en
Feedback
4 612
Subscribers
-324 hours
-147 days
-3730 days
Posts Archive
EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
" በዚህ ኑሮ ውድነት ዘይት ለማይገዛ የጡረታ ገንዘብ ለሀገር የለፉ ባለውለታዎች በዚህ ልክ ባይገላቱ ጥሩ ነው " - ጡረተኞች ‎ ‎ዛሬ በሀዋሳ ከተማ በተለያዩ ባንክ ቤቶች በር ላይ ከወትሮው በተለየ
+2
" በዚህ ኑሮ ውድነት ዘይት ለማይገዛ የጡረታ ገንዘብ ለሀገር የለፉ ባለውለታዎች በዚህ ልክ ባይገላቱ ጥሩ ነው " - ጡረተኞች ‎ ‎ዛሬ በሀዋሳ ከተማ በተለያዩ ባንክ ቤቶች በር ላይ ከወትሮው በተለየ መልኩ በርከት ያለ ቁጥር ያላቸው አረጋዊያን እናቶችና አባቶች ተሰልፈው የተመለከተው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ሀዋሳ ቤተሰብ ጉዳዩን ለማጣራት ሞክሯል። ‎ ተዘዋውረን በተመለከትናቸው፣ የተለያዩ የባንክ ቅርንጫፎች በርከት ያሉ ጡረተኞች ተሰልፈውና ገሚሱም ተቀምጠው ወረፋ በመጠባበቅ ላይ የነበሩ ሲሆን የሰልፉን ምክንያትና ስላለው ሁኔታ ቲክቫህ ኢትዮጵያ አነጋግሯቸዋል። ‎ ‎ጡረተኞች እንደሚሉት ከዚህ ቀደም በየዓመቱ የጡረታ ውል ማደስና ቆጠራ ከሐምሌ ወር ጀምሮ እየተከናወነ ጎን ለጎን ክፍያው ይፈፀም እንደነበር በመግለፅ ዘንድሮ ባንኮች " ሳታሳድሱ የጡረታ ገንዘብ አይከፈላችሁም " በማለታቸው ሰልፍና ወረፋ መብዛቱን ገልፀዋል። ‎ ‎የኢትዮጵያ ማህበራዊ ዋስትና ኤጄንሲ አማካኝነት በባንኮች በኩል ለጡረተኞች በተላከ የSMS አጭር የፅሁፍ መልዕክት የጡረታ መታወቂያ ዕድሳት ከሐምሌ 1/2018 ዓ/ም እስከ መስከረም 30/2019 ዓ/ም እንደሚከናወን የተገለፀ ቢሆንም ባንኮች " ካላሳደሳችሁ ክፍያ አይፈፀምም " በሚል አገልግሎት ሊሰጧቸው አለመፈለጋቸውን ጡረተኞችና የጡረታ ባለመብቶች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል። ‎ ‎ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ አንድ የቀድሞ ጦር ሠራዊት አባልና የመንግስት እርሻ ልማት ሰራተኛ " በዚህ ኑሮ ውድነት ዘይት ለማይገዛ የጡረታ ገንዘብ ለሀገር የለፉ ባለውለታዎች በዚህ ልክ ባይንገላቱ ጥሩ ነበር " ያሉ ሲሆን " አስቀድሞውኑ በተላከው አጭር የፅሁፍ መልዕክት ቀን በመገደብ አገልግሎቱ እንደ ቀድሞ አለመሆኑና ጡረተኞች መታወቂያቸውን ካላሳደሱ ገንዘብ እንደማይከፈላቸው ቢገለፅ ሰልፍና ወረፋው በዚህ ልክ አይሆንም ነበር " ሲሉ ተናግረዋል። ‎ ‎" በአንዳንድ የባንክ ሠራተኞች ያለው መስተንግዶ ጡረታ መብት ሳይሆን ምፅዋትና ድጎማ ይመስላል፤ ለነዚህ የሀገር ባለውለታዎች ክብር በማይመጥን ሁኔታ ነው የሚስተናገዱት " ያሉ ሌላ አስተያየት ሰጪ " አሁን ላይ በስራ ላይ ያሉ ወጣቶችና ጎልማሶች ይህ ሕይወት ነገ የነሱም እንደሆነ ተረድተው እነዚህን አቅም የሌላቸውን አረጋዊያን፣ አካል ጉዳተኞችን፣ አልፎም ሕመምተኞች መንከባከብ እና ማገዝ ሲሆን ሲሆን ማመስገን ያስፈልጋል " ብለዋል። ‎ ‎ኤጀንሲው ምን ምላሽ ሰጠ ? ‎ ‎ቲክቫህ ኢትዮጵያ በመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር የደቡብ ሪጅን ኃላፊ አቶ ተሾመ ባብሳ ስለ ጉዳዩ ጠይቋቸዋል። " እስከ ከሐምሌ 1/2018 ዓ/ም ጀምሮ እስከ መስከረም 30/2019 ዓ/ም የተባለው አጠቃላይ የማሳደሻ ጊዜ ነው " ያሉ ሲሆን " የጡረታ ባለመብቶች ግን እስከ ሐምሌ 30/2018 ዓ/ም ብቻ አሳድሰው እንዲጨርሱ ማስታወቂያ አስቀድሞ ተለጥፏል " ሲሉ ገልፀዋል። ‎ " ‎እስከ ሐምሌ 30/2018 ዓ/ም ክፍያ አይከለከልም " ያሉት አቶ ተሾመ " ከሐምሌ 30 በኋላም ባንኮች ክፍያ መከልከል የሚችሉት ከኤጀንሲው ያላሳደሱ ሰዎች ክፍያ እንዲቆም የዕገዳ ደብዳቤ ሲፃፍ ነው " ብለዋል። ‎ ‎በአጭር የፅሑፍ መልዕክት ስለተላለፈው የእስከ መስከረም 30/2019 ዓ/ም ዕድሳት መልዕክት የተጠየቁት አቶ ተሾመ " ባንክ የሚከተለው የራሱን አካሄድ ነው እኛ የምንከተለው የራሳችንን ነው "ብለው በኛ በኩል ጡረተኞችን ለማገዝ ሲባል ከሐምሌ 1-3 በየባንክ ቅርጫፉ የኤጀንሲውን ባለሙያዎች በመላክ ለማሳደስ ባለሙያ መድበናል ሲሉ ተናግረዋል። ‎ ‎ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰልፎቹን ካስተዋለባቸው ባንኮች ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጆች በጉዳዩ ላይ ምላሽና ማብራሪያ ለማግኘት ያደረገው ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም ለሰልፉና ወረፋው ግን ሁለቱም አካላት የተናበበና ግልፅ መልዕክት ለጡረታ ባለመብቶች ባለማስተላለፋቸው መሆኑ አስተውሏል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሃምሌ 2 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
የቀድሞዉ የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላሕ ዓሊ ኻሜኒ ተቀበሩ። አሜሪካ እና እስራኤል ባለፈዉ የካቲት ማብቂያ ላይ የገደሏቸዉ የኢራን የፖለቲካና የኃይማኖት መሪ አያቶላሕ ዓሊ ኻሜኒ ዛሬ ተቀበሩ። እስራኤ
+1
የቀድሞዉ የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላሕ ዓሊ ኻሜኒ ተቀበሩ። አሜሪካ እና እስራኤል ባለፈዉ የካቲት ማብቂያ ላይ የገደሏቸዉ የኢራን የፖለቲካና የኃይማኖት መሪ አያቶላሕ ዓሊ ኻሜኒ ዛሬ ተቀበሩ። እስራኤልና አሜሪካ በኢራን ላይ ጦርነት በከፈቱበት ዕለት የካቲት 28 ቀን 2026 ከኻሜኒ ሌላ ሴት ልጃቸዉን፣ የልጅ ልጃቸውን ፣ አማቻቸውንና 11 ባለሥልጣኖቻቸውን ገድለዋል። ባለቤታቸውም ክፉኛ ቆስለዉ ኋላ ሞተዋል። የኻሜኒ ሥልጣን የያዙት ያሁኑ የኢራን ጠቅላይ መሪ ሞጅታባ ኻሜኒ የዚያን ቀን ቆስለዋል። ሞጅታባሕ ጠቅላይ መሪነቱን ሥልጣን ቢይዙም እስከ ዛሬ ድረስ ለሕዝብ እይታ አልቀረቡም።  ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ለአባታቸው በተደረገው የሽኝት ሥርዓትም ሆነ በዛሬው የቀብር ሥርዓት ላይ አልተገኙም። ኢራንን ከ30 ዓመታት በላይ የመሩት ዓሊ ኻሜኒ ዛሬ የተቀበሩት በሐገሪቱ ሰሜን-ምሥራቅ ቅዱስ የቀብር ሥፍራ ማሻሐ,ድ ዉስጥ ነዉ። ማሽሐድ የኻሚኔይ የትዉልድ ሥፍራም ናት። የኻምኔይ አስከሬን ወደ ቀብሩ ስፍራ ከመወሰዱ ከሰዓታት በፊት የአሜሪካ ጦር ርዕሠ-ከተማ ቴሕራንን ከማሻሐድ ከተማ ጋር የሚያገኛኘውን የባቡር መስመር ጨምሮ የተለያዩ የኢራን የመሠረተ-ልማት አውታሮችን አውድሟል። ይሁንና በቀብር ሥርዓቱ ላይ ለመገኘት በመቶ ሺሕ የሚቆጠር የኢራን ሕዝብ የማሻሐድ ከተማን አጥለቅልቋት ነዉ የዋለዉ። ሕዝቡ የብቀላ ጥሪ ምልክት የሆነውን ቀይ አርማ እያዉለበለበ እስከ ቀብሩ ሥፍራ ድረስ ተጉዟል። መረጃው የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው። ሃምሌ 2 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሻምፒዮን ሆነ። በ2018 የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍፃሜ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርስቲ ሲዳማ ቡናን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል። ለወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርስቲ የድል ግቦች
