ar
Feedback
Prosperity Party A.A - ብልፅግና

Prosperity Party A.A - ብልፅግና

الذهاب إلى القناة على Telegram

የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Prosperity Party A.A - ብልፅግና

تُعد قناة Prosperity Party A.A - ብልፅግና (@prosperityaddis) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 13 172 مشتركاً، محتلاً المرتبة 4 082 في فئة السياسة والمرتبة 2 575 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 13 172 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 30 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -1 943، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -162، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 6.39‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 4.71‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 842 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 620 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 0.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 31 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة السياسة.

13 172
المشتركون
-16224 ساعات
-3427 أيام
-1 94330 أيام
أرشيف المشاركات
photo content

ነገን ታሳቢ ያደረገ አረንጓዴ ልማት፤ ለትውልድ የሚሸጋገር ሀገራዊ ቅርስ ነው! ችግኝ መትከል ከተፈጥሮ ጋር መልካም መስተጋብር በመፍጠር ትውልድ ተሻጋሪ ቅርስ መትከል ነው፡፡ የነገን ትውልድ ተስፋ ያለመልማል፣ የአዕዋፋትን እና የእንስሳትን ህይወትም ይታደጋል፡፡ ታላላቅ ወንዞቻችን እንዲሁም ሌሎች የገፀ ምድር እና የከርሰ ምድር የውሀ ሀብቶቻችንም ህልውናቸው ቀጣይነት የሚኖረው ለአረንጓዴ ልማት በምንሰጠው ትኩረት ልክ መሆኑን ልብ ማለት ይገባል፡፡ ዛሬ የምንተክለው ችግኝ የአሁኑን ትውልድ ፍላጎት ብቻ የሚያሟላ ብቻ ሳይሆን ለመጪው ትውልድ የሚተርፍ ውድ ቅርስ ነው። ከተፈጥሮ ጋር ያልተጣጣመ፣ ነገን ታሳቢ ያላደረገ ልማት በምንም መልኩ ዘላቂነት ሊኖረው አይችልም፡፡ በአየር ንብረት መዛባት ምክንያት የሚከሰቱ የድርቅ፣ የጎርፍ፣ የበረሀማነት መስፋፋት እና መሰል ትላልቅ አደጋዎች ሀገራትን በእጅጉ እየፈተኑ ይገኛሉ፡፡ ኢትዮጵያንም የአየር ንብረት መዛባት በተደጋጋሚ ዋጋ አስከፍሏታል፡፡ ነገን አሻግሮ የመመልከት የበጎ እሳቤ መገለጫ የሆነው አረንጓዴ አሻራ ተፈጥሯዊ አደጋዎችን ቀድመን የምንከላከልበት ቁልፍ መፍትሄ ነው፡፡ ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ ኢትዮጵያ እየተገበረችው የሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ የሀገር ፍቅርን ከአካባቢ ጥበቃ ጋር ያገናኘ ታላቅ ተግባር ነው። ይህ ንቅናቄ ሁሉንም ዜጋ የሚያሳትፍ፣ የጋራ ሀላፊነትን የሚያጎለብት እና ለትውልድ የሚተርፍ አሻራ የሚያስቀምጥ መልካም ተግባር ነው። ዛሬ የምንተክለው ችግኝ ከአፈር ጋር የሚቀላቀል ተራ ዘር አይደለም፤ የነገው ትውልድ ህልም፣ የሀገራችን አረንጓዴ ዕድገት እና የወደፊት ተስፋ መሰረት የሚጣልበት ዘላቂ ልማት ነው፡፡ የዛሬ ትውልድ ለነገው ትውልድ የሚያበረክተው ከሁሉ የላቀ ስጦታ ነገን ታሳቢ ያደረገ አረንጓዴ ልማት መሆኑን በመገንዘብ ርብርባችንን ልናጠናክር ይገባል፡፡ በብልፅግ ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት #aa_prosperity

የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ወቅት ላይ እንገኛለን። ከስምንት ቢሊዮን በላይ ችግኞች ለተከላ ዝግጁ በሆኑበት በዚህ ወቅት፣ አረንጓዴ ለሆነች ነገ፣ ሁላችንም ተስፋን እንትከል! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ወቅት ላይ እንገኛለን። ከስምንት ቢሊዮን በላይ ችግኞች ለተከላ ዝግጁ በሆኑበት በዚህ ወቅት፣ አረንጓዴ ለሆነች ነገ፣ ሁላችንም ተስፋን እንትከል! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) #aa_prosperity

photo content

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ ለህዝባችን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት፣ ለሀገራችን ማንሰራራት! የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የባህል፣ የቋንቋ፣ የሀይማኖት፣ የብሔር፣ የሀሳብ ልዩነቶቻቸውን ጌጥ አድርገው፣ በብዝሀነት ደምቀው የጋራ ሀገራቸውን እንዲገነቡ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አበርክቶው ላቅ ያለ ነው፡፡ በጎ ፈቃደኞች ለተቸገሩት አለኝታነታቸውን ሲያሳዩ በመካከላቸው ያለው የመተሳሰብ መንፈስ ስለሚዳብር በህዝባችን መካከል ያለው ማህበራዊ ትስስር ይበልጥ ይጠናከራል፡፡ በተለያዩ የሀገር ክፍሎች የሚከናወኑ ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች አንዱ የሌላውን ባህል እና አኗኗር እንዲያውቅ በማድረግ ህብር አብሮነትን ያጠብቃሉ፡፡ ይህም የአብሮነት እሴትን በማጠናከር ለሀገረ መንግስት ግንባታው ጭምር ትልቅ አቅም ይፈጥራል፡፡ ዜጎች በአካባቢያቸው በሚደረጉ የልማት ስራዎች ላይ በንቃት እንዲሳተፉ በማድረግ የባለቤትነት ስሜትንም ከፍ ያደርጋል። መንግስት ብቻውን ሊሸፍናቸው የማይችላቸውን የማህበራዊ አገልግሎት ክፍተቶች በበጎ ፈቃደኞች ሲሞሉ የህዝባችን አዳጊ የልማት ፍላጎቶች ምላሽ ያገኛሉ፤ ዕድገታችንም ይፋጠናል፡፡ በጎ ፈቃደኞች በጉልበታቸው፣ በእውቀታቸው እና በገንዘባቸው የሚያበረክቱት የማይተካ አስተዋፅዖ መንግስት በጀቱን ለሌሎች መሰረተ ልማቶች እንዲያውል ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። ተፈጥሯዊ ወይም ሰው ሰራሽ አደጋዎች ሲያጋጥሙ በጎ ፈቃደኞች የመጀመሪያ ምላሽ ሰጪ በመሆን የዜጎችን ህይወት እና ንብረት ይታደጋሉ። በጎ ፈቃደኞች በደም ልገሳ፣ በጤና ግንዛቤ እና ህመምተኞችን በመንከባከብ እንዲሁም በማከም የሀገርን የጤና ስርዓት ያጠናክራሉ። ለተቸገሩ ዜጎች የምግብ፣ የልብስ እና የመጠለያ ድጋፍ በማድረግ ብሩህ ተስፋን ይፈነጥቃሉ፤ አብሮ የማደግ ባህልንም ያዳብራሉ፡፡ ችግኝ መትከልን፣ ቆሻሻን ማስወገድን የመሳሰሉ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎችን በማከናወንም በጎ ፈቃደኞች የተፈጥሮን ስነ-ምህዳር ከጥፋት ይታደጋሉ። ወጣቶች በበጎ ፈቃድ ስራ ሲሳተፉ የስራ ባህልን፣ ዲሲፕሊንን እና የሃላፊነት ስሜትን ይገነባሉ፡፡ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ለወጣቶች ተግባራዊ ልምድን እና የስራ ክህሎትን ስለሚያጎናፅፍ ብቁ ዜጋ ለማፍራትም አጋዥ ነው፡፡ ለአረጋውያን፣ ለአካል ጉዳተኞች እና ለህጻናት በሚደረጉ የበጎ ፈቃድ ድጋፍ እና እንክብካቤዎች ማህበረሰቡ ውስጥ ፍትሀዊነት ይሰፍናል፡፡ በጎ ፈቃደኛ ባለሙያዎች በሙያቸው የድርሻቸውን ሲወጡ የዕውቀት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ይፋጠናል፡፡ ዜጎች ክብራቸው ተጠብቆላቸው፣ በእኩልነት እንዲኖሩም ለፍትህ እና ለሰብአዊ መብት የሚቆሙ በጎ ፈቃደኞች አወንታዊ አስተዋፅኦ ማበርከት የሚችሉበት ዕድል ሰፊ ነው። የቱሪስት መስህቦችን በማጽዳት እና በማስተዋወቅ የሀገርን የቱሪዝም ዘርፍ ማሳደግም አንዱ የበጎነት ተግባር ነው። በማስተማር አገልግሎት በመሰማራት፣ አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁሶችን በማሰባሰብ የሀገርን የትምህርት ሽፋን እና ጥራት ማሻሻልም ለጋራ ዕድገታችን ፅኑ መሰረት ይጥላል። ለሴቶች የክህሎት ስልጠና በመስጠት በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እና በሀገር ግንባታ ላይ እንዲሳተፉ ማገዝም ከበጎነት ተግባራቶች መካከል የሚጠቀስ ነው። በጎ ማድረግ የህሊና እርካታን ይፈጥራል፤ ይህም መልካም ስብዕና ያለው ዜጋ በመፍጠር ሀገርን ከሙስና እና ከሌሎች ብልሹ አሰራሮች ይታደጋል። ባህላዊ እሴቶችን እና ታሪክን በመንከባከብ በጎ ፈቃደኞች የሀገርን ማንነት ይጠብቃሉ። በዓለም አቀፍ በጎ ፈቃድ ስራዎች የሚሳተፉ ዜጎች ደግሞ የሀገርን መልካም ስም በማስተዋወቅ የህዝብ ለህዝብ ዲፕሎማሲን ያጠናክራሉ። በክረምቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በከተማችን 18 አካባቢ ዋና ዋና አገልግሎቶች ተለይተው ተቋማዊ በሆነ መልኩ እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ዘርፈ ብዙ ፋይዳ በአግባቡ በመረዳት በእውቀታችን፣ በጉልበታችን እንዲሁም በገንዘባችን የድርሻችንን በማበርከት የወገን አለኝታነታችንን በተግባር ማረጋገጥ ከሁላችንም ይጠበቃል፡፡ በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት #aa_prosperity

