1 201
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-1530 days
Posts Archive
1 201
Repost from ትዳር እና ኢስላም 🌷🌹🥀
🌀ታላቅ የሙሓደራ ፕሮግራም📱
🔠🔠🔠🔠🔠🔠🔠🔠
😚🥰☺️🔤🔤🔤🔤🅰️🔤 ግሩፕ ላይ የዳዕዋ ፕሮግራም አዘጋጅተን እየጠበቅናችሁ እንገኛለን።
ተጋባዥ 🔠🔠🔠🔠🔠🔠🔠🔠
✅ኡስታዝ Dr. ሰኢድ ሙሳ
ርዕስ ➦ጥቂት ጥቆማዎች ለጀማሪ ዱአቶች✅
✅ኡስታዝ አቡ አብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ
ርዕስ➦በሶላት ዉስጥ ያለን ኹሹእ✔️
✅ኡስታዝ አቡ ሱፊያን
ርዕስ ➦የቀልብ መድረቅ✔️
✅ኡስታዝ አቡ ሂበቲላህ
ርዕስ➦ አላህን መፍራት✔️
✅ኡስታዝ አቡ ሀፍሷ ሙሀመድ
ርዕስ➦ከኛ ምን ይጠበቃል?✔️
💠ኡስታዝ አብዱ ሽኩር አቡ ፈዉዛን
ርዕስ ➦መልካም ስነ ምግባር✔️
🔢የፕሮግራሙ መሪ :-🔘 ሰዒድ ሙሐመድ {አቡ ሑዘይፋ}✅
✍️ኑ አብረን የሱና ኡስታዞቻችን መፅሀፍ በጋራ እናሰራጭ⚙️
❄️ቀን ዛሬ ጁማዓ✈️
ሰአት ⭐️ ከምሽቱ 3:15 ጀምሮ
ኑ
ሙሓደራው የሚካሄድበት ግሩፕ
መርከዝ አቡ ፈውዛን🔤✈️🔤
👇👇👇
t.me/merkez_abu_fewzan
t.me/merkez_abu_fewzan
1 201
በሹብሃ የወደቁ ወንድሞች የጠየቁት ጥያቄ እና መልሶች
በ ኡስታዝ ኸድር አሕመድ አል ከሚሴ(አቡ ሓቲም)
https://t.me/UstazKedirAhmed/8218
https://t.me/UstazKedirAhmed/8218
1 201
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
فَإِن قَالَ قَائِل قد أنكرتم قَول الْمُعْتَزلَة والقدرية والجهمية والحرورية والرافضة والمرجئة فعرفونَا قَوْلكُم الَّذِي بِهِ تَقولُونَ وديانتكم الَّتِي بهَا تدينون
“የሙዕተዚላንም፣ የቀደሪያንም፣ የጀህሚያንም፣ የሐሩሪያንም፣ የራፊዷንም፣ የሙርጂአንም አቋም ከተቃወማችሁ የምታራምዱትን አቋም፣ የምታምኑበትን እምነት ንገሩን የሚል ካለ…” ይልና ከላይ የጠቀስኩትን ምላሽ ያስከትላል፡፡ በደንብ ያስተውሉት፡፡ በነዚህ ነጥቦች ላይ ዐቂዳው ከሙዕተዚላና ጀህሚያ ዐቂዳ የተለየ እንደሆነ በግልፅ ቋንቋ እያስረዳ ነው፡፡ ይህንንም ንግግር ኢብኑ ዐሳኪር ስላሰፈረው “ወሃ.ብዮች አስገብተውበት ነው” የሚለው የአሕ'ባሽ ጩኸት ከንቱ ማጭበርበር እንደሆነ ግልፅ ይሆናል፡፡ መቼም በ571 ሂጅሪያ የሞተው ኢብኑ ዐሳኪር በወሃ.ቢዮች ተሸውዶ ነው እንደማይሉ እንገምታለን፡፡ እርግጠኛም ባንሆን!
[ነጥብ አራት]፡- ተገዶ ይሆን የፃፈው?
