ለህፃናት መጫወቻ፣ ለአዋቂዎች ማረፊያና ለአገልግሎት መስጫ የሚሆኑ በርካታ የህዝብ መጠቀሚያ ስፍራዎችን በውስጡ አካቶ ይዟል። ፕሮጀክቱ የሀገርን ከፍታና የዜጎችን የኑሮ ጥራት ማሻሻል እንደሚቻል ያሳየ ህያው ምስክር ነው!! በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ

የቀበና ወንዝ እና የአካባቢው አንፀባራቂ ለውጥ ለከተማችን ተጨማሪ ፍካት! የጠራ ራዕይ ፣ አሻጋሪ እሳቤ፣ የጋራ ህልም ፣ የጋራ ርብርብ ለጋራ ድል አብቅቷል። ክቡር ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ ፣ የአዲስ አበባ ከንቲባ ክብርት አዳነች አቤቤ እና ሌሎችም በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ሰርቶ በማሰራት የስራ መርህ ለከተማችን ትንሳኤ ታሪካዊ አሻራቸውን አሳርፈዋል። ወጣቶች ፣ ሴቶች ፣ ባለሀብቶች ፣ አካል ጉዳተኞች ፣ አረጋዊያን ሁሉም የከተማችን ነዋሪዎች በከተማችን ፈጣን የዕድገት ግስጋሴ ላይ የድርሻውን ተወጥቷል፤ በየዘርፉ የተመዘገበውን ውጤትም በጋራ ተቋድሰዋል ፤ ለላቀ ድልም ቃል ኪዳናቸውን አድሰዋል። የከተማችን ሁለንተናዊ ተምሳሌትነት ጉዞ በተደመረ አቅም አቅም ፣ በላቀ ተነሳሽነት ተጠናክሮ ቀጥሏል። በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለህዝባችን አገልግሎት መስጠት የጀመረው የእንጦጦ - ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት የከተማችንን የቱሪስት መዳረሻነት በማሳደግ ተምሳሌትነቷን አስፍቷል። ቀበና ወንዝ ተደቅኖበት በነበረው ከፍተኛ ብክለት ፣ በጎርፍ እና በአፈር መንሸራተት እንዲሁም በፀጥታ ችግር የስጋት ህይወት ሲኖሩ የቆዩ የአካባቢው ነዋሪዎችም ተገቢው ምትክ ቦታ እና ካሳ ተሰጥቷቸው የተሻለ ህይወት የሚኖሩበት ዕድል ተፈጥሯል። የቀበና ወንዝ እና የአካባቢው መልማት፣ መለወጥና የስዕበት ማዕከል መሆኑም ጥቅሙ ለከተማችን ነዋሪዎች ብቻም ሳይሆን ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን ነው። የከተማችን ከፍታ ከሆነው ከእንጦጦ ተራራ የሚነሳውና እስከ ቀበና አደባባይ 10 ነጥብ 5 ኪሜ ርዝመት ያለው ይህ ፕሮጀክት አጠቃላይ ስፋቱ 87 ነጥብ 6 ሄክታር ነው። በውብ ተፈጥሯዊ ገፅታ የተከበበ መንገድ ፣ ደረጃቸውን የጠበቁ ድልድዮች ፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳዎች ፣ የመኪና ፓርኪንግ ፣ ቤተ መፅሀፍት ፣ መፀዳጃ ቤት ፣ የህፃናት መጫዎቻ ፣ መሰብሰቢያ አዳራሽ ፣ ፕላዛዎች ፣ በርካታ የንግድ ቤቶች እና ሌሎችም መሰረተ ልማቶች እና የህዝብ መገልገያዎች የተካተቱበት ይህ ፕሮጀክት የዚህ ትውልድ ደማቅ አሻራ ፣ የመጪው ትውልድ ምንዳ ነው። የዘላቂ እድገት እሳቤ ውጤት የሆነው ፣ ከተፈጥሮ ጋር የተስማማው ይህ ፕሮጀክት መለስተኛ ግድቦችን ፣ ማራኪ ፏፏቴዎችን እንዲሁም ለምግብነት የሚውሉ እፅዋት የተካተቱበት ሰፋፊ የአረንጓዴ ልማት በውስጡ ይዟል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ እና የክ/ከተማ አመራሮች ሰሞኑን በክቡር ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ የተመረቀውን የእንጦጦ - ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በመጎብኘት ተጨማሪ ልምድ እና ተሞክሮዎችን ቀስመዋል። ለረጅም ዘመን ትኩረት ተነፍጎት ለከፍተኛ ብክለት እንዲሁም ለህገ ወጥ ግንባታዎች ተጋልጦ የቆየው የቀበና ወንዝና አካባቢው በተባበሩ እጆች ፣ በተደመሩ አቅሞች ማራኪ ገፅታን በመላበሱ የብዙዎችን ትኩረት መሳቡን በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ /ፅ /ቤት የልዩ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳርዳር ብርሀኑ ለጎብኝዎች በሰጡት ማብራሪያ አስገንዝበዋል። በቀጣይም ሌሎች በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ፕሮጀክቱን እንደሚጎበኙት ይጠበቃል። በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ /ፅ /ቤት #aa_prosperity

የዘላቂ ልማታችን ተስፋ፣ የከፍታ ጉዞአችን ተጨማሪ አቅም! የእንጦጦ- ቀበና ወንዝ ዳር ፕሮጀክት! ፀጋዎቻችን በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላችን ከተማችንን የሚያሳድጉ፣ የነዋሪዎችን ህይወት የሚያሻሽሉ በርካታ አቅሞች ሲባክኑ ቆይተዋል፡፡ ሩቅ የማለም ፣ አቅዶ የመተግበር የዳበረ የስራ ባህል በመፈጠሩ አዲስ አበባ የቁልቁለት ጉዞዋ ተገትቶ ወደ ከፍታዋ እየገሰገሰች ትገኛለች፡፡ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በመጣው የተለወጠ እሳቤ የጉስቁልና ታሪኳ የሚወገድበት ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ ከተማችን በቆሻሻነት የምትጠቀስበት አሮጌው የታሪክ ምዕራፍ ተዘግቷል፡፡ አዲስ አበባ አሁን ላይ በየትኛውም ዓለም አቀፍ መመዘኛ ተስፋ የሚጣልባት በፈጣን እድገት ውስጥ የምትገኝ ተወዳዳሪ ከተማ ሆናለች፡፡ የከተማችን ፈጣን ዕድገት የነዋሪዎችን የኑሮ ደረጃ ከማሻሻል በተጨማሪ የወንዞቻችንን ትንሳኤም አብስሯል፡፡ ህልውናቸው ተመናምኖ በስም ብቻ ወደ መታወስ ተቃርበው የነበሩ ቀበናን የመሳሰሉ ወንዞቻችን የልጅነት ትዝታ ከመሆን ወጥተው በአዲስ ማንሰራራት ተጨባጭ እውነታ ሆነዋል፡፡ ህፃናት የሚቦርቁባቸው ውብ መጫዎቻዎች፣ ወጣቶች በአካል የሚገነቡባቸው የስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ የረጅም እርቀት አትሌቶች ልምምድ የሚያደርጉባቸው ምቹ መንገዶች፣ አረጋዊያን ነፋሻማ አየር የሚቀበሉባቸው ምቹ ሆኔታዎች ተፈጥረዋል፤ በእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት፡፡ ለብዙዎች የስራ ዕድል የሚፈጥሩ የተለያዩ ሱቆች፣ ካፍቴሪያዎች እና መሰል አገልግሎት መስጫዎችም የልማታችንን ሰው ተኮርነት አመላካች ናቸው፡፡ በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት #aa_prosperity

የእንጦጦ- ቀበና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት የዘላቂና ሰው ተኮር ልማታችን አንዱ ማሳያ ነው! አዲስ አበባ በተራሮች የተከበበች፣ በርካታ ወንዞች፣ የተለያዩ እፅዋትና አዕዋፋት እንዲሁም ለኑሮ ተስማሚ የአየር ንብረት ያላት በተፈጥሮ የታደለች ከተማ ብትሆንም በየጊዜው እየተራቆተች የደን ሽፋኗ 2 ነጥብ 8 በመቶ ከመድረሱ ባሻገር ሁሉም ለማለት በሚያስደፍር ሁኔታ ወንዞቿም ለከፍተኛ ብክለት ተዳርገው እንደነበር ለከተማችን ነዋሪዎች መንገር ለቀባሪ እንደ ማርዳት ነው፡፡ በየዓመቱ ሚሊዮኖች እያሳረፉት በሚገኘው አረንጓዴ አሻራ የከተማችን የደን ሽፋን 24 በመቶ የደረሰ ሲሆን ዓለም አቀፍ ስታንዳርድ የሆነውን የ30 በመቶ የደን ሽፋን ለማሟላት ርብርቡ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ከተሞች የህንፃ ጫካ ብቻ አይደሉም በሚል መርህ ከተፈጥሮ ጋር የተስማማ ዘላቂ ኢኮኖሚ ለመገንባት እየተደረገ የሚገኘው እንቅስቃሴ የመዲናችንን ልምላሜ መልሷል፡፡ ከከተማችን ተፈጥሯዊ ፀጋዎች መካከል የሆኑት ወንዞቻችንም በቆሻሻ ክምር ተሞልተው አስታዋሽ አጥተው ቆይተዋል፡፡ የብዙዎች ትውስታ የሆነው የቀበና ወንዝ ተጋርጦበት የቆየውን የህልውና አደጋ ለአብነት መጥቀስ ይቻላል፡፡ ከእንጦጦ ተራራ ስር ኩልል ብሎ የሚወርደው የቀበና ወንዝ ከመነሻው ወረድ እንዳለ ጀምሮ የቆሻሻ መጣያ በመደረጉ ወደ ቆሻሻነት ተቀይሮ ቆይቷል፡፡ የወንዙን መውረጃ ተከትለው ማዶና ማዶ የተገነቡ ቤቶች የወንዝ ዳርቻን መልካም መዓዛ እና መልካም ገፅታ ሳይሆን መጥፎ ሽታን እና አስቀያሚ ገፅታን ተጎራብተው ኖረዋል፡፡ የወንዙ መውረጃ በቆሻሻ በመሞላቱም በተለይም በክረምት ወቅት የሚከሰተው ከፍተኛ ጎርፍ በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ የህልውና ስጋት ፈጥሮ ቆይቷል፡፡ በቀበና ወንዝ ላይ ተደቅኖ የነበረው የህልውና አዳጋ እና ከፍተኛ ብክለት በከተማችን በተለይም በአካባቢው ነዋሪዎች የእለት ከዕለት እንቅስቃሴ ላይ ትልቅ ተግዳሮት ሆኖ ቆይቷል፡፡ በሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት በክቡር ጠ/ሚ ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በተቀመጠው የወንዝ ዳርቻን የማልማት አቅጣጫ የለማው ቀበና ወንዝ እና አካባቢው አሁን ላይ የስዕበት ማዕከል ወደመሆን ተሸጋግሯል፡፡ በአንድ በኩል በአካባቢው በአስቸጋሪ ሁኔታ የነበሩ ነዋሪዎችን ህይወት በመታደግ ለኑሮ ምቹ በሆነ አካባቢ የሚኖሩበት ዕድል የተፈጠረ ሲሆን፤ የቀበና ወንዝ እና የአካባቢው ልማት ለመላው የከተማችን ህዝብ ግልጋሎት የሚሰጥ የዚህ ትውልድ አሻራ፣ የመጪው ትውልድ ምንዳ ነው፡፡ የእንጦጦ ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በቆሻሻ ተጋርዶ የነበረውን የከተማችንን ማራኪ ገፅታ በመግለጥ የቱሪስት መዳረሻ ማድረግ አስችሏል፡፡ ማንሰራራት ከጀመረው የቀበና ወንዝ ባሻገር በአካባቢው የሚገኙ ሀገር በቀል እፅዋት የሚለግሱት መልካም መዓዛ አካባቢውን ለብዙዎች ተመራጭ እንደሚያደርገው ይጠበቃል፡፡ ደረጃቸውን የጠበቁ ድልድዮች፣ በርከት ያሉ መለስተኛ ግድቦች ፣ ሰፋፊ የአረንጓዴ ልማት ቦታዎች፣ እረጃጅም የእግረኛ እና የብስክሌት መንገዶች፣ የህፃናትና የታዳጊዎች መጫዎቻዎች፣ የስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ ፕላዛዎች፣ ሱቆች፣ ካፍቴሪያዎች እና ሌሎችም መሰረተ ልማቶች አልፎ ለመሄድ ጭምር አስቸጋሪ የነበረውን የቀበና ወንዝ አካባቢ የቱሪስት መዳረሻ አድርገውታል፡፡ ልማታችን የህዝባችንን ህይወት የሚያሻሽል ሰው ተኮር ነው፡፡ ልማታችን የዛሬውን ትውልድ ተጠቃሚነት ብቻም ሳይሆን የመጪውን ትውልድ ጥቅም የሚያስጠብቅ፣ ከተፈጥሮ ጋር የተሰናሰነ ነው፡፡ በመሀል ከተማ የጀመረው የመልሶ ግንባታ ስራችን ሁሉንም የከተማችንን አካባቢዎች ተደራሽ በማድረግ የህዝባችንን ፍትሀዊና ዘላቂ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ይጓዛል፡፡ በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት #aa_prosperity

የእንጦጦ- ቀበና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት የዘላቂና ሰው ተኮር ልማታችን አንዱ ማሳያ ነው! አዲስ አበባ በተራሮች የተከበበች፣ በርካታ ወንዞች፣ የተለያዩ እፅዋትና አዕዋፋት እንዲሁም ለኑሮ ተስማሚ የአየር ንብረት ያላት በተፈጥሮ የታደለች ከተማ ብትሆንም በየጊዜው እየተራቆተች የደን ሽፋኗ 2 ነጥብ 8 በመቶ ከመድረሱ ባሻገር ሁሉም ለማለት በሚያስደፍር ሁኔታ ወንዞቿም ለከፍተኛ ብክለት ተዳርገው እንደነበር ለከተማችን ነዋሪዎች መንገር ለቀባሪ እንደ ማርዳት ነው፡፡ በየዓመቱ ሚሊዮኖች እያሳረፉት በሚገኘው አረንጓዴ አሻራ የከተማችን የደን ሽፋን 24 በመቶ የደረሰ ሲሆን ዓለም አቀፍ ስታንዳርድ የሆነውን የ30 በመቶ የደን ሽፋን ለማሟላት ርብርቡ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ከተሞች