+7
ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሻምፒዮን ሆነ። በ2018 የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍፃሜ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርስቲ ሲዳማ ቡናን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል። ለወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርስቲ የድል ግቦችን ጋናዊው አጥቂ ኮንኮኒ ሀፊዝ እና በየነ ባንጃ አስቆጥሯል። ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርስቲ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ መሆን ችሏል። ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርስቲ ቀጣይ አመት ኢትዮጵያን ወክሎ በ አፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ  የሚሳተፍ ይሆናል። ቲክቫህ ስፖርት ሃምሌ 2 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethsport 

EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ከኡጋንዳ የተቀነባበረ የበሬ ሥጋ ወደ ኢትዮጵያ እንዲገባ የተሰጠ ፈቃድም ሆነ የተደረገ ስምምነት የሌለ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። "ኡጋንዳ በንግድ ስምምነት የታገዘ የተቀነባበረ የበሬ ሥጋ
+1
ከኡጋንዳ የተቀነባበረ የበሬ ሥጋ ወደ ኢትዮጵያ እንዲገባ የተሰጠ ፈቃድም ሆነ የተደረገ ስምምነት የሌለ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። "ኡጋንዳ በንግድ ስምምነት የታገዘ የተቀነባበረ የበሬ ሥጋ ምርቷን ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ መላክ ጀምራለች" በሚል በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃንና ማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሰራጨ ያለውን መረጃ አስመልክቶ የግብርና ሚኒስቴር ማብራሪያ ሰጥቷል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በኡጋንዳ በኩል ለተባለው ጉዳይ የተሰጠ ምንም ዓይነት የገቢ ንግድ ፈቃድም ሆነ የተደረገ የሁለትዮሽ ስምምነት አለመኖሩን በይፋ አስታውቋል። በግብርና ሚኒስቴር የእንስሳት እና አሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) ጉዳዩን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ፣ ይህ መረጃ በምን መንገድ ሾልኮ ሊወጣ እንደቻለ በውል እንደማይታወቅና ሁኔታው ለዘርፉ ትልቅ ስጋት (ሪስክ) በመሆኑ በጥብቅ ሊመረመርና ሊጣራ የሚገባው ጉዳይ መሆኑን አሳስበዋል። " በእኔ በኩል ምንም የተሰጠ ፍቃድ የለም። እንደ ብራዚል የመግባቢያ ስምምነት ሁሉ የለም በኡጋንዳ ጉዳይ " ብለዋል። ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም፣ " ምናልባት  'ስማግል አድርገው' /በህገወጥ መንገድ/ ይሁን ሌላ በዚህ በግብርና ባለሥልጣን በግብርና ሚኒስቴርም የተፈቀደ እንዲገባ የተደረገ ነገር የለም። ሌሎች አማራጮች ካሉ ማየትና ማጣራት ነው " ሲሉ ገልጸዋል። ዶ/ር ፍቅሩ የአገሪቱን አጠቃላይ የንግድ አቅጣጫና የነጻ ገበያ መርህን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ፣ አፍሪካ አህጉራዊ የነጻ ገበያ ቀጠናን እየገነባች ባለችበት በአሁኑ ወቅት ማንኛውም አምራች ምርቱን እንዳይሸጥና እንዳይነግድ መከልከል እንደማይቻል አስገንዝበዋል። " እኔ ብቻ ልሽጥ " የሚል አካሄድ ከነጻ ገበያ መርህ ጋር እንደማይሄድ የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታው፣ ኢትዮጵያ ማድረግ ያለባት በተቻለ መጠን የአገር ውስጥ ምርት እንዲጨምር ማድረግ፣ የምርቱን ጥራት ማሻሻል እና የአገር ውስጥ አምራቾችን ተወዳዳሪነት ማሳደግ ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሆነ ገልጸዋል። በዚህም መሰረት በገበያ ውስጥ ጥራቱን የጠበቀ ምርት ያመረተ ተወዳዳሪ ሆኖ የሚሸጥበት፣ ሸማቹም የፈለገውን የሚገዛበት አሰራር እንደሚኖር አብራርተዋል። በሌላ በኩል፥ ዶ/ር ፍቅሩ ከብራዚል ጋር ስላለው የንግድ ግንኙነት የተፈጠረውን የተሳሳተ ግንዛቤ ለመቅረፍ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፣ ከብራዚል ጋር የተደረገው ስምምነት ለሥጋ ምርት ሳይሆን ለአገር ውስጥ የዶሮ እርባታ ዘርፍ ማሻሻያ የሚውል መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም መሰረት ከአገር ውጭ እየገባ ያለው ምርት ለዝርያ ማሻሻያ የሚሆኑ ወላጅ ጫጩቶችን ለማስገኘት የሚረዳ የለማ እንቁላል (የፅንስ ሽል) እንጂ ለምግብነት የሚውል እንቁላል ወይም ሥጋ አለመሆኑን አስገንዝበዋል። ይህ አሰራር በአገር ውስጥ ሚታየውን የጫጩት ፍላጎት ክፍተት ለመሙላትና የአገር ውስጥ ምርታማነትን በዘላቂነት ለማሳደግ ታስቦ እየተሰራበት ያለ ስራ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በአሁኑ ወቅት የለማ እንቁላል ወደ አገር ውስጥ የማስገባቱ ሂደት በከፍተኛ ሁኔታ የተጀመረ ባይሆንም፣ በአገር ውስጥ የጫጩት እጥረት በሚያጋጥምበት ጊዜ ገብቶ ተፈልፍሎ ለገበያ እንዲቀርብ የሚደረግበት አሰራር መዘርጋቱን አብራርተዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሃምሌ 2 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ሶስት ተጠርጣሪዎች ተይዘዋል። ... ጉዳዩን ማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ ለማቀጣጠል ጥረቶች እየተደረጉ ነው " - ፖሊስ በትግራይ ክልል በሁለት ሊቃነ ጳጳሳት ላይ " ተቃጥቷል " በተ
