4 553
Подписчики
-424 часа
-117 дней
Нет данных30 дней
Архив постов
4 553
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
" መሬቱ ነው፣ ዝናቡ አቁሮ ነው፣ ጎርፉ ወደ ፍሳሽ መውረጃ ስላልገባ ነው፣ የኔ ችግር አይደለም፣ የመንገዶች ባለስልጣን ችግር ነው፣ ብሎ ማሳበብ ምክንያት አይሆንም፤ ከተጠያቂነት ነጻ አያደርግም " - አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ
በክረምት ወቅት አሽከርካሪዎች መንገድ ላይ የተጠራቀመን የዝናብ ወይም የፍሳሽ ውሃ እግረኞች ላይ ረጭተው ሲያልፉ ማየት የተለመደ ነው።
ነገር ግን በኢፌዴሪ የወንጀል ህግ ከአንቀጽ 820 ጀምሮ እና በተከታዮቹ እንዲሁም የኢፌዴሪ ሚኒስትሮች ምክር ቤት ባወጣው የመንገድ የትራንስፖርት ደንብ ድርጊቱ በደንብ መተላለፍ ወንጀል ተቆጥሮ ከ3 ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት ወይም በገንዘብ መቀጮ እንደሚያስቀጣ ዓለም አቀፍ የህግ ባለሙያ እና ጠበቃ አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
የህግ ባለሙያው እና ጠበቃው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ ?
" አንድ አሽከርካሪ መንገድ ላይ እያሽከረከረ በሚሄድበት ወቅት የእግርኞችን ደህንነት በተጠበቀ ሁኔታ ማሽከርከር እንዳለበት የመንገድ ደህንነት፣ የስነ-ስርዓት ደንብ እና የፌደራል የወንጀል ህግ በግልጽ ይደነግጋል።
በአሽከርካሪዎች እንደዚህ አይነት ጉዳት የሚደርሰው በቸልተኝነት ነው። በእግርኛው ላይ ላደረሰው ጉዳት በደረቅ ወንጀል (ታስቦበት በተፈጸመ ከባድ ወንጀል) ሳይሆን በቸልተኝነት በፍጸመው የደንብ መተላለፍ ወንጀል ተጠያቂ ይሆናል።
እንደዚህ አይነት ወንጀል ሰርተው በፍርድ ቤት ክስ ቀርቦባቸው ጥፋተኛ ከተባሉ በደንብ መተላለፍ ወንጀሎች በመደበኛው የወንጀል ህግ ሶስት አመት በማይበልጥ ቀላል እሰራት ወይም በአማራጭ በገንዘብ መቀጮ ይቀጣሉ።
ይህ ሊሆን የሚችለው ግን ጉዳት የደረሰበት አካል የተሽከርካሪውን የሰሌዳ ቁጥር ይዞ ለፖሊስ አመልክቶ ከሆነ እና በአሽከርካሪው ቸልተኝነት ምክንያት የተጠራቀመው ውሃ በሰውየው ላይ ተረጭቶ እንዳበላሸው በምስክር ማረጋገጥ ሲችል ነው።
የዝናብ ውሃም ይሁን ሌላ ማንኛውም ፈሳሽ በተጠራቀመበት ቦታ ላይ አሽከርካሪው እግረኛውን ቀስ ብሎ ማሳለፍ እና በዝግታ ማሽከርከር ሲገባው ተሽከርካሪው በመጣበት ፍጥነት ግለሰቡን ረጭቶት ከሄደ ተጠያቂ ነው። እንደዚህ አይነት ነገሮች ሲፈጠሩ አሽከርካሪው በረጨበት አካባቢ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ማመልከት ይጠበቃል።
በኢፌዴሪ የወንጀል ህግ ከአንቀጽ 820 ጀምሮ እና በተከታዮቹ ደንብ መተላለፍን በተመለከተ የወጡ የወንጀል ተጠያቂነት ድንጋጌዎች አሉ።
ሌላው የኢፌዴሪ ሚኒስትሮች ምክር ቤት ባወጣው የመንገድ ትራንስፖርት ደንብ አሽከርካሪዎች የመንገድ ደህንነትን ባከበረ፣ በተጠበቀ ሁኔታ ማሽከርከር እንዳለባቸው እና በቸልተኝነት ለሚፈጽሙት ማንኛውም ወንጀል ተጠያቂ እንደሚሆኑ አስቀምጧል።
በተጨማሪም በስልክ እና በላፕቶፕ ላይ ጉዳት ካደረሰ በፍትሐ ብሔር ሁሉ መክሰስ ይቻላል። ግን ምስክሮች ያስፈልጋሉ። በቸልተኝነት ለደረሰ ጉዳት ካሳ የመጠየቅ መብት እንዳላቸው የፍትሐብሔር ህጉም በግልጽ አስቀምጧል።
በክረምት ወቅት በከፍተኛ የዝናብ መጠን አስፋልቶች ላይ ውሃ ሊከማች ይችላል፣ ውሃ የራሱ የፍሰት ስርዓት ስላለው በአንድ ጊዜ ወደ ፍሳሽ መውረጃ ላይ ላይገባ ይችላል። አሽከርካሪዎች በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ለእግርኞች ቅድሚያ የሰጠ፣ እግርኞችን ያከበረ እንቅስቃሴ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
በውሃ እና በመጸዳጃ ቤት ፍሳሽ እግረኛን ረጭተው ቢሄዱ በፈጸሙት የቸልተኝነት ጥፋት በህግ ይጠየቃሉ። የሞራል ኃላፊነትም እንዳለባቸው ማወቅ አለባቸው።
አሽከርካሪዎች ደረጃውን እና ምቾቱን በተጠበቀ ተሽከርካሪ ውስጥ ሆነው ሲሄዱ የእግርኛውን እንቅስቃሴ እና ሁኔታ ደግሞ ያከበረ፣ የጠበቀ እንቅስቃሴ የማድረግ ግዴታ አለባቸው።
' መሬቱ ነው፣ ዝናቡ አቁሮ ነው፣ ጎርፉ ወደ ፍሳሽ መውረጃ ስላልገባ ነው፣ የኔ ችግር አይደለም፣ የመንገዶች ባለስልጣን ችግር ነው ' ብሎ ማሳበብ ምክንያት አይሆንም፤ ከተጠያቂነት ነጻ አያደርግም።
እንደዚህ አይነት ጥፋት የሰራ ተሽከርካሪ የሰሌዳ ቁጥሩ እስከተያዘ ድረስ ተጠያቂ ነው።
አሽከርካሪው ድርጊቱን ቢክድ እንኳ ተጠያቂ ለማድረግ የተበደለው አካል የተሽከርካሪውን የሰሌዳ ቁጥር ይዞ ለፖሊስ ማመልከት እና ሁኔታውን በቅርበት ያየ የአይን ምስክር ማቅረብ ይኖርበታል።
ድርጊቱን የተመለከቱ ሰዎችም የምስክርነት ቃል መስጠታቸው ግለሰቡን እንደ መተባበር ሳይሆን የፍትህ ስርዓቱን እንደ ማገዝ የሚቆጠር በመሆኑ፣ ምስክርነታቸውን መስጠት አለባቸው።
አሽከርካሪዎች እንደዚህ አይነት ነገሮች በህግ ተጠያቂነትን እንደሚያመጡ አውቀው ህጉን አክብረው ሊንቀሳቀሱ ይገባል። "
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 553
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
#SaudiArabia
በሳዑዲ አረቢያ በቀጥታ የማኅበራዊ ሚዲያ (ቲክቶክ) ስርጭት ላይ የግድያ ወንጀል ፈጽሟል የተባለ ኢትዮጵያዊ ከአምስት ግብረ አበሮቹ ጋር በሳዑዲ የጸጥታ አካላት መያዛቸውን በሪያድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ።
ኤምባሲው እንዳለው፣ በሳዑዲ ድንበርና በረሃማ አካባቢዎች በአንዳንድ ኢትዮጵያውያን መካከል ግጭትና ግድያ መፈጸሙን ተከትሎ ጉዳዩ በቅርበት ሲከታተል ቆይቷል።
በተጨማሪም ጉዳዩን በማኅበራዊ ሚዲያ በማሰራጨትና በማራገብ ተጠርጥረው ከ100 በላይ ግለሰቦች መያዛቸውንና ጉዳያቸውም በሕግ እየታየ መሆኑን ኤምባሲው ገልጿል።
ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 553
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+2
በትግራይ እና ዓፋር ክልሎች አዋሳኝ አካባቢ ከ12 ሰዓታት በላይ የቆየ የደን ቃጠሎ ጉዳት አደረሰ።
ቃጠሎው ነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. በትግራይ ምሥራቃዊ ዞን፣ ፃዕዳ እምባ ወረዳ፣ ከዓፋር ክልል ዳሉል ወረዳ ጋር በሚዋሰነው የሐዊለ ቀበሌ አካባቢ መነሳቱን የዞኑ አስተዳደር አስታውቋል።
በእሳቱ 4.125 ሄክታር የሚገመት ደንና የግጦሽ ሳር መውደሙ ተገልጿል። በተለይም የገራህቲ ጥብቅ ደን በቃጠሎው ጉዳት ደርሶበታል።
የቃጠሎው መንስኤ እስካሁን ያልታወቀ ሲሆን፣ ምክንያቱን ለማጣራት ምርመራ መጀመሩ ታውቋል።
የትግራይ ክልል ምሥራቃዊ ዞን አስተዳደር እንዳስታወቀው በአካባቢው ነዋሪዎች ባህላዊ የእሳት ማጥፊያ ዘዴዎች በመጠቀም ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 5፡30 ላይ ቃጠሎው ሙሉ በሙሉ ማስቆም ተችሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 553
Got a Telegram channel with 2,000+ subscribers?