የህንፃ ጫካ ብቻ አይደሉም በሚል መርህ ከተፈጥሮ ጋር የተስማማ ዘላቂ ኢኮኖሚ ለመገንባት እየተደረገ የሚገኘው እንቅስቃሴ የመዲናችንን ልምላሜ መልሷል፡፡ ከከተማችን ተፈጥሯዊ ፀጋዎች መካከል የሆኑት ወንዞቻችንም በቆሻሻ ክምር ተሞልተው አስታዋሽ አጥተው ቆይተዋል፡፡ የብዙዎች ትውስታ የሆነው የቀበና ወንዝ ተጋርጦበት የቆየውን የህልውና አደጋ ለአብነት መጥቀስ ይቻላል፡፡ ከእንጦጦ ተራራ ስር ኩልል ብሎ የሚወርደው የቀበና ወንዝ ከመነሻው ወረድ እንዳለ ጀምሮ የቆሻሻ መጣያ በመደረጉ ወደ ቆሻሻነት ተቀይሮ ቆይቷል፡፡ የወንዙን መውረጃ ተከትለው ማዶና ማዶ የተገነቡ ቤቶች የወንዝ ዳርቻን መልካም መዓዛ እና መልካም ገፅታ ሳይሆን መጥፎ ሽታን እና አስቀያሚ ገፅታን ተጎራብተው ኖረዋል፡፡ የወንዙ መውረጃ በቆሻሻ በመሞላቱም በተለይም በክረምት ወቅት የሚከሰተው ከፍተኛ ጎርፍ በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ የህልውና ስጋት ፈጥሮ ቆይቷል፡፡ በቀበና ወንዝ ላይ ተደቅኖ የነበረው የህልውና አዳጋ እና ከፍተኛ ብክለት በከተማችን በተለይም በአካባቢው ነዋሪዎች የእለት ከዕለት እንቅስቃሴ ላይ ትልቅ ተግዳሮት ሆኖ ቆይቷል፡፡ በሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት በክቡር ጠ/ሚ ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በተቀመጠው የወንዝ ዳርቻን የማልማት አቅጣጫ የለማው ቀበና ወንዝ እና አካባቢው አሁን ላይ የስዕበት ማዕከል ወደመሆን ተሸጋግሯል፡፡ በአንድ በኩል በአካባቢው በአስቸጋሪ ሁኔታ የነበሩ ነዋሪዎችን ህይወት በመታደግ ለኑሮ ምቹ በሆነ አካባቢ የሚኖሩበት ዕድል የተፈጠረ ሲሆን፤ የቀበና ወንዝ እና የአካባቢው ልማት ለመላው የከተማችን ህዝብ ግልጋሎት የሚሰጥ የዚህ ትውልድ አሻራ፣ የመጪው ትውልድ ምንዳ ነው፡፡ የእንጦጦ ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በቆሻሻ ተጋርዶ የነበረውን የከተማችንን ማራኪ ገፅታ በመግለጥ የቱሪስት መዳረሻ ማድረግ አስችሏል፡፡ ማንሰራራት ከጀመረው የቀበና ወንዝ ባሻገር በአካባቢው የሚገኙ ሀገር በቀል እፅዋት የሚለግሱት መልካም መዓዛ አካባቢውን ለብዙዎች ተመራጭ እንደሚያደርገው ይጠበቃል፡፡ ደረጃቸውን የጠበቁ ድልድዮች፣ በርከት ያሉ መለስተኛ ግድቦች ፣ ሰፋፊ የአረንጓዴ ልማት ቦታዎች፣ እረጃጅም የእግረኛ እና የብስክሌት መንገዶች፣ የህፃናትና የታዳጊዎች መጫዎቻዎች፣ የስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ ፕላዛዎች፣ ሱቆች፣ ካፍቴሪያዎች እና ሌሎችም መሰረተ ልማቶች አልፎ ለመሄድ ጭምር አስቸጋሪ የነበረውን የቀበና ወንዝ አካባቢ የቱሪስት መዳረሻ አድርገውታል፡፡ ልማታችን የህዝባችንን ህይወት የሚያሻሽል ሰው ተኮር ነው፡፡ ልማታችን የዛሬውን ትውልድ ተጠቃሚነት ብቻም ሳይሆን የመጪውን ትውልድ ጥቅም የሚያስጠብቅ፣ ከተፈጥሮ ጋር የተሰናሰነ ነው፡፡ በመሀል ከተማ የጀመረው የመልሶ ግንባታ ስራችን ሁሉንም የከተማችንን አካባቢዎች ተደራሽ በማድረግ የህዝባችንን ፍትሀዊና ዘላቂ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ይጓዛል፡፡ በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት #aa_prosperity

ቀበና! በትጉህ እጆች ትንሳኤው ተበስሯል! ወደ ቀደመ ከፍታው ተመልሷል! ጠቢባን የተቃኙለት ፣ ታዳጊዎች የዋኙበት ፣ የብዙዎች የልጅነት ትውስታ ፣ አዲስ አበባ ሲባል ቀድመው ከሚመጡ ወንዞች አንዱ ! ቀበና ! ባለግርማ ሞገሱ የቀበና ወንዝ በአያያዝ ጉድለት የክረምት ጎርፍ ብቻ ወደ መሆን የተሸጋገረበት የህልውና አደጋ ተጋርጦበት ቆይቷል። ለብዙ አገልግሎት ሲጠጥ የነበረው የቀበና ወንዝ በጊዜ ሂደት አይደለም ለመዋኛ ለእይታም ከማይመችበት ሁኔታ ደርሶ እንደነበር የትናንት ትውስታችን ነው፡፡ በተለወጠ አስተሳሰብ፣ በተሻጋሪ እይታ ፣ በዳበረ የስራ ባህል ውብ አበባ መሆን እንደጀመሩት አሮጌ የከተማችን መንደሮች ፣ ቀበናን የመሳሰሉ ወንዞቻችንም የጉስቁልና ታሪካቸው ተሽሮ የማንሰራሪያ ጊዜአቸው ተበስሯል። የአዲስ አበባ ከፍታ ከሆነው ከታሪካዊው የእንጦጦ ተራራ የሚመነጨው ታሪካዊው ወንዝ ወደ ቀድሞ ከፍታው ተመልሷል። ታዳጊዎች የሚዋኙባቸው የነበሩ የቀበና ወንዝ የተለያዩ ቦታዎችአሁን ላይ የቆሻሻ ክምራቸው ተወግዶ መለስተኛ ግድቦች ሆነዋል። በተለይም ቀበና አደባባይ ወይም ኮከበ ፅባህ ት/ቤት አካባቢ የተፈጠረውን መለስተኛ ግድብ የተመለከተ የከተማችን ነዋሪ እንዲህም ይቻላል እንዴ ? ብሎ እንደሚጠይቅ ጥርጥር የለውም። በቦታው ከተፈጠረው ግዙፍ ግድብ ባሻገር ለብዙዎች የስራ ዕድል የፈጠሩት የንግድ ማዕከላት አይንን ገለጥ አድርጎ መስራት ከተቻለ ታምር መስራት እንደሚቻል አመላካች ናቸው። ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ የሁለተኛውን ዙር የኮሪደር ልማት ሲያስጀምሩ በወንዝ ዳር ፕሮጀክት እንዲለማ ባስቀመጡት አቅጣጫ የለማው የእንጦጦ - ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት የወንዙን ህልውና ከማስጠበቅ ባሻገር የከተማችንን ተምሳሌታዊ ጉዞ አንድ ደረጃ ወደ ፊት አራምዷል። የነዋሪዎችን ህይወት በሚያሻሽል መልኩ አዲስ አበባን ውብ አበባ ለማድረግ የተጀመረው ቅንጅታዊ ርብርብ በከተማችን ውስጥ የሚፈስሱ ወንዞች ተፈጥሯዊ ንፅህና እንዲመለስ በማድረግ ለነዋሪዎቻችን ዘርፈ ብዙ ጥቅም የሚሰጡበትን ዕድል ፈጥሯል፤ ቀበና ወንዝ አንዱ ማሳያ ነው። የወንዝ ዳርን ተከትለው በተሰሩ ቤቶች የሚኖሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ብቻም