#Update " ሶስት ተጠርጣሪዎች ተይዘዋል። ... ጉዳዩን ማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ ለማቀጣጠል ጥረቶች እየተደረጉ ነው " - ፖሊስ በትግራይ ክልል በሁለት ሊቃነ ጳጳሳት ላይ " ተቃጥቷል " በተባለው የግድያ ሙከራ ጉዳይ ሦስት ተጠርጣሪዎች መያዛቸውን የአክሱም ከተማ ፖሊስ አስታውቋል። ፖሊስ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ ፣ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. በአበው ሊቃነ ጳጳሳቱ የመኖሪያ ቅጥር ግቢ ውስጥ አንድ ጥይት ብቻ መተኮሱን አረጋግጧል። እንደ ፖሊስ መግለጫ ፣ ጥይቱን የተኮሰው በተቋሙ የጥበቃ ሠራተኛ ሲሆን ፣ በጉዳዩ ዋና ተጠርጣሪ ከተባለው የጥበቃ ሠራተኛ ጋር ሌሎች ሁለት ተጠርጣሪዎችም በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ገልጿል። ፖሊስ  " ማንኛውም የወንጀል ድርጊት ከሕዝብና ከፖሊስ ዓይን ማምለጥ አይችልም " በማለት ፣ ጉዳዩን በጥልቀት የሚያጣራና ለሕግ የሚያቀርብ የምርመራ ቡድን መቋቋሙን አስታውቋል። በተጨማሪ ፣ ጉዳዩን ከእውነታው ውጭ ለማቅረብና ለማቀጣጠል በማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ ጥረቶች እየተደረጉ መሆናቸውን ጠቅሶ ፣ ሕዝቡ ከሚመለከታቸው ባለሥልጣናት የሚሰጡ የተረጋገጡ መረጃዎችን ብቻ እንዲጠቀም ጥሪ አቅርቧል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሃምሌ 2 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia            

EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
" ድርጅቱ ከለላ ከመስጠት ይልቅ ከሥራ አባሮናል " - ቅሬታ አቅራቢዎች 👉 " ጥበቃዎች በፍቃደኝነት እንጂ የሚያስገድዳቸው የለም። እኛ ያባረርነው ሰራተኛ የለም ! " - ኮሜርሻል ኖሚኒስ ⚫️ "
+1
" ድርጅቱ ከለላ ከመስጠት ይልቅ ከሥራ አባሮናል " - ቅሬታ አቅራቢዎች 👉 " ጥበቃዎች በፍቃደኝነት እንጂ የሚያስገድዳቸው የለም። እኛ ያባረርነው ሰራተኛ የለም ! " - ኮሜርሻል ኖሚኒስ ⚫️ " እኛ ጋር ' እንደዚህ ሆንኩ ' ብሎ በይፋ ያመለከተ  የለም፤ ነገር ግን ' ሰልጥናችሁ ተዋጉ ' ተብለዋል የሚሉ መረጃዎችን በወሬ ደረጃ ሰምተናል ለወረዳችን ግን የቀረበ ጥያቄ የለም " - ኮሚኒኬሽን በምዕራብ ጎጃም ዞን በደንበጫ ከተማ አስተዳደር በሚገኙ ባንኮች ውስጥ በጥበቃ ሥራ ላይ የተሰማሩ ሠራተኞች፣ ከመደበኛ ሥራቸው ጎን ለጎን ለአካባቢው ሰላምና ደህንነት ሲባል "በሚሊሻነት ካልተዋጋችሁ" በሚል ከአካባቢው የጸጥታ አካላት ከፍተኛ ተጽዕኖ፣ እስራት፣ ድብደባ እና ከከተማ የማባረር እርምጃ እየተወሰደባቸው መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ አቅርበዋል። ሠራተኞቹ የደረሰባቸውን በደል ለቀጣሪ ድርጅታቸው ለኮሜርሻል ኖሚኒስ ቢያመለክቱም፣ ድርጅቱ ከለላ ከመስጠት ይልቅ ከሥራ እንዳባረራቸውና በዚህም ሳቢያ ራሳቸውና ቤተሰቦቻቸው ለከፋ ችግር መጋለጣቸውን በምሬት ተናግረዋል። ይሁን እንጂ የኮሜርሻል ኖሚኒስ ደብረ ማርቆስ ቅርንጫፍ የሰው ኃይል አስተዳደር ይህንን ክስ ያስተባብላል። ድርጅቱ ፤ ​"ጥበቃዎች በፍቃደኝነት እንጂ የሚያስገድዳቸው የለም። እኛ ያባረርነው ሰራተኛ የለም፤ ነገር ግን ደንበጫ ከተማ ላይ ከሌሎች አካባቢዎች በተለየ ሁኔታ ተፅዕኖ ተፈጥሮባቸዋል። ከተቀጠሩበት የባንክ ጥበቃ ጎን ለጎን 'ከሚኒሻ ጋር ሆናችሁ ተዋጉ' እየተባሉ ነው፤ በፍቃደኝነት በእረፍት ሰዓታቸው የሚያገለግሉ እንዲሁም ሥራቸውን ጥለው የተሰደዱ አሉ" ሲል አስታውቋል። ከቅሬታ አቅራቢዎቹ መካከል በባንክ ጥበቃ ባለሙያነት ለ8 ዓመታት ያገለገሉ ሠራተኛ፣ ሕመምተኛ በመሆናቸው ፍላጎትና አቅም እንደሌላቸው ቢገልጹም፣ ተጨማሪውን ህዝባዊ ግዳጅ ባለመቀበላቸው ምክንያት ለሁለት ሳምንታት ታስረውና ተደብድበው ከሥራ መባረራቸውንና አሁን ላይ መደበኛ የጥበቃ ሥራቸውን ብቻ መሥራት እንደሚፈልጉ ጠቅሰዋል። በተቃራኒው ድርጅቱ ፤ በደንበጫ ከተማ ላይ ለአገርና ለሕዝብ ሰላም ሲባል ጥበቃዎች እንዲያግዙ የሚፈልጉት የከተማዋ አመራሮች "ጥበቃዎቻችሁን እኛን እንዲያግዙን ለምን አታደርጉም?" በሚል መጠየቃቸውን አምኗል። ሆኖም "ወቅታዊ ሁኔታው አስቸጋሪ ስለሆነ አይቻልም" የሚል ምላሽ እየሰጠ መሆኑንና በጥበቃ ሥራቸው ላይ ብቻ እንዲያተኩሩ ከአመራሮቹ ጋር እየተነጋገረ መሆኑን ገልጿል። ሌላኛው ቅሬታ አቅራቢ ለ10 ዓመታት በሰራዊት አባልነት በታማኝነት ያገለገሉና በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ውጊያ ላይ ሳሉ አንድ ዓይናቸውን ያጡ የ13 ዓመት የባንክ ጥበቃ ሠራተኛ ናቸው። እርሳቸውም ባላቸው የአካል ጉዳት ምክንያት ተጨማሪ ግዳጅ ለመቀበል እንደማይችሉ ገልጸው፣ የጉልበት ሥራ እንኳ እንዳይሠሩ ከከተማ በመባረራቸው ልጆቻቸውን የሚመግቡበት አጥተው ቤተሰቦቻቸውን በየዘመዱ ለመበተን መገደዳቸውን በምሬት ተናግረዋል። ሠራተኞቹ አክለውም በአካባቢው ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ ግዳጅ እንዲወጡ ከተደረጉት የሥራ ባልደረቦቻቸው መካከል የሦስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን አመልክተዋል። እንደ ጥበቃዎቹ ገለጻ 50 አለቃ ልንገር በለጠ (ንግድ ባንክ)፣ አስር አለቃ ይሁኔ በቃሉ (አቢሲኒያ ባንክ) እና ደጀን ባወቀ (ጸደይ ባንክ) የተባሉ ሠራተኞች ተገድለዋል። ይህንኑ በተመለከተ የኮሜርሻል ኖሚኒስ ደብረ ማርቆስ ቅርንጫፍ ማብራሪያ የሰጠ ሲሆን፤ ሞቱ ከተባሉት ሦስት ሠራተኞች መካከል ለአካባቢው ሰላምና ደህንነት ተሰልፎ የሞተው አንዱ ብቻ ሲሆን፣ ሁለቱ ግን በተፈጥሯዊ ሕመም ምክንያት መሞታቸውን ገልጿል። ወደ ደንበጫ ከተማ መግባት ከተከለከሉ አንድ ዓመት ሊሆናቸው እንደተቃረበ የሚገልጹት ሠራተኞቹ፣ ከተማ ገብቶ የተገኘ ጥበቃ "የፋኖ ቃል አቀባይ ነው" እየተባለ እንደሚደበደብና እንደሚታሰር ገልጸው፣ ከየትኛውም አካል ጋር ግንኙነት እንደሌላቸውና የቀን ሥራ እንኳ ሠርተው ልጆቻቸውን እንዲያሳድጉ ፍትሕ እንዲሰጣቸው ተማጽነዋል። ኮሜርሻል ኖሚኒስ ችግሩን ለመቅረፍ ከከተማዋ አመራሮች ጋር በተደጋጋሚ ቢነጋገርም ፣ አመራሮቹ አሁንም "ያግዙን" የሚል አቋም እንዳላቸውና በዚያ ላይ አመራሮቹ በተደጋጋሚ ስለሚቀያየሩ ችግሩን በዘላቂነት መፍታት እንዳልተቻለ ማነቆውን ገልጿል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን በተመለከተ የከተማዋን አመራሮች ያነጋገረ ሲሆን፣ የኮሙኒኬሽን ኃላፊው አቶ እናውጋው ፤ "እኛ ጋር ' እንደዚህ ሆንኩ ' ብሎ በይፋ ያመለከተ  የለም፤ ነገር ግን ' ሰልጥናችሁ ተዋጉ ' ተብለዋል የሚሉ መረጃዎችን በወሬ ደረጃ ሰምተናል ለወረዳችን ግን የቀረበ ጥያቄ የለም " ብለው ለተሻለ መረጃ ወደ ከንቲባው መርተዋል። የደንበጫ ከተማ ከንቲባ አቶ ሙሉቀን መኮነን ግን ፤ " መረጃ ጠያቂው የባንክ ጥበቃ ወይም በጫካ ያለ ታጣቂ መሆንህን ስለማላውቅ መረጃ አልሰጥም" በማለት ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል። ጋዜጠኛው መታወቂያ ለመላክ ቢጠይቅም " በዚህ ጉዳይ ላይ እና ከጸጥታ ጋር በተያያዘ ለማላውቀው ሰው ማብራሪያ አልሰጥም" በሚል የስልኩን ጥሪ አቋርጠውታል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሃምሌ 2 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