photo content

ተስፋን እንትከል! ፈጣን ዕድገታችንን እናስቀጥል! 800 ሚሊዮን ችግኞች በአንድ ጀምበር ለመትከል 3 ቀናት ብቻ ቀርተዋል! የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ከዘላቂ የልማት ግቦቻችን ጋር የተጣጣመ፣ የአሁኑን ትውልድ ብቻም ሳይሆን የመጪውን ትውልድ ፍትሀዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ የሚሊዮኖች ታሪካዊ አሻራ ነው፡፡ የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ አሳሳቢነቱ በእጅጉ እየጨመረ በሚገኝበት በዚህ ዘመን ኢትዮጵያ እየወሰደችው የሚገኘው ህዝብን በነቂስ የሚያሳትፍ የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ሌሎችም አርአያ የሚያደርጉት አዋጭ ስትራቴጂካዊ ስልት ነው፡፡ ተፈጥሮን በማራቆት የሚመዘገብ የሀገራት እድገት በምንም መልኩ ዘላቂነት ይኖረዋል ተብሎ አይታሰብም፡፡ ቀጣይነት ያለው እድገት ተፈጥሮን በማራቆት ሳይሆን ተፈጥሮን በአግባቡ በመንከባከብ የሚረጋገጥ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የጀመረችው ተፈጥሮን የመንከባከብ አዳጊ ባህል እያደር የሚፈኩ ውጤቶች እንደሚኖሩት ይጠበቃል፡፡ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር መተግበር በጀመረባቸው የመጀመሪያዎቹ ዓመታት የተተከሉ ለምግብነት የሚያገለግሉ ችግኞች ከጥላነት ባሻገር ለምግብነት ደርሰዋል፡፡ ባለፉት 7 ዓመታት የተተከሉት 48 ቢሊዮን አካባቢ ችግኞች ከደለል መሞላት የታደጓቸው ግድቦች፣ የተከላከሉት የአፈር መሸርሸር እንዲሁም የታደጓቸው እንስሳት፣ አዕዋፋት እና እፅዋት በዋጋ የሚተመን አይደለም፡፡ ከሶስት ቀናት በኋላ ሀምሌ 27/2018 ዓ/ም በሚካሄደው በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር አሻራችንን በማሳረፍ ሀገራችን የምትፅፈው ደማቅ ታሪክ ተጋሪ ለመሆን እንዘጋጅ፡፡ በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት #aa_prosperity