እስካሁን ኪታቡ የአቡል ሐሰን እንደሆነ፣ በውስጡም አሕ'ባሾች ከሚቀጥፉት በተለየ የአላህን ከዐርሹ በላይ መሆን፣ ለአላህ ፊት፣ እጅና አይን አለው ብሎ እንዳፀደቀ በማያወላዳ መልኩ ተመልክተናል፡፡ አሕ'ባሾች (አሽዐሪያና ማቱሪዲያ) ግን ልክ እንደ አይጥ ናቸው፡፡ አንዱን ጉድጓድ ስትደፍኑባቸው በሌላ አቅጣጫ ቆፍረው ይዘልቃሉ፡፡ በዚያ ስታሯሩጧቸው ደግሞ በሌላ በኩል ይመጣሉ፡፡ እዚህም ላይ የምናየው ይህንኑ ነው፡፡ ኪታቡ የአቡል ሐሰን ለመሆኑ እጅግ በርካታ ዑለማዎች እንደመሰከሩ ያረጋገጠው ሙሐመድ ዛሂዱል ከውሠሪ የተባለ የዘመናችን ጀህ'ሚይ “አልኢባናህ” የአቡል ሐሰን ኪታብ እንደሆነ ለማመን ተገዷል። ሆኖም ግን አምኖበት ሳይሆን ከሐንበሊዮች ጋር ለመኗኗርና በሂደት ለመቀየር የተጠቀመበት ስልት ነው ሲል አዲስ ቅጥፈት ጠንስሷል። [ተዕሊቃቱል ከውሠሪ ዐላ ተብዪን፡ 392]
"ወሃ.ቢዮች አስገብተውበት ነው" ለሚሉት የሃገራችን አሕባሾች "የለም ራሱ ነው የፃፈው" እያለ እንደሆነ አስተውላችኋል? የቅጥፈት ነገር እንዲህ አንዱ ሌላውን ይጠልፋል።
ብቻ ዐቂዳን ያክል ከባድ ጉዳይ ለመኗኗር ብሎ የማያምንበትን አዘጋጅቶ ለትውልድ አስተላለፈ ማለት ለአቡል ሐሰን ትልቅ ስድብ ነው። ይሄ ክስ ድሮም ተነስቶ ነበር። ያኔ ክሱን ያነሱት ግን “አቡል ሐሰን ሲያስመስል እንጂ ከሙዕተዚላ ከልቡ አልተመለሰም” የሚሉ ጠላቶቹ ነበሩ። ዛሬ ደግሞ “ወዳጅ ነን” የሚሉት ሆነዋል። እነዚያኞቹ በአስመሳይነት እነዚህኞቹ ደግሞ በፈሪነት እየከሰሱት ነው፡፡ የጥንቱን ክስ “አንድ ሙስሊም እንዴት ይዘቱ ልክ አይደለም የሚለውንና የማያምንበትን ኪታብ አዘጋጅቶ ለትውልድ ያስተላልፋል?!” በማለት ኢብኑ ዐሳኪር በብስጭት ተከላክሏል። [ተብዪን፡ 388] ይሄ ዛሬም ተገዶ ነው የፃፈው ለሚሉ ሰዎች አንድ መልስ ነው፡፡
ሁለተኛ ኪታቡ ቀደምት አሽዐሪዮች በፅኑ የሚያምኑበት እንደነበረ የተናገሩ ዑለማዎችን አሳልፌያለሁ፡፡ እርሱ ተገዶ ነው የፃፈው እንበል፣ ይሁን፡፡ ተከታዮቹ እንዴት በዚህ ኪታብ ማመንን መረጡ? ውሸ'ታም ጥሩ የማስታወስ ችሎታ ያስፈልገዋል፡፡ ካልሆነ ግን እንዲህ ሲተረማመስ ራሱን ያጋልጣል፡፡
[ነጥብ አምስት]፡- ከአልኢባናህ ባሻገር!
አቡል ሐሰን የአላህን ከዐርሹ በላይ መሆን ያፀደቀው፣ ለአላህ ሁለት እጆች፣ ሁለት አይኖች፣… እንዳሉት እንደሚያምን ያረጋገጠው በ“አልኢባናህ” ኪታቡ ብቻ አይደለም። ዘሀቢ እንዲህ ይላሉ፡- “ለአቡል ሐሰን በአላህ መገለጫዎች ላይ የሰለፎችን መዝሀብ መሰረቶች የሚጠቅስባቸው በኡሱል ላይ የተዘጋጁ አራት ኪታቦችን አይቻለሁ። በውስጣቸው በሲፋት ላይ የመጡ ዘገባዎች ‘እንደመጡ ይተላለፋሉ። በዚህም አምናለሁ። ተእዊል አይደረጉም’ ይላል።” [አሲ፞የር፡ 15/86]
የአራተኛውን ኪታብ ስም አላውቅም፡፡ ሶስቱ ግን አልኢባናህ፣ መቃላቱል ኢስላሚዪ፞ን እና ሪሳላ ኢላ አህሊ ሠ፞ግር ናቸው፣ ወላሁ አዕለም፡፡ ከአልኢባናህ በተጨማሪ በነዚህ ኪታቦችም ውስጥ ከአህሉ ሱና፞ ጋር የሚገጥመውን ዐቂዳውን በግልፅ ያሰፈረ ሲሆን የዛሬውን የአሕባ'ሾች እምነት ከአህሉ ሱና፞ ኢጅማዕ ያፈነገጠ የሙዕተዚላ እምነት እንደሆነ በማያሻማ መልኩ አስቀምጧል፡፡ ይህም እነዚህን የዐቂዳ ነጥቦች “ወሃ.ቢዮች አስገብተውበት ነው” የሚሉ ዋሾዎችን አከርካሪ የሚሰብር ነው፡፡ ይህንን ሊንክ ይከተሉና በዚህ ዙሪያ የፃፍኩትን መመልከት ይችላሉ፡፡ https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=3473393672732079&id=100001844423938