የቤት ኪራይ ጭማሪ " የ11.5% ጭማሪ አነስተኛ ይመስላል፤ በዓለምአቀፍ ደረጃ ሲታይ ግን እጅግ ከፍተኛ ጭማሪ ነው የተደረገው " - የኢትዮጵያ ሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት 👉 " ሞሎች፣ የጋራ
+1
የቤት ኪራይ ጭማሪ " የ11.5% ጭማሪ አነስተኛ ይመስላል፤ በዓለምአቀፍ ደረጃ ሲታይ ግን እጅግ ከፍተኛ ጭማሪ ነው የተደረገው " - የኢትዮጵያ ሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት 👉 " ሞሎች፣ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ሥር ያሉ ሱቆች ቀድመው የገዙ የሚያከራዩበት ዋጋ ለመስማት የሚዘገንን ነው! " የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት አስተዳደር ቢሮ ዛሬ ጠዋት ይፋ ያደረገው የ11.5% የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ " እጅግ ከፍተኛ " ፣ " አብዛኛው ተከራይ ከፍተኛ ጭማሪ ከተደረበትና ከተፈናቀለ በኋላ ይፋ የተደረገ " በመሆኑ የዘገዬ ውሳኔ መሆኑን የኢትዮጵያ ሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት ለቲክቫህ ኢትዮጵያን ገለጸ። የድርጅቱ መስራችና ዋና ዳይሬክተር አቶ ቁምላቸው አበበ በሰጡን ቃል፣ " 11.5% የሚለው ጭማሪ ከኛ ሀገር የዋጋ ግሽበት አንፃር ተመጣጣኝ ቢሆንም ከሌሎች ሀገራት ጋር ሲታይ ከፍተኛ ነው " ሲሉ ተናግረዋል። " በሌሎች ሀገራት የቤት ኪራይ ጭማሪ የሚደረገው ቤቱን ለማስጠገን የሚያስፈልግ ወጭ ታሳቢ ተደርጎ ከነጠላ አሀዝ ያላለፈ ጭማሪ ነው " ያሉት አቶ ቁምላቸው፣ " የኛ 11.5% ጭማሪ አነስተኛ ይመስላል፤ በዓለምአቀፍ ደረጃ ሲታይ ግን እጅግ ከፍተኛ ጭማሪ ነው የተደረገው " ሲሉ ገልጸዋል። " ለዛውም ለቤቶቹ ፦ - ጥገና ለማድረግ፣ - ቀለም ለመቀባት፣ - ቤት ውስጥ ያሉ ነገሮችን ለማስተካከል ጭምር ነው ? ጭማሪ የተደረገው የሚለው ሳይታሰብ ለዋጋ ግሽበት ብቻ የተደረገ ጭማሪ ነው " ብለውታል። የከተማዋ ቤቶች ልማት አስተዳደር ደግሞ፣ ጭማሪው " በጥናት የተደገፈ ፣ የነዋሪውን የመክፈል አቅም ያገናዘበ ፣ አከራዮች ወቅታዊውን የኢኮኖሚ ሁኔታ ያገናዘበ ፍትሐዊ ገቢ እንዲያገኙ " የሚያስችል ብሎታል። የሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት በሌላ በኩል፥ " የቢሮው ውሳኔ እንደ መነሻ ይበል የሚያሰኝ ቢሆንም፣ ማስተካከያው ይፋ መደረግ የነበረበት በግንቦትና ሚያዚያ ወር ነበር፤ በጣም የዘገየ ነው " ብሏል። " አብዛኛው ተከራይ ከኪራይ ከተፈናቀለ፣ ከፍተኛ የኪራይ ጭማሪ ከተደረገበት በኋላ ነው ውሳኔው ይፋ የተደረገው " ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል። ተከራዮች በበኩላቸው፣ የኪራይ ጭማሪው 11.5% ሆኖ ከመወሰኑ በፊት ፦ • " ቤቴን ላድስ ነው" • " ቤተሰብ ሊገባበት ነው " በሚል ሰበብ የተጋነነ ጭማሪ እንደተደረገባቸው ቅሬታ እያቀረቡ ሲሆን፣ ቲክቫህ ኢትዮጵያም ለዚህ ምን አይነት መፍትሄ ያስፈልጋል ? ሲል ድርጅቱን ጠይቋል። የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ቁምላቸው አበበ፣ " የዚህ መመሪያ አንዱ ፈታኝ ነገር አፈጻጸሙ እንዴት ይሆናል ? እግር በእግር ተከታትሎ ማን ያስፈጽመዋል ? " የሚለው መሆኑን ገልጸው፣ ከዚህ በፊት ቤቱ ተከራይቶበት የነበረው ዋጋና አሁን ስንት እንደሚሆን ስለሚታወቅ የጭማሪው አፈጻጸም ስርዓታዊ እንዲሆን አሳስበዋል። " ዛሬ ይፋ የሆነው ውሳኔ፣ እንዴት ይፈጸማል ? ማስፈጸሚያ ስልቱ ምንድን ነው ? የሚለው ግልጽ አይደለም " ብለው በጥናቱ ድርጅታቸው እንዳልተሳተፈ አመልክተዋል። " እንዲህ አይነት ጥናቶች ሲደረጉ እንደ እኛ አይነት የሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅቶችን፣ ተከራዩን፣ አከራዩን በግልጽ ማወያየት ይገባል " ብለዋል። ጉዳዩ በአከራዮችና ተከራዮች መካከል ጭቅጭቅ እንዳያስከትል አፈጻጸሙ ለወረዳ ብቻ ሳይተው የበላይ የመንግስት አካል መከታተል አለበት ባይ ናቸው። ከ50 እስከ 100% ኪራይ ጭማሪ እንደተደረገ፣ በተለይ በጋራ መኖሪያ ቤቶች ፦ ° ባለአንድ መኝታ ቤት ከ9፣ 10 ሺሕ ተነስቶ እስከ 22 ሺሕ ብር እንደደረሰ፤ ° 15፣ 16 ሺሕ ብር ሲከራይ የነበረው ባለሁለት መኝታ ቤት 28፣ 30 ሺሕ መከራየትና መጠራት እንደተጀመረ ከዚህ ቀደም ማሳወቃቸውንም አስታውሰዋል። " አሁን የወጣው ውሳኔ ቀድሞ ባስቸኳይ ይፋ እንዲደረግ፣ እርምጃ እንዲወሰድ አሳስበን ነበር " ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ " ያን ካሳሰብን በኋላ ዛሬ ይፋ የሆነው ውሳኔ የዘገዬ ነው " ሲሉም ተችተዋል። የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ በበኩሉ፣ " ዋጋ ጭማሪው እና የውል እድሳቱ መነሻ የሚሆነው ከዚህ ቀደም በነበረው ውል ላይ የተቀመጠው የኪራይ ዋጋ ብቻ ነው " ሲል አስታውቋል። የሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት በሌላ በኩል በሰጠን ገለጻ፣ በቤት ኪራይ ብቻ ሳይሆን በሌሎች የመንግስት አገልግሎቶች፣ የንግድ ዘርፎች ላይ እንዲሁ ተመሳሳይ የዋጋ ጣሪያ የትርፍ ህዳግ ሊወሰን ይገባል ሲል በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሳስቧል። የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ስለአጠቃላይ ችግሩና መፍትሄው አክለው ምን አሉ ? " ለቤት ኪራይ መወደድ ትልቅ ጫና የፈጠረው በኮሪደር ልማቱ በርካታ ቤቶች ፈርሰው በቂ ተጨማሪ ቤት ባለመገንባቱ በቤት ኪራይ ላይ የመጣው ጫና ነው። ከፍተኛ የመኖሪያ ቤት እጥረት፤ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት፤ የኑሮ ውድነት አለ። መንግስት በተለይ ለደመወዝተኛው የዋጋ ግሽበቱን ታሳቢ ያደረገ የደመወዝ ጭማሪ ሊያደርግ ይገባል። ላለው የዋጋ ግሽበት አንዱ ምክንያት የመኖሪያ ቤት እጥረት ነው። እጥረቱ በዘላቂነት ሊቀረፍ የሚችለው በተለያዩ አማራጮች መኖሪያ ቤቶችን በመገንባት ነው። ሌላው ፥ በቤት ኪራይ ከፍተኛ ጭማሪ የሚያደርገው ህገወጥም፣ ህጋዊም ደላላ ነው። ከቤት ባለቤት ደውሎ 'ይህን ያህል ላከራይልህ' በማለት። ዘላቂው መፍትሄ በአከራይና ተከራይ መካከል ያለውን ደላላ በማስወጣት አከራዩ እና ተከራዩ የሚገናኝበትን የቴክኖሎጂ መተግበሪያ መዘርጋት ነው።  