photo content

ለምድራችን በረከት፣ ለዘላቂ ዕድገታችን አስተማማኝ መሰረት! አረንጓዴ አሻራ ለትውልዱ ተስፋን የምንተክልበት ታሪካዊ ሁነት! ፓርቲያችን ያስቀመጠው በሀገራዊ አቅም ላይ መሰረትን ያደረገ የዘላቂ ዕድገት አቅጣጫ እውን እንዲሆን የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ፋይዳው ብዙ ነው፡፡ የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም የሀገራችንን የደን ሽፋን በከፍተኛ ደረጃ በመጨመር፣ የደን መመናመንን በመግታት ለመጪው ትውልድ የለመለመች ኢትዮጵያን ለማሻገር ወሳኝ ነው፡፡ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን አሉታዊ ተፅዕኖ ለመቀነስ ቁልፍ ሚና የሚጫወተው የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም የአፈር መሸርሸርን በመከላከል ለምርታማነት ጉልህ ሚና ይጫወታል፡፡ የከርሰ ምድር ውሃ እንዲሞላ በማድረግ የውሃ ምንጮች እንዳይደርቁም ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረክታል፡፡ አረንጓዴ አሻራ የተለያዩ እንስሳትና እፅዋት እንዲሁም አዕዋፋት እንዳይጠፉና ወደ ሌሎች ሀገራትም እንዳይሰደዱ ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ለብዝሀ ህይወት መጠበቅም ዋስትና ይሰጣል፡፡ የዝናብ ስርጭትን በማስተካከል ድርቅና እሱን ተከትሎ የሚመጣውን የምርታማነት ችግር ለማስወገድም አረንጓዴ አሻራ ሚናው ላቅ ያለ ነው፡፡ የደን ውጤቶች የበርካታ ሀገራት ኢንዱስትሪዎችም የጀርባ አጥንት መሆናቸው ይታወቃል፡፡ ኢትዮጵያም የአየር ንብረቷን ከማረጋገጥ ባሻገር ለተለያዩ የፈርኒቸር ምርቶች አስተማማኝ ግብዓት እንዲኖራት ስለሚያስችል ኢንዱስትሪውን ይበልጥ ያነቃቃል፡፡ የክቡር ጠ/ሚ ዐብይ አህመድ ኢኒሸቲቭ የሆነው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብራችን ለምግብነት የሚያገለግሉ የተለያዩ አትክልትና ፍራፍሬዎች እንዲተከሉ በማድረግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለሚደረገው ርብርብም ተጨማሪ አቅም ፈጥሯል፡፡ ሀገራችን በተለይም በቀንድ ከብት ከቀዳሚዎቹ ተርታ የምትሰለፍ በመሆኗ የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራማችን በእንስሳት መኖ ላይ የሚያጋጥመውን ሰፋ ያለ ችግር ለማቃለልም የማይተካ ሚና ያበረክታል፡፡ ኢትዮጵያ ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመሳሰሉ ግድቦችን እየገነባች የታዳሽ ሀይል አቅርቦቷን በእጅጉ እያስፋፋች በመሆኑ ታላላቅ ግድቦቻችን የተመጣጠነ ውሀ እንዲኖራቸው በማድረጉ በኩልም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር አስተማማኝ ዋስትና ነው፡፡ ለመዲናችን አዲስ አበበባ አንፀባራቂ ዕድገት ጉልህ ሚና እያበረከተ ለሚገኘው የቱሪዝን ዘርፍም መርሀ ግብሩ ትልቅ አቅም መፍጠሩን መገንዘብ ይቻላል፡፡ ሀገር አቀፍ የህዝብ ተሳትፎን በማሳደግ ህዝባችን በወንድማማችነት እና በእህትማማችነት ስሜት ለጋራ ልማት በአብሮነት እንዲነሳ በማድረግ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ማህበራዊ መስተጋብርን ከፍ አድርጓል፡፡ ተዘርዝረው ከማያልቁ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳዎቹ ባሻገር በዲፕሎማሲው መስክም የኢትዮጵያን ተፅዕኖ ፈጣሪነት አሳድጓል፡፡ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት መዛባት መኖሩን በማስረዳት መተባበር እንደሚገባ ከመጠየቅ ወጥታ አንገቷን ቀና አድርጋ መሞገት የምትችልበትን ተጨባጭ ድል አስመዝግባለች፡፡ ሚሊዮኖችን በማሳተፍ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን መትከል የቻለችው ኢትዮጵያ ለምድራችን ልምላሜ፣ ለመጪው ትውልድ ብሩህ ተስፋ በታሪክ ሲዘከር የሚኖር አሻራዋን እያሳረፈች ትገኛለች፡፡ በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት #aa_prosperity