ለምሳሌ ያክል እንዲህ ብሏል፡- “ሙዕተዚላዎች፡ የአላ፞ህ መውረድ ማለት የተአምራቱ መውረድ ነው፤ ወይም መልአኩ ትእዛዙን ይዞ መውረዱ ነው ብለዋል።” [መቃላቱል ኢስላሚዪን፡ 291] ይሄ የአሕባሽ ዐቂዳ እንደሆነ አስተውሉ! የራሱን ዐቂዳ ሲገልፅ ግን “ጌታ - ዐዘ፞ ወጀለ፞ - ወደ ቅርቢቷ ሰማይ በመውረድ ‘ለማኝ አለ?’ ‘ምህረት ጠያቂ አለ? ይላል’ የሚሉ ሙሐዲሦች የሚያረጋግጧቸውን ዘገባዎች በሙሉ እናምንባቸዋለን። ሌሎችም ያስተላለፏቸውንና ያፀደቋቸውንም እንዲሁ። የማፈንገጥና የማጥመም ሰዎች ከሚያራምዱት በተቃራኒ እናምንባቸዋለን” ብሏል፡፡ “ወሃ.ቢዮች አስገብተውት ነው” እንዳትሉ የምታከብሩት ኢብኑ ዐሳኪር ነው ያስተላለፈው፡፡ [ተብዪን፡ 161] ምን ይሻላል?
ያላችሁ ምርጫ ሁለት ነው። ወይ ሐቁን መርምራችሁ አቡል ሐሰን ወዳስተማረው የአህለ ሱና፞ ኢጅማዕ መመለስ፡፡ አለያ ግን “አቡል ሐሰንም ወሃ.ቢይ ነው፡፡ እኛ ሙዕተዚላ እንጂ አሽዐርዮ፞ች አይደለንም” በማለት በድፍረት ሚናችሁን መለየት፡፡ ሁለተኛውን አንመርጥላችሁም፡፡
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ ህዳር 24/2012)
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
1 201
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የአቡል ሐሰን አልኢባና እና የአሕ.ባሽ ማጭበርበር
~
አሕ.ባሾች ራሳቸውን ወደ አቡል ሐሰን አልአሽዐሪይ እንደሚያስጠጉ የሚታወቅ ነው። እንዲያውም የአቡል ሐሰን ተከታዮች ማለትም “አሽዐርዮች” በመሆናቸው ሲጎረሩና ሲጀነኑ ማየት የተለመደ ነው፡፡ ያለ ምንም ሃፍረት “ዐቂዳችን የተደራጀው በአቡል ሐሰን ነው” ሲሉም ይደመጣሉ። ለዚህም ሲሉ የአቡል ሐሰንን ዘር መቁጠር እና ገድሎቹን መተንተን ላይ ሲደክሙ ይታያሉ።
አቡል ሐሰን አርባ አመት የሙዕተዚላ አስተሳሰብ አራማጅ ሆኖ እየዋለለ እድሜውን ከፈጀ በኋላ መጨረሻ ላይ አላህ አድሎት ጥሏቸው ወጥቷል። ተውበቱን የሚመሰክሩ ኪታቦችንም ፅፏል። አሕ.ባሾች (አሽዐሪዮች) ግን በስሙ ከመነገድ ውጪ በተግባር የሚከተሉት እሱን ሳይሆን እሱ የሸሻቸውን ሙዕተዚላዎች ነው። ከዚያ ግን በአቡል ሐሰን የተፃፉ ኪታቦች ሲቀርቡላቸው አይናቸውን በጨው አጥበው ይክዳሉ። ለምሳሌ ያክል “አልኢባናህ” በተሰኘው ኪታቡ አላህ ከዐርሹ በላይ እንደሆነ፣ በየሌሊቱ ወደ ቅርቢቷ ሰማይ እንደሚወርድ፣ እጅና አይን እንዳለው በሚገባ አፅድቋል። ይሄ ሐቅ ደግሞ ለአሕ.ባሾች ሰቅፎ የሚይዝ የጎን ውጋት፣ አእምሮን የሚያጨናንቅ የራስ ምታት ነው። “የወሃ.ቢዮች እምነት ነው” በማለት ሌት ተቀን የሚያብጠለጥሉት ዐቂዳ ልክ አልፈው በሚቆልሉት “ኢማማቸው” የአህለ ሱና ዐቂዳ እንደሆነ መነገሩ መቋቋም የማይችሉት አስደንጋጭ መብረቅ ነው። እናስ ምን ይሻላል? እናማ አይንን ጨፍኖ ኪታቡ የአቡል ሐሰን አይደለም ብሎ መሽምጠጥ ነዋ! አይከብድም? ራስን ማታለል ደግሞ ምን ይከብዳል?! ሰው በስላሴስ እያመነ አይደል? እውነትን ከስሜት ነፃ ሆነው ለሚፈልጉ አካላት ግን ጥቂት ነጥቦችን ማለት እፈልጋለሁ፡፡
[ነጥብ አንድ]፡- እውን አልኢባናህ ኪታብ የሱ አይደለም? ዑለማዎች ምን ብለዋል?
“አልኢባናህ” የተሰኘው ኪታብ የአቡል ሐሰን ለመሆኑ በርካታ አሽ.ዐሪዮች መስክረዋል፡፡ ለምሳሌ ያክል በይሀቂይ በ“አልኢዕቲቃድ” [96፣ 109]፣ ኢብኑ ዐሳኪር በ“ተብዪን" [25፣ 152፣ 171፣ 388፣ 389]፣ ኢብኑ ፈርሑን በ“አዲ፞ባጅ” [2/95]፣ ኢብኑ ሐጀር በ“ሊሳኑል ሚዛን” [4/486]፣ ሀይተሚይ በ“አልፈታወል ሐዲሢያህ” [52፣ 153]፣ ሙርተዷ ዘቢዲ በ“አልኢትሓፍ” [2/4] አሽ.ዐሪዮች ዘንድ የማይጠረጠሩ ግን “አልኢባናህ” የአቡል ሐሰን እንደሆነ የመሰከሩ ናቸው። ይህ ሁሉ ባለበት ኪታቡ የአቡል ሐሰን አይደለም እያሉ አጉል መድረቅረቅ ራስን ትዝብት ላይ መጣል ነው ትርፉ፡፡
ከነዚህ በተጨማሪ ኢብኑ ነዲም (385 ሂ.)፣ አልሓፊዝ አሕመድ ብኑ ሣቢት አጠ፞ርቂይ፣ አቡ ዑሥማን አሷ፞ቡኒይ፣ አልአህዋዚይ (446 ሂ.)፣ አቡል ፈትሕ ነስር አልመቅዲሲይ፣ አቡል መዓሊ ሙጀሊ፞ይ ከነዚሁ ውስጥ ናቸው።
[ነጥብ ሁለት] ከኪታቡ ተመልሶ ይሆን?
“ምናባት ከዚህ ኪታቡ ተውበት አድርጎ ከሆነስ?” እንዳይባል “አልኢባናህ” የመጨረሻ ኪታቡ እንደሆነ ብዙዎች መስክረዋል። ለምሳሌ፡-
1. አቡል ሐሰን ከሙዕ.ተዚላ ሲወጣ ቀድሞ ሲለ፞ጠፉበት ከነበሩ ነገሮች በሙሉ ተመልሶ መጨረሻ ላይ የረጋው በዚህ ኪታብ ላይ ነው ይላል ኢብኑ ደርባስ (659 ሂ.)። [ሪሳለቱ ዘ፞ብ ዐን አቢል ሐሰን አልአሽዐሪ፡ 107]
2. ቀደም ባለው ዘመን የነበሩ አሽዐርዮች በ“አልኢባና” ኪታብ መልእክት በፅኑ ያምኑ እንደነበር ኢብኑ ዐሳኪርም መስክሯል። [ተብዪን፡ 388]
3. ሱብኪም “አሻ.ዒራዎች በዘገባው የሚተማመኑበት ኪታብ ነው” ብሎ ያወድሳል። [ጦበቃቱ ሱ፞ብኪ፡ 1/133]
ታዲያ ዛሬ ኪታቡን የሚያስተባብሉት ምን ቤት ናቸው?! በአቡል ሐሰን ስም የሚነግዱ አታላዮች ናቸው።
[ነጥብ ሶስት]፡- “ወሃ.ቢዮች ኪታቡ ውስጥ የራሳቸውን ሃሳብ ሰንቅረውበታል”
አንዳንዶች ደግሞ ኪታቡ የአቡል ሐሰን መሆኑን ለማስተባበል ቢከብዳቸው ሌላ ዘዴ ዘይደዋል፡፡ እርሱም በኪታቡ ውስጥ የሚገኙት ከአሻ.ዒራ እምነት ጋር የሚጋጩት ነጥቦች “ወሃ.ቢዮች በራሳቸው አስገብተው አሳትመውት እንጂ ኦርጂናሉ ኢባናህ ውስጥ እነዚህ ነጥቦች አይገኙም” የሚል ነው፡፡ ቅጥፈት የማያልቅባቸው ፍጡሮች! ይህንን ያፈጠጠ ያገጠጠ ውሸት በቀላሉ እርቃን ማስቀረት ይቻላል፡፡ ለዚህም የኢብኑ ዐሳኪር ማረጋገጫ በቂ ነው፡፡
ኢብኑ ዐሳኪር አሕ'ባሾች (አሽ.ዐሪዮች) ዘንድ በክፉ የሚታማ አይደለም፡፡ እንዲያውም ወገንተኝነት በሚንፀባረቅበት መልኩ ጭምር ከአቡል ሐሰን የሚከላከል ነው፡፡ ለዚህም “ተብዪኑ ከዚቢል ሙፍተሪ” የተሰኘው ኪታቡን መመልከት ይቻላል፡፡ ይህንን ኪታብ ያዘጋጀው ከአቡል ሐሰን አልአሽዐሪይ ለመከላከል ነው፡፡ ኪታቡ ከነ ግድፈቶቹ ወሳኝ ቁም ነገሮችን ይዟል፡፡ ለምሳሌ አልኢባናህ ኪታብ የአቡል ሐሰን እንደሆነ፣ የአቡል ሐሰን የመጨረሻ አቋምም በዚህ ኪታብ ላይ የሰፈረው እንደሆነ፣ ኪታቡ የሱ ለመሆኑ በርካታ ዑለማዎች እንደመሰከሩና እንዳደነቁት ያሰፈረ ሲሆን ከዚህም በዘለለ ከዚህ ኪታብ እየቀነጨበ ያቀረባቸው ነጥቦች የአሕ'ባሾችን ወሽመጥ የሚበጥሱ ናቸው፡፡ ለምን? ምክንያቱም ዛሬ “በወሃ.ብዮች የተሰነቀሩ ናቸው” የሚሏቸውን መልእክቶች በዚህ ከአቡል ሐሰን ለመከላከል ባዘጋጀው ስራው ውስጥ ጠቅሷቸው እናገኛቸዋለንና፡፡ ማመሳከሪያ ልጥቀስ፡–
التَّمَسُّك بِكِتَاب اللَّه وَسنة نبيه صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ وَمَا رُوِيَ عَن الصَّحَابَة وَالتَّابِعِينَ وأئمة الحَدِيث وَنحن بذلك معتصمون وَبِمَا كَانَ عَلَيْهِ أَحْمد بن حَنْبَل نضّر اللَّه وَجهه وَرفع دَرَجَته وأجزل مثوبته قَائِلُونَ وَلمن خَالف قَوْله قَوْله مجانبون