በተያያዘ፥ ከፍተኛ የቤት ግንባታ ማድረግ፤ የሊዝ ዋጋ መቀነስ ይገባል። የኛ ሀገር ሊዝ እነ ኒዮርክ፣ ለንደን ያስከፍሉታል ከሚባለው አያንስም በሚል ነው የሚተቸው። ስለዚህ በካሬ ሜትር የሊዝ ዋጋ መቀነስና የመሬት አቅርቦቱን ሌሎች አማራጮችን ፈልጎ መፍትሄ ማማጣት ያስፈልጋል። ያለው ችግር የመኖሪያ ቤት ብቻ አይደለም። የንግድ ቤቶችም በከፍተኛ ዋጋ ነው የሚከራዩት። በከፍተኛ ዋጋ የተከራየ ነጋዴ ባለሱቅ ያንን ዋጋ የሚጭነው ሸማቹ ላይ ነው። ሞሎች፣ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ሥር ያሉ ሱቆችን ቀድመው የገዙ ሰዎች የሚያከራዩበት ዋጋ ለመስማት የሚዘገንን ነው፤ ይሄ መስተካከል አለበት። ለንግድ የኪራይ ቤቶችም ታሪፍና የዋጋ ጣሪያ ሊቀመጥ ይገባል " ብለዋል። በሌላ በኩል ፥ " በአከራዮች ላይ በጣም ስለተጋነነ እንጅ አንዳንድ አከራዮች ደግሞ ልጆች የሚያስተምሩት ባለአንድ መኝታ ቤት ካላቸው ያን አከራይተው፣ ከከተማ ወጣ ያለ ቤት ተከራይተው ነው። የኑሮ ውድነቱ በአከራዩም በተከራዩም ስለሆነ ይህን ችግር ለመፍታት አስታራቂ መፍትሄ ያሻል " ሲሉ አስገንዝበዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ሃምሌ 1 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
" አንድ ሊትር ሲሰጡ/ሲቀዱ ሙሉ አንድ ሊትር አይደለም መለኪያው " - የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን (ለቲክቫህ ኢትዮጵያ) 👉 " ማደያዎች ላይ ነዳጅ እንዳያቀርቡ እርምጃ ስለተወሰደ አቅርቦቱ ላይ ች
+1
" አንድ ሊትር ሲሰጡ/ሲቀዱ ሙሉ አንድ ሊትር አይደለም መለኪያው " - የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን (ለቲክቫህ ኢትዮጵያ) 👉 " ማደያዎች ላይ ነዳጅ እንዳያቀርቡ እርምጃ ስለተወሰደ አቅርቦቱ ላይ ችግር አይፈጥርም! " የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን፣ ከግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ በተለያዩ ከተሞች "ድንገተኛ የኢንስፔክስን ስምሪት በነዳጅ ማደያዎች የመቅጃ ማሽን (ዲስፔንሰር) ላይ ምርመራ በማድረግ 12 ማደያዎች ማሽኖቻቸው ትክክለኛውን ልኬት የማያሳዩ እና የነዳጅ ቅሸባ የሚፈጸምባቸው መሆኑን" ማረጋገጡን ዛሬ አሳውቋል። ባለስልጣኑ ማደያዎቹ "ከሰኔ 23/2018 ዓ/ም ጀምሮ እንደ ጥፋታቸው መጠን ከአንድ እስከ ሁለት ወር የነዳጅ ጭነት ዕገዳ" እንደተደረገባቸውም ገልጿል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስለጉዳዩ የተጠቃቸው የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ደስታው መኳንንት (ዶ/ር)፣ " አንድ ሊትር ሲሰጡ/ሲቀዱ ሙሉ አንድ ሊትር አይደለም መለኪያው። 800፣ 900 ሚሊ ሊትር ይሆናል። ለትነት የሚፈቀድ መገጠን አለ፤ ከዚያ በላይ መቀሸብ ህገወጥነት ነው " ብለዋል። ማህበረሰቡ ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ቀላል እንዳልሆነም ገልጸዋል። በሌላ በኩል፥ አንዳንድ አሽከርካሪዎች ባለስልጣኑ የወሰደው እርምጃ ተገቢ መሆኑን በመግለጽ፣ ነዳጅ እንዳያቀርቡ እርምጃ መውሰዱ በማደያዎች ላይ ተሽከርካሪዎች ነዳጅ ሲቀዱ ከእስከዛሬው የበለጠ መስተጓጎል እንዳያስከትል የቅጣቱ አይነት ከዚህ የተለየ ቢሆን የሚል አስተያየት ሲሰጡ ተስተውለዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ ከነዳጅ አቅርቦት ጋር በተያያዘ ተሽከርካሪዎች ማደያ ላይ መጉላላት እንደሚገጥማቸው በተደጋጋሚ ቅሬታ ይቀርባል፤ የተወሰደው እርምጃ ነዳጅ በሚቀዱ ተሽከርካሪዎች ላይ መጉላላትን አያስከትልም ወይ ? ከምን አንጻር ታስቦ የተወሰደ እርምጃ ነው ? ሲል ባለስልጣኑን ጠይቋል። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ደስታው መኳንንት (ዶ/ር)፣ እርምጃው " መጉላላት አይፈጥርም " ሲሉ መልሰዋል። " እርምጃ በተወሰደባቸው ማደያዎች ምክንያት ምንም አይነት ችግር አይፈጠርም " ነው ያሉት። አክለውም ፣ " ገና በአቅርቦት ላይ ችግር ይፈጠራል ተብሎ ህገወጦችን መደበቅ ተገቢነት የለውም " ብለዋል። " የማደያ ችግር አይደለም ያለው " ያሉት ደስታው (ዶ/ር)፣ " እርምጃ በተወሰደባቸው ማደያዎች ዙሪያ ሌላ ማደያ አለ። ቢያንስ አንድ፣ ሁለት ወይም ሦስት ይኖራል " ሲሉ ገልጸዋል። ለምሳሌ፣ " አዲስ አበባ ላይ ወደ 130 ማደያ ነው ያለው። አራት፣ አምስት ማደያዎች ላይ (ነዳጅ እንዳያቀርቡ) እርምጃ ስለተወሰደ አቅርቦቱ ላይ ችግር አይፈጥርም፤ ሌሎችም አካባቢዎች ተመሳሳይ ነው የሚሆነው " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል። " ችግር ያለባቸው ከድርጊታቸው እንዲታረሙ ነው እርምጃ የምንወስደው። እስካሁን በወስድናቸው እርምጃዎች በጣም Critical የሆነ የአቅርቦት ችግር ያለበት የለም። ምክንያቱም በአንድ ከተማ ውስጥ ከሦስት፣ አራት በላይ ማደያ ነው ያለው " ብለዋል። "ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ቅሬታ የቀረበው አሁን በቅርቡ ነው። እኛ ኦፕሬሽን የምንሰራው በተደጋጋሚ ነው። ግንቦት 29 ነው የሚለው ደብዳቤው እንዳየኸው። በቅርቡ ነው ልክ የኢንስፔክሽን ስራው ሲጀመር ማስጮህ የተጀመረው " ሲሉ ተናግረዋል። " እርምጃ የተወሰደባቸው በቀጣይም ቀናት ይፋ የሚደረጉ ሌሎች ማደያዎች አሉ " ሲሉም የጠቆሙት ዋና ዳይሬክተሩ ስንት እንደሆኑ ስንጠይቃቸው " በተቋሙ የፌስቡክ ገጽ ነው የሚገለጸው " ብለዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ሃምሌ 1 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ገቢዎች ሚኒስቴር ዛሬ ለጀመረው አዲሱ በጀት ዓመት የግብር ከፋዮች ምደባ (segementation) አድርጓል። ገቢዎች ሚኒስቴር ይፋ ያደረገው የግብር ከፋዮች ምደባ በየሦስት አመቱ የሚከናወን መሆኑ የ
+1