photo content

ለሀገራችን ልምላሜ! ለከተማችን ውበት! አረንጓዴ አሻራ የአብሮነታችን ድምቀት! በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም 4 ቀናት ብቻ ቀሩት! ጎረቤት ሀገራትን እና ሌሎችንም የሚያረሰርሱ ድንበር ተሻጋሪ ወንዞች እያሏት የተጠማች፣ ለም አፈር እያላት ተመፅዋች፣ ሆና የኖረችውን የሀገራችንን ታሪካዊ ስብራቶች እየጠገኑ ከሚገኙ ውጤታማ እርምጃዎች አንዱ ነው፤ አረንጓዴ አሻራ፡፡ የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ(ዶ/ር) የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሸቲቭ መተግበር ከጀመረበት 2011 ዓ.ም ጀምሮ የህዝባችን ችግኝ የመትከል ብቻም ሳይሆን ችግኞችን የመንከባከብ ባህል በእጅጉ ተሻሽሏል፡፡ በተጨባጭም የሀገራችን የደን ሀብት ከመራቆት ወደ ማንሰራራት ተሸጋግሯል፡፡ ለሀገራዊ ዓላማ በአብሮነት መሰባሰቢያ፣ ወንድማማችነትን እና እህትማማችነትን ማጥበቂያ፣ የጋራ ብሩህ ነገን መገንቢያ የሆነው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የህዝባችንን አብሮነት አጠናክሯል፡፡ የሀገርን ጉዳይ ከግል እና ከቡድን ፍላጎቶች በማስቀደም ብዝሀ ማንነቶች፣ ብዝሀ ሀሳቦች በአንድነት የሚስተጋቡበት በመሆኑ ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታም ምቹ መደላድል የሚፈጥር ነው፡፡ የምንተክላት እያንዳንዷ ችግኝ የነገ ልምላሜያችን፣ የነገ ጥላችን እንዲሁም የነገ ውበታችን ናት፡፡ ተፍጥሮ በብዙ መልኩ አሟልታ ሰጥታናለች፡፡ በአግባቡ መያዝ ስላልቻልን ድርቅን ለመሳሰሉ ተፈጥሯዊ አደጋዎች በእጅጉ ተጋልጠን ቆይተናል፡፡ አረንጓዴ አሻራ ኢትዮጵያን ከነበረችበት ከፍተኛ የመራቆት ደረጃ በማውጣት ለዓለም የአየር ንብረት መጠበቅ ተምሳሌት ያደረገ ተግባራዊ እርምጃ ነው፡፡ በጥቂት ዓመታት ውስጥ 48 ቢሊዮን ችግኞችን መትከል እራሱን የቻለ የገዘፈ ታሪክ ነው፤ ከ4 ቀናት በኋላ የምናካሂደው በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ደግሞ አይበገሬነታችንን ጭምር ለዓለም የምናሳይበት ታሪካዊ ሁነት ነው፡፡ በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት #aa_prosperity