Then it’s time to stop posting for free.
With Ads Galaxy, you can monetize your Telegram channel and start earning from the audience you already have.
Your first $500 could be closer than you think.
Link: https://t.me/Ads_Galaxy_bot?start=REF770190998629F
Monetize now!
4 553
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
" በሕግ ክርክር ላይ ያለ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ የካሳ ጥያቄ አለበን " - ኢ/ር አሸብር ባልቻ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢ/ር አሸብር ባልቻ ተቋሙ የፕሮጀክቶችን ግንባታ ለማፋጠን በሚያደርገው እንቅስቃሴ ውስጥ የካሳ ክፍያ ጉዳይ ዋነኛውና አስቸጋሪው ማነቆ መሆኑን ገልጸዋል።
እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለጻ፣ ተቋሙ ለካሳ ክፍያ በቢሊዮን የሚቆጠር ብር እያወጣ የሚገኝ ሲሆን አሁንም ድረስ በሕግ ክርክር ላይ ያለ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ የካሳ ጥያቄ እንዳለበት ይፋ አድርገዋል።
ኢ/ር አሸብር በንግግራቸው ወቅት፣ ድሮ የተሰሩ ፕሮጀክቶች ሳይቀሩ አሁንም ድረስ ለተቋሙ ትልቅ የካሳ ክፍያ ጫና እና ችግር እየፈጠሩ መሆኑን ጠቁመዋል።
በተለይም ካለአግባብ በተለያዩ ክፍሎች የሚሰጡ የድጋፍ ደብዳቤዎች እና የሀሰት መረጃዎች ተቋሙን ላልተገባ የካሳ ክፍያ እያጋለጡት መሆኑን ገልጸዋል።
ዋና ሥራ አስፈፃሚው “ካለአግባብ በየክፍሉ የሚሰጡባቸው ድጋፍና የሀሰት መረጃዎች ላልተገባ የካሳ ክፍያ እንድንጋለጥ ያደረጉት ሁኔታ አለ” ብለዋል።
ከአዲሱ የካሳ አዋጅ ጋር ተያይዞ ያሉ ክፍተቶችንም ሲያስረዱ ደግሞ "አዲሱ አዋጅ ክልሎች ለልማት የሚነሱ ሰዎችን የካሳ ክፍያ ራሳቸው እንዲችሉ የሚደነግግ ቢሆንም፣ የአፈጻጸም መመሪያው ባለመውጣቱ ምክንያት ክልሎች ይህንን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት አልጀመሩም" ነው ያሉት።
ይህ መመሪያ አለመኖሩ ደግሞ ተቋሙ ለሚጀምራቸው አዳዲስ ፕሮጀክቶች ተጨማሪ ማነቆ እየሆነበት እንደሚገኝ ኢ/ር አሸብር ጠቁመዋል።
የካሳ ክፍያ አሠራሩና አዲሱ አዋጅ ወደ መሬት ወርዶ ተግባራዊ ባለመሆኑ ምክንያት የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ፕሮጀክቶች በታቀደላቸው ጊዜ እንዳይጠናቀቁ እንቅፋት እየሆነባቸው እንደሚገኝ ተገልጿል።
ኢ/ር አሸብር ባልቻ አክለውም “አዲሱ የካሳ ክፍያ አዋጅ የሚያሰራ አይደለም፤ ይልቁንም የበለጠ ማነቆ እየፈጠረ ነው” በማለት ተቋሙን ለተደራራቢ የካሳ ክፍያ የዳረገውን ችግር አመልክተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
4 553
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
#France
#Paris
በፈረንሳይ፣ ፓሪስ ከተማ " የግብረሰዶማውያን ማህበር ፕሬዚዳንት " እንደሆነ የተነገረለት እና እራሱም የፖሊስ መኮንን የሆነው ፒየር ፒካቬት የተባለ ግለሰብ በጠርሙስ ተቀጥቅጦ ጉዳት ደርሶበት ሆስፒታል መግባቱን ከፍራንስ 24 ዘገባ ተመልክተናል።
ፒካቬት በፓሪስ መሃል በሚገኘው ማራይስ አካባቢ ከአንድ ባር ከወጣ በኋላ በአንድ ግለሰብ በጠርሙስ መቀጥቀጡ ተገልጿል።
ጥቃቱ በሰውነቱ ላይ በርካታ ጉዳቶችን እንዲደርስበት ያደረገ ሲሆን የውስጥ ደም መፍሰስና የጭንቅላት ቁስልም እንደደረሰበት ተዘግቧል።
ፓሪስ ውስጥ የግብረሰዶማውያን መብት ተሟጋች ማህበር ፕሬዝዳንት የሆነው ፒካቬት እራሱን የፖሊስ መኮንን መሆኑን በመግለጽ የፖሊስ መታወቂያውን ቢያሳይም፣ ተጠርጣሪው ጥቃቱን እንዳላቆመ ተመላክቷል።
በጥቃቱ ወቅትም ጥቃት አድራሹ " አጸያፊ ነው " ስላለው የግብረሰዶማዊነት ተግባር በስድብና በኃይለ ቃል ግለሰቡን ሲናገረው እንደነበር ተመላክቷል።
ተጠርጣሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን ከዚህ በፊት የወንጀል መዝገብ እንደሌለው ተገልጿል።
የፓሪስ ከንቲባ ኤማኑኤል ግሬጎዋር ጥቃቱን አውግዘዋል። " ፓሪስ ለሁሉም ሰዎች የነፃነትና የደህንነት ከተማ ሆና ትቀጥላለች " ሲሉ መናገራቸው ነው የተሰማው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 553
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ውጤት ይፋ ተደርጓል።
ተማሪዎች https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት Remedial Examination ከሚለው ስር View Results የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤታቸውን በመመልከት ላይ ይገኛሉ።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ " ሙሉ ውጤታችን Disqualified ተደርጓል " ያሉ በርካታ ተማሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ አቅርበዋል።
ተማሪዎቹ " ይፋ በተደረገው የፈተና ውጤት ላይ የገጠመን ከፍተኛ ችግር እንዲሰማልን እንፈልጋለን " ብለዋል።
ቅሬታቸውን ካቀረቡት መካከል በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳንይንስ ተማሪዎች ውጤታቸው " ሙሉ በሙሉ Disqualified " የተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ፥ በደብረ ብርሃን፣ ወሎ፣ አርባ ምንጭ፣ ሚዛን ቴፒ፣ ሰመራ፣ ባህርዳር፣ ወልቂጤ፣ ኦዳ ቡልቱም፣ ጎንደር ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ የተለያዩ ተማሪዎች ውጤት ላይ ተመሳሳይ ችግር እንደገጠማቸው አመልክተዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ቅሬታቸውን ተመልክቶ ምክንያቱን በመለየትና በማሳወቅ እንዲሁም በመመርመር አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም የተሰጠውን ሀገር አቀፍ የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና 53,620 ተፈታኞች መውሰዳቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 553
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
ግምታዊ ዋጋቸው ከ300 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሆኑ ከ4,500 በላይ የሚሆኑ የከባድ ጭነትና የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካዎች በጂቡቲ ወደብ ከ8 ወራት በላይ ቆመው ይገኛሉ።
