1 201
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-1530 days
Posts Archive
1 201
Repost from SadatKemal Abu Meryem
ረመዳን ቀን 12
ነብዩ ኢሳ እና ነብዩ ሙሐመድ (የአላህ ሰላት እና ሰላም በነሱ ላይ ይሁን)
ሶስት ዱአዎች
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/2439
1 201
Repost from SadatKemal Abu Meryem
ረመዳን ቀን 11
ነብዩ ጌታ አይደሉም።
የአህባሾች ቲቪ?
ሁለት ዱአዎች
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/2437
1 201
🌙 👉ረመዷናዊ ምክር - 06👈🌙
🎙🎙🎙በሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደም ሀፊዘሁላህ
📖ስለ ዚክር (አላህን ማውሳት) ተዳሷል
🗓ዛሬ እሮብ ረመዷን 10-1445 (መጋቢት 11-2016) ከዓሱር ሰላት በኃላ ፉሪ አቡበክር አስ'ሲዲቅ መስጂድ የተሰጠ ምክር ነው ።
https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn
https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam
1 201
🌙 👉ረመዷናዊ ምክር - 05👈🌙
🎙🎙🎙በሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደም ሀፊዘሁላህ
📖ስለ ዱዓ አሳሳቢነት ተዳሷል
🗓ዛሬ ማክሰኞ ረመዷን 09-1445 (መጋቢት 10-2016) ከዓሱር ሰላት በኃላ ፉሪ አቡበክር አስ'ሲዲቅ መስጂድ የተሰጠ ምክር ነው ።
https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn
https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam
1 201
Repost from SadatKemal Abu Meryem
ረመዳን ቀን 10
ጂብሪል (አለይሂ ሰላም)
ሁለት ዱአዎች
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/2434
1 201
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ዘካ የሌለባቸው ንብረቶች
~
① ለንግድ ሳይሆን ለቤት ፍጆታ የተቀመጡ ንብረቶች (ሸቀጣ ሸቀጥ፣ ምግቦች፣ እህሎች፣ መገልገያ ቁሳቁስ፣ የቤት መኪና፣ መገልገያ እንስሳት፣ ለሽያጭ ያልቀረቡ አልባሳት) ዘካ የለባቸውም።
② ለሽያጭ ሳይሆን ለኪራይ የተዘጋጁ ቤቶች፣ መኪናዎች፣ ማሽኖች፣ ወዘተ በራሳቸው ዘካ የለባቸውም። ዘካ የሚመለከታቸው ከኪራይ የተሰበሰበው ገንዘብ ለዘካ መጠን ደርሶ አመት ከሞላው ነው።
③ ማምረቻ ፋብሪካዎች ለሽያጭ ታልመው የተገዙ ካልሆነ በስተቀር በራሳቸው ዘካ የለባቸውም። ዘካ የሚኖረው ለገበያ በሚያቀርቡት ምርት ላይ ነው። የንግድ መገልገያ ማሽኖችና አጋዥ መኪናዎች፣ ፍሪጆች፣ ቋሚ ቁሳቁሶች፣ ዘካ የለባቸውም። ዘካ የሚመለከታቸው በሚያስገኙት ገቢ ላይ ወይም ራሳቸው ለሽያጭ የተገዙ ሲሆን ነው።
④ ከወርቅና ብር ውጭ ያሉ ማእድኖች (አልማዝ፣ ፕላቲነም፣ ውድ የሆኑ የድንጋይ አይነቶች፣ …) በራሳቸው ዘካ የለባቸውም። ለንግድ ከዋሉ ግን እንደማንኛውም የንግድ ሸቀጥ ዘካ ይመለከታቸዋል።
⑥ የህዝብ ማመላለሻና የጭነት መኪኖች በገቢያቸው እንጂ በራሳቸው ዘካ የለባቸውም። የሚያስገቡት ገቢ ለዘካ መጠን ከደረሰ በኋላ አመት ከሞላው የአጠቃላዩን 2•5% ዘካ ይወጣል። [መጅሙዑል ፈታዋ፣ ኢብኑ ባዝ: 14/181] [ፈታወ ለጅነቲ ዳኢማህ: 9/349]
⑦ ለሽያጭ ወይም ለአገልግሎት መሆን አለመሆኑን በቁርጥ ያልተወሰነበት ቤት ወይም መኪና ዘካ የለበትም።
⑧ ተበዳሪው ችግረኛ በመሆኑ ወይም የሚያጉላላ በመሆኑ ወይም በመካዱ ይመለሳል ተብሎ ተስፋ የማይጣልበት ብድር ዘካ አይወጣበትም። እጅ ከገባ ግን ለብዙ አመታት የቆየ ቢሆን እንኳ የአንድ አመት ዘካ ይወጣለታል ይላሉ ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን ረሒመሁላህ።
⑨ ለትርፍ ሳይሆን ለህዝባዊ ጉዳይ ወይም ለኸይር ስራ ታልሞ (ለምሳሌ ችግር፣ አደጋ፣ ሞት፣ ህመም ሲደርስ ለመረዳዳት፣…) በበጎ ፈቃኞች መዋጮ የሚሰበሰብ ገንዘብ ለዘካ መጠን ቢደርስም ዘካ የለበትም። [ፈታወ ዘካ፣ ኢብኑ ባዝ: 48]
ዘካ የሚመለከታቸውን የንብረት አይነቶች በቀጣይ አቀርባለሁ፣ ኢንሻአላህ።
"ሼር" ብታደርጉት ባርከላሁ ፊኩም።
=
( Ibnu Munewor ፣ ሚያዚያ 21/2013)
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
1 201
Repost from SadatKemal Abu Meryem
ረመዳን ቀን 9
በነብይነታቸው መመስከር ምን ያስፈርዳል?
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/2432
1 201
Repost from Muzemil Behja Abu Hanif
ጾመኛ ሆኖ ምራቅን መዋጥ‼
====================
✍ «ምራቅን መዋጥ ፆምን የሚያበላሽ የሚመስላቸው ሰዎች አሉ፡፡ በዚህም የተነሳ አንድ ቦታ ከተቀመጡ አካባቢያቸውን ምራቅ በምራቅ ሲያደርጉት ያጋጥማል፡፡ ምራቅ ፆም ያበላሻልን?
1. መደበኛ ወይም ከወትሮው ያልበዛ ከሆነ
ከተለመደው ያልተጋነነ ምራቅ ከአፍ አውጥተው ካልመለሱት በስተቀር ባለበት ሁኔታ ቢዋጥ ፆም እንደማያበላሽ ኢብኑ ሐዝምና ነወዊይ የዑለማእ ወጥ ስምምነት (ኢጅማዕ) ጠቅሰዋል፡፡
2. ታስቦበት ባልሆነ መንገድ ከበዛና ከተጠራቀመስ?
ሆን ብለን ሳናጠራቅመው እንዲሁ ወሬ ስናወራ ወይም ቁርኣን ስንቀራ፣… ምራቃችን ሊበዛ ይችላል፡፡ ይህንንስ የዋጠ ፆሙ ይበላሻል? ነወዊይ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡- “ሳይታሰብበት ብዙ ምራቅ ቢጠራቀም፣ ለምሳሌ ንግግሩ በመብዛቱና መሰል ሰበብ የተነሳ ሆን ብሎ ሳያደርገው ቢበዛና ቢውጠው (በሻፍዒያ መዝሀብ) ያለ ልዩነት ፆሙ አልተበላሸም፡፡” ይሄ የብዙ ዑለማዎች አቋም ነው፡፡
3. ታስቦበት ከተጠራቀመስ?
አንድ ሰው ሆነ ብሎ ምራቁን ካጠራቀመ በኋላ ቢወጠው ፆሙ ይበላሻል ወይስ አይበላሸም በሚለው ላይ ውዝግብ አለበት፡፡ በሻፍዒያ መዝሀብ ትክክለኛው አቋም ሐንበሊያም ዘንድ እንዲሁ “ፆሙ አይበላሽም” የሚለው ነው፡፡ ሸይኽ ኢብኑል ዑሠይሚንም ረሒመሁላህ “ፆሙ አይበላሽም” የሚለውን መርጠዋል፡፡ ሆኖም ግን እራስን ከውዝግብ ማራቅ ተገቢ ነውና መጠንቀቁ ሰላማዊ ምርጫ ነው፡፡
አክታን መዋጥስ?
~~~
4. ከአቅም በላይ ከሆነ
ማስወገድ በማይችለው መልኩ ከጭንቅላቱ ቀጥታ ወደታች የሚወርድ አክታ ከሆነ ሊጠነቀቀው አይችልም፡፡ አላህ ደግሞ ከአቅም በላይ በሆነ ነገር አይዝም፡፡
5. መቆጣጠር ሲቻል ቢዋጥስ?
ነገር ግን ስራዬ ብሎ አውጥቶ አፉ ጋር ካደረሰው በኋላ መትፋት ሲችል ቢውጠው ፆሙ ይበላሻል ያሉ ዐሊሞች አሉ፡፡ ከፊሎቹ ግን ይህም ቢሆን አይበላሽም ብለዋል፡፡ ለምሳሌ ሸይኽ ኢብኑል ዑሠይሚን ረሒመሁላህ “ፆሙ አይበላሽም” የሚለውን መርጠዋል፡፡ ታዲያ “ፆሙ አያበላሽም” ይበሉ እንጂ ድርጊቱ ፆመኛ ለሆነም ይሁን ላልሆነ ሰው ሐራም እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ አንደኛ አፀያፊ ነው፡፡ ሁለተኛ ምናልባትም በሽታ አምጪ ተህዋሲያንን የተሸከመ ሊሆን ስለሚችል ወደ ሆድ ሲገባ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል የሚል ነው፡፡ [ሸርሑል ሙምቲዕ፡ 6/428] እራስን ከውዝግብ ለማራቅ ሲባል መራቁም እራሱን የቻለ ዋጋ አለው፡፡ ወልላሁ አዕለም፡፡»
ኢብኑ ሙነወር
https://t.me/IbnuMunewor
1 201
Repost from SadatKemal Abu Meryem
ረመዳን ቀን 7
የመጀመሪያው እና የመጨረሻው መልክተኞች ኑሕ እና ሙሐመድ (ሰለላሁ አለይሂም ወሰለም)
ሁለት ዱአዎች
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/2428
1 201
Repost from Muzemil Behja Abu Hanif
ውዷ እህቴ !!
ይሄ ሁሉ ላንቺ ክብር ሲባል ነው ፤ የማንም ጫት ቃሚና ወጠጤ አፍ መክፈቻ እንዳትሆኚ ፤ እንዲሁም ወንዶች ባንቺ እንዳይፈተኑ ነውና ለመልዕክተኛው ትዕዛዝ ከአሁኑ ሰዓት ጀምሮ ሰምቻለው ታዝዣለው በይ።ልብስሽም ረጅም ፣ ወፍራም ፣ መላ አካልሽን የሚሸፍን ፣ ሰፊ ይሁን።ይህ ሳይሆን ከቀረ ግን የመልዕክተኛውን ትዕዛዝ በመጣስሽ እንዲሁም ወንዶችን በመፈተንሽ ከአሏህ የሆነ ቁጣ በማትረፍሽ "የቆጡን አወርድ ብላ የብብቷን ጣለች " እንደሚባለው ትሆኚያለሽ።ማለትም ሱና የሆነን ነገር እሰራለው(ተራዊሕ እሰግዳለው) ብለሽ አሏህ ሐራም ያደረጋቸውን ነገሮች ሰርተሽ ኪሳራ በኪሳራ ሆነሽ ትመለሻለሽ።
እህቴ አሏህ ከዘልዛሎች ይጠብቅሽና ተስተካከይ እሺ ‼
አሏህ በሁሉም ነገራችን ላይ ለሱ ህግጋቶች ተገዢ ያድርገን‼ ኣሚን
1 201
Repost from Muzemil Behja Abu Hanif
ተራዊሕ ሶላት ላይ እየተለመዱ የመጡ ስህተቶች ‼
➊ ሰፍን ማበላሸት
ልክ ሶፍን ማዘበራረቅ ሱና ነው የተባለ ይመስል በተለያዩ መስጂዶች ላይ ተራዊሕ በሚሰግገድበት ሰዓት ቅጥ ያጡ ሰፎችን ማየት እየተለመደ መጥቷል።ይህ ተግባር ሰፍን ማሰተካከል አስመልክቶ የመጡ ሐዲሶችን ካለማወቅ ወይም አውቆም ቦታ ካለመስጠት(የአብዛኞቻችን መርራር ሁኔታ) የመጣ ነው።ያላወቀቱን ለማሳወቅ የረሱትን ለማስታወስ የተወሰኑ ሰፍ ማሰተካከልን አስመልክተው የመጡ ማስረጃዎችን እንይ፦
(1) "ألا تصفون كما تصف الملائكة عند ربها ؟" فقلنا يا رسول الله وكيف تصف الملائكة عند ربها؟ قال" يتمون الصفوف الأول ويترصون في الصف" رواه المسلم
መልዕክተኛው ﷺ እንዲህ አሉ ፦
" ( ሶላት ላይ) መላኢኮች ጌታቸው ዘንድ እንደሚሰለፉት አትሰለፉምን? "
እኛም " መላኢኮች ጌታቸው ዘንድ እንዴት ነው ሚሰለፉት?" አልናቸው
እሳቸውም "የመጀመሪያ የመጀመሪያ ሰፎችን( ከፊት ለፊታቸው ያለውን ሰፍ) ይሞላሉ ፤ በሰፋቸውም ይጥጠጋጋሉ" አሉ ( ሙስሊም ዘግበውታል)
(2) "سووا صفوفكم فإن تسوية الصف من تمام الصلاة" متفق عليه
"ሰፎቻችሁን አስተካክሉ፤ሰፍን ማስተካከል ሶላትን ከሟሟላት ነው" ( ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
"فإن تسوية الصف من إقامة الصلاة"
"ሰፍን ማስተካከል ሶላትን ቀጥ አድርጎ ከመስገድ ነው" (ቡኻሪ ዘግበውታል)
(3) "لتسون صفوفكم أو ليخالفن الله بين وجوهكم"متفق عليه
"ሰፎቻችሁን ታስተካክላላቹ ፤ ወይም( የማታስተካክሉ ከሆነ) አሏህ ፊቶቻችሁን ይቀያይረዋል"( ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
★ "አሏህ ፊቶቻችሁን ይቀያይረዋል" ለሚለው የመልዕክተኛው ﷺ ንግግር ከተሰጡ ማብራሪያዎች መካከል አንዱ
"በመካከላቹ አለመግባባትን ይፈጥራል" የሚለው የኡለሞች ማብራሪያ ይገኝበታል።
(4) "لا تختلفوا فتختلف قلوبكم"رواه أبو داود
"በሰፎቻችሁ አትለያዩ ፤ ልባችሁ ይለያያል"
(አቡ ዳውድ ዘግበውታል)
ስለዚህ እነዚህ ሐዲሶች ውስጥ ከተጠቀሱት ዛቻዎች ለመትረፍ ሰፎቻችንን ቀጥ ማድረግና ማስተካከል ይኖርብናል።ይሞቃል፣ይጨንቃል፣አየር ፍለጋ፣……… ወዘተ በሚል ውሃ የማያነሳ ምክንያት ሰፎችን አናዘበራርቅ ፤ መስጂድ ሳይሞላ በረንዳ ላይ አንስገድ።
➋ ቁርኣንን ከኢማም ጋር አብሮ ማንበብ
ድምፅ ከፍ ተደርጎ ቁርአን የሚነበብባቸው ሶላቶች ላይ ተከታዮች ማድረግ ያለባቸው ፋቲሃን ከቀሩ በኋላ የኢማሙን ቂርኣት ማዳመጥ ነው።ከፋቲሃ በኋላ ኢማሙ ረጅምም ሱራ ይቅራ አጭር ፤ የምናቀውንም ይሁን የማናቀውን ሱራ ይቅራ እኛ ማድረግ ያለብን ሓሳባችንን ስብስብ አድርገን የኢማሙን ቂርኣት ማዳመጥ ነው።አንዳንድ ሰዎች ኢማሙ ረጅም ሱራ የሚቀራ ከሆነ እነሱ የሚያውቁትን አጭር ሱራ እየደጋገሙ ይቀራሉ።ይህ ትክክል አይደለም።የኛን ቂርኣት ትተን የኢማሙን ቂርኣት ነው ማድመጥ ያለብን።ፋቲሃ ከቀራን በኋላ ዝም ብለን የኢማሙን ቂርኣት የምናዳምጠው እኛ የማናቀውን ሱራ ሲቀራ ብቻ ሳይሆን የምናቀውንም ሱራ ሲቀራ ጭምር ነው።
➌ መስጂድ ውስጥ ድምፅን ከፍ አድርጎ ማውራት
ብዙ ሰዎች ተራዊሕ እየተሰገደ ሲደክማቸው እረፍት ይወስዳሉ።ይህ ምንም ችግር ያለው ነገር አይደለም ፤ ችግሩ ያለው ለእረፍት በተቀመጥንበት ሰአት ዝም ብሎ ቁጭ ከማለትና የኢማሙን ቂርኣት ከማዳመጥ ይልቅ የተለያዩ አጀንዳዎችን እያነሱ የሰጋጆችን ቀልብ በሚሰርቅ መልኩ ማውራቱ ነው።ይህ ተግባር አንድ ሊሰግድ መስጂድ ከገባ ሰው የሚጠበቅ አይደለምና ከዚህ ድርጊት እንቆጠብ።"አተርፍ ባይ አጉዳይ" አንሁን ‼ መስጂድ የሄድነው ሰግደን ወደ አሏህ ለመቃረብ እንጂ ሰጋጆችን አዛ አድርጎ የአሏህን ቁጣ ተሸክሞ ለመመለስ አይደለም። ስለዚህ የቻልነውን ያህል ሰግደን ሲደክመን ዝም ብለን በመቀመጥ እረፍት ማድረግ ነው ያለብን።አሏሁ ሱብሃነሁ ወተዓላ ቁርኣን ሲቀራ ምን ማድረግ እንዳለብን ሲነግረን እንዲህ ይለናል ፦
" وَإِذَا قُرِئَ الْقُرْآنُ فَاسْتَمِعُوا لَهُ وَأَنصِتُوا لَعَلَّكُمْ تُرْحَمُونَ "
ቁርኣንም በተነበበ ጊዜ እርሱን አዳምጡ፡፡ ጸጥም በሉ፡፡ ይታዘንላችኋልና፡፡( አል አዕራፍ 204)
ከዚህም ብሶ ሶላት እየተሰገደ መስጂድ ወስጥ ሶሻል ሚዲያን መጠቀም ደግሞ ምንኛ የከረፋ ሸይጧናዊ ተግባር ነው!? ለመሆኑ ሁለመናችንን የሚከታተል አምላክ እንዳለን ዘነጋን?? ለአሏህ ቤት ያለንስ ክብር ምን ዋጠው!? ከቶውኑ የሙስሊም ተግባር ነውን!?... ብቻ አሏህ ይድረስልን!!
➌ ቁጭ ብሎ ጠብቆ ጠብቆ ኢማሙ ሩኩዕ ሲያደርግ እየሮጡ መጥቶ ሶላቱን መቀላቀል።
እንዲህ የምናደርግ ሰዎች ከዚህ ተግባራችን ልንታቀብ ይገባል ምክንያቱም መልዕክተኛው ﷺ እንዲህ ይሉናልና
ﻳﻘﻮﻝ ﷺ : " ﻻ ﺻﻼﺓ ﻟﻤﻦ ﻟﻢ ﻳﻘﺮﺃ ﺑﻔﺎﺗﺤﺔ ﺍﻟﻜﺘﺎب" متفق عليه
"ፋቲሃን ላልቀራ ሰው ሶላት የለውም" ( ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
ስለዚህ ቁጭ ብለን ጠብቀን ጠብቀን ኢማሙ ሩኩዕ ሊያደርግ ሲል እየሮጥን ሄደን ፋቲሃን ሳንቀራ ሩኩዕ ብናደርግም ረከዓውን አላገኘነውም ነው ሚባለው ፤ ስለዚህ ያንን ረከዓ መድገም ይጠበቅብናል። ከመጀመሪያው ጀምረን ሶላቱን ከኢማሙ ጋር መከተል ካልቻልን ማድረግ ያለብን ቢያንስ ቢያንስ ፋቲሃ ለመቅራት የሚያስችለን ያህል ጊዜ አስቀርተን ወደ ሶላቱ እንቀላቀል።ያለበለዚያ ግን ረከዓውን መድገም ይኖርብናል።
ማስታወሻ‼
ከቤቱ እየመጣ ወይም ዉዱዕ ለማድረግም ይሁን ለሌላ ጉዳይ ከመስጂድ ወጥቶ ሲመለስ ኢማሙን ሩኩዕ ላይ ቢያገኘውና ሳይነሳ ከደረሰበት መቀላቀል ይችላል።ረከዓውንም የግድ ድገም አንለውም ምክንያቱም ፋትሃውን የተወው ሆን ብሎ አይደለምና።ነገር ግን ይህም ሆኖ ሳለ ረከዓውን ደግሞ ቢሰግድ ምንም ችግር የለውም ፤ ይልቁንም ከኡለሞች ልዩነት ለመውጣት የተሻለ ይሆናል።ረከዓውን በግዴታነት ይድገም የሚባለው ሆን ብሎ ቁጭ ብሎ ጠብቆ ኢማሙ ለሩኩዕ ሲወርድ ተንደርድሮ የሚመጣውና ሶላቱን የሚቀላቀለው ነው።
➎ ሽቶ ተቀባብቶ ፤ ተገላልጦ መውጣት( ሴቶችን ብቻ የሚመለከት ነው)
በመሰረቱ ሴቶች መስጂድ ከሚሰግዱት ይልቅ ቤታቸው ውስጥ ተሰትረው የሚሰግዱት ሶላት ይበልጣል።ነገር ግን መስጂድ ሄደን እንሰግዳለን ካሉ አንከለክላቸውም።ባይሆን ወደ መስጂድ ሲሄዱ እንዴት መሄድ እንዳለባቸው አስመልክቶ መልዕክተኛችን ﷺ
እንዲህ ይላሉ ፦
"ﻻ ﺗﻤﻨﻌﻮﺍ ﺇﻣﺎﺀ ﺍﻟﻠﻪ ﻣﺴﺎﺟﺪ ﺍﻟﻠﻪ ﻭﻟﻜﻦ
ﻟﻴﺨﺮﺟﻦ ﻭﻫﻦ ﺗﻔﻼﺕ" رواه أبو داود
"የአሏህ ሴት ባሮችን የአሏህን መስጂዶች አትከልክሏቸው( ከመሄድ) ፤ ነገር ግን እነሱ "ተፊላት" ሆነው ይውጡ" (አቡ ዳውድ ዘግበውታል)
✔ "ተፊላት" ለሚለው የመልዕተኛው ﷺ ንግግር ከተሰጡት ማብራሪያዎች መካከል
—ሽቶ ሳይቀቡ
—ወንዶችን የሚፈትን የትኛውንም ነገር ሳይጠቀሙ
— ከቃሉ ቋንቋዊ መሰረት ተነስተው መጥፎ ጠረን ያለው፣ ማድቤት በሚሰሩበት ልብስ ይውጡ የሚል ትርጉም ሰጥተውታል።
1 201
Repost from Muzemil Behja Abu Hanif
ወንድሜ ቴምር በእጅህ ይዘህ ለማፍጠር ውሃ አትፈልግ‼
ተወዳጅ የሆኑ የፆም አዳቦች
1—ስሁርን መመገብ በፆም ላይ ከተደነገጉ ህግጋቶች መካከል አንዱና አንዲሁም የኛ የሙስሊሞች ፆም ከከሀዲያን ፆም የሚለይበት ሱና ነው።መልዕክተኛውም ﷺ እንዲህ በማለት ስሁር እንድንመገብ ያዙናል
"تسحروا فإن في السحور بركة" روه متفق عليه
"ስሁርን ተመገቡ፤ በስሁር ላይ በረካ አለ"
(ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
ስለዚህ ይህንን ነብያዊ ትዕዛዝን ለመተግበር የተቻለንን ሁሉ እናድርግ።ብዙ ሰዎች ስሁር ከበላው ጨጓራዬ ያመኛል በማለት ከዚህ የመልዕክተኛው ﷺ ፈለግ ወደኃላ ይላሉና እኛም እንደዛ እንዳንሆን።ያም ማለት ጨጓራችን እያመመን እንብላ ማለት ሳይሆን ሸሪዓችን ለዚህ አማራጩን ሰቶናልና ያንን አማራጭ እንጠቀም ነው።ለምሳሌ ለስሁርነት ከምንጠቀማቸው የምግብ አይነቶች ሁሉ ቴምር የተሻለ መሆኑን ሲነግሩን እንዲህ ይሉናል
"نعم سحور المؤمن التمر" روه أبو داود
"የሙዕሚን ስሁሩ ቴምር መሆኑ ምንኛ ያማረ ነው"
ቴምርም የማይስማማን ከሆነ ውሃን በመጠቀም የስሁርን አጅር ማግኘት እንደምንችል የሚያሳይ ሐዲስ ተዘግቦ እናገኛለን።ይህም
"السحور كله بركة فلا تدعوه ولو أن يجرع أحدكم جرعة من ماء فإن الله وملائكته يصلون على المتسحرين" رواه أحمد
"ስሁር ሁሉ ነገሩ በረካ ነውና አትተዉት፤አንድ ጊዜ ውሃ መጎንጨት እንኳን ቢሆን( ስሁርን አትተዉት)፤ አሏህ እና መላዕክቶቹ ስሁርን በሚመገቡ ሰዎች ላይ ሶለዋት ያወርዳሉ።"( ኢማሙ አህመድ ዘግበውታል)
ግዴታ ላልሆነ ነገር ይህ ሁሉ መከራ ምን አመጣው ሚል አይጠፋም።እናም ወዳጄ የምንም መከራ መጥቶ አይደለም ነገር ግን ቀላል ነገር ሰርተን ለምን ትልቅ አጅር የምናገኝበትን መልካም አጋጣሚ አንጠቀምም ነው ሀሳቤ።
ማስታወሻ‼
ስሁርን ስንበላ ወደ ሱብሒ ሰዓት ማስጠጋቱን አንርሳ ምክንያቱም
1— ስሁርን ወደ ሱብሒ አስጠግቶ መብላት የመልክተኛችን ፈለግ ስለሆነ።በመልክተኛው ﷺ ስሁር መጨረስና ለሱብሒ አዛን እስኪባል ድረስ የነበረው ክፍተት 50 የቁርአን አንቀፆችን ለማንበብ የሚያስችል ጊዜ ብቻ እንደነበረ ሰሓቦቻቸው ነግረውናል።
2—ብዙዎች ከሚሰሩት ከባድ ጥፋት ለመትረፍ ይረዳናልና።ብዙ ሰዎች ስሁርን በግዜ በልተው ይተኙና ሱብሒ ሶላትን ግዜው ካለፈ በሗላ ይሰግዳሉ።ይህ ተግባር አደገኛ ተግባር ነውና እንዲህ የምናደርግ ሰዎች ልንጠነቀቅ ይገባል።የተሻለው ስሁርን አርፍደን በልተን በዛው ሱብሒን መስገድ ነው።
(2) የፍጥር ሰአት እንደገባ ቶሎ ማፍጠር
ቶሎ ማፍጠርን አስመልክቶ እንዲህ የሚል ሐዲስ መጥቷል
"لا يزال الناس بخير ما عجلوا الفطر" متفق عليه
"ሰዎች ፍጥር እስካቻኮሉ ድረስ መልካም ነገር ላይ ከመሆን አይወገዱም"( ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
አሏህም ሐዲሰል ቁድሲይ ላይ እንዲህ ይለናል
"إن أحب عبادي إلي أعجلهم فطرا" رواه الترمذي
"እኔ ዘንድ ይበልጥ ተወዳጅ የሆኑት ባሮቼ ፊጥርን የሚያቻኩሉት ናቸው"( ቲርሚዚ ዘግበውታል)
በሸሪአችን ሰአቱ ከገባ ባገኘነው የምግብ አይነት ማፍጠር የተፈቀደ ነው።ነገር ግን በዚህ መልኩ ቢሆን የተሻለና የተመረጠ ይሆናል።ይህም
1—ከተገኘ እሸት ቴምር( እኛ ጋር ይገኛል ተብሎ አይታሰብም)
2—ካልተገኘ የበሰለውን ቴምር(አሁን ሀገራችን ላይ በየ ሱቁ የሚሸጠው ቴምር)
3—ሁለቱም ከታጡ ደሞ በውሃ ማፍጠር
ይህንን አስመልክቶ እንዲህ የሚል ሐዲስ ተዘግቦ እናገኛለን
"كان النبي يفطر قبل أن يصلي على رطبات، فإن لم تكن رطبات فتمرات، فإن لم تكن تمرات حسا حسوات من ماء" رواه أحمد والترمذي
"ነብያችን ﷺ ከመስገዳቸው( መጝሪብን) በፊት በእሸት ቴምር ያፈጥሩ ነበረ፤ እሸት ቴምር ከሌለ ደሞ በበሰለው ቴምር፤ የበሰለው ቴምር ከሌለ ደሞ የተወሰነ ውሃን ይጎነጩ ነበር።"
( ኢማሙ አህመድና ቲርሚዚ ዘግበውታል)
ከዚህ እንደምንረዳው ከውሃ ቴምር ይቀደማል።በዚህም መሰረት ቴምርን ይዞ ለማፍጠር ውሃ መፈለግ የተሻለውን ትቶ ወዳነሰው ነገር መሄድ ይሆንብናልና በያዝነው ቴምር እናፍጥር።
ሶስቱም ካልተገኙ ግን በተገኘው የምግብ አይነት ማፍጠር እንችላለን።ከዚህ በዘለለ ግን የፍጥር ሰኣት ደርሶ ምንም አይነት ምግብ የሌለበት ቦታ ከሆነ ያለው( ለምሳሌ ጉዞ ላይ ከሆነ) በልቡ ማፍጠርን ይነይታል እንጂ ምንም ካጣ ጣቱን ይጥባ ወይም ምራቁን ሰብስቦ ይዋጥ የሚባል ነገር የለም ምክንያቱም ምንም ማስረጃ የለውምና።
እናስተውል‼
ከማፍጠራችን ጋር መልዕክተኛው ﷺ ፆመኛ በሚያፈጥርበት ሰአት የሚያደርገው ዱአ አይመለስም ስላሉ ዱአ ማድረግን አንዘንጋ።
4—ከዋጂብ ሶላቶች በተጨማሪ ሱና ሶላቶች ላይ መበርታት
5—ሶደቃ ማብዛት በተለይም ፆመኛን ማስፈጠር ላይ እንትጋ
6— ዚክር ላይ መበርታት
አሏህ እንዲህ በማለት እሱን እንድናወሳው ያዘናል
فَاذْكُرُونِي أَذْكُرْكُمْ وَاشْكُرُوا لِي وَلَا تَكْفُرُونِ
"አስታውሱኝም፤ አስታውሳችኋለሁና ለኔም አመስግኑ፤ አትካዱኝም፡፡"
ስለዚህ ከሶላት በኋላ፣ጥዋት ላይ፣ሲመሽ፣ስናፈጥር፣ወደ መስጂድ ስንሄድ...............ወዘተ የሚባሉ ዚክሮችን ማለትን አንርሳ
7— ባገኘነውና በተመቸን አጋጣሚ ቤሰቦቻችንም ይሁን ሌሎችን ዚያራ ማድረግን ልማዳችን እናድርግ።በተለይም ከወለጆቻችን ተለይተን የምንኖር እህትና ወንድሞች ወላጆች "ወልጄ ባዶ ቀረው " የሚሉበት ዘመን ላይ ነው ያለነውና ከሸሪዓዊ ግዴታ ባለፈ ቀልባቸውን ላለመስበር ስንል ምንም ልናደርግላቸው ባንችልም እንኳን እኛ እነሱን ብለን ያሉበት ድረስ መሄዳችን ብቻ ውስጣቸው ላይ የሚፈጥረው ትልቅ ደስታ አለና ምን ይዤ ነው ምሄደው ምንም የለኝም ሳንል እንዘይራቸው።ከሀገር ውጭ ያለን ደሞ እርቂያለው ሳንል ባለንበት ሆነን በስልክ እናስታውሳቸው።
8— ፆመኛ በሆንበት ሰኣት ይህንን ፆም እየተመኙት ሳያገኙት ወደ አኼራ የሄዱ ብዙዎች አሉና እኛን ለዚህ ፆም ስለወፈቀን ምስጋናችንን ማድረስ ይኖርብናል ምክንያቱም አሏህ እንዲህ ብሏልና
وَإِذْ تَأَذَّنَ رَبُّكُمْ لَئِن شَكَرْتُمْ لَأَزِيدَنَّكُمْ ۖ وَلَئِن كَفَرْتُمْ إِنَّ عَذَابِي لَشَدِيدٌ
ጌታችሁም «ብታመሰግኑ በእርግጥ እጨምርላችኋለሁ ብትክዱም (እቀጣችኋለሁ) ቅጣቴ በእርግጥ ብርቱ ነውና» በማለት ባስታወቀ ጊዜ (አስታውሱ)፡፡
. በፀጋዎቹ ላይ እሱን ከማመስገን አንዘናጋ።
.
.
.
.
.
.
እንደተለመደው እነዚህን ለምሳሌነት ጠቀስኩ እንጂ ተወዳጅ የሆኑ የፆም አዳቦች እነዚህ ብቻ ናቸው ማለቴ አይደለም።አስተዋይ ማመላከት ይበቃዋል ነውና ነገሩ ለማመለካት ነው እነዚህን የጠቆምኩት።ጠቅለል ባለ መልኩ በሸሪዓችን በተወዳጅነት የተደነገጉ ነገራቶችን ረመዷን ላይ ከሌላው ጊዜ በተሻለ መልኩ በመተግበር ረመዷን ላይ ለምንሰራቸው ስህተቶች ማበሻና ረመዳናችንን በእነዚህ ተወዳጅ አዳቦች ያማረና የተሳካ እናድርገው።
አሏህ እሱ ለሚወደው ሁሉ ይግጠመን‼‼