ገቢዎች ሚኒስቴር ዛሬ ለጀመረው አዲሱ በጀት ዓመት የግብር ከፋዮች ምደባ (segementation) አድርጓል። ገቢዎች ሚኒስቴር ይፋ ያደረገው የግብር ከፋዮች ምደባ በየሦስት አመቱ የሚከናወን መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ከሃምሌ 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ ግብር ከፋዮች ታክስ የሚከፍሉትም ሆነ ማንኛውንም አገልግሎት የሚያገኙት አዲስ በተመደቡበት ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በኩል ብቻ ይሆናል። በገቢዎች ሚኒስቴር ስር ያሉ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችም በአዲሱ ምደባ መሰረት ወደ ቅርንጫፎቻቸው የተመደቡ ግብር ከፋዮችን ዝርዝር ይፋ በማድረግ ላይ ይገኛሉ። ቲክቫህ ኢትዮጵያ የምደባው አስፈላጊነት ምንድነው ? ሲል የገቢዎች ሚኒስቴርን ጠይቋል። ሚኒስቴሩ በሰጠን ምላሽ የግብር ከፋዮች ምደባ ወይም "ሰግሜንቴሽን" በየሦስት ዓመቱ የሚከናወን አሠራር መሆኑን በመግለጽ፣ ዋና ዓላማውም ለአገልግሎት አሰጣጥ ምቹ ሁኔታን መፍጠር መሆኑን ነግሮናል። "ይህ ምደባ ግብር ከፋዮችን እንደየሥራ ዘርፋቸውና እንደየገቢ መጠናቸው በተመሳሳይ "ክላስተር" እንዲመደቡ ያደርጋል" ያለ ሲሆን ይህም ቅርንጫፎች ለተመደቡላቸው ግብር ከፋዮች እንደየባህሪያቸው ልዩ ድጋፍና አገልግሎት እንዲሰጡ ያስችላቸዋል ብሎናል። በተጨማሪም የንግድ ተቋማት እያደጉ ሲሄዱ ከአነስተኛ ወደ መካከለኛ፣ ከመካከለኛ ደግሞ ወደ ከፍተኛ ግብር ከፋይነት የሚሸጋገሩበት፣ እንዲሁም የንግድ እንቅስቃሴያቸው ሲቀንስ ወደ ታች የሚወርዱበት ሁኔታ መኖሩ ምደባውን አስፈላጊ እንደሚያደርገው ተገልጿል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ግብር ከፋዮች በቅርብ ርቀት አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግም የሎኬሽን ወይም የቦታ ምቹነት ታሳቢ ተደርጓል ነው ያለው። ለዚህም በቅርቡ ሦስተኛው የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በግሎባል አካባቢ መከፈቱ ተጠቅሷል። ሚኒስቴሩ በሰጠን ማብራሪያ "አንድ ሰው(ግብር ከፋይ) እንደ ንግዱ ባህሪ ባለበት ግብር የመክፈል አቅም ላይ ላይቆይ መቻሉ ፣ንግዱ ሲያድግ ወደ ከፍተኛ ወይም መካከለኛ ፣ መካከለኛው ደግሞ ወደ ከፍተኛ አንዳንዱ ደግሞ እየደከመ ከሄደ ከፍተኛ የተባለው ወደ መካከለኛ ሊወርድ ይችላል ይህም ምደባውን ለማከናወን ሌላው ምክንያት ነው" ብሎናል። በአሁኑ ወቅትም አዳዲስ የተከፈቱና ነባር ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች ወደ እነሱ የተመደቡ ግብር ከፋዮችን ዝርዝር ይፋ እያደረጉ ጥሪ እያቀረቡ ይገኛሉ። ቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ሃምሌ 1 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ከቀጥተኛ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ራሳቸውን ማግለላቸውን አስታወቁ። ባለፉት 5 ዓመታት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጠንካራ ተቃዋሚነታቸውና በደፋር ተናጋሪነታቸው የሚታወቁት ደሳለኝ
+1
ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ከቀጥተኛ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ራሳቸውን ማግለላቸውን አስታወቁ። ባለፉት 5 ዓመታት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጠንካራ ተቃዋሚነታቸውና በደፋር ተናጋሪነታቸው የሚታወቁት ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር)፣ ከማንኛውም ቀጥተኛ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ራሳቸውን ማግለላቸውን በይፋ አስታወቁ። በትላንትናው ዕለት የፓርላማ ቆይታቸውን ያጠናቀቁት ደሳለኝ (ዶ/ር)፣ ከማንኛውም ፓርቲ አባልነትም ሆነ ደጋፊነት መውጣታቸውን ገልጸዋል። ደሳለኝ (ዶ/ር)፤ "በትናንትናው የምክር ቤቱ ጉባዔ ላይ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ 'አብረን እንስራ' በማለት ላቀረቡልን ጥሪና ላሳዩን አክብሮት ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ" ብለዋል። " ከጉባዔው መጠናቀቅ በኋላ ጥያቄ ያቀረብን የተቃዋሚ የምክር ቤት አባላት ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር በነበረን የችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር ላይ፣ በ7ኛው ዙር ምርጫ በባሕር ዳር ከተማ ለመወዳደር ተመዝግቤ ቢሆን ኑሮ እጩ ላለማቅረብ ወስነው እንደነበር ገልጸውልኛል " ያሉት ደሳለኝ (ዶ/ር)፤ " በምክር ቤቱ ሳነሳቸው የነበሩ ሀሳቦች ጠቃሚ እንደነበሩ፣ በትኩረት እንደሚወስዷቸው እና በምክር ቤቱ ብቀጥል ፍላጎታቸው እንደነበር የገለጹልኝን ሀሳብም በበጎ ጎኑ እና በቅንነት ተመልክቼዋለሁ " ሲሉ ገልጸዋል። ደሳለኝ (ዶ/ር) ላለፉት 10 ዓመታት የሕዝብን አደራ ለመወጣት ካደረጉት ከፍተኛ ጥረትና ድካም በኋላ፣ አሁን ላይ ትኩረታቸውን በሙያቸው ሀገራቸውን ማገልገል፣ ጎን ለጎን ወደ ግሉ ዘርፍ በመግባት በፈጠራ ሥራዎች (Startups) ላይ መሰማራት እና ለቤተሰባቸው ጊዜ መስጠት ላይ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል። ቀጥተኛ ፖለቲካውን ቢሰናበቱም፣ የአማራን ሕዝብ አንድነትና ከሌሎች ወንድም ሕዝቦች ጋር ያለውን አብሮነት በሚያጠናክሩ ማኅበራዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በሙያቸው ማገዛቸውን እንደሚቀጥሉ አረጋግጠው፤ አዲሱ የ2019 ዓ.ም ለኢትዮጵያ የእውነተኛ ሰላምና የተስፋ ዘመን እንዲሆን ተመኝተዋል። ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ወደ ፖለቲካው ከመግባታቸው በፊት በነበራቸው የዩኒቨርሲቲ መምህርነት ሕይወታቸው እንዲሁም የጣና ሐይቅን ከእንቦጭ አረም ለመታደግ በአክቲቪዝም እና የሀገር በቀል ሲቪክ ማኅበራትን በግንባር ቀደምትነት በመምራት ሰፊ የማኅበረሰብ አገልግሎት በማበርከት ይታወቃሉ። ቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ @tikvahethiopia

EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray : ከማዕከል ራሱን ለይቶ ያዋቀረው የ " ትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ሰላማ ከፍተኛ ቤተ ክህነት ጽህፈት ቤት " በሁለት አበው ሊቃነ ጳጳሳት ላይ ያነጣጠረ የግድያ