አስመጪዎቹ፣ ተሽከርካሪዎቹን ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት የገንዘብ ሚኒሰቴርንና የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴርን ይሁንታን ባለማግኘታቸው ለከፍተኛ ኪሳራ እየተዳረጉ መሆኑን ጠቁመው ጠ/ሚ ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) መፍትሔ እንዲሰጧቸው ጥያቄ ማቅረባቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።
ተሽከርካሪዎቹ በጂቡቲ የቆሙበት ምክንያት ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጋዝ ማምረት በመጀመሯ ምክንያት ከመስከረም 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ፣ በቤንዚንና በናፍጣ የሚሠሩ የጭነትና የሕዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪዎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ፣ የገንዘብ ሚኒሰቴር ባስተላለፈው መመሪያው ምክንያት ነው።
ከመቶ በላይ የሚሆኑ አስመጪ ነጋዴዎች፥ ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒሰቴር በተሰጣቸው ተሸከርካሪዎችን የማስገቢያ ፈቃድ መሠረት "በነዳጅና ናፍጣ" የሚሠሩ ተሸከርካዎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ ከመከልከሉ በፊት ግዥ ከሚፈጽሙባቸው ተሸከርካሪዎችን አምራች አገሮች ግዥ ፈጽመው ያስጫኑ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
ገንዘብ ሚኒስቴር ተሸከርካሪዎች እንዳይገቡ በጻፈው ደብዳቤ (መመሪያ) በግዥ ሒደት ላይ ያሉና ግዥያቸው ተጠናቆ የተጫኑ ተሽከርካሪዎች እስከ 6 ወራት ድረስ ክልከላው ሳይመለከታቸው እንዲገቡ መፍቀዱን ሰነዶቹ ያስረዳሉ፡፡
አስመጪዎቹ ገንዘብ ሚኒስቴር መመሪያ ከማስተላለፉ በፊት በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ የማስገቢያ ፈቃድ አግኝተው ኤልሲ (LC) በመክፈት ከአምራች አገሮች ጋር የግዥ ውል ፈጽመው ተሸከርካሪዎቹ እንዲጫኑ በማዘዝ፣ አንዳንዶቹ ቀረጥና ታክስ ጭምር በመክፈል ተሸከርካሪዎቹን ወደ አገር ውሰጥ የማሰገባት ሂደት አስጀምረው እንደነበር ለጠ/ሚኒሰትሩ ባቀረቡት የአቤቱታ ደብዳቤ ላይ ገልጸዋል፡፡
ተሸከርካሪዎቹን ከወደብ ማንሳት ያልተቻለው በአንድ በኩል የአፈጻጸምና የማጣራት ሂደት ጊዜ በመውሰዱ ተያያዥ በሆኑ አስተዳደራዊ ክፍተቶች ምክንያት በተፈጠረው ችግር ምክንያት መሆኑን አሰረድተዋል።
አስመጪዎቹ፥ በሕጋዊ አሠራር ሂደት አልሲ (LC) በመክፈትና የባንክ የክፍያ ሥርዓት ለውጭ አቅራቢዎችና አምራቾች የተላለፈ በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር የውጭ ምንዛሪ የተከፈለባቸው ከ4,500 በላይ ከባድ የጭነትና የሕዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪዎች በጂቡቲ ወደብ ቆመው ፦
1. በቀን ከ90,000 ዶላር ላይ ዲሜሬጅ እየተከፈለባቸው መሆኑን፤
2. በየቀኑ ከሚከፈለው የውጭ ምንዛሪ በተጨማሪ፣ ተሸከርካሪዎቹ በጂቡቲ ባለው ከፍተኛ ሙቀትና ጨው ከፍተኛ የቴክኒክና አካላዊ ጉዳት እየደረሰባቸው መሆኑ፤
3. የዴሜሬጅ ክፍያ ባለመከፈሉ የጂቡቲ መንግሥት ተሸከርካሪዎቹን በጨረታ የመሸጥ አደጋ እንደተጋረጠባቸው፤
4. ተሸከርካሪዎቹን ለመግዛት ከተለያዩ ባንኮች ለወስዱት የውጭ ምንዛሪ በዋስትና ያስያዙት ንብረት (ኮላተራል) በሐራጅ የመሸጥ አደጋ እየደረሰባቸው መሆኑን፣
5. በብሔራዊ ባንክ በForeign Exchange Delinquent List ውስጥ የመመዝገብ አደጋ እያጋጠማቸው መሆኑን፤
...በመጠቆም ጠቅላይ ሚኒሰትሩ መፍትሄ እንዲሰጧቸው ተማጽነዋል፡፡
መንግሥት ተሽከርካሪዎቹ ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡ ቢያደርግ፣ ከታክስና ቀረጥ (ባለፉት ወራቶች) ከ1.8 ቢሊዮን ብር በላይ ያገኝ የነበረውን ገቢ ማጣቱን በጉምሩክ ኮሚሽን በተጣራ መረጀ መረጋገጡን አክለዋል።
ከተሽከርካሪዎቹ ጋር በተያያዘ ጉምሩክ ኮሚሽንም በጂቡቲና በአገር ውስጥ ስለቆሙት ተሸከርካሪዎች በሚመለከት ግንቦት 11/2018 ዓ.ም. ለገንዘብ ሚኒስቴር ደብዳቤ ፅፎ ነበር።
በቤንዚንና ናፍጣ የሚሠሩ የጭነትና የሕዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪዎች፣ ከመስከረም 30 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እንዳይገቡ መከልከሉን፣ ቀደም ብሎ በሂደት ላይ የነበሩትንና በተፈቀደው 6 ወራት ውስጥ ጂቡቲ ደርሰው የቆሙ ተሸከርካዎችን በሚመለከት መፍትሔ እንዲሰጠው ጠይቋል።
ኮሚሽኑ ከባድ የጭነትና የሕዝብ ማመላለሻ አስመጪዎች ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒሰቴር የማስገቢያ ፈቃድ እንደተሰጣቸው በደብዳቤው አረጋግጧል፡፡
ግዥ የፈጸሙ፣ ቀረጥና ታክስ የከፈሉና ትራዚት የተፈቀደላቸው፤ ማስገቢያ ፈቃድ ተሰጥቷቸው ዲክላራሲዮን ያልቀረበባቸው መኖራቸውን፣ እንዲሁም አገር ውስጥ ገብተው በጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች በኩል የማስገቢያ ፈቃዶች ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር በኩል ተጣርተው እንዲላኩ በተደጋጋሚ ቢጠይቅም ምላሽ ማግኘት እንዳልቻለ ገልጿል፡፡
ተሸከርካሪዎቹ በጂቡቲ ፍሪ ዞን ለረዥም ጊዜ በመቆየታቸው፣ ከፍተኛ የዲሜሬጅ ክፍያ እየተጠየቀባቸው መሆኑንና ወደ አገር ውሰጥ ማምጣት ካልተቻለ የጂቡቲ መንግሥት በጨረታ እንደሚሸጣቸው ማሰጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው አስመጪዎች እንደነገሩት ኮሚሽኑ አረጋግጧል፡፡
በመሆኑም ተሽከርካሪዎቹ ወደ አገር ውስጥ ገብተው በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር በኩል ማረጋገጫ እስከሚሰጣቸው ድረስ በጉምሩክ ቁጥጥር ሥር እንዲቆዩ አስመጪዎች መጠየቃቸውን ኮሚሽኑ ለገንዘብ ሚኒስቴር በጻፈው ደበዳቤ አስታውቋል።
በጂቡቲ ከቆሙት ተሸከርካሪዎች ውስጥ አብዛኛዎቹ ቀረጥና ታክስ የተከፈለባቸው መሆኑን፣ አገር ውስጥ ገብተው ያለተለቀቁትና ከሌሎች ተመሳሳይ ተሽከርካሪዎች መንግሥት ከ1.8 ሚሊዮን ብር በላይ ከቀረጥና ታክስ ሊሰበስብ እንደሚችል ኮሚሽኑ አረጋግጦ፣ በተሰጣቸው የማስገቢያ ፈቃድ መሠረት የጉምሩክ ሥነ ሥርዓት ተፈጽሞባቸው ወደ አገር ውሰጥ እንዲገቡ ውሳኔ እንዲሰጥበት ገንዘብ ሚኒስቴርን የጠየቀ ቢሆንም ምላሽ አላገኘም።