“የአላህን መፅሐፍ፣ የነብዩን ﷺ ሱና፞ እንዲሁም ሶሐቦች፣ ታቢዒዮ፞ችና የሐዲሥ ኢማሞች የነበሩበትን አጥብቆ መያዝ ነው። እኛ ይህንን አጥብቀን የምንይዝ ነን። አሕመድ ብኑ ሐንበል - አላህን ፊቱን ያብራለት፣ ደረጃውን ከፍ ያድርግለት፣ ምንዳውን ያነባብርለትና - በነበረበት አቋም ላይ የምናስተጋባ ነን። አቋሙ ከሱ አቋም ጋር የተፃረረን የምንርቅ ነን።”
ቀጥሎም ከመሰረታዊ የኢማን ክፍሎች ጋር የአላህን ከዐርሽ በላይ መሆን፣ ለአላህ ፊት፣ እጅና አይን እንዳሉት የቁርኣን አንቀፆችን እያጣቀሰ ያፀድቃል። [ተብዪን፡ 157-158] እነዚህ መልእክቶች ቃል በቃል በአቡል ሐሰን አልኢባና ኪታብ [ገፅ፡ 20 - 21] የሚገኙ ናቸው፡፡ አለፍ ብሎም አላህ ለልቅናው በሚገባ መልኩ ከሁሉም ነገር በላይ ከዐርሹ ላይ እንደሆነ ያሰፈረ ሲሆን ይህን መልእክት ቃል በቃል ኢብኑ ዐሳኪር አስፍሮት እናገኘዋለን፡፡ የኢባናን ገፅ 21 ከተብዪን ገፅ 300 ጋር ያገናዝቡ።
የአላህን ከዐርሹ በላይ መሆን፣ እጅ፣ ፊት፣ አይን መኖሩን ማስተባበል አሽዐሪያን ከሙዕተዚላና ከጀህሚያ ጋር አንድ ከሚያደርጓቸው ጥመቶች ውስጥ ናቸው፡፡ ይህ ሐቂቃ ሲወጣባቸው አሕ'ባሾች/ አሽዐርዮች ምን ይላሉ? “በነዚህ ነጥቦች ላይ የሙዕተዚላዎች አቋም የአህሉ ሱና አቋም ነው” ይላሉ፡፡ ይሄ ቅጥፈታቸው ግን ሌላ ያላሰቡት ቅርቃር ውስጥ ነው የሚከታቸው፡፡ ምክንያቱም አቡል ሐሰን አልአሽዐሪ ሙዕተዚላዎች ለአላህ ፊት፣ እጅ፣ አይን መኖሩን እንዳስተባበሉ፣ ወደ ቅርቢቷ ሰማይ እንደሚወርድ የሚጠቁመውንም ሐዲሥ እንዳልተቀበሉ ከዘረዘረ በኋላ የሱ አቋም ከነሱ እንደሚለይ እንዲህ ሲል ግልፅ አድርጓልና፡-
1 201
Repost from ትዳር እና ኢስላም 🌷🌹🥀
🌸የጁምዓ ሱናዎች🌸
መታጠብና መቀባባት
ፀጉርን ማበጠር
የተሻለውን ልብስ መልበስ ሽቶ መቀባት
መፋቂያ መጠቀም/ቡርሽ
በጊዜ ወደ መስጅድ መሄድ
ዱዓ ሙስተጃብ የምትሆንበትን ጊዜ መጠባበቅ በነብዩ ላይ ሶለዋት ማብዛት
ሱረቱል ካህፍን መቅራት
ሱና ሶላቶችን ሲገቡ መስገድ
በአደብ ተቀምጦ ኹጥባን ማድመጥ
اللهم صّلِ وسَلّمْ عَلۓِ نَبِيْنَامُحَمد
اللهم صّلِ وسَلّمْ عَلۓِ نَبِيْنَامُحَمد
اللهم صّلِ وسَلّمْ عَلۓِ نَبِيْنَامُحَمد
اللهم صّلِ وسَلّمْ عَلۓِ نَبِيْنَامُحَمد
اللهم صّلِ وسَلّمْ عَلۓِ نَبِيْنَامُحَمد
اللهم صّلِ وسَلّمْ عَلۓِ نَبِيْنَامُحَمد
اللهم صّلِ وسَلّمْ عَلۓِ نَبِيْنَامُحَمد
اللهم صّلِ وسَلّمْ عَلۓِ نَبِيْنَامُحَمد
للهم صّلِ وسَلّمْ عَلۓِ نَبِيْنَامُحَمد
اللهم صّلِ وسَلّمْ عَلۓِ نَبِيْنَامُحَمد
اللهم صّلِ وسَلّمْ عَلۓِ نَبِيْنَامُحَمد
اللهم صّلِ وسَلّمْ عَلۓِ نَبِيْنَامُحَمد
اللهم صّلِ وسَلّمْ عَلۓِ نَبِيْنَامُحَمد
اللهم صّلِ وسَلّمْ عَلۓِ نَبِيْنَامُحَمد
اللهم صّلِ وسَلّمْ عَلۓِ نَبِيْنَامحمد
اللهم صّلِ وسَلّمْ عَلۓِ نَبِيْنَامُحَمد
اللهم صّلِ وسَلّمْ عَلۓِ نَبِيْنَامُحَمد
اللهم صّلِ وسَلّمْ عَلۓِ نَبِيْنَامُحَمد
t.me/tdarna_islam
1 201
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
መልእክት ለኸጢቦች
~
በቅርብ ጊዜ ስለ መውሊድ ቢድዐ ያላስተማራችሁ ከሆነ የዛሬን ጁሙዐ ህዝባችንን ከዚህ ቢድዐ ለማስጠንቀቅ ብታውሉት ትልቅ ኸይር ነው። የመውሊድ ቢድዐ በሺዐዎች የተጀመረ እንደሆነ፣ በውስጡ ሺርክን ጨምሮ ብዙ ጥፋት እንደሚፈፀምበት፣ የቢድዐን አደጋዎች፣ ሙስሊም ለሐቅ / ለማስረጃ ክፍት ሊሆን እንደሚገባ፣ ወዘተ ወሳኝ ነጥቦችን ማንሳኑ ላይ ብታተኩሩ ባረከላሁ ፊኩም፡፡
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
1 201
🎙 በ ኡስታዝ ኸድር አሕመድ አል ከሚሴ(አቡ ጁወይሪያ)
ተቀርተው የተጠናቀቁ ሙሉ ዱሩሶችን በቀላሉ ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑት
0⃣1⃣ ኪታቡ ተውሒድ ፈውዛን 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/4860
0⃣2⃣ ኡሱሉ ሱና ኢማሙ አሕመድ ኢብኑ ሃምበል 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/1760
0⃣3⃣ ቀዋዒዱል አርባኣ 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/5459
0⃣4⃣ አርባዒን አነወዊያ 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/1802
0⃣5⃣ ሀዚሂ ደዕወቱና ወአቂደቱና 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/4588
0⃣6⃣ ኩን ሰለፊየን አለል ጃዳህ 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/2030
0⃣7⃣ ሚን ዑሱል አቂደቱል አህለ ሱና ወል ጀማዓ 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/4545
0⃣8⃣ ዓቂደቱል አህሊ ሱናቲ ወልጀማዓሕ 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/2068
0⃣9⃣ አቂደቱ ሰለፍ ወዓስሓቡል ሓዲስ 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/5195
1⃣0⃣ ሰላሰቱል ኡሱል (ኡሱሉ ሰላሳ) 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/5483
1⃣1⃣ ፈትሁ ረቡል በሪያ ቢተልኺሲል ሃመዊያ (ተልኺስ)👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/2562
1⃣2⃣ ኪታቡ ተውሒድ ሙሓመድ አብዱል ወሓብ👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/2644
1⃣3⃣ሸርህ አቂደቱል ዋሲጢያ ሊል ሀሊል ኻራስ👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/5450
1⃣4⃣ ዑምደቱል አሕካም ሚን ከላሚ ኸይሪል አናም👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/2984
1⃣5⃣ ሸርሁ መንዙመቱል ሓዒያ ሸይኽ ፈውዛን 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/3207
1⃣6⃣ አል ኡሱል ሚን ዒልመል ኡሱል 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/3265
1⃣7⃣ ሸርሑ ሙስጦለሁል ሓዲስ 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/3428
1⃣8⃣ ኹዝ አቂደተከ ሚነል ኪታቢ ወሱነቲ ሰሒሓ
👇https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/3461