photo content
+7

የአንድ እቅድ አንድ ሪፖርት ስርአት በመዘርጋት እና በማጠናከር የፓርቲውን አሰራር ዲጂታላይዝ በማድረግና ዲጂታል ብልፅግና ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ስራዎች ተከናውነዋል ።አምባሳደር ሀሰን አብዱልቃድር የብልፅግና ፓርቲ የስትራቴጂ ሥራ አመራርና የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ የ2018 ዓመታዊ የእቅድ አፈፃፀም እና የ2019 እቅድ ላይ የተዘጋጀ መድረክ በሐረር ከተማ እያካሄደ ይገኛል ። በብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽሕፈት ቤት በሚኒስትር ማዕረግ የስትራቴጂ ሥራ አመራርና የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ ኃላፊ አምባሳደር ሀሰን አብዱልቃድር በመክፈቻ መድረኩ ላይ እንደተናገሩት በተለይ የ2018 አፈጻጸም ለመገምገም እና በአመቱ የነበሩትን ጥንካሬዎች እንዲሁም ክፍተቶች በመሙላት ለ2019 የሚደረግ የዝግጅት የውይይት መድረክ እንደሚሆን አንስተዋል ። ምንም እንኳን ዘርፉ በጣም ጥቂት ዓመት ዕድሜ ያለው ቢሆንም በአንድ ዓመት ውስጥ ዘርፈ ብዙ ስራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል። በ2018 በጀት ዓመት በተለይም ከአንድ ዕቅድ፣ ከአንድ ሪፖርት እና የምዘና ስርዓቱን ከማዘመን አንጻር የተጀመሩ አበረታች ስራዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል ። በዚህ የጋራ መድረክ አንዱ ከአንዱ የሚማማርበት፣ ልምድና ተሞክሮ የሚለዋወጥበት፣ የተሻለ አፈጻጸም ያላቸው ክልሎች ተሞክሯቸውን የሚያካፍሉበት መድረክ ስለሆነ የተሻለ ስራ አጠናክሮ ለመቀጠል ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው አስረድተዋል። ይህንን የቴክኖሎጂ ማዘመን ስራ እንዲሁም አጠቃላይ የፓርቲ ስራዎችን ወደ ሲስተም እና ወደ ዲጂታል ምዝገባ ለማዛወር በሚደረገው ሂደት ውስጥ በዚህ ዓመት የተሰሩ ስራዎች እንደሚገመገም እና ቀጣይ አቅጣጫዎችን የሚቀመጥ መሆኑን አብራርተዋል። በተጨማሪም ይህ መድረክ በነገው ዕለት በተለይ ከአንድ ዕቅድ፣ ከአንድ ሪፖርት እና ከዲጂታል ምዝገባ ጋር ተያይዞ ልምድና ብቃት ባላቸው የስራ ኃላፊዎች ስልጠና እንደሚኖር ጠቁመዋል ። የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ በበኩላቸው ይህ መድረክ መዘጋጀቱ በዋናነት ኢትዮጵያ ለማየት ለማወቅ እና አብሮነትን ለማጠናከር ያለመ መሆኑን ጠቁመዋል። ስራዎች ከመገምገም ባሻገር ሌሎች ለተያዙ የውህደትና ብዝሃነት በተለይ የነበሩትን የፖለቲካ ስብራቶች ከመጠገን አንጻር እንደዚህ ዓይነት መድረኮች በየቦታቸው መዘጋጀት አብሮነታችንን፣ ወንድማማችነታችንን እና እህትማማችነታችንን ወደ ተሻለ ደረጃ እንደሚያሻግር አክለዋል። ፖለቲካችንን ወደ ስታንዳርድ የማምጣት ስራ ለመስራት ፓርቲዉ ዝግጅቶች አድርጎ ወደ ትግበራ መግባቱን አንስተው ይህንን በጥልቀት በመወያየት፣ ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የተሻለ፣ ከፍ ወደ አለ ደረጃ የሚያሻግር ሰፊ ውይይት እንደሚደረግ ጠቁመዋል ። በውይይቱ መድረክም የሁሉም ክልሎች አመታዊ አፈፃፀም ሪፖርተር እየቀረበ ሰፊ ውይይት እየተደረገ ይገኛል ። #aa_prosperity