#Tigray : ከማዕከል ራሱን ለይቶ ያዋቀረው የ " ትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ሰላማ ከፍተኛ ቤተ ክህነት ጽህፈት ቤት " በሁለት አበው ሊቃነ ጳጳሳት ላይ ያነጣጠረ የግድያ ሙከራ መፈጸሙን አስታውቋል። ጥቃቱ ያነጣጠረው በብፁዕ አቡነ አረጋዊ እና ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ላይ መሆኑን አመልክቷል። ጥቃቱ የተፈጸመው ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ከሌሊቱ 6፡30 ገደማ በአክሱም ከተማ በሚገኘው መኖሪያ ግቢያቸው ውስጥ ነው። የአክሱም ከተማ አስተዳደር በበኩሉ በዕለቱ በአበው ሊቃነ ጳጳሳቱ መኖሪያ ግቢ ውስጥ አንድ ጥይት መተኮሱን አረጋግጧል። ይሁን እንጂ " ነገሩ ከሚገባው በላይ እየተጋነነ ነው " ብሏል። ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑን ገልጿል። ሃምሌ 1 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
" ዋጋ ጭማሪውና የውል እደሳቱ መነሻ የሚሆነው ከዚህ ቀደም በነበረው ውል ላይ የተቀመጠው የኪራይ ዋጋ ብቻ ነው " - ቢሮው በ2019 ዓ/ም በአዲስ አበባ ከተማ፣ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 1
" ዋጋ ጭማሪውና የውል እደሳቱ መነሻ የሚሆነው ከዚህ ቀደም በነበረው ውል ላይ የተቀመጠው የኪራይ ዋጋ ብቻ ነው " - ቢሮው በ2019 ዓ/ም በአዲስ አበባ ከተማ፣ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ የጸደቀ ሲሆን ሕገ-ወጥ " የመንደር እና የአካባቢ ውሎች " በጥብቅ ተከልክለዋል። ዋጋ ጭማሪውና የውል እደሳቱ መነሻ የሚሆነው ከዚህ ቀደም በነበረው ውል ላይ የተቀመጠው የኪራይ ዋጋ ብቻ መሆኑን የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታውቋል፡፡ በመላው ከተማዋ የሚገኙ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ-ተከራይ አዲስ የውል እድሳት ምዝገባ ከዛሬ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በይፋ መተግበር መጀመሩ ተገልጿል። የተጣሉ ጥብቅ ክልከላዎች ምን ምን ናቸው ? አዲሱን የውል እድሳት ምዝገባና የተቀመጠውን የዋጋ ጣሪያ ወደ ጎን በመተው የሚፈጸሙ ማናቸውም ሕገ-ወጥ ድርጊቶች ላይ ጥብቅ ክልከላ ተጥሏል። በዚህም መሠረት ፡- - በቢሮው ከተመዘገበው እና ከሚመዘገበው ውል እንዲሁም ከሚሰጠው አቅጣጫ ውጭ፣ «ልዩ ውል» በሚል የሚፈጸሙ ማናቸውም የመንደር ውሎች፤ - ከሕጋዊ አሰራር ውጭ የሚደረጉ የአካባቢ ውሎች፤ - በጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) አካባቢ የሚደረጉ ማናቸውም ዓይነት ሕገ-ወጥ ውሎች ሙሉ በሙሉ የተከለከሉ ናቸው። ማንኛውም አከራይ እና ተከራይ እነዚህን የተከለከሉ ሕገ-ወጥ ውሎች ይዘው ሲገኙ ወይም ከተቀመጠው የ11.5% የዋጋ ጭማሪ ጣሪያ በላይ ፈጽመው ከተገኙ ቢሮው ሕጋዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን አስጠንቅቋል። ሃምሌ 1 ቀን 2018 ዓ/ም #TikvahEthiopiaFamilyAA @tikvahethiopia

EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
በአዲስ አበባ የ2019 ዓ.ም የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ ተወሰነ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ እና በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ መደበኛ ያልሆኑ አሰራ
+1
በአዲስ አበባ የ2019 ዓ.ም የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ ተወሰነ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ እና በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ መደበኛ ያልሆኑ አሰራሮችን ለመግታት የ2019 በጀት ዓመት የቤት ኪራይ ዓመታዊ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ እንዲጸድቅ መወሰኑን የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ። ይህ የዋጋ ማስተካከያ ውሳኔ ቀደም ሲል በወጣው የቤት ኪራይ ቁጥጥር አዋጅ መሠረት የተወሰነ ሲሆን፣ በከተማዋ የተካሄደ ሳይንሳዊ ጥናትንና የነዋሪውን የመክፈል አቅም ያገናዘበ መሆኑ ተገልጿል። ውሳኔው አከራዮች ወቅታዊውን የኢኮኖሚ ሁኔታ ያገናዘበ ፍትሐዊ ገቢ እንዲያገኙ የሚያስችል ሲሆን፣ ተከራዮች ደግሞ ካልተገባ የዋጋ ጭማሪና መፈናቀል ድነው የተረጋጋ ሕይወት እንዲመሩ ለማድረግ ያለመ ነው ተብሏል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ በመላው ከተማዋ የሚገኙ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ-ተከራይ አዲስ የውል ምዝገባና የውል እድሳት ከዛሬ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም ክፍለ ከተሞች በሚገኙ የቤቶች አስተዳደር ጽሕፈት ቤቶች በይፋ መጀመሩ ቢሮው አያይዞ ገልጿል። ቢሮው አክሎም፣ " ይህ አሰራር በከተማዋ ያለውን የኑሮ ውድነት ጫና በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ አለው " ብሏል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሃምሌ 1 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Iran #USA የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) ፤ " ኢራን በሆርሙዝ ሰርጥ ሶስት የንግድ እና የነዳጅ ጫኝ መርከቦች ላይ የድሮን ጥቃት ፈጽማለች " በማለት እንደ በስትራቴጂካዊ የኢራን ቦታዎች ላይ ከባድ የአየር ድብደባ ፈጽሟል። የመካከለኛው ምስራቅ ውጥረት ዳግም በእጅጉ አገርሽቷል። ኢራን፣ ዋሽንግተን ኦማን አቅራቢያ አዳዲስ የባህር መስመሮችን ለመክፈት ጥረት እያደረገች እንደሆነና ይህም የተደረሰውን የመግባቢያ ስምምነት (MoU) የሚጥስ እንደሆነ ትገልጻለች። ይህ እየተባለ ባለበት ሰዓትና ኢራንም መረከቦች በዛ እንዳያልፉ ባስጠነቀቀችበት ሰዓት ነው ኦማን አቅራቢያ 3 መርከቦች የተመቱ። አሜሪካም ፣ ለተፈጸመው ጥቃት መላሽ ለመስጠት ወሳኝ ስትራቴጂካዊ የሚባሉ የኢራን ወደብ ቦታዎች ደብድባለች። ከዚህ ወታደራዊ እርምጃ ትንሽ ቀደም ብሎ፣ የአሜሪካው ግምጃ ቤት ለኢራን ተሰጥቶ የነበረውን ጊዜያዊ የነዳጅ ማዕቀብ ማቃለያ በይፋ የሰረዘ ሲሆን ይህም ቴህራን በሕጋዊ መንገድ ነዳጅ ወደ ውጭ የመላክ አቅሟን ያግደዋል። ኢራን፣ አሜሪካ " የተደረሰውን ስምምነት ጥሳለች " የሚል ክስ እያቀረበችባት ነው። አሁን ላይ የተፈጠረው ሁኔታ ዓለም አቀፍ ነዳጅ ዋጋ እንዲጨምር አድርጓል። ቪድዮ፦ ከማህበራዊ ሚዲያ/ኢራን ሀምሌ 1 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ParliamentQuotes " በቅርቡ ጥናት አጥንተን ነበር። ከግማሽ በላይ ከ50% በላይ የሙስሊም ማህበረሰብ ያለባቸው ወረዳዎች አብዛኛው ሙስሊም የሆነበት ወረዳዎች 1,263 ቤተክርስቲያኖች አሉ፤