ሳይሆኑ ሌላውም የከተማችን ነዋሪ በአንድም በሌላም በወንዞች መበከል ለተለያዩ የጤና እክሎች ተጋላጭ ሆነው ቆይቷል። ከምንም በላይ ግን በወንዙ ዳርና ዳር የሚኖሩ ነዋሪዎች ከጤና እክል በተጨማሪ በተለይም በክረምቱ ወራት ለሚፈጠር የጎርፍ እና የአፈር መሸርሸር አደጋ ተጋላጭነታቸው ከፍ ያለ ነበር። መነሻውን የከተማችን ከፍታ ከሆነው ከእንጦጦ ተራራ ያደረገው ፣ 87 ነጥብ 6 ሄክታር መሬት የሚሸፍነው ፣ 10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ግዙፉ የእንጦጦ - ቀበና ወንዝና የወንዝ ዳር ፕሮጀክት ወንዙን ብቻም ሳይሆን የስጋት ህይወት ይኖሩ የነበሩ በርካታ ነዋሪዎቻችንን ታድጓል። የእንጦጦ - ቀበና ወንዝ እና የወንዝ ዳር ፕሮጀክት የወንዙን ህልውና በመታደግ ለከተማችን ገፅታ ግንባታ ጉልህ ሚና የሚያበረክት የቱሪስት መዳረሻ ማዕከል አድርጎታል። በአካባቢው ለነበሩ ነዋሪዎችም ከአስቸጋሪና ከስጋት ህይወት በማላቀቅ የተሻለ ምትክ እና ካሳ አግኝተው ለኑሮ ምቹ በሆነ አካባቢ የሚኖሩበትን ሁኔታ መፍጠር አስችሏል። በገደላማእና የጤና ጠንቅ ፣ የፀጥታ ስጋት ሆነው በቆዩ አስቸጋሪ የቀበና ወንዝ ዳርቻ ቦታዎች የነበሩ ነዋሪዎችም "በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ " እንደሚባለው በአንድ በኩል ብዙ ትዝታ ያሳለፉበት እና የህልውና አደጋ ተጋርጦበት የቆየው የቀበና ወንዝ ለከተማችን ነዋሪ ጥቅም ላይ እንዲውልና ወደቀድሞ ዝናው እንዲመለስ የሚያስችል ልማት በመሰራቱ ፤ በሌላ በኩል ደግሞ በወንዙ መበከልና በአፈር መሸርሸር ምክንያት የስጋት ህይወት ከሚኖሩበት አካባቢ ወጥተው ፣ ተገቢውን ካሳና ምትክ አግኝተው የተሻለ መሰረተ ልማት ወዳለበት አካባቢ በመሄዳቸው ደስታቸው እጥፍ ድርብ መሆኑን ሲናገሩ ይደመጣል። የብዙዎች የልጅነት ትውስታ ፣ ለነዋሪዎች የንፁህ ውሃ ምንጭ ሆኖ የቆየው የቀበና ወንዝ ተፋሰስ በባለቤትነት በእንክብካቤ ባለመያዙ የህልውና አደጋ ተጋርጦበት ቆይቷል። ከነፋሻማው የእንጦጦ ተራራማ አካባቢ ኩልል ብሎ የሚወርደው የቀበና ወንዝ ብዙ ርቀት ሳይጓዝ ፈሳሽ እና ደረቅ ቆሻሻዎች መጣያ እንጅ የተዜመለት ስመ ገናናው ቀበና አይመስልም ነበር። በተፈጥሯዊና በሰው ሰራሽ መስህቦች ከተዋበው የእንጦጦ ተራራ ተነስቶ ፒኮክ መናፈሻ የሚደርሰው የቀበና ወንዝ ዳር ፕሮጀክት የአካባቢውን ብቻም ሳይሆን የከተማችንን የቱሪስት መዳረሻነት ከፍ አድርጓል። የተለያዩ ሀገር በቀል እፅዋትን ፣ ለከተማችንም ተጨማሪ የውሃ አቅም የሚሆኑ ምንጮችን ፣ አዕዋፋትን እና እፅዋትን በስሩ የያዘው እንጦጦ እና አካባቢው በቀበና ወንዝ ዳር ፕሮጀክት መለስተኛ የውሃ ግድቦችም ስለተገነቡለት ለከተማችን ነዋሪዎች ከሚሰጠው ዘርፈ ብዙ ግልጋሎት ባሻገር ለእፅዋት ፣ ለእንስሳት እንዲሁም ለአዕዋፋት መበራከት ሚናው የጎላ ነው። በቀበና ወንዝ ዳርቻዎች የተገነቡ መለስተኛ ግድቦች የውሀውን ንፅህና ከመጠበቅ ባሻገርም በጋም ክረምትም የሚፈስ ወንዝ እንዲሆንም ትልቅ አቅም ይፈጥሩለታል። በትክክለኛ የልማት አቅጣጫ ፣ የትናንት ትውስታን መለስ ብሎ በቃኘ ፣ ነገን አሻግሮ በተመለከተ ሰው ተኮር እሳቤ ፣ ቃልን በተግባር በተረጎመ ትጋት ወደ ነበርነት ተቀይሮ የነበረው የቀበና ወንዝ ዳግም ማንሰራራት ችሏል። ከእንጦጦ ጀምሮ ያለው የቀበና ወንዝ ዳርቻም አልፎ ለመሄድ ከሚያስቸግር ብክለት ወጥቶ ለአካባቢው እንዲሁም ለከተማችን ተጨማሪ የቱሪስት ማዕከል ሆኗል። ይህ ደማቅ የታሪክ አሻራ ውጤታማነቱ የሚረጋገጠው በአግባቡ በመገልገል የከተማችንን ፀጋዎች ለመጪው ትውልድ ማሸጋገር ሲቻል በመሆኑ ከዳግም ብክለት መከላከልና መጠበቅ ከሁላችንም ይጠበቃል:: መልካም የስራ ሳምንት ይሁንልን! ይሁንላችሁ! በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት #aa_prosperity

እናመሰግናለን !! ያስቀመጥናቸውን የምርጫ መንትያ ግቦች ያሳካው ህዝባችን ነው! በ7ኛው ዙር ሃገራዊ ምርጫ ያሸነፈችው ኢትዮጵያ ናት ፤ ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ ያደረጉት ደግሞ ህዝቦቿ ናቸው። ውድ የከተማችን ነዋሪዎች ምርጫውን ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሃዊ፣ ነፃ ሆኖ በስኬትና በውጤት እንድናጠናቅቅ ስላደረጋችሁ እና የብልፅግና ፖሊሲና ስትራቴጂ ብሔራዊ ጥቅሞቻችን ያረጋግጣል ብላችሁ ፓርቲያችንን ብልፅግናን በአብላጫ ድምፅ ስለመረጣችሁ እናመሰግናለን። ሃገርን ማፅናት፣ ሰላምን ዘላቂ ማድረግ፣ ብሔራዊ ጥቅማችንን ማረጋገጥ የኢትዮጵያችን የመቻል ማሳያዎች ናቸው ። ለበርካታ የሚዲያ ዘመቻዎች፣ ከውጭም ከውስጥም ለነበሩ ጫናዎች ጆሮ ሳትሰጡ የኢትዮጵያን የመቻል አቅም ያረጋገጣችሁ የከተማችን ነዋሪዎችን በፓርቲያችንና በመንግስታችን ሥም እናመሰግናለን። ሌሊት ወጥታችሁ ከቴክኖሎጂ መስተጓጎል ጋር በተፈጠረው እንግልት ሳትሰላቹ፣ ቀኑን ሙሉ ደከመኝ ሳትሉ እስከሌሊት በፅናት በመሰለፍ የኢትዮጵያ ዴሞክራሲ እንዲረጋገጥ አድርጋችኋል። ልማታችን እንዲቀጥል፣ ሰላማችን እንዲረጋገጥ አድርጋችኋል። ፓርቲያችን ብልፅግናን ስትመርጡ ምንም ችግር የለም ብላችሁ ሳይሆን፣ ያልተመለሱ ጥያቄዎች በሂደት ይመለሳሉ፣ ያልጨረስናቸው ስራዎች በሂደት ያልቃሉ፣ የጎደለው ይሞላል ብላችሁ እምነት ሰጥታችሁ ነው። የሰጣችሁን አደራ ነውና እኛም በታማኝነትና በመሰጠት፣ በትጋትና በቁርጠኝነት፣ 24/7 በመስራት አዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ በቁርጠኝነት የምንሰራ መሆኑን ላረጋግጥላችሁ እፈልጋለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ! # ከንቲባ አዳነች አቤቤ