photo content
+6

የግብርና ትራንስፎርሜሽን በኢትዮጵያ አይቀሬ መሆኑን የባሌ አርሶ አደሮች ስኬት በግልጽ ይመሰክራል- ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) የብልፅግና ፓርቲ ህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ አመራሮች በባሌ ዞን ሲናና ወረዳ በክላስተር የለማ የስንዴ ማሳን የጎበኙ ሲሆን፣ የዘርፉ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በጉብኝቱ ወቅት "የግብርና ትራንስፎርሜሽን በኢትዮጵያ አይቀሬ መሆኑን የባሌ አርሶ አደሮች ስኬት በግልጽ ይመሰክራል" ብለዋል። ይህ የባሌ ዞን የስንዴ ልማት ስኬት ብልፅግና ፓርቲ ለግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ ለገጠር መዋቅራዊ ሽግግር፣ ለሜካናይዜሽን እና ለኢንዱስትሪያላይዜሽን የሰጠውን ከፍተኛ ትኩረትና የፖሊሲ ፍሬ የሚያሳይ ትልቅ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትርጉም ያለው ክስተት ነው። መንግሥት የግብርና መሣሪያዎች ከቀረጥ ነፃ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ያደረገው ውሳኔ በቀላሉ የሚታይ የግብር ማሻሻያ ሳይሆን፣ የግብርናውን ክፍለ-ኢኮኖሚ ከመሰረቱ ለመቀየር የተወሰደ ስትራቴጂካዊ የፖሊሲ እርምጃ ነው። በሲናና ወረዳ የአስተራረስ ዘዴው ከባህላዊ ወደ ዘመናዊ ተቀይሮ 74% በላይ በሜካናይዜሽን መሸፈኑ፣ የፓርቲው የልማት ፖሊሲዎች ከወረቀት ወጥተው የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት በተግባር ማሳደጋቸውን የሚያረጋግጥ ነው። የግብርና ትራንስፎርሜሽን የመጨረሻ ግብ የምርት መጠን መጨመር ብቻ ሳይሆን የአርሶ አደሩን የአስተራረስ ባህልና የማህበራዊ-ኢኮኖሚ ግንኙነት ማዘመን ነው። አርሶ አደሮች በክላስተር ተደራጅተው በጋራ የሚያርሱበት፣ የሚወቅጡበት እና የሚሰበስቡበት አዲስ የስራ ባህል መፍጠራቸው የተበታተነውን ባህላዊ የገጠር ኢኮኖሚ ወደ ተደራጀና ዘመናዊ የምርት ኃይል ቀይሮታል። በወረዳው የሚገኙ አርሶ አደሮች በራሳቸው አቅም ፋብሪካ ለመመሥረት በዝግጅት ላይ መሆናቸው፣ የብልፅግና ፓርቲን የኢንዱስትሪ ሽግግር ራዕይ መሬት ያወረደ ትልቅ ማሳያ ነው። አርሶ አደሩ በጥሬ ምርት አቅራቢነት ብቻ ሳይወሰን የምርት እሴት ጨማሪ እና ባለፋብሪካ የሚሆንበት መንገድ መከፈቱ፣ የገጠር ካፒታል ወደ ኢንዱስትሪ መዋዕለ-ነዋይ የመሸጋገሩ ትልቅ መዋቅራዊ እርምጃ ነው። ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ እንደገለጹት፣ ይህንን የመሬት ላይ ስኬት ወደ ሙሉ ሀገራዊ ብልፅግና ለመቀየር ከአርሶ አደሩ ነባራዊ ሁኔታ ጋር የተጣጣመ ውጤታማ የኮሙኒኬሽን መንገድ መጠቀም ወሳኝ ነው። የህዝቡን ንቃተ-ህሊና የሚያሳድግ እና የልማት ባለቤትነቱን የሚያረጋግጥ የመረጃ ልውውጥ ማድረግ የትራንስፎርሜሽኑን ዘላቂነት ያረጋግጣል። በአጠቃላይ፣ "ባሌ ኢትዮጵያን የመመገብ የተፈጥሮ ፀጋ ያለው አካባቢ ነው" የሚለው እውነት አሁን በቴክኖሎጂ፣ በፖሊሲ ድጋፍ እና በህዝብ ተሳትፎ ታግዞ የሀገሪቱን የምግብ ሉዓላዊነት የሚያረጋግጥ ትልቅ ኃይል ሆኗል። ይህም የብልፅግና ፓርቲ የኢኮኖሚ ፍልስፍና የሀገሪቱን የነገ ተስፋ በራስ አቅም የመገንባት አቅሙን በተግባር ያሳየበት ማረጋገጫ ነው።

photo content

800 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ደማቅ ታሪክ ለመፃፍ 5 ቀናት ብቻ ይቀሩናል! በአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ባለፉት የለውጥ ዓመታት 48 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል የማይቻል የሚመስልን ታምር በተጨባጭ ማሳካት ተችሏል፡፡ በድርቅ እና በረሀብ የምትታወቀው ኢትዮጵያ አሁን ላይ የልምላሜ ቀንዲል ወደመሆን እየተሸጋገረች ትገኛለች፡፡ በየዓመቱ የተተከሉ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞች ‹‹በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ›› እንደሚባለው ዘርፈ ብዙ ጥቅሞችን እየሰጡ ይገኛሉ፡፡ የአየር ንብረትን ከመጠበቅ ባሻገር የቡና ኤክስፖርታችን በእጅጉ እንዲጨምር፣ የሌሎች ፍራፍሬዎች ምርታማነትም ከእጥፍ በላይ እንዲያድግ፣ በአጠቃላይ ለምግብ ሉዓላዊነት ለሚደረገው ርብርብ አረንጓዴ አሻራ የጎላ ሚና ማበርከት ጀምሯል፡፡ መርሀ ግብሩ የአፈር መሸርሸርን ቀንሷል፤ በመጥፋት አፋፍ ላይ የነበሩንት እና ጠፍተው የነበሩትን ወንዞች እና ሀይቆች ህልውና መታደጉንም የሀሮሚያን ሀይቅ መጥቀስ ይቻላል፡፡ የመዲናችን አዲስ አበባ የደን ሽፋን ከ2 ነጥብ 8 ወደ 24 በመቶ ከፍ ያለውም በዚሁ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ነው፡፡ በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ደማቅ ታሪክ ለመፃፍ እንዘጋጅ! በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት #aa_prosperity

photo content
+8

photo content
+9

የብልፅግና ፓርቲ ህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ አመራሮች አረንጓዴ አሻራቸውን በመዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ቅጥር ቅቢ ውስጥ አኑረዋል። የዘርፉ ከፍተኛ አመራሮች በዞኑ የተለያዩ የልማት ስራዎችንና የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን እየጎበኙ ይገኛሉ። በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ተክለን ሌላ አዲስ ታሪክ ለመፃፍ 5 ቀናት ብቻ ቀርተዋል። #aa_prosperity