1⃣9⃣ ኢና ኩና ፊ ጃሂሊያ 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/3497
2⃣0⃣ ሙምቲዕ ሸርሑ አል አጅሩሚያ 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/3749
2⃣1⃣ ሉምዓቱል ኢዕቲቃድ ሊል ዑሰይሚን 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/3882
2⃣2⃣ ተብሲሩል ኸለፍ 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/4885
2⃣3⃣ ኢስቲቅባሉ ሸህሪ ረመዷን 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/3925
2⃣4⃣ ሚንሐጅ ፊርቀቱ ናጂያ ወጧኢፈቱ መንሱራ 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/3985
2⃣5⃣ ኹላሰቱል ኑሪል የቂን ጁዝ —1 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/4025
2⃣6⃣ ተብሲሩል ባዲዒን ቢስጢላሓት አል ሙሓዲሲን 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/4073
2⃣7⃣ ቀዋዒዱል ሙስላ ፊ ሲፋቲላሂ ወዓስማኢል ሑስና👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/4125
2⃣8⃣ ረውደቱል ባዲዒን ሚን አሓዲሲ ሰይዲል ሙረሰሊን👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/4145
2⃣9⃣ ብሉግ አል መራም ሚን አዲለቲል አሕካም👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/4448
3⃣0⃣ ተንቢሑ ዘዊል አፍሐም ኢላ ረእቢ ሰድኢ ወልዊአሚ አላ መንሐጅ ሰለፊል ኪራም👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/4515
3⃣1⃣ ኡሱሉ ሲታ ሊል ዑሰይሚን 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/4578
3⃣2⃣ ሸርህ ከሽፉ አሹብሀት 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/4669
3⃣3⃣ ተቅሪቡ ተድሙሪያ 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/4790
3⃣4⃣ አል አጅዊበቱል ሙፊዳህ ሸይኽ ፈውዛን 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/5041
3⃣5⃣ ነዋቂዱል ኢስላም ሊሸይኽ ሷሊህ አል ፈውዛን 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/5064
3⃣6⃣ ጂናየቱ ተመዩዕ አለል መንሀጂ ሰለፍ 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/5086
3⃣7⃣ ቱህፈቱ ሰኒያ ሸርህ መንዙመቱል ሓኢያ 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/5142
3⃣8⃣ አሓሱ ዓለል መወዳህ ወኢእቲላፍ ወተሕዚር ሚነል ፊርቀቲ ወል ኢኽቲላፍ 👇
https://t.me/ABUJUWEYRIYAA/5523
ይቀጥላል…
ይቀጥላል……
1 201
🔥 من ابتدع في الإسلام فقد زعم أن محمدا خان الرسالة
قال إمام دار الهجرة مالك بن أنس رحمه الله تعالى: (من ابتدع في الإسلام بدعة يراها حسنة فقد زعم أن محمدا خان الرسالة، لأن الله يقول: (اليوم أكملت لكم دينكم) فما لم يكن يومئذ دينا فلا يكون اليوم دينا) (الاعتصام للشاطبي) (٤٩/١).
1 201
Repost from Muzemil Behja Abu Hanif
✅ሸይኽ አል-አላማህ ሙቅቢል አል-ዋዲዒይ አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ ብለዋል፡-
“አህሉል-ሱና የእውቀትና የትምህርት ባለቤቶች ናቸው እንደዚሁም ወደ አላህ ኪታብና ወደ መልዕክተኛው((ﷺ))ሱና ጥሪ የሚያደርጉ ወንዶች/ጀግኖች ናቸው።
📚المصارعة : ( ص١٧٢ )
https://t.me/Abu_Abdellah_As_Selefiy
1 201
Repost from د.عبدالعزيز بن ريس الريس
📌شرح حديث " من حُسنِ إسلام المرء تركه ما لا يعنيه "
https://youtu.be/VvtQH1Pfy0s?si=Ir2AIJJwgQpRX0wW
د. عبدالعزيز بن ريس الريس
1 201
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
አስገዳጅ ሁኔታ ሲገጥም ፊትን ለወንድ መግለጥ
~
አንዳንዴ ፊታቸውን ከባዳ ወንዶች የሚሸፍኑ እህቶቻችን እንዲገልጡ የሚገፋ ጫና ይገጥማቸዋል። ለምሳሌ ጥጋበኛ እጅ ላይ ወድቀው ካልገለጡ ለከባድ ጥቃት ሊጋለጡ ይችላሉ። በመሰል ሁኔታዎች ላይ መግለጥ ይችላሉ? ወይስ ችግሩ የፈለገ ቢከፋ እምቢ ማለት አለባቸው?
አስገዳጅ ሁኔታ ሲገጥም የማይፈቀድ ነገር ይፈቀዳል። الضرورات تبيح المحظورات የሚለው የፊቅህ መርህ ጠንካራ መነሻ ያለውና የታወቀ ነው። አላህ እንዲህ ይላል፦
{ لَا یُكَلِّفُ ٱللَّهُ نَفۡسًا إِلَّا وُسۡعَهَاۚ }
አላህ ነፍስን ከችሎታዋ በላይ አያስገድዳትም።" [አልበቀረህ: 286]
በአስገዳጅ ሁኔታ ህይወትን ለማትረፍ በክት መብላት ይቻላል። ተጨባጭ የሆነ አስገዳጅ ሁኔታ ከገጠመ የክህደት ንግግር በመናገርም ራስን ማትረፍ ይቻላል።
{ مَن كَ.فَرَ بِٱللَّهِ مِنۢ بَعۡدِ إِیمَـٰنِهِۦۤ إِلَّا مَنۡ أُكۡرِهَ وَقَلۡبُهُۥ مُطۡمَىِٕنُّۢ بِٱلۡإِیمَـٰنِ }
"ከእምነቱ በኋላ በአላህ የካደ ሰው (ብርቱ ቅጣት አልለው)፡፡ ልቡ በእምነት የረጋ ሁኖ (በክህደት ቃል በመናገር) የተገደደ ሰው ብቻ ሲቀር።" [አነሕል: 106]
ሌሎችም ጉዳዮች እንዲሁ ይታያሉ። የሙስሊሟ ለባዳ ወንዶች ፊቷን መግለጥም በዚሁ አግባብ የሚታይ ይሆናል። ይህንን መርህ በመንተራስ አስገዳጅ ጉዳይ ሲገጥም ጊዜ ሴት ልጅ ፊቷን መግለጥ እንደምትችል ዓሊሞች ይገልፃሉ። በዚህ ላይ በምሳሌነት ከሚጠቀሱ ምክንያቶች ውስጥ የሚከተሉትን ማንሳት ይቻላል:-
1ኛ፦ በማጨት ጊዜ :- ይሄ ሐዲሦች የመጡበት እንዲሁም ኢጅማዕ ያለበት በመሆኑ ለብዙ ሰውም የሚሰወር ስላልመሰለኝ ለማሳጠር ያክል በዚሁ ልለፈው።
2ኛ፦ ለህክምና፦ ጉዳቱ ያለበት ክፍል ፊትም ሆነ ሌላ ክፍል መግለጥ ይቻላል። ከተቻለ ባል ወይም ሌላ መሕረም (ቅርብ ቤተሰብ) አብሮ መኖር አለበት። ባይሆን ሴት ሃኪም ካለ ወደ ወንድ፣ ሙስሊም ካለ ወደ ሌላ መሄድ አይገባም ይላሉ ዓሊሞች። ለህክምና በሚያስፈልገው መጠን ሃኪሙ አካሏን መመልከት ይችላል ይላሉ ኢብኑ ቁዳማ። [አልሙግኒ፡ 7/459]
በነገራችን ላይ ጦር ሜዳ ላይ ሴቶች ሶሐቢያት ወንዶችን ያክሙ ነበር። ኡሙ ዐጢያህ - ረዲየሏሁ ዐንሃ - እንዲህ ትላለች፦
غَزَوْتُ مَعَ رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ سَبْعَ غَزَوَاتٍ أَخْلُفُهُمْ فِي رِحَالِهِمْ، فَأَصْنَعُ لَهُمُ الطَّعَامَ، وَأُدَاوِي الْجَرْحَى وَأَقُومُ عَلَى الْمَرْضَى
"ከአላህ መልእክተኛ ﷺ ጋር ሰባት ዘመቻዎችን ዘምቻለሁ። እቃዎቻቸውን እጠብቅ፣