ጉምሩክ ኮሚሽን ነሐሴ 2/2018 ዓ.ም. በድጋሚ ለገንዘብ ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ፣ ቀደም ብሎ በግንቦት ወር የተጻፈውን ደብዳቤ አስታውሶ፣ አስመጪዎቹ ከተለያዩ ንግድ ባንኮች የባንክ ፈቃድ አግኝተው የትራንዚት ፈቃድ ያላቸውና የሌላቸው መሆናቸውን ጠቁሞ፤ አገር ውስጥ ያለገቡ በነዳጅ የሚሠሩ፦
- ከባድ የጭነትና የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶች፣
- በአገር ውስጥ ለመገጣጠም ተገዝተው አገር ውስጥ ያልገቡ (CKD እና SKD) ተሸከርካሪዎች፣
- በመልቲ ሞዳል ሥርዓት ተጓጉዘው በአገር ውስጥ ባሉ የተለያዩ ደረቅ ወደቦች ውስጥ የሚገኙ ተሸከርካሪዎችን ማስተናገድ ስለሚቻልበት ሁኔታ ውሳኔ አንዲሰጠው ጠይቋል።
አስመጪዎቹም በተደጋጋሚ ገንዘብ ሚኒስቴርን ተመላልሰው በአካልና በደብዳቤ ቢጠይቁትም፣ አንድ ጊዜ የሚመለከተው ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴርን መሆኑንና እሱን እንደማይመለከተው በመግለጽ ሌላ ጊዜ ደግሞ ጉዳያቸው የሚፈታው በጠ/ሚ ጽ/ቤት በኩል እንደሆነ ከመግለጽ ባለፈ መፍትሔ የሚሰጣቸው በማጣታቸው ጠ/ሚ ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) መፍትሄ እንዲሰጧቸው ጠይቀዋል።
አስመጪዎቹ ከባንኮች ለወሰዱት ብድር ያስያዟቸው ንብረቶች ለጨረታ ሊቀርቡ እንደሚችሉና በስራቸው ያሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ሠራተኞችም ሥራ ሊያጡ እንደሚችሉ በማመልከት የማስገቢያ ጊዜው እንዲራዘምና ተሽከርካሪዎቹ ወደ ኢትዮጵያ ገብተው በጉምሩክ ኮሚሽን ቁጥጥር ስር እንዲሆኑ ጠይቀዋል።
በተጨማሪም፣ የኢትዮጵየ ብሔራዊ ባንክ በ " Foreign Exchange Delinquent List " እንዳያስገባቸው እንዲያርጉላቸው ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ን ተማጽነዋል።
ከተቻለ በአካል ቀርበው በተሟላ ማስረጃ በአጭሩ እንዲያስረዷቸውና እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
ነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 553
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+4
" በድርቁ ምክንያት በደረሰባቸው ከፍተኛ የኑሮ ጫና እና የተስፋ መቁረጥ ስሜት ሰባት ወንዶች በአንድ ቀን መርዝ ጠጥተው ራሳቸውን ለማጥፋት ሙከራ አድርገው የሁለቱ ህይወት አልፏል " - ጃን አሞራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት
• ከ4 ሺህ በላይ ነፍሰጡርና አጥቢ እናቶች ለምግብ እጥረት ተጋልጠዋል።
• ከ3 ሺህ በላይ እንስሳት በመኖ እና በውሃ እጥረት ምክንያት ሞተዋል።
(ቲክቫህ ኢትዮጵያ)
በሰሜን ጎንደር ዞን በጃና ሞራ ወረዳ የተከሰተው አስከፊ ድርቅ በአካባቢው ማህበረሰብ ላይ መጠነ ሰፊ ሰብአዊ ቀውስ እያስከተለ እንደሚገኝ ተገልጿል።
በወረዳው ስር ከሚገኙ 38 ቀበሌዎች መካከል 18ቱ በድርቅ የተጎዱ ሲሆን፣ በዚህም ምክንያት ከ96 ሺህ በላይ ሰዎች ለከፋ የምግብ እና የውሃ እጥረት መጋለጣቸውን የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሷሊህ ሃሰን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
በአካባቢው የተከሰተው የዝናብ እጥረት ለችግሩ ዋነኛ መንስኤ መሆኑን ሃላፊው አመልክተዋል።
በአካባቢው በተለምዶ በግንቦት ወር መጀመር የነበረበት ዝናብ እስከ ሃምሌ 19 ቀን ድረስ በመዘግየቱ አርሶ አደሩ ሰብሉን በወቅቱ ለመዝራት አልቻለም።
በወረዳው ካሉ አጠቃላይ 38 ቀበሌዎች ውስጥ 5ቱ ለመጀመርያ ጊዜ ዝናብ ያገኙት ሐምሌ 19 ቀን ሲሆን ክረምት ከገባ 4 ቀን ብቻ ዝናብ ያገኙ 5 ቀበሌዎችም ስለመኖራቸው ጠቁመዋል።
ከተዘራው 25 ሺ ሄክታር በላይ መሬት ውስጥም ከ8 ሺህ 1 መቶ ሄክታር በላይ የሚሆነው ጭራሽ ሳይበቅል የቀረ ሲሆን፣ በተለይም የጤፍ ሰብል ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ መውደሙን ታውቋል ይህም በአካባቢው ከፍተኛ የምግብ ዋስትና እክል መፍጠሩ ተገልጿል።
ተዘርቶ ከበቀለው ሰብልም 4 ሺ ሄክታር የሚሆነው የጠወለገ ነው ያሉ ሲሆን በአጠቃላይ ወረዳው ካለው 26 ሺ 659 ሄክታር የእርሻ መሬት ላይ የበቀለው 12 ሺ 126 ሄክታር የሚሆነው ማሳ የተጎዳ መሆኑን እና ምናልባት ለዘር እና ለመኖ ካልሆነ በቀር ለምግብነት በማይሆን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ይህ የድርቅ አደጋ በሰው ህይወትና በስነ-ልቦና ላይ እያደረሰ ያለው ጉዳት እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱንም አቶ ሷሊህ ነግረውናል።
በወረዳው ከሚገኙ ቀበሌዎች አንዱ በሆነው በዋሰል ቀበሌ ውስጥ በድርቁ ምክንያት በደረሰባቸው ከፍተኛ የኑሮ ጫና እና የተስፋ መቁረጥ ስሜት ሰባት ወንዶች በአንድ ቀን ውስጥ መርዝ ጠጥተው ራሳቸውን ለማጥፋት ሙከራ ማድረጋቸው ተሰምቷል።
ከእነዚህም መካከል የሁለቱ ህይወት ወዲያውኑ ሲያልፍ፣ አምስቱ በህክምና እርዳታ መተርፋቸውን የጽ/ቤቱ ሃላፊ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ከምግብ እጥረት ጋር ተያይዞም በአሁኑ ወቅት 71 ህጻናት በከፍተኛ የምግብ እጥረት፣ 5029 ህጻናት ደግሞ በመካከለኛ ደረጃ የምግብ እጥረት ላይ ይገኛሉ።
በተጨማሪም ከ4 ሺህ በላይ ነፍሰጡርና አጥቢ እናቶች ለተመሳሳይ ችግር ተጋልጠዋል።
የወንዞች ፍሰት ከ90 በመቶ በላይ በመቀነሱ፣ ህዝቡ ቆሻሻ ውሃ ለመጠጣት ተገዷል። በዚህም ምክንያት እንደ እከክ፣ ወባ እና የደም ተቅማጥ ያሉ ተላላፊ በሽታዎች በወረዳው በስፋት እየተከሰቱ መሆኑ ተመላክቷል።
እስካሁን ባለው መረጃ ከ3 ሺህ በላይ እንስሳት በመኖ እና በውሃ እጥረት ምክንያት የሞቱ ሲሆን፣ ቁጥራቸው ወደ 4 ሺህ የሚጠጉ እንስሳት ደግሞ የተሻለ ሳርና ውሃ ፍለጋ ወደ ጎረቤት አካባቢዎች ተሰደዋል።
በተጨማሪም የአባ ሰንጋ (Anthrax) በሽታ በአካባቢው መከሰቱ የታወቀ ቢሆንም፣ ወረዳው ላይ ምንም አይነት የመድሃኒት ክምችት ባለመኖሩ እና በክልል ደረጃም መድሃኒት ጠፍቶ በገንዘብ ለመግዛት ባለመቻሉ የእንስሳቱ እልቂት ሊባባስ እንደሚችል ስጋት ተፈጥሯል።
እስካሁን ድረስ የመንግስትም ሆነ የሌሎች ተራድኦ ድርጅቶች ድጋፍ በቂ አለመሆኑን የገለጹት አቶ ሷሊህ፣ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በሁለት ቀበሌዎች ላይ ጥናት መጀመሩን ጠቅሰዋል።
ይሁን እንጂ ችግሩ ካለው ስፋትና ጥልቀት አንጻር አፋጣኝ የምግብ፣ የመድሃኒት እና የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ካልተመቻቸ ሁኔታው ወደማይመለስ ጥፋት ሊያመራ እንደሚችል በማሳሰብ፣ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ አስቸኳይ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 24 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 553
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
የገቢዎች ሚኒስቴር የኤክሳይዝ ታክስ ከፋይ የሆኑ የማምረቻ ተቋማት፣ በተለይም የቢራና የታሸጉ መጠጦች ፋብሪካዎች ውስጥ ከፍተኛ ጥራት ያላቸው የክትትል ካሜራዎችን መግጠም መጀመሩ ካፒታል ጋዜጣ ዘገበ።
እንደ ጋዜጣው ዘገባ መንግሥት ለዲጂታል የክትትል ሥርዓቱ ወደ 300 ሚሊዮን ብር የሚገመት በጀት መድቧል።
ካሜራዎቹ የምርት መስመሮችን፣ የማሸጊያ ክፍሎችን፣ መጋዘኖችን፣ የጭነት መውጫዎችንና የምርት መጓጓዣን በቅጽበት ለመከታተል እንደሚውሉ ተገልጿል።
ሥርዓቱም የፋብሪካዎች ትክክለኛ ምርት ከሚያሳውቁት የምርት መጠን ጋር ያለውን ልዩነት በመቆጣጠር የግብር ማምለጫን ለመቀነስ ያለመ ነው።
በመመሪያዎቹ መሠረት አልኮል፣ ቢራ፣ ወይን፣ የታሸገ ውሃ፣ ትምባሆ፣ ሽቶ እና ጣፋጭ ወይም ካርቦኔትድ መጠጦችን ጨምሮ ኤክሳይዝ ታክስ የሚጣልባቸው ምርቶች በዲጂታል ኮድ ወይም በኤክሳይዝ ማህተም እንዲለዩ ይደረጋል።
በተጨማሪም ፋብሪካዎች የምርት እና የማጓጓዣ ሂደታቸውን በርቀት ለመከታተል የሚያስችሉ የቴክኖሎጂ ሥርዓቶችን በራሳቸው ወጪ እንዲያስገቡ መመሪያ መኖሩ ተጠቅሷል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የካፒታል ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
4 553
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
ማይጨው ከተማ ሙሉ በሙሉ ከኤሌክትሪክ አገልግሎት ውጪ ሆነች።
ከተማዋ ከዛሬ እሁድ ነሐሴ 24/2018 ዓ.ም ከቀኑ 5፡30 ጀምሮ ነው ሙሉ በሙሉ ከኤሌክትሪክ አገልግሎት ውጪ የሆነችው።
የኤሌክትሪክ መቋረጡ ወደ ከተማዋ ኤሌክትሪክ የሚያስተላልፉ ስድስት የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ታዎሮች በመውደቃቸው መሆኑን የማይጨው ከተማ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
ታዎሮቹ በተፈጥሮ አደጋ መውደቃቸውን የገለጸው ጽህፈት ቤቱ፣ አደጋው በደቡባዊ ዞኑ ራያ ዓዘቦ ወረዳ፣ ካራ-ዓዲሻዎ ቀበሌ በሚገኝ አካባቢ መከሰቱን ጠቁሟል።
በተመሳሳይ፣ የማይጨው ከተማና አካባቢዋ የመብራት ኃይል ቅርንጫፍ አገልግሎት ታዎሮቹ የወደቁት ንፋስ የቀላቀለ ኃይለኛ ዝናብ ባስከተለው አደጋ መሆኑን ገልጿል።
የተበላሹትን ታውሮች በአስቸኳይ ለመጠገን ርብርብ እየተደረገ ቢሆንም የጥገና ሥራው ቀናት ሊወስድ እንደሚችል የአገልግሎት መስጫ ማዕከሉ አስታውቋል።
በመሆኑም ህዝቡ ጥገናው እስኪጠናቀቅ በትዕግስት እንዲጠብቅ ጥሪ ቀርቧል።
እሁድ ነሐሴ 24/2018 ዓ.ም የክረምት ዝናብ በበቂ ሁኔታ ያላገኙ በርካታ አካባቢዎች ዝናብ ማግኘታቸውም ታውቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 24 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 553
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ከጣሊያን አበዳሪ ተቋማት ጋር 400 ሚሊየን ዶላር የንግድ ብድር ለመበደር ድርድር ላይ መሆኑን ገልጿል።
• ድርድሩ እየተካሄደ ያለው ኢትዮጵያ ለኮይሻ ፕሮጀክት ብቻ በልዩ ሁኔታ የንግድ ብድር እንድትወስድ የአለም የገንዘብ ድርጅት(IMF) ፈቃድ መስጠቱን ተከትሎ ነው።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምና በ2019 ዋና ዋና እቅዶች ዙሪያ በሰጠው ማብራሪያ በአሁኑ ሰዓት እየተገነቡ ከሚገኙ ግዙፍ ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነው ኮይሻ ግድብን በሚመለከት ማብራሪያ ሰጥቷል።
እንደ ተቋሙ ገለጻ፣ የኮይሻ ግድብ ግንባታ አሁን ላይ 77 በመቶ ደርሷል።
የተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢ/ር አሸብር ባልቻ በሰጡት ማብራሪያ ፕሮጀክቱ ከፍተኛ የፋይናንስ ችግር ቢያጋጥመውም መንግስት ባደረገው ድጋፍና ተቋሙ ራሱ ባገኘው ገቢ አማካኝነት ፕሮጀክቱ እንዲቀጥልና ውጤታማ እንዲሆን ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።
ለ2019 በጀት ዓመት ደግሞ የግንባታ አፈጻጸሙን ከ77 በመቶ ወደ 87 በመቶ ማድረስ፣ የግድቡን ከፍታ 201 ሜትር ማድረስና ግድቡን ራሱን ሙሉ በሙሉ ማጠናቀቅ ማቀዳቸውን አስታውቀዋል።
ይሁን እንጂ ኃይል የሚያመነጨው ተርባይን ለኃይል ማመንጨት ዝግጁ ባይሆንም ግድቡ ራሱ እንዲጠናቀቅ ማድረግ ላይ ትኩረት መደረጉን አስረድተዋል።
ነገር ግን ኮይሻ ላይ አሁንም ድረስ ከፍተኛ የፋይናንስ እጥረት መኖሩን ሃላፊው አረጋግጠዋል።
እንደ ኢ/ር አሸብር ባልቻ ገለጻ "ኮይሻ ላይ አሁንም የበጀት ክፍተት አለብን" ብለው፣ የፕሮጀክቱ ጠቅላላ ወጪ ወደ 3 ቢሊዮን ዩሮ የሚጠጋ ሲሆን፣ ይህም ምንም ዓይነት ኃይል ገና ሳያመነጭ የሚፈለግ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ መሆኑን አብራርተዋል።
ይህንን የፋይናንስ ክፍተት ለመሙላት የአለም የገንዘብ ድርጅት(IMF) ለኮይሻ ፕሮጀክት ብቻ በልዩ ሁኔታ የንግድ ብድር (Commercial Loan) እንዲበደር ፈቃድ መስጠቱን ጠቁመው፣ ተቋሙ ከጣሊያን አበዳሪ ተቋማት ጋር ድርድር ላይ መሆኑን ገልጸዋል።
በቅርቡ በተደረገው ድርድር የጣሊያን አበዳሪ ተቋማት ወደ 400 ሚሊዮን ዩሮ ለማበደር ፈቃደኝነታቸውን ማሳየታቸውን ገልጸው፣ ጠቅላላ ወደ 500 ሚሊዮን ዩሮ በላይ ከሚያስፈልገው ወጪ ውስጥ 400 ሚሊዮኑ ከጣሊያን ባንኮች ከተገኘ በኋላ ቀሪውን ተቋሙ በራሱ አቅም በመሸፈን ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ ማቀዳቸውን አስረድተዋል።
ፕሮጀክቱ ኦርጅናል ውል ሲፈረም በሰባት ዓመት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ቢታቀድም፣ ከዚያ ጊዜ ገደብ አልፎ ሁለት እና ሶስት ዓመታት እንደተጨመሩበት ተገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ነሐሴ 24 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 553
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
320 ነጥብ ያመጡት ቄስ ሰይፉ ተስፋይ !
