1 201
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-1530 days
Posts Archive
1 201
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የሸዋል ስድስት ቀናትን ፆም የሚመለከቱ ነጥቦች
~
1. ከሸዋል ስድስት ቀናትን መፆም ፋይዳው ምንድነው?
መልስ፦ ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
مَنْ صَامَ رَمَضَانَ ثُمَّ أَتْبَعَهُ سِتًّا مِنْ شَوَّالٍ كَانَ كَصِيَامِ الدَّهْرِ
“ረመዷንን ፁሞ ከዚያም ከሸዋል ስድስት ያስከተለው አመት እንደመፆም ነው።” [ሙስሊም፡ 1164]
ስለዚህ ስድስት ቀናትን በሸዋል ወር ውስጥ መፆም አጅሩ ከረመዷን ወር ፆም ጋር የሚቆራኝ ነው ማለት ነው።
2. ከሸዋል ስድስት ቀናትን መፆም የሚጠቁመው ሐዲሥ ሰነዱ አስተማማኝ ነውን?
መልስ፦ ሐዲሡ ሚዛን በሚደፋ አቋም ለማስረጃነት በቂ ነው። ዝርዝር የፈለገ ይህንን ሊንክ ተከትሎ ይመልከት፦ https://tinyurl.com/mucfx3ny
3. ከሸዋል ውጭ ባሉ ወራት ውስጥ ስድስት ቀናት ቢፆም የሸዋልን ፆም ይተካልን?
መልስ፦ ማስረጃ የመጣው ሸዋልን በተመለከተ ብቻ ነው። ከዚህ ውጭ ለማለት የሚያስችል መረጃ የለም።
4. አከታትሎ ነው ወይስ አፈራርቆ ነው የሚፆሙት?
መልስ፦ በሸዋል ወር ውስጥ እስከሆነ ድረስ አከታትሎም ይሁን አፈራርቆ፣ ቀጥታ ከዒድ በኋላም ይሁን አዘግይቶ በፈለገው መልኩ መፆም ይችላል።
5. ፆሙን ከሸዋል አንድ መጀመር ይቻላል?
መልስ፦ ሸዋል አንድ ዒድ ነው። በዒድ ቀን መፆም ደግሞ አይፈቀድም።
6. ቀዷእ ያለበት ሰው ሸዋልን መፆም ይችላል?
መልስ፦ ከፊል ዓሊሞች አይቻልም ይላሉ። የአብዛኞቹ ዓሊሞች አቋም ግን ይቻላል የሚል ነው። ጠንካራውም አቋም ይሄ ነው። ይህንን ከሚጠቁሙ መረጃዎች ውስጥ፦
[ማስረጃ አንድ]፦
እናታችን ዓኢሻህ ረዲየላሁ ዐንሃ እንዲህ ብላለች፦
كانَ يَكونُ عَلَيَّ الصَّوْمُ مِن رَمَضَانَ ، فَما أسْتَطِيعُ أنْ أقْضِيَ إلَّا في شَعْبَانَ
ከረመዷን (ያልፆምኩት) ፆም ይኖርብኝ ነበር። በሸዕባን እንጂ ቀዷኡን ማውጣት አልችልም ነበር።” [ቡኻሪ፡ 1149] [ሙስሊም፡ 1849]
ልብ በሉ! ሸዕባን በኢስላማዊው አቆጣጠር ከረመዷን በፊት ያለው ወር ነው። የረመዷንን ቀዷእ ሳታወጣ ቀጣዩ ረመዷን ሲቃረብ ነበር የምትፆመው። በዚህ መሃል ላይ ትልልቅ አጅር ያላቸው የዐረፋ ፆም፣ የዐሹራእ ፆም፣... አሉ። ዓኢሻ ይህን ሁሉ አትፆምም ነበር፣ ከአመት እስካመት ሱና ፆም አትፆምም ነበር ብሎ ማሰብ ይከብዳል።
“አይ ለሳቸው ስትል ነበርኮ የረመዷንን ቀዷእ የምታዘገየው” ከተባለ “አዎ። ነብያችን ﷺ ሸዕባንን አብዛኛውን ይፆሙት ስለነበር ሸዕባን ላይ ቀዷእ ለማውጣት ሰፊ ጊዜ ይኖራታል። ግና እሳቸውኮ
* ዐረፋና ዐሹራእ ይፆሙ ነበር።
* በሌሎችም ወራት “አያፈጥሩም እስከምንል ድረስ ይፆሙ ነበር” ብላለች ዓኢሻ። [ቡኻሪ፡ 1969]
* ከየወሩ ሶስት ቀን ይፆሙ ነበር። [አቡ ዳውድ፡ 507]
* በየ ሳምንቱም ሰኞና ሐሙስም ይፆሙ ነበር። [ቲርሚዚይ፡ 745]
* በተጨማሪም “ከረመዷን ቀጥሎ በላጩ ፆም የሙሐረም ወር ፆም ነው”ብለዋል። [1163]
* በየወሩ “አያመል ቢድ” ማለትም 13ኛ፣ 14ኛ እና 15ኛ ቀናትን መፆምንም አዘዋል። [ነሳኢ፡ 7/222] [ቲርሚዚይ፡ 761]
ይህ ሁሉ ከመሆኑ ጋር የረመዷንን ቀዷእ እስከ ሸዕባን ድረስ የምታዘገይበት አንዱ ምክንያት ቀጣይ ረመዷን እስካልገባ ድረስ ማዘግየት ስለሚቻል ነው። እንጂ በዚህ ሁሉ መሃልም መፆም ትችል ነበር።
[ማስረጃ ሁለት]፦
የረመዷንን ቀዷእ ወሩ እንዳለቀ ወዲያውኑ አከታትሎ መፆም ግዴታ አይደለም። ይሄ የብዙሃን ዑለማእ አቋም ነው። ቀጣይ ረመዷን እስካልገባ ድረስ ማዘግየት ይቻላል። ወዲያውና አከታትሎ መፈፀም ግዴታ ካልሆነ ደግሞ መሃል ግዴታ ያልሆኑ ፆሞችን መፈፀም የተከለከለ አይሆንም። ይህ እንግዲህ ቀዷእ ላለበት ሰው በላጩ አፈፃፀም ቀድሞ ቀዷኡን መፆም፣ ከዚያም የሸዋልን ስድስት ማስከተል ከመሆኑ ጋር ነው።
ነገር ግን በወር አበባ ወይም በሌላ ምክንያት በርከት ያለ ቀዷእ ያለ ከሆነ ሸዋልን ለመፆም በቂ ጊዜ ላይኖር ይችላል። ወይም የፆሙ ጊዜ በመደራረቡ ሊከብድ ይችላል። በዚህና መሰል ሁኔታ ላይ ላለ አካል ሸዋልን የመፆም አጅር እንዳያልፈው ቢያስቀድምና ቀዷኡን አረፍ ብሎ ቆይቶ ቢፆም የሚከለክለው ግልፅ ማስረጃ የለም።
ብዥታዎች፦
-
የግዴታ ፆምን ቀዷእ ሳይፆሙ ሱና ፆም መፆም አይቻልም የሚሉ ዓሊሞች እንዳሉ ገልጫለሁ። ከሚጠቅሷቸው ማስረጃዎች ውስጥ፦
[አንዱ]
መግቢያዬ ላይ የጠቀስኩትን “ረመዷንን ፁሞ ከዚያም ከሸዋል ስድስት ያስከተለው አመት እንደመፆም ነው” የሚለውን ሐዲሥ ነው። ማስረጃ የሚያደርጉበት አግባብ የተጠቀሰው አጅር ሙሉ ረመዷንን ፁሞ ከዚያም ከሸዋል ስድስት ያስከተለን ነው የሚል ነው።
ይሄ ግን አብዛኛው ሙስሊም ረመዷንን ሙሉውን ስለሚፆም በዚህ መልኩ ተገለፀ እንጂ በተጨባጭ ሸሪዐዊ ምክንያት ሙሉውን ያልፆመ ሰው ከተጠቀሰው አጅር ውጭ ይሆናል ማለት አይደለም። ለምሳሌ ያክል ነብያችን ﷺ “ረመዷንን አምኖና አጅሩን አስቦ የፆመ ሰው ያለፈው ወንጀሉ ይማርለታል” ብለዋል። ይህ ማለት ግን በወር አበባ ምክንያት ሙሉውን ያልፆመች ሴት ይህንን አጅር አታገኝም ማለት አይደለም።
[ሁለተኛ] ማስረጃ የሚያደርጉት ተከታዩን ሐዲሥ ነው፦
من أدركَ رمضانَ وعليهِ من رمضانَ شيءٌ لم يقضهِ، لم يتقبَّل منهُ ومن صامَ تطوُّعًا وعليهِ من رمضانَ شيءٌ لم يقضهِ، فإنَّهُ لا يتقبَّلُ منهُ حتَّى يصومَهُ
“በሱ ላይ ቀዷእ ያላወጣው የረመዷን ፆም እያለበት ረመዷን የደረሰበት ሰው አላህ አይቀበለውም። በሱ ላይ ቀዷእ ያላወጣው የረመዷን ፆም እያለበት ግዴታ ያልሆነ ፆም የፆመ ሰው ቀዷኡን እስከሚፆም ድረስ ተቀባይነት አይቀበለውም።” [ሙስነድ አሕመድ፡ 8606]
መልስ፦ ዶዒፍ ነው። [አልዒለል፣ ኢብኑ አቢ ሓቲም፡ 768]
[ሶስተኛ] የሚጠቀሰው እንዲህ የሚል ነው፦
አንድ ሰው፡ “የረመዷን ቀዷእ አለብኝ። ከመሆኑም ጋር አስሩን ትርፍ ፆም ልፆም ፈልጌ ነበር” ሲል አቡ ሁረይራህ ረዲየላሁ ዐንሁ፡ “አይሆንም። ይልቁንም በአላህ ሐቅ ጀምር፣ እሱን ቀዷእ አውጣ። ከዚያ በኋላ የፈለግከውን ትርፍ ፆም ፁም” አሉ። [ሙሶነፍ ዐብዲረዛቅ፡ 7715]
መልስ፦ ግንዛቤው ላይ የተለያዩ ሃሳቦች ከመሰንዘራቸው ጋር ቀጥታውን ስንወስድ ከዓኢሻ ሐዲሥ ጋር የሚቃረን ነው። የዓኢሻ ሐዲሥ ደግሞ የነብዩ ﷺ ኢቅራር (ማፅደቅ) ያለበት ስለሆነ ቅድሚያ ይሰጠዋል።
[ማጠቃለያ]:-
ስለዚህ የረመዳን ፆም ቀዷ ያለበት ሰው
① ለቀዷው ሰፊ ጊዜ ስላለና
② የሸዋል ጊዜ አጭር ስለሆነ ሸዋልን አስቀድሞ መፆም ይችላል።
* ይህንን ነጥብ ዘለግ አድርጌ መዳሰስ የፈልግኩት ሸዋል ቢያልፍም እንኳ ቀዳኡን ሳይፆሙ የሸዋልን ስድስት ቀናት መፆም አይቻልም የሚሉ ዑለማዎችን ፈትዋ ነጥለው ትኩረት የሚሰጡ ስላሉ ነው። ቀደም ብዬ እንደጠቀስኩት መፆም ይቻላል የሚለው አቋም የብዙሃን ዑለማእ ምርጫ ነው። በሸይኽ ሙቅቢል ፈትዋ ፅሁፌን ላሳርግ:-
1 201
"" የዒድ ግብዣ ""
📢 በ ኡስታዝ ኸድር አሕመድ አል ከሚሴ (አቡ ሓቲም)
https://t.me/UstazKedirAhmed
https://t.me/UstazKedirAhmed
https://t.me/UstazKedirAhmed
1 201
Repost from Muzemil Behja Abu Hanif
الله أكبر
الله أكبر
الله أكبر
لا إله إلا الله
الله أكبر
الله أكبر
ولله الحمد
كبّروا وهلّلوا.. عظّموا شعائر الله
🕋عيد مبارك تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال كل عم وأنتم بخير.
1 201
Repost from Muzemil Behja Abu Hanif
عيدكم مبارك !
تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال !
ዒዱኩም ሙባረክ ተቀበለሏሁ ሚን'ና ወሚንኩም ሷሊሃል አዕማል !
ዒዳችሁ የተባረከ ይሁንላችሁ ፤ ከእናንተም ሆነ ከእኛ መልካም ስራችንን አላህ ይቀበለን ።
✍️ ወንድማችሁ አቡ ሂበቲ
https://t.me/Menhaje_Selefiya
1 201
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
በየተክቢራዎቹ እጅን እስከ ትከሻ ወይም ጆሮ ድረስ ማንሳት ከሰለፎች ተገኝቷል። [ሙሶነፍ ዐብዲረዛቅ፡ 5699] ይሄ የብዙሃኑ ዑለማእ አቋም እንደሆነም በገዊይ ጠቅሰዋል። [ሸርሑ ሱናህ፡ 4/310]
4.9. በየተክቢራዎቹ መሃል የሚባልን ዚክር በተመለከተ ከነብዩ ﷺ የተላለፈ ሶሒሕ ማስረጃ የለም። (ክፍተቱ ካለ) አላህን ማመስገንና በነብዩ ﷺ ላይ ሶለዋት ማውረድ እንደሚቻል ከኢብኑ መስዑድ ተገኝቷል። [አልኢርዋእ፡ 642]
4.10. የተክቢራዎቹን ቁጥር የተጠራጠረ እርግጠኛ የሆነበትን ዝቅተኛውን ይዞ ቀሪውን ይሞላል።
4.11. ልክ እንደሌሎች ሶላቶች የመክፈቻ ዱዓእ መቅራቱ ተገቢ ሲሆን ቦታውም ከመክፈቻው ተክቢራ ቀጥሎ ከተጨማሪዎቹ ተክቢራዎች በፊት መሆን እንዳለበት የብዙሃን ዑለማዎች እይታ ነው።
4.12. ፋቲሐን መቅራት ግዴታ ነው። ከዚህ በተጨማሪ ለኢማሙ ሱረቱል አዕላን እና ሱረቱል ጋሺያን ወይም ሱረቱል ቃፍና ሱረቱል ቀመርን መቅራቱ ከሱና ነው። [ሙስሊም] ለኢማሙ በቂራአህ ድምፅን ከፍ ማድረግ ሱና ነው።
4.13. የዒድ ሰላት ያለፈው ሰው ሳይሰላመት ከደረሰ ያገኘውን አብሮ ሰግዶ ያለፈውን ይሞላል። ከተሰላመተ በኋላ የደረሰ ደግሞ ካገኘ ከሰዎች ጋር ካልሆነ ብቻውንም ቢሆን ይሰግዳል። በሆነ ምክንያት ወደ መስገጃው ቦታ መውጣት ያልቻሉ ከቤታቸውም ቢሆን መስገድ ይችላሉ። [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 369]፣ [ቡኻሪይ፣ ተዕሊቅ፡ 2/471]
4.14. ከዒድ ሶላት በፊትም በኋላም ከመስገጃው ቦታ የሚሰገድ መደበኛ ሱና የለም። ቤት ከተመለሱ በኋላ ግን ነብዩ ﷺ 2 ረከዐ ይሰግዱ ነበር። [ቡኻሪይ]፣ [አልኢርዋእ፡ 3/100] የዒዱ ሶላት የሚሰገደው መስጂድ ውስጥ ከሆነ ግን መስጂድ እንደገባን የዒድ ሱና ሳይሆን “ተሒየተል መስጂድ” መስገድ አለብን።
4.15. ዒድ መሆኑ ከእኩለ-ቀን በኋላ ከታወቀ በቀጣዩ ቀን ይሰገዳል። [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 1050]
4.16. ዒድድና ጁሙዐ በአንድ ቀን ከገጠሙ፡- የዒድ ሶላትን የሰገደ ሰው ጁሙዐ ሰላት ላይ የመገኘት ግዴታ የለበትም። [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 984]
5. ኹጥባ፡-
5.1. የሚደረገው ከሶላት በኋላ ነው። [ቡኻሪይ፡ 963] [ሙስሊም፡ 888]
5.2. ለኹጥባው ሚንበር ይዞ መውጣት ከሱና አይደለም። [ቡኻሪይ፡ 956]
5.3. ኹጥባው አንዳንዶች እንደሚሉት አንድ ብቻ ሳይሆን ሁለት ነው። ከሰለፎች የተገኘው በዚህ መልኩ ነው። ኢብኑ ሐዝም የዑለማእ ስምምነት አለበት ብለዋል። [አልሙሐላ: 3/543] ዝርዝር የፈለገ በዚህ ሊንክ ይግባ። https://rb.gy/m3wrx
5.4. ኹጥባውን ማዳመጡ ግዴታም ባይሆን ተወዳጅ ነው። [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 2289]
5.5. ኹጥባው እየተደረገ ወሬ ማውራት አይገባም።
6. የዒድ ቀን ምግብ፡-
6.1. ዒደል ፊጥርን እና ዒደል አድሐን መፆም ፈፅሞ አይፈቀድም! [ቡኻሪይና ሙስሊም] እንዲሁም ከዒደል አድሐ በኋላ ያሉትን ሶስቱን ቀናትም (አያመ ተሸሪቅ) ሐጅ ላይ ሆኖ እርድ ያላገኘ ሰው ካልሆነ በስተቀር ለሌሎች መፆም አይፈቀድም። [ቡኻሪይ] [አሶሒሐ፡ 3573]
6.2. በዒደል ፊጥር ቀን ወደ ሶላት የሚውወጣው ከተመገቡ በኋላ ነው። የዒደል አድሐ ቀን ግን ሳይመገቡ ወጥቶ ከሶላት በኋላ መመገብ ከሱና ነው። [ቡኻሪይና ሙስሊም] [ሙስነድ አሕመድ፡ 23042]
6.3. በዒደል ፊጥር የምንመገበው ተምር ቢሆንና በተናጠል በዊትር ብንበላው የነብዩ ﷺ ሱና ነው። [ቡኻሪይ] ተምር ከሌለ ቤት ያፈራውን በመቅመስ በልቶ የመውጣቱን ሱና ልንተገብር ይገባል።
6.4. በዒደል አድሐ ቀን ከሶላት መልስ መጀመሪያ የሚፈፀመው መመገብ ሳይሆን ኡዱሒያን ማረድ ነው። [ሙስነድ አሕመድ፡ 23042]
አላህ መልካም ስራዎቻችንን ይቀበለን። ኣሚን።
(ኢብኑ ሙነወር፣ መስከረም 22/2007)
=
* ቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
* ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL
* ዋትሳፕ፦ https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M
1 201
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ዒድ - ህግጋትና ስርአቱ
~
በኢስላም አመታዊ በአሎቻችን ሁለት ናቸው። እነሱም ዒደል ፊጥርና ዒደል አድሐ። የመጀመሪያው ረመዳን እንዳለቀ በሸዋል ወር የመጀመሪያ ቀን ላይ ይውላል። ሁለተኛው - ዒደል አድሐ- ደግሞ የዙልሒጃ ወር በ10ኛው ቀን ላይ። ነብዩ ﷺ መዲና ሲገቡ የመዲና ሰዎች የሚጫወቱባቸው ሁለት በአላት ነበሯቸው። “ምንድን ናቸው እነኚህ ቀናት?” ሲሉ ጠየቁ መልእክተኛው ﷺ። እነሱም “ከጃሂሊያህ ዘመን ጀምሮ የምንጫወትባቸው ቀናት ናቸው” ብለው መለሱ። ነብዩ ﷺ “አላህ ከነሱ በተሻሉ ቀናት ተክቷችኋል፡- በአድሐ ቀን እና በፊጥር ቀን” አሉ። [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 1039]
ጥቂት ስለዒድ፡-
1. ቀኑ የደስታ ቀን ነው፡-
1.1. “ተቀበለላሁ ሚና ወሚንኩም” እያሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት መለዋወጥ ከሶሐቦች ተገኝቷል። [አልፈታዋ፡ 24/253]
1.2. ልጃገረዶች እየዘፈኑ መጫወት ይችላሉ። [ቡኻሪ፡ 949] [ሙስሊም፡ 892]
1.3. እለቱ የደስታ፣ የመብያና የመጠጫ ቀን ነው። [ሶሒሑ ቲርሚዚይ፡ 777]
1.4. ስለሆነም ቀብር ዚያራና የመሳሰሉ የእለቱን የደስታ ድባብ የሚያደፈርሱ ድርጊቶችን መፈፀም አይገባም። [አልኢብዳዕ፡ 263]
1.5. የምንደሰትበት ግን ፈፅሞ በሐራም ነገር መሆን የለበትም። “የትም ብትሆን አላህን ፍራ!” የሚለው ሐዲሥ አይረሳ።
2. ተክቢራ፡-
2.1. የሚባልበት ጊዜ፡-
* በዒደል ፊጥር - የረመዷን ወር መጨረሻ ቀን ፀሐይ ከጠለቀችበት ወይም የሸዋል ጨረቃ ከታየችበት ጊዜ ጀምሮ ነው። ምክንያቱም አላህ ተክቢራውን ከረመዷን ፍፃሜ ጋር አያይዞ ነውና የገለፀው። [አልበቀረህ፡ 185] ተክቢራው እስከ ዒድ ሰላት ድረስ ይዘልቃል።
* በዒደል አድሐ - ደግሞ ከዐረፋ ቀን ፈጅር ሶላት አንስቶ እስከ ዙልሒጃ 13 ዐስር ድረስ ከግዴታ ሰላቶች በኋላ ተክቢራ ማድረጉ ከሶሐቦች ተገኝቷል። [አልኢርዋእ፡ 653] እንዲያውም ኢጅማዕ (ወጥ ስምምነት) የመጣበት ጉዳይ እንደሆነ ነወዊይና ኢብኑ ረጀብ ጠቅሰዋል። [አልመጅሙዕ፡ 5/32] [ፈትሑል ባሪ] በዒደል ፊጥር ጊዜ ከግዴታ ሶላቶች በኋላ ተክቢራ ማድረጉ በቂ ማስረጃ የለውም።
2.3. አደራረጉ፡- ሁሉም በየፊናው እንጂ አንዱ እያወጣ ሌሎች በመከተል በህብረት ባንድ ድምፅ አይባልም። [መጅሙዑፈታዋ ኢብኒ ባዝ፡ 13/21] ባይሆን ይሄ ጉዳይ በዑለማዎች የተለያየ ሀሳብ የተሰነዘረበት ፊቅሃዊ ጉዳይ እንደመሆኑ ጉዳዩን በልኩ መያዝ ይገባል።
2.4. ድምፅን በተክቢራ ከፍ ማድረግ የተወደደ ነው። [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 4934]
2.5. ተክቢራው ሴቶችንም በተመሳሳይ የሚመለከት ነው። [ቡኻሪና ሙስሊም] ድምፃቸውን ግን ዝቅ ሊያደርጉ እንደሚገባ ዑለማዎች ይመክራሉ።
2.5. አንዳንድ አካባቢዎች እንደሚታየው በተክቢራ ሙሉ ሌሊቱን ሳይተኙ ማሳለፍ፣ ሰፈር ጎረቤቱን በከፍተኛ ድምፅ ማወክ ማስረጃ የሌለው ስራ ነው። “የሁለቱን ዒድ ሌሊቶች ነቅቶ ያደረ ሰው ልቦች በሚሞቱበት ቀን ልቡ አይሞትም” የሚለው “ሐዲሥ” በነብዩ ﷺ ላይ የተቀጠፈ እንጂ ጤነኛ መረጃ አይደለም። [አዶዒፋህ፡ 520]
2.6. ከሶሐቦች የተለያዩ የተክቢራ አፈፃፀሞች የመጡ ሲሆን የተለየ አይነት ገደብ የለውም። ከሰሐቦች የተገኙትን መያዙ በላጭ ነው።
2.7. እነዚህን ተክቢራዎች ማለት በጀማዐ ለሰገደም፣ ብቻውን ለሰገደም የተወደደ ነው። ግዴታ ግን አይደለም። [ሸርሑል ሙምቲዕ፡ 5/165]
3. ወደ መስገጃው ቦታ መውጣት፡-
3.1. ወደ መስገጃ ቦታ ሲወጣ መታጠብን፣ ሽቶ መቀባትን የሚመለከት ከሶሐቢዩ ኢብኑ ዑመር ተገኝቷል። [አልኢርዋእ፡ 104] ከነብዩ ﷺ ግን ምንም የለም። የመታጠቢያ ጊዜውም ከእለቱ ፈጅር ሶላት መልስ ቢሆን ይመረጣል። ይህን የሚያመላክት ከሰለፎች ተገኝቷል። [አልመጣሊቡል ዓሊያህ፡ 2753]፣ [አሕካሙል ዒደይን ሊልፊርያቢይ፡ 16] ትጥበቱም ሴት ከወንድ፣ ህፃን ከአዋቂ ሳይለይ ሁሉንም እንደሚመለከት ነወዊይ ጠቁመዋል። [አልመጅሙዕ፡ 2/233]
3.2. በእለቱ አቅም በፈቀደ ባማረ ልብስ ሽክ ማለት ተወዳጅ ነው። [ቡኻሪና ሙስሊም]
3.3. ለቻለ ሰው ወደ መስገጃው ቦታ በእግር መሄዱ ሱና ነው። [አልኢርዋእ፡ 636]
3.4. የወር አበባ ላይ ያሉ ሴቶች ወደ መስገጃው ሜዳ መውጣታቸው ከሱና ነው። ከመስገጃው ቦታ ግን ገለል ይላሉ። [ቡኻሪ] ሴቶች ወደ መስገጃው ቦታ ሲወጡ ሽቶ ከመቀባትና ካላስፈላጊ አለባበስ መራቅ አለባቸው።
3.5. ስጋትና እንቅፋት ከሌለ ልጆችም ሊወጡ እንደሚችሉ የሚጠቁም ማስረጃ አለ። [ቡኻሪ፡ 977] ባይሆን ሰጋጆችን እንዳይበጠብጡ ወላጆች ሊቆጣጠሯቸው ይገባል።
3.6. ከመስገጃው ቦታ ሲመለሱ መንገድ ቀይሮ መመለሱ በላጭ ነው። [ቡኻሪ፡ 986]
4. የዒድ ሶላት፡-
4.1. ሶላቱን በተመለከተ ሚዛን የሚደፋው አቋም “ግዴታ ነው” የሚለው እንደሆነ ኢብኑ ተይሚያ፣ ሶንዓኒይ፣ ሲዲቅ ሐሰን ኻን፣ ሸውካኒይ፣ አልባኒይ፣ ኢብኑ ዑሠይሚን እና ሌሎችም አስረግጠው ተናግረዋል።
4.2. ወቅቱ፡- ፀሀይ ወጥታ የጦር ቁመት ያክል ከፍ ካለች ጀምሮ በአናት ትይዩ እስከምትሆን ድረስ ያለው ነው። የዒደል ፊጥር ሶላት ዘግየት፣ የዒደል አድሐ ደግሞ ቀደም ቢል ተመራጭ ነው። [አተልኺስ፡ 144] [ሙስነዱ ሻፊዒይ፡ 74] ምክንያቱም የዒደል ፊጥር ጊዜ ዘግየት ማለቱ ዘካተል ፊጥር ለሚሰጡ ሰዎች ጊዜ እንዲኖራቸው ሲያደርግ የዒደል አድሐ ጊዜ ቀደም ማለቱ ደግሞ ከሶላት ቶሎ ተመልሰው ኡዱሒያ የሚያርዱበት ጊዜ እንዲያገኙ ያደርጋቸዋል።
4.3. የሚሰገድበት ቦታ፡- ዝናብ፣ የፀጥታ ስጋት፣ ወዘተ ካልኖረ ወጣ ያለ ሰፊ ሜዳ ላይ መሆኑ ሱና ነው። [ቡኻሪይና ሙስሊም]
4.4. ለዒድ ሶላት አዛንም ኢቃማም አይደረግም። [ቡኻሪይ፡ 962] [ሙስሊም፡ 886]
4.5. የረከዐው ብዛት፡- 2 ነው። [ቡኻሪይ፡ 964] [ሙስሊም፡ 884]
4.6. የዒድ ሶላት ውስጥ ያሉት ተጨማሪ ተክቢራዎቹ ሙስተሐብ እንጂ ግዴታ አይደሉምና በመርሳትም ሆነ ሆን ተብሎ ቢቀሩ ሶላቱ አይበላሽም። [አልሙግኒ፡ 3/275]
4.7. ቁጥራቸውም የመጀመሪያው ረከዐ ላይ ከመክፈቻው ተክቢራ ውጭ 7፤ ሁለተኛው ረከዐ ላይ ደግሞ ከመነሻው ተክቢራ ውጭ 5 ተክቢራ ነው። ይሄ ከብዙሃኑ ሶሐቦችና አኢማዎች የተገኘው እንደሆነ ኢብኑ ተይሚያ ገልፀዋል። [አልፈታዋ፡ 24/220] ብዙሃኑ ዑለማዎች ያሉትም እዚህ ላይ ነው። ባይሆን የመጀመሪያውን 7 የሁለተኛውን ስድስት፣ የመጀመሪያውን 6 የሁለተኛውን 5 ማድረጉም ተገኝቷል። 4፣ 11፣ 12፣ 13 ተክቢራዎችን ማለት እንደሚቻልም ከሰለፎች ተገኝቷል። ከዚህ በመነሳት ነገሩ ሰፊ እንደሆነና በሶሒሕ ማስረጃ በመጡት ሁሉ መስራት እንደሚቻል ያሳያል ይላሉ ሸይኹል አልባኒይ ረሒመሁላህ። [አልኢርዋእ፡ 639]
4.8. በተጨማሪ የዒድ ተክቢራዎች ላይ እጅን ማንሳት ከሶሐቦች፣ ከዐጣእ፣ አውዛዒይ፣ አቡ ሐኒፋህ፣ ሻፊዒይ፣ አሕመድና ሌሎችም ተገኝቷል። ነብዩ ﷺ ደግሞ ጥቅል በሆነ መልኩ የሶላት ተክቢራዎች ላይ እጃቸውን ያነሱ እንደነበር ማስረጃ አለ። [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 715]
1 201
Repost from SadatKemal Abu Meryem
ረመዳን ቀን 25
አየቱል ኩርሲ
ሁለት ዱአዎች
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/2473
1 201
🔖አዲስ ተከታታይ ትምህርት
📚 الأصول الثلاثة وأدلتها لشيخ الإسلام محمد بن عبدالوهاب رحمه الله تعالى -٠٢
✸| ክፍል 02
🔗 የዳውንሎድ ሊንኩን ይጫኑ Mp3
https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn/4223
═════ ≪ °📓🖇📓° ≫ ════
የኪታቡን ሶፍት ኮፒ በ Pdf መልክ በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ ↓↓↓
https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn/4220
═════ ≪ °📓🖇📓° ≫ ════
🕌 በፉሪ አቡበክር አስ-ሲዲቅ መስጂድ ለሙእተኪፎች የተዘጋጀ ኮርስ
🗓 ዛሬ ሰኞ ረመዷን 22-1445 ሂጅሪ (23 -07-2016)[01-04-2024] ከዙሁር ሰላት በኃላ የተሰጠ ደርስ ነው
🎙በሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደም
ሀፊዘሁላህ ወረዓህ
📍ትምህርቱን ለመከታተል ቻናሎቹን ይቀላቀሉ 👇👇👇
https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam
&
http://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn
1 201
Repost from SadatKemal Abu Meryem
ረመደን ቀን 23
አላህ ከአርሽ በላይ ነው
አንድ ዱአ
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/2469
