1 201
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-1530 days
Posts Archive
1 201
Repost from SadatKemal Abu Meryem
ተውሒድ ታላቁ አደራ
በድምፅ ማስረጃ የተደገፈ
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/6382
1 201
🔖አዲስ ተከታታይ ትምህርት
📚 الأصول الثلاثة لشيخ الإسلام محمد بن عبدالوهاب رحمه الله تعالى -٠١
✸| ክፍል 01 (የመጀመሪያው ክፍል)
🔗 የዳውንሎድ ሊንኩን ይጫኑ Mp3
https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn/4222
═════ ≪ °📓🖇📓° ≫ ════
የኪታቡን ሶፍት ኮፒ በ Pdf መልክ በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ ↓↓↓
https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn/4220
═════ ≪ °📓🖇📓° ≫ ════
🕌 በፉሪ አቡበክር አስ-ሲዲቅ መስጂድ ለሙእተኪፎች የተዘጋጀ ኮርስ
🗓 ዛሬ እሁድ ረመዷን 21-1445 ሂጅሪ (22 -07-2016)[31-03-2024] ከዙሁር ሰላት በኃላ የተሰጠ ደርስ ነው
🎙በሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደም
ሀፊዘሁላህ ወረዓህ
📍ትምህርቱን ለመከታተል ቻናሎቹን ይቀላቀሉ 👇👇👇
https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam
&
http://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn
1 201
Repost from قناة دروس فضيلة الشيخ محمد زين بن آدم الحبشي - Sheikh Muhammed Zain Adam - ሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደም
🌹 بشرى سارة 🌹
የዐሽረል አዋኺር ኮርስ
📚 በኮርሱ የሚቀራው ኪታብ :- ''ሠለሠቱል ኡሱል"
🎙 ኪታቡን ሚያቀሩት :- ሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደም
🕌 ትምህርቱ የሚሰጥበት ቦታ:- ፉሪ(በፉሪ ሜዳ ፊት ለፊት ባለው ቅያስ ገባ ብሎ) አቡበክር አስሲዲቅ መስጂድ
🕖 የትምህርቱ ቀንና ሰዐት :- ዐሽረል አዋኺር ከዙህር ሰላት በኃላ
🗓 ትምህርቱ ሚጀመረው :- እሁድ ረመዳን 21-1445 ሂጅሪ ይሆናል።
* በአካል ተገኝታችሁ መከታተል ለማትችሉ በዚህ የቴሌግራም ቻናል በቀጥታ ስርጭት ይተላለፋል እንዲሁም ሪከርዱም ይለቀቃል ኢንሻአሏህ።
https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam
&
https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn
1 201
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱሁ።
ውድ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች! ይህ አዲስ የተከፈተ የጀመዐችን ቻናል ነው። የተከፈተበት አላማ ጀማዐው ላይ ያሉ የተለያዩ ፕሮግራሞችን ለመለጠፍ እና ጠቃሚ ነጥቦችን ለመተዋወስ ነው። ለምታውቋቸው የጀማዐችን ልጆች ሊንኩን forward በማድረግ ከቻናሉ እንዲጠቀሙ እንዲሁም ቻናሉንም እንድታጠናክሩ እንጠይቃለን።
بارك الله فيكم
https://t.me/Wku_ms_Official_Channel
1 201
Repost from Muzemil Behja Abu Hanif
ይህን መሰረት በማድረግ የምንሰራቸው ዒባዳዎች እና አፈፃፀማቸው ሁሉ በማስረጃ የተደገፉ መሆን ይኖርባቸዋል።ይህ ሳይሆን ከቀረ ግን በሐዲሶቹ መሰረት ስራችን ከንቱ ይሆናል እንዲሁም የመልዕክተኛውን ፈለግ የተጣረስን እንሆናለን።የመልዕክተኛውን ፈለግ መጣረስ ደሞ በዱንያም በአኼራም መዘዙ የከፋ ነውና እንጠቀቅ።
አሏህ ይህን አስመልክቶ እንዲህ ይለናል
فَلْيَحْذَرِ الَّذِينَ يُخَالِفُونَ عَنْ أَمْرِهِ أَن تُصِيبَهُمْ فِتْنَةٌ أَوْ يُصِيبَهُمْ عَذَابٌ أَلِيمٌ
እነዚያ ትዕዛዙን ( የመልዕተኛውን) የሚጥሱ መከራ እንዳትደርስባቸው ወይም አሳማሚ ቅጣት እንዳያገኛቸው ይጠንቀቁ፡፡[ አል— ኑር ፡ 63]
ማስታወሻ ‼
ማስተላለፍ የፈለኩት መልእክት የረመዷንን ግማሽ ሆን ብሎ እየጠበቁ ሶደቃ ማውጣት በዲናችን ምንም መሰረት የለውም ማለት ነው።ሆን ብሎ እየጠበቁ ሚለው ሀሳብ ይሰመርበት።ምክንያቱም ሆን ብሎ ሳይሆን አጋጣሚ ሆኖ ሰውዬው የተመቻቸለት ወይም የተሳካለት የረመዷን ግማሽ ላይ ቢሆንና በረመዷን ግማሽ ሶደቃ ቢያወጣ ምንም ችግር የለውምና።
አሏህ የመልዕተኛውን ፈለግ ከመቃረን ይጠብቀን ‼
1 201
Repost from Muzemil Behja Abu Hanif
" ሶመን ሶደቃ " ‼
ሶደቃ በዲነል ኢስላም ከተደነገጉ ትላልቅ ዒባዳዎች መካከል አንዱ ነው።አሏሁ (ሱብሓነሁ ወተዓላ) ቁርኣኑ ላይ ሶደቃ የአማኞች መገለጫ አድርጎ በተለያዩ የቁርኣን አንቀፆች ላይ ይነግረናል።ለምሳሌ ያህል የተወሰኑትን እንይ ፦
" الَّذِينَ يُقِيمُونَ الصَّلَاةَ وَمِمَّا رَزَقْنَاهُمْ يُنفِقُونَ"
" ሙእሚኖች ማለት እነዚያ ሶላትን ደንቡን አሟልተው የሚሰግዱ ፤ ከሰጠናቸውም ሲሳይ የሚለግሱ ናቸው፡፡ " [አል አንፋል 3]
"الَّذِينَ يُؤْمِنُونَ بِالْغَيْبِ وَيُقِيمُونَ الصَّلَاةَ وَمِمَّا رَزَقْنَاهُمْ يُنفِقُونَ "
" ለነዚያ በሩቁ ነገር የሚያምኑ ሶላትንም ደንቡን ጠብቀው የሚሰግዱ ከሰጠናቸውም ሲሳይ የሚቸሩ ለኾኑት" [አልበቀራህ 2]
"وَأَنفِقُوا مِن مَّا رَزَقْنَاكُم مِّن قَبْلِ أَن يَأْتِيَ أَحَدَكُمُ الْمَوْت فَيَقُولَ رَبِّ لَوْلَا أَخَّرْتَنِي إِلَىٰ أَجَلٍ قَرِيبٍ فَأَصَّدَّقَ وَأَكُن مِّنَ الصَّالِحِينَ"
" አንዳችሁንም ሞት ሳይመጣውና ጌታዬ ሆይ! እንድመጸውትና ከደጋጐቹም ሰዎች እንድኾን ወደ ጥቂት ጊዜ ብታቆየኝ ኖሮ እመኛለሁ ከማለቱ በፊት ከሰጠናችሁ ሲሳይ ለግሱ፡፡"
[አል ሙናፊቁን]
يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا أَنفِقُوا مِمَّا رَزَقْنَاكُم مِّن قَبْلِ أَن يَأْتِيَ يَوْمٌ لَّا بَيْعٌ فِيهِ وَلَا خُلَّةٌ وَلَا شَفَاعَةٌ ۗ وَالْكَافِرُونَ هُمُ الظَّالِمُونَ
እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በርሱ ውስጥ ሽያጭ ፣ ወዳጅነትም፣ ምልጃም የሌለበት ቀን ከመምጣቱ በፊት ከሰጠናችሁ ነገር ለግሱ፡፡[ አል በቀራህ]
الَّذِينَ يُنفِقُونَ أَمْوَالَهُم بِاللَّيْلِ وَالنَّهَارِ سِرًّا وَعَلَانِيَةً فَلَهُمْ أَجْرُهُمْ عِندَ رَبِّهِمْ وَلَا خَوْفٌ عَلَيْهِمْ وَلَا هُمْ يَحْزَنُونَ
እነዚያ ገንዘቦቻቸውን በሌሊትና በቀን በድብቅም በግልጽም የሚለግሱ ለእነርሱ በጌታቸው ዘንድ ምንዳቸው አላቸው፡፡ በእነርሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም እነርሱም አያዝኑም፡፡[አል በቀራህ]
: ከሐዲስ ፦
(1) ﻗﺎﻝ ﺭﺳﻮﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ : (ﻣﺎ ﻣِﻦ ﻳَﻮﻡٍ ﻳُﺼْﺒِﺢُ ﺍﻟﻌِﺒﺎﺩُ ﻓِﻴﻪِ، ﺇﻟَّﺎ ﻣَﻠَﻜﺎﻥِ ﻳَﻨْﺰِﻻﻥِ، ﻓﻴَﻘﻮﻝُ ﺃﺣَﺪُﻫُﻤﺎ : ﺍﻟﻠَّﻬُﻢَّ ﺃﻋْﻂِ ﻣُﻨْﻔِﻘًﺎ ﺧَﻠَﻔًﺎ، ﻭﻳﻘﻮﻝُ ﺍﻵﺧَﺮُ : ﺍﻟﻠَّﻬُﻢَّ ﺃﻋْﻂِ ﻣُﻤْﺴِﻜًﺎ ﺗَﻠَﻔًﺎ) ﺭﻭﺍﻩ ﺍﻟﺒﺨﺎﺭ
ባሮች በእርሱ የሚያነጉበት አንድም ቀን የለም ሁለት መላኢኮች ቢወርዱ እንጂ
አንደኛው "አሏህ ሆይ የሚለግስን ሰው ምትክ ስጠው" ይላል
ሌላኛው ደሞ " አሏህ ሆይ ቋጣሪ የሆነን ሰው ጥፋት ስጠው " ይላል [ቡኻሪ ዘግበውታል]
(2) ﻗﺎﻝ ﺭﺳﻮﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ: " ﻳﺎ ﻣَﻌْﺸَﺮَ ﺍﻟﻨِّﺴَﺎﺀِ، ﺗَﺼَﺪَّﻗْﻦَ، ﻓﺈﻧِّﻲ ﺭَﺃَﻳْﺘُﻜُﻦَّ ﺃﻛْﺜَﺮَ ﺃﻫْﻞِ ﺍﻟﻨَّﺎﺭِ ........ "متفق عليه
"እናንተ የሴት ስብስቦች ሆይ አብዝሃኛው የጀሀነም ጓዶች እናንተ ሆናችሁ አይቻችኋለውና ሶደቃ አድርጉ.........." [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል]
(3) ﻗﺎﻝ ﺭﺳﻮﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ: ( ﻣﺎ ﻣِﻨﻜُﻢ ﻣِﻦ ﺃﺣَﺪٍ ﺇﻟَّﺎ ﺳَﻴُﻜَﻠِّﻤُﻪُ ﺍﻟﻠَّﻪُ، ﻟﻴﺲَ ﺑﻴْﻨَﻪُ ﻭﺑﻴْﻨَﻪُ ﺗُﺮْﺟُﻤﺎﻥٌ، ﻓَﻴَﻨْﻈُﺮُ ﺃﻳْﻤَﻦَ ﻣﻨﻪ ﻓﻼ ﻳَﺮَﻯ ﺇﻟَّﺎ ﻣﺎ ﻗَﺪَّﻡَ، ﻭﻳَﻨْﻈُﺮُ ﺃﺷْﺄَﻡَ ﻣﻨﻪ ﻓﻼ ﻳَﺮَﻯ ﺇﻟَّﺎ ﻣﺎ ﻗَﺪَّﻡَ، ﻭﻳَﻨْﻈُﺮُ ﺑﻴْﻦَ ﻳَﺪَﻳْﻪِ ﻓﻼ ﻳَﺮَﻯ ﺇﻟَّﺎ ﺍﻟﻨَّﺎﺭَ ﺗِﻠْﻘﺎﺀَ ﻭﺟْﻬِﻪِ، ﻓﺎﺗَّﻘُﻮﺍ ﺍﻟﻨَّﺎﺭَ ﻭﻟﻮ ﺑﺸِﻖِّ ﺗَﻤْﺮَﺓٍ) ﺭﻭﺍﻩ ﻣﺴﻠﻢ
ከእናንተ መካከል አንድም ሰው የለም በአሏህና በእሱ መካከል ምንም ተርጓሚ ሳይኖር ቢያናግረው እንጂ፤( ባሪያው) ወደ ቀኝ ያያል ያሳለፈውን እንጂ አይመለከትም፤ ወደ ግራ ያያል ያሳለፈውን እንጂ አይመለከትም፤ ወደ ፊት ለፊቱ ያያል ከፊት ለፊቱ እሳትን እንጂ አይመለከትም፤በቴምር ግማሽ እንኳን ቢሆን እሳትን ተጠንቀቁ።[ ሙስሊም ዘግበውታል]
(4) ﻋﻦ ﺃﺑﻲ ﻫﺮﻳﺮﺓ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﺃﻥ ﺭﺳﻮﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﺍﻟﺼﻼﺓ ﻭﺍﻟﺴﻼﻡ ﻗﺎﻝ : ﻗﺎﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻧﻔﻖ ﻳﺎ ﺍﺑﻦ ﺁﺩﻡ ﺃﻧﻔﻖ ﻋﻠﻴﻚ ﺭﻭﺍﻩ ﺍﻟﺒﺨﺎﺭﻱ ﻭﻣﺴﻠﻢ
አሏህ እንዲህ ይላል ፦
"አንተ የአደም ልጅ ሆይ ለግስ እለግስሃለው" [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል]
ስለዚህ በነዚህ እና መሰል በርካታ መረጃዎች መሰረት በቻልነው አቅም መስሰደቅ ይኖርብናል።በቴምር ግማሽ እንኳን ቢሆን እሳትን ተጠንቀቋት ተብለናልና ሶደቃ ለማድረግ የግድ ሚሊኒየር ወይም ቢሊኒየር መሆን አይጠበቅብንም ፤ እንደውም ሐዲስ ላይ እንደተወሳው ሀብታም ሆነን ከምናደርገው ሶደቃ ይልቅ ገንዘቡን ለራሳችን እየፈለግነው ድህነትን እየፈራን የምናደርገው ሶደቃ ይበልጣል።ስለዚህ እንደአቂሚቲ የተቻለንን በማድረግ በዚህ ዒባዳ ላይ ለአኼራችን አሻራችንን እናሳርፍ።ሌላኛው ወሳኙና ማወቅ ያለብን ነገር ሶደቃ ዒባዳ እንደመሆኑ መጠን ሶደቃ የምናደርግበት መንገድ ከሸሪዓዊ አስተምህሮ ጋር የሚፃረር ይዘት ያለው መሆን የለበትም።በሸሪዓችን የጊዜ ገደብ ያልተደረገላቸውን ዒባዳዎች ያለምንም ማስረጃ በእራሳችን ጊዜ የጊዜ ገደብ ማበጀት ዒባዳውን ወደ አሏህ መቃረቢያ ከመሆን አውጥቶ በሸሪዓችን በጥብቅ ወደተወገዘው ቢድዓ ይወስደዋል።ከንዲህ አይነቱ ተግባር የሚካተተው በሀገራችን ላይ በሰፊው የተለመደ የሆነው " ሶመን ሶደቃ " ተብሎ የሚጠራውና በረመዷን አስራ አምስተኛው ቀን ላይ የሚደረገው ሶደቃ ( አርዶም ይሁን ሌላ ነገር አዘጋጅቶ ሰውን ሰብስቦ ማብላት) አንዱ ነው።ሶደቃ በሸሪዓችን ትልቅ የሆነ ዒባዳ እንደሆነ ከላይ በቁርኣንና በሐዲስ ማስረጃዎች ለማብራራት ሞክሪያለው።ይሁን እንጂ በዲናችን ሶደቃ ለማውጣት ተብሎ የተመደበ የጊዜ ገደብ የለም።እኛ አቅማችን በፈቀደልን በየትኛውም ሰኣት የቻልነውን ያህል እንሰድቃለን ፤ ከዛ ውጪ ግን ያለምንም ሸሪዓዊ ማስረጃ ሰው ስላደረገው ብቻ ወይም በአካባቢያችን ስለተለመደ....የሚሉ
መሰል የሆኑ በዲን ምንፅር ሲታዩ ውሃ የማይቋጥሩ ምክንያቶችን እየደረደርን በዲናችን ምንም የተረጋገጠ ማስረጃ የሌለውን ተግባር ከመስራት ልንቆጠብ ይገባል።ስለዚህ በየአመቱ ረመዷን በመጣ ቁጥር የረመዷንን ግማሽ ሆን ብሎ ጠብቆ ሶደቃ ማውጣት ምንም አይነት ማስረጃ ያለው ተግባር አይደለምና ከድርጊታችን እንታቀብ ፤ ለሰዎችም ግንዛቤ እንፍጠር።
መልዕክተኛው( ዐለይሂ ሶላቱ ወስሰላም) እንዲህ ይላሉ ፦
1— "من أحدث في أمرنا هذا ما ليس منه فهو رد" [ متفق علي]
"በዚህ ጉዳያችን (በዲናችን) ላይ ከሱ ያልሆነን አዲስ ነገር ያመጣ ስራው ተመላሽ ነው" [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል]
2— "من عمل عملا ليس عليه أمرنا فهو رد"(رواه مسلم)
"የእኛ ትዕዛዝ የሌለበትን ስራ የሰራ ስራው ተመላሽ ነው" [ሙስሊም ዘግበውታል]
1 201
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ከፆም ጋር የተያያዙ ጥቂት ነጥቦች
~
1- ፆመኛ ሆኖ ረስቶ የበላ ወይም የጠጣ ፆሙን ይቀጥላል። ያበላውና ያጠጣው አላህ ነው። [ቡኻሪና ሙስሊም]
2- ፆመኛ ሰው አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ምግብ መቅመስ ይቻላል። ባይሆን ከቀመሱ በኋላ መትፋት ግዴታ ነው። ሆን ተብሎ ካልተዋጠ ቢያመልጥም ፆም አይበላሽም።
3- ፆመኛ ሰው ከቀትር በፊትም ይሁን በኋላ መፋቂያ መጠቀም ይችላል። በዚህ ላይ የመጣ ገደብ የለም።
4- ከወር አበባና የወሊድ ደም ውጭ ከፆመኛ ሰው ያለ ፍላጎት፣ ያለ ምርጫ በራሱ ከሰውነት የሚወጣ ደም ፆም አያበላሽም። ለምሳሌ የኢስቲሓዳህ (የበሽታ) ደም፣ የነስር ደም። [መጅሙዑል ፈታዋ፣ ኢብኑ ተይሚያ: 25/267]
እንዲሁም ሆነ ተብሎ ለሆነ ጉዳይ (ለምሳሌ ለህክምና ምርመራ) የሚወሰድ ደም ወይም በሆነ ምክንያት (ለምሳሌ ጥርስን በመንቀል ወይም ቁስልን በመብጣት) የሚፈስ ደም ፆም አያበላሽም። [ፈትሑ ዚል ጀላሊ ወልኢክራም፣ ኢብኑ ዑሠይሚን: 7/208]
=
የቴሌግራም ቻናል:-
https://t.me/IbnuMunewor
1 201
Repost from SadatKemal Abu Meryem
ረመደን ቀን 14
ለሰይጣን ማረድ
ሁለት ዱአዎች
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/2443