" ትምህርት ፍላጎትና ተነሳሽነት ካለ ዕድሜ አይገድበውም " የሚለውን እውነታ በተግባር ያሳዩት ቄስ ሰይፉ ተስፋይ፣ በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና 320 ነጥብ በማምጣት ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት ከሚጠባበቁ ተፈታኞች መካከል ተጠቃሽ ሆነዋል።
ቄስ ሰይፉ ተስፋይ በትግራይ ክልል፣ ደቡባዊ ዞን፣ ሰለዋ ወረዳ፣ ደጀን ቀበሌ፣ ግራዛፎ መንደር ነዋሪ ናቸው።
የ66 ዕድሜ ባለፀጋው ቄስ ሰይፉ፣ በሰለዋ ከተማ በሚገኘው የአንበሳ ባንክ የጥበቃ ሠራተኛ በመሆን እየሰሩ ነው። ከሥራቸው ጎን ለጎን ግን ትምህርታቸውን በመቀጠል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ለመፈተን ችለዋል።
በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በትግራይ ክልል ፈተናቸውን ከወሰዱ 29 ሺህ ተፈታኞች መካከል ቄስ ሰይፉም አንዱ ሲሆኑ፣ 320 ነጥብ በማምጣት የማለፊያ ውጤት ካመጡ 3,146 ተፈታኞች መካከል አንዱ ናቸው።
የቄስ ሰይፉ ውጤት በማህበራዊ ሚዲያ ትኩረት ያገኘ ሲሆን የሚሰሩበት ባንክም በተሳካላቸው ውጤት በመደሰት ሽልማት አበርክቶላቸዋል።
የቄስ ሰይፉ ታሪክ ትምህርት ለመማር ዕድሜ፣ ሥራ ወይም ሌላ ሁኔታ እንቅፋት እንዳልሆነ፣ ፍላጎትና ተነሳሽነት ካለ ሰው የፈለገውን ግብ ለማሳካት እንደሚችል ያሳያል።
ቄስ ሰይፉ ባለትዳርና የ6 ልጆች አባት ናቸው።
ነሐሴ 23 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 553
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
በካማሽ ዞን የሰዎችን ህይወት እስከመንጠቅ ተደጋጋሚ የታጣቂዎችን ጥቃት ሲያስተናግድ በቆዬ ቦታ ሰሞኑንም የከፋ ጥቃት መፈጸሙ ተገለጸ።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሽ ዞን ምዥጋ ወረዳ "አንገር ሜጢ" ወይም "አይሻንጅድም" በተባለ ቀበሌ ላይ የታጠቁ ኃይሎች ባደረሱት ጥቃት፣ በሰዎች ላይ ጉዳት መደረሱን፣ በርካቶች መፈናቀላቸውን፣ በቤትና ንብረት ላይ አስከፊ ውድመት መድረሱን ነዋሪዎችና የክልሉ ምክር ቤት አባል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የካማሽ ዞን የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን አመራር ጥቃቱ መፈጸሙን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል። የክልሉ ም/ቤት አባል አቶ ለሜሳ ኔኖ፣ "ሁለት ሰዎች ተገድለዋል። በርካታ ቤቶች ተቃጥለዋል" ብለዋል።
በፊትም "የሸኔ ታጣቂ ቡድን ተደጋጋሚ ጥቃት ፈጽሞበት በነበረው አንገር ሚጤ ቀበሌ ሰሞኑንም በርካታ ቤቶች አቃጥሎ አውድሟል። የቁም ከብቶችም ዘርፎ ነዋሪዎቹ ወደ ጫካ ተበታትነው በሕይወት መኖራቸው አስጊ ላይ ነው" ሲሉም ገልጸዋል።
በአካባቢው ከሁለት ቀናት በፊት የተኩስ ሩምታ እንደነበር ገልጸው፣ "ቤት ብቻ ሳይሆን ከቤት ውስጥ የነበረ የእህል ማከቻ ጎተራ ጭምር ነው ያወደሙት። ጥቃቱ ሲፈጸም ዘንድሮ ብቻ የአሁኑ ለሦስተኛ ጊዜ ነው በማለት ጥቃቱ መደጋገሙን አስረድተዋል።
ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ?
አንድ ነዋሪ በሰጡን ቃል፣ ከአምስት ሺህ በላይ ነዋሪዎች ተፈናቅለዋል፣ ከ1 ሺሕ በላይ ቤቶች ተቃጥለዋል ተብሎ እንደሚገመት ገልጸዋል። በመቶዎች ኩንታል የሚገመት እህል መቃጠሉን፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ከብቶች ተነድተው መወሰዳቸውንም ተናግረዋል።
ሌላኛው የዓይን እማኝ ነዋሪ፣ "አይሻንጅድም ቀበሌ ላይ ትልቅ ችግር ነው የተፈጠረው እኔም እዛው ነበርኩ። ጥቃቱ ቦታው ላይ ተደጋጋሚ ሆኗል፤ አሁን ለሦስተኛ ጊዜ ነው የተፈጸመው፤ ታጣቂዎቹ ከተማ ላይ ገቡ፤ ከዚያ በኋላ ቤት ማቃጠል ጀመሩ፤ ህዝቡም በየጫካ ነው የተበተነው" ሲሉ ነግረውናል።
ነዋሪዎቹ የት እንደደረሱ እየተፈለገ መሆኑን በማስረዳት፤ "በህይወት የት አካባቢ እንዳሉ እንኳ አይታቅም" ያሉት ነዋሪው፣ "ይህን ድርጊት የፈጸመው የተቀናጄ ኃይል ነው፤ 'ገዳ ኮማንዶ' የሚባልም አለበት፣ 'ኦነግ ሸኔ'ም አለበት" ብለዋል።
ተጎጂዎችም እንዳሉ ገልጸው፣ "የጠፉትን ለመፈለግም ተቸግረናል። የሚመለከተው አካል ይድረስልን። ቤቶችን በነዳጅ ነው ያቃጠሏቸው። የተቀመጡ ምርቶ ተቃጥለዋል" ሲሉ ተናግረዋል።
ሌላኛው ነዋሪ፣ መንግስት "ሸኔ" ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን በዚሁ ቀበሌ፣ ጥቃት መፈጸሙን ገልጸው፣ "ፍላጎቱ ምን እንደሆነ ባናውቅም፤ ጥቃቱ ዘንድሮ ብቻ አሁን ለሦስተኛ ጊዜ ነው የተፈጸመው። የአሁኑ ጥቃት ከበድ ያለ ነው" ብለዋል።
"ቀበሌው ላይ የነበረው ንብረት ሙሉ ለሙሉ የወደመበት ጥቃት ነው የተፈጸመው። የተፈጸው ድርጊት ያማል። አንድ ቀበሌ ወድሟል። ቤት፣ ንብረት የሚባል ነገር የለም። ያስከተሏቸው መሳሪያ ያልያዙ ግለሰቦች ነዳጅና ቤንዚን ይዘው ነው ታጣቂዎቹ ጥቃት ከከፈቱ በኋላ ሙሉ በሙሉ ቀበሌውን ያቃጠሉት" ብለዋል።
"ጥቃት ለመፈጸም እንደ መንደርደሪያ የሚጠቀሙት 8ኛ፣ 4ኛ ከሚባሉ አካባቢዎች ነው። ይህ ጥቃት ከመፈጸሙ በፊት የተለያዩ ምልክቶች ይታዩ ነበር፤ ታጣቂዎቹ ጥቃት ለመፈጸም ሲሰባሰቡ ለሚመለከታቸው መረጃ ብንሰጥም የመንግስት ጸጥታ ኃይሎች ቦታው ላይ ገብተው እርምጃ ያለመውሰድ ችግር ነበር" ነው ያሉት።
የክልሉ ምክር ቤት አባል አቶ ለሜሳ ኔኖ ትናንት የነበረውን ሁኔታ ሲያስረዱ፣ መከላከያ በቦታው ገብቶ በጥቃቱ ከአካባቢው የሸሹ ሰዎችን እያሰባሰበ መሆኑም ሲገልጹ፣ ነዋሪዎችም በስፍራው የሚስተዋለው ጥቃት በዘላቂነት እንዲያስቆም ጠይቀዋል።
ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አለ?
የካማሺ ዞን መንግስት ኮሚዩኒኬሽን አካል አቶ ቦካ አቦሴ፣ በቀበሌው ጥቃት ተፈጸመ መባሉን "ትክክል ነው። ጸረ ሰላም ኃይሎች ጥቃት አድርሰዋል። ቤት ንብረት ወድሟል" ብለዋል። ቦታው በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል እና በኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ መሆኑንም ተናግረዋል።
በጥቃቱ የደረሰውን የጉዳት መጠን የሚመለከት ዝርዝር መረጃ ገና እንዳልደረሳቸው፣ ሲደርሳቸው እንሚያሳውቁ ገልጸው፣ አሁን አካባቢው በሰላማዊ ሁኔታ እንደማገኝ አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
4 553
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪዎችን ቅበላ በፍጥነት እንዲያከናውኑ እየተሠራ ነው።
የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)፥ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ምልመላና ቅበላ ካከናወኑ በኋላ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም በፍጥነት ጥሪ እንዲያደርጉ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም እንዲጀምር መርሐ ግብር የተያዘ ሲሆን እሱን ለመጠበቅ እየተሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
4 553
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
32 ኤርትራውያንና 3 የሰዎች አዘዋዋሪዎች በአርባምንጭ ተያዙ።
በሕገወጥ መንገድ ሲዘዋወሩ የነበሩ 32 የኤርትራ ዜጎች ሁለት ተቀባይና አንድ አሽከርካሪ ከነ ተሽከርካሪው በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን የአርባምንጭ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ክበበው አዳል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቀዋል።
ኤርትራዊያኑ መነሻቸውን ከመሃል ሀገር በማድረግ በአርባምንጭ ኮንሶ ጂንካ በኩል ወደ ኬንያ ለመሸጋገር ሲንቀሳቀሱ እንደነበር የገለጹት ኮማንደር ክበበው፣ ከሕብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማና በፀጥታ መዋቅሩ ቅንጅታዊ ክትትል በሲቀላ ክ/ከተማ ነጭ ሳር ቀበሌ ሲያትል አልጋ ቤት ግራውንድ ስር ባለ አዳራሽ ፍራሾችን በመጣል ከተሸሸጉበት መያዛቸውን ተናግረዋል።
በአጠቃላይ 11 ወንዶች፣ 14 ሴቶች እና 7 ህጻናት በድምሩ 32 ኤርትራውያን ናቸው የተያዙት።
በተጨማሪ ሁለት አዘዋዋሪዎች እንዲሁም ስደተኞችን ወደ አርባ ምንጭ ያመጣ የሰሌዳ ቁጥር " ኮድ 3-23042 አአ " ሀይሩፍ መኪናና አሽከርካሪውን በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን አዛዡ አስታውቀዋል።
በተዘዋዋሪዎቹ ዙሪያ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑንና ስደተኞቹን ለክልሉ ፖሊስ አሳልፎ የመስጠት ሂደት እንደሚከናወን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 553
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
#ችሎት
በሽብር ተግባር ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት የኢህአፓ አባላት ላይ የፌደራል ፖሊስ የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ እንዲያቀርብ ለመጨረሻ ጊዜ 7 ተጨማሪ ቀናት ተፈቀደለት።
በትላንትናው ዕለት በዋለው ችሎት የፌዴራል ፖሊስ በሽብር ተግባር ጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ያዋላቸውን የኢህአፓ አባላት እና የፓርቲው ጠበቃ አቶ ይስሃቅ ወልዳይ ፣ አቶ አበበ አካሉ እንዲሁም አቶ አበራ ንጉስን ላይ ተጨማሪ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ መጠየቁን መዘገባችን ይታወሳል።
ፌደራል ፖሊስ ተጨማሪ ቀናት የጠየቀው ማስረጃ ለማደራጀት፣ የባንክ መረጃዎችን ለመተንተንና ቀሪ የምስክሮችን ቃል ለመቀበል በሚል ነው።
በፌደራል ፖሊስ የተጠየቀው የተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ላይ ብይን ለመስጠት ለዛሬ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ፖሊስ ከጠየቀው 14 ቀናት ውስጥ 7 ቀናትን ለመጨረሻ ጊዜ ፈቅዷል።
የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለጹት ፍርድ ቤቱ የፖሊስን የምርመራ መዝገብ እንዲቀርብ አዞ "የፖሊስን የምርመራ መዝገብ ሂደቱን" ተመልክቷል።
ችሎቱ በመዝገቡ ላይ "የፎረንሲክ እና የቴክኒክ ማስረጃዎች መቅረባቸውን ተመልክቷል ያሉት አቶ ሰለሞን ለሽብር ተጠርጣሪ "በቂ" ናቸው ማለቱንና ቀሪ ስራዎችን አጠናቆ እንዲያቀርብ ማሳሰቡን ተናግረዋል።
እስካሁን ሁለት ምስክሮች ብቻ የተሰሙ ሲሆን ፖሊስ "ቀሪ አለን" በማለቱ ምስክሮችን ለመስማት ብቻ ተጨማሪ ጊዜ መሰጠቱን ጠበቃው ነግረውናል።
የቀሩ ተጨማሪ ምስክሮችን ቃል ተቀብሎ የምርመራ መዘገቡን ለማጠናቀቅ ብቻ "ለመጨረሻ ጊዜ ለነሃሴ 28/2018 ዓም ተቀጥሯል" ነው ያሉት።
ፖሊስ 14 ቀን ቢጠይቅም ፍርድ ቤቱ የፈቀደው "ሰባት ቀን ብቻ" ነው።
ፖሊስ ምርመራውን አጠናቆ በሚያቀርብበት በነሃሴ 28 ቀን ተጠርጣሪዎች ያቀረቡት የዋስትና መብት ጥያቄ አብሮ የሚታይ መሆኑን አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አብራርተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 553
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
" ከሀምሌ አንድ ጀምሮ ባሉት 50 ያህል ቀናት ውስጥ ብቻ 15 ሺ እንስሳት በድርቁ ምክንያት ሞተዋል " - የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት (ለቲክቫህ ኢትዮጵያ)
• በተከሰተው ከባድ የዝናብ እጥረትና ድርቅ ከ95 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ለከፍተኛ ችግር ተጋልጠዋል ተብሏል።
በሰሜን ጎንደር ዞን በየዳ ወረዳ ባለፉት ጥቂት አመታት በየተወሰነ ጊዜ ይከሰት የነበረው የዝናብ እጥረት ዘንድሮ በከፋ ሁኔታ ማጋጠሙን ተከትሎ፣ በወረዳው ከሚገኙ 22 ቀበሌዎች መካከል በ18ቱ ላይ ከፍተኛ የድርቅ አደጋ መከሰቱ የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።
የወረዳው የግብርና ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ገ/ህይወት በላይነህ በተከሰተው ድርቅ ምክንያት በወረዳው ከሚኖሩ 122 ሺህ ነዋሪዎች መካከል ከ95 ሺህ 500 በላይ የሚሆኑት ለከፍተኛ ችግር መጋለጣቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ሃላፊው ገበተለይም በደጋማ አካባቢዎች ቀድሞ መጣል የነበረበት ዝናብ እስከ ሀምሌ 19 ቀን ድረስ በመዘግየቱና አሁንም በተቆራረጠ ሁኔታ በመጣሉ በአካባቢው ግብርና ላይ ከፍተኛ ጥፋት አድርሷል ብለውናል።
እንደ ጽህፈት ቤቱ መረጃ፣ በወረዳው በዘር ተሸፍኖ ከነበረው 17 ሺ 75 ሄክታር መሬት ውስጥ ከ14 ሺህ 375 ሄክታር በላይ የሚሆነው በድርቁ ምክንያት ተመቷል።
ከዚህ በተጨማሪም ከ450 ሄክታር በላይ መሬት ላይ የበቀለው ዘር በመድረቁ ምክንያት ተገልብጦ እንዲታረስ የተገደደ ሲሆን፣ 2 ሺህ 228 ሄክታር የሚሆነው ሰብል ደግሞ ድርቁን ተከትሎ በመጣ የተባይና የበሽታ ወረርሽኝ መውደሙ ታውቋል።
ይህም የአካባቢውን የሰብል ምርት በእጅጉ እንደሚቀንሰውና የቀጣይ ጊዜ የምግብ ዋስትናን አደጋ ላይ እንደሚጥል ገልጸዋል።
የድርቁ አደጋ በሰውና በሰብል ላይ ብቻ ሳይወሰን በእንስሳት ሀብት ላይም ከባድ ጉዳት እያደረሰ ይገኛል ያሉት አቶ ገ/ህይወት ካለፈው ሀምሌ 1/2018 ዓም ጀምሮ ባሉት 50 ያህል ቀናት ውስጥ ብቻ ወደ 15 ሺ በላይ እንስሳት በድርቁ ምክንያት መሞታቸው ተረጋግጧል ብለዋል።
ይህንን ሁኔታ ተከትሎም፣ እስካሁን ወደ 6 ሺ 550 የሚጠጉ ነዋሪዎች መተዳደሪያ ፍለጋ አካባቢያቸውን ለቀው ወደ ተለያዩ ቦታዎች መሰደዳቸውንም አክለው ገልጸዋል።
ምንም እንኳን እስካሁን በድርቁ ምክንያት የጠፋ የሰው ህይወት ባይኖርም፣ አሁን ያለው ሰብል በቀጣይ ቀናት በቂ ዝናብ ካላገኘ ችግሩ ወደ ከፋ ደረጃ ሊሸጋገር እንደሚችል ተጨባጭ ስጋት አለ ነው ያሉት።
የወረዳው አስተዳደር ችግሩን ለመቋቋም ህዝቡን የማረጋጋትና የእርጥበት ጥበቃ ስራዎችን የመስራት ጥረት እያደረገ መሆኑን አስታውቀዋል።
"ይሁን እንጂ የችግሩ ስፋት ከወረዳው አቅም በላይ እየሆነ በመምጣቱ፣ የዞንና የክልል ከፍተኛ ባለሙያዎች እንዲሁም የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት በአካባቢው ተገኝተው የጉዳቱን መጠን እንዲያጠኑ ተደርጓል" ያሉ ሲሆን የሚመለከታቸው አካላት ለተጎዱ ወገኖች አስቸኳይ ድጋፍ እንዲያደርጉና ለቀጣዩ አስቸጋሪ ጊዜ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እንዲያጠናከሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 553
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
" ከሀምሌ አንድ ጀምሮ ባሉት 50 ያህል ቀናት ውስጥ ብቻ 15 ሺ እንስሳት በድርቁ ምክንያት ሞተዋል " - የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት (ለቲክቫህ ኢትዮጵያ)
• በተከሰተው ከባድ የዝናብ እጥረትና ድርቅ ከ95 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ለከፍተኛ ችግር ተጋልጠዋል ተብሏል።
በሰሜን ጎንደር ዞን በየዳ ወረዳ ባለፉት ጥቂት አመታት በየተወሰነ ጊዜ ይከሰት የነበረው የዝናብ እጥረት ዘንድሮ በከፋ ሁኔታ ማጋጠሙን ተከትሎ፣ በወረዳው ከሚገኙ 22 ቀበሌዎች መካከል በ18ቱ ላይ ከፍተኛ የድርቅ አደጋ መከሰቱ የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።
የወረዳው የግብርና ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ገ/ህይወት በላይነህ በተከሰተው ድርቅ ምክንያት በወረዳው ከሚኖሩ 122 ሺህ ነዋሪዎች መካከል ከ95 ሺህ 500 በላይ የሚሆኑት ለከፍተኛ ችግር መጋለጣቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ሃላፊው ገበተለይም በደጋማ አካባቢዎች ቀድሞ መጣል የነበረበት ዝናብ እስከ ሀምሌ 19 ቀን ድረስ በመዘግየቱና አሁንም በተቆራረጠ ሁኔታ በመጣሉ በአካባቢው ግብርና ላይ ከፍተኛ ጥፋት አድርሷል ብለውናል።
እንደ ጽህፈት ቤቱ መረጃ፣ በወረዳው በዘር ተሸፍኖ ከነበረው 17 ሺ 75 ሄክታር መሬት ውስጥ ከ14 ሺህ 375 ሄክታር በላይ የሚሆነው በድርቁ ምክንያት ተመቷል።
ከዚህ በተጨማሪም ከ450 ሄክታር በላይ መሬት ላይ የበቀለው ዘር በመድረቁ ምክንያት ተገልብጦ እንዲታረስ የተገደደ ሲሆን፣ 2 ሺህ 228 ሄክታር የሚሆነው ሰብል ደግሞ ድርቁን ተከትሎ በመጣ የተባይና የበሽታ ወረርሽኝ መውደሙ ታውቋል።
ይህም የአካባቢውን የሰብል ምርት በእጅጉ እንደሚቀንሰውና የቀጣይ ጊዜ የምግብ ዋስትናን አደጋ ላይ እንደሚጥል ገልጸዋል።
የድርቁ አደጋ በሰውና በሰብል ላይ ብቻ ሳይወሰን በእንስሳት ሀብት ላይም ከባድ ጉዳት እያደረሰ ይገኛል ያሉት አቶ ገ/ህይወት ካለፈው ሀምሌ 1/2018 ዓም ጀምሮ ባሉት 50 ያህል ቀናት ውስጥ ብቻ ወደ 15 ሺ በላይ እንስሳት በድርቁ ምክንያት መሞታቸው ተረጋግጧል ብለዋል።
ይህንን ሁኔታ ተከትሎም፣ እስካሁን ወደ 6 ሺ 550 የሚጠጉ ነዋሪዎች መተዳደሪያ ፍለጋ አካባቢያቸውን ለቀው ወደ ተለያዩ ቦታዎች መሰደዳቸውንም አክለው ገልጸዋል።
ምንም እንኳን እስካሁን በድርቁ ምክንያት የጠፋ የሰው ህይወት ባይኖርም፣ አሁን ያለው ሰብል በቀጣይ ቀናት በቂ ዝናብ ካላገኘ ችግሩ ወደ ከፋ ደረጃ ሊሸጋገር እንደሚችል ተጨባጭ ስጋት አለ ነው ያሉት።
የወረዳው አስተዳደር ችግሩን ለመቋቋም ህዝቡን የማረጋጋትና የእርጥበት ጥበቃ ስራዎችን የመስራት ጥረት እያደረገ መሆኑን አስታውቀዋል።
"ይሁን እንጂ የችግሩ ስፋት ከወረዳው አቅም በላይ እየሆነ በመምጣቱ፣ የዞንና የክልል ከፍተኛ ባለሙያዎች እንዲሁም የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት በአካባቢው ተገኝተው የጉዳቱን መጠን እንዲያጠኑ ተደርጓል" ያሉ ሲሆን የሚመለከታቸው አካላት ለተጎዱ ወገኖች አስቸኳይ ድጋፍ እንዲያደርጉና ለቀጣዩ አስቸጋሪ ጊዜ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እንዲያጠናከሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
4 553
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል በ 2018 በጀት ዓመት 124.2 ቢሊየን ብር ጠቅላላ ገቢ ማግኘቱን አሳውቋል።
• ተቋሙ በበጀት አመቱ ያገኘው የተጣራ ትርፍ 39.5 ቢሊየን ብር ነው።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል የ 2018 በጀት አመት ክንውን ሪፖርቱን እና የ 2019 በጀት ዓመት ዋና ዋና እቅዶችን ይፋ አድርጓል።
ተቋሚ በአሁኑ ሰዓት 21 የሃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ያሉት ሲሆን በእነዚህ ሃይል ማመንጫ ጣቢያዎች 9ሺ 730 ሜዋ ሃይል የማመንጨት አቅም ያለው መሆኑን ገልጿል።
ነገር ግን በማመንጨት አቅም ደረጃ እንጂ ሁሌም ይህን ያህል ሃይል ሲፈለግ የማመንጨት አቅም አለው ማለት አለመሆኑን ተብራርቷል።
ተቋሙ በበጀት አመቱ ይዞት ከነበረው እቅድ 91.88 በመቶ አፈጻጸም ማስመዝገቡን ያሳወቀ ሲሆን ያገኘው ትርፍም በተቋሙ ታሪክ ከፍተኛ መሆኑን ዋና ስራ አስፈጻሚው ኢ/ር አሸብር ባልቻ ተናግረዋል።
ተቋሙ ካለው አጠቃላይ የኃይል ምርት ውስጥ 95 በመቶ የሚሆነው ከውኃ ኃይል (Hydro) የሚገኝ ሲሆን፣ ቀሪው 5 በመቶ ደግሞ ከነፋስ ኃይል የሚመነጭ ነው።
በአሁኑ ወቅት ተቋሙ በድምሩ 9,730 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው 21 የኃይል ማመንጫዎች ያሉት ሲሆን ከእነዚህ 15 የውኃ ኃይል ማመንጫዎች (9,201 ሜጋ ዋት)፣ 5 የነፋስ ኃይል ማመንጫዎች (504 ሜጋ ዋት)፣ 1 የእንፋሎት (Geothermal) ኃይል ማመንጫ (25 ሜጋ ዋት) ማመንጨት ችሏል።
የተቋሙ አጠቃላይ ሀብት 900.54 ቢሊዮን ብር መድርሱንና የተፈቀደ ካፒታሉ 1.3 ትሪሊዮን ብር፣ የተከፈለ ካፒታሉ ደግሞ 585 ቢሊዮን ብር መሆኑን ተገልጿል ኢ/ር አሸብር ገልጸዋል።
ተቋሙ የሚያመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል በዋናነት ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል ሲሆን፣ 93.5 በመቶ የሚሆነው ለሀገር ውስጥ፣ ቀሪው 6.5 በመቶ ደግሞ ለውጭ ሀገራት ኤክስፖርት የሚደረግ መሆኑን ተቋሙ ይፋ ካደረገው መረጃ ላይ ተብራርቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