#ParliamentQuotes " በቅርቡ ጥናት አጥንተን ነበር። ከግማሽ በላይ ከ50% በላይ የሙስሊም ማህበረሰብ ያለባቸው ወረዳዎች አብዛኛው ሙስሊም የሆነበት ወረዳዎች 1,263 ቤተክርስቲያኖች አሉ፤ አብዛኛው እስላም የሆነበት አካባቢ ፤ ከ1 ሺህ ውስጥ ስንት ቦታ ነው ግጭት የምንሰማው ነው አሁን ? የሃይማኖት ግጭት ካለ አብዛኛው ሙስሊም ያለበት አካባቢ ሁሉም ቦታ ግጭት ይጠበቅ ነበር ፤ ግን የእስልምና ባህሪ ግጭት አይደለም ፤ የክርስትና ባህሪ ግጭት አይደለም። ክርስቲያኖች የበዙባቸው አካባቢዎችም እንደዚሁ መስጂዶች አሉ የምንሰማው ችግር ግን ጥቂት ቦታ ነው። በዚህ ሁሉ ስፋት ችግር አንሰማም። አስተውላችሁ ከሆነ ነውጠኞች ክብሪት ፣ ጭድ ይዘው ይለኩሳሉ። ጀሌዎቻቸው እዚሁ አዲስ አበባ ተቀምጠው ቤንዚን እያርከፈከፉ እሳቱን ያራግቡታል። ለኳሽ እና አራጋቢ ማዶ ለማዶ ተቀምጠው ችግሩን የእምነት ፣ የብሄር መልክ ለመስጠ ይሞክራሉ። " - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ParliamentQuotes " የዋጋ ግሽበት ኢትዮጵያ ውስጥ ሊቀር አይችልም 10% እድገት እያመጣን የዋጋ ግሽበትን 0 ማደረግ አንችልም መጠበቅ የለባቹም ፤ ጤናማ በሆነ መንገድ ሲንግድ ዲጂት ከሆነ
#ParliamentQuotes " የዋጋ ግሽበት ኢትዮጵያ ውስጥ ሊቀር አይችልም 10% እድገት እያመጣን የዋጋ ግሽበትን 0 ማደረግ አንችልም መጠበቅ የለባቹም ፤ ጤናማ በሆነ መንገድ ሲንግድ ዲጂት ከሆነ ከእድገታችን ጋር የሚሄድ ከሆነ አይቀሬ ነው። ችግሩ የሰዎች በገቢያቸው ህይወታቸውን የመደጎም አቅማቸው ውስን መሆን ነው ለዛ ገቢን በሚመለከት በጣም ብዙ ስራ ይጠበቅብናል። የኢትዮጵያን በተለይ በግሉ ዘርፍ ያለውን ትንሹን የደሞዝ መጠን (minimum wage) መመርመር እና ማስተካከያ ማድረግ ያስፈልጋል። " - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ParliamentQuotes " ቋሚ ደሞዝ የሚከፈላቸው የመንግስት እና የግል ድርጅቶች ሰራተኞች፣ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የከተማ ነዋሪዎች፣ አነስተኛ ነጋዴዎች፣ አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች እ
#ParliamentQuotes " ቋሚ ደሞዝ የሚከፈላቸው የመንግስት እና የግል ድርጅቶች ሰራተኞች፣ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የከተማ ነዋሪዎች፣ አነስተኛ ነጋዴዎች፣ አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ወገኖቻችን በስውር ረሀብ ውስጥ ወድቀዋል።  የቤት ኪራይ ከአብዛኛው ዜጎቻችን ወርሃዊ ገቢ በላይ ሆኗል። በአሁኑ ወቅት በሀገራችን መካከለኛ የሚባል የህብረተሰብ መደብ ጠፍቶ ጥቂት እጅግ የበለፀጉ እና አብዛኛው በድህነት የሚማቅቅ ሁለት መደቦች ሆነዋል። " - ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ParliamentQuotes " ከደመወዙ 35% ግብር ፣ 7% ጡረታ በድምሩ 42% ይቆረጣል። ከ58% ደመወዙ ላይ በእያንዳንዱ በሚሸምተው ሸቀጥ 15% ቫት (VAT) ይቆረጣል። ትራንዛክሽን ላይ ንግድ
#ParliamentQuotes " ከደመወዙ 35% ግብር ፣ 7% ጡረታ በድምሩ 42% ይቆረጣል። ከ58% ደመወዙ ላይ በእያንዳንዱ በሚሸምተው ሸቀጥ 15% ቫት (VAT) ይቆረጣል። ትራንዛክሽን ላይ ንግድ ባንክ ለሰርቪስና ቫት እያለ ሌሎችም የማይታወቁ ተቆራጮችን ይቆርጣል።  ሰራተኛው ለውሃ፣ ለመብራት ለሌሎችም አገልግሎቶች ይቆረጥበታል። እነዚህ ሁሉ ተዳምረው ኑሮን መቋቋም አቅቶታልና ለዚህ ታጋሽ ሲቪል ሰርቪስ እና አነስተኛ ኑሮ ላይ ላለው ዜጋ ምን ታስቦለታል ? ከሚመሰርቱት መንግሥት ምን እንጠብቅ ?  " - አቶ ባርጠማ ፍቃዱ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+4
ፎቶ/ቪድዮ ፦ ዛሬ ከተካሄደው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ማጠናቀቂያ በኋላ፣ በምክር ቤቱ ቅጥር ጊቢ ውስጥ ጠ/ ሚዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በዚህ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ላለፉት 5 ዓመታት በፓርላማው መድረክ የሕዝብን ድምፅ ሲያስተጋቡና የተለያዩ አገራዊ ጥያቄዎችን በንቃት ሲያቀርቡ የቆዩ ተሰናባች ተቃዋሚ የምክር ቤት አባላት ተሳትፈዋል። ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

EBS TV
4 613
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
" 50 ዓመት ፓርቲ መርተህ ፓርቲ የሚተኩ ሰዎች ካልፈጠርክ ሌላ 1000 (ዓመት) ቢሰጥህም አትፈጥርም ማለት ነው ! " ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ፦ " የዛሬ 20 እና 30 ዓመት አሁን ያለው መ
" 50 ዓመት ፓርቲ መርተህ ፓርቲ የሚተኩ ሰዎች ካልፈጠርክ ሌላ 1000 (ዓመት) ቢሰጥህም አትፈጥርም ማለት ነው ! " ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ፦ " የዛሬ 20 እና 30 ዓመት አሁን ያለው መንግሥት፣ አሁን እዚህ ፊትለፊት የምታይዋቸው ሰዎች ከወረዱ በኋላ ተመልሰው መጥተው ኢትዮጵያን እንምራ ካሉ ኢትዮጵያ ሞታለች ማለት ነው። ኢትዮጵያ ለዘመኑ፣ ለሲዝን ሚመጥን መሪ መፍጠር ካልቻለች ሰዎች እየወጡ እየወረዱ የሚመላለሱባት ከሆነ ኮሌክቲቭሊ ሞታለች ማለት ነው። ይሄ የሚያኮራ ነገር አይደለም፤ የሚያሳፍር ነገር ነው። 50 ዓመት ፓርቲ መርተህ ፓርቲ የሚተኩ ሰዎች ካልፈጠርክ ሌላ 1000 (ዓመት) ቢሰጥህም አትፈጥርም ማለት ነው። TPLF 50 ዓመት የፖለቲካ ፓርቲ አንጋፋ ፓርቲ ሆኖ ወጣቱን ትውልድ ማመን ካልቻለ ኪሳራ ነው። በፍጹም አትጠብቁ ድልና TPLF አራምባ እና ቆቦ ናቸው። ለምን መሰላችሁ የሚያሳየው ነገር  ፦ - new blood - new thought - new direction የማይቀበል ኃይል በነበረው ነገር የትም አይደርስም። ያም ቢሆን እኛ የምንፈልገው ሰላም ነው። ከማንም ቢሆን መነጋገር፣ ሰላምና ልማት ነው የምንፈልገው። ከግጭት አናተርፍም፤ አይጠቅመንም። በተለይ በተለይ ትግራይ አካባቢ የኛ ትልቁ ምኞት ባህርዳር ፣ ጎንደር፣ ጅማ፣ አርባምንጭ የምናየውን የኮሪደር ልማት መቐለ ማየት ነው። ምኞታችን እሱ ነው። ከዚህ ውጭ ያለው ጉዳይ አጠቅመንም አንፈልገውም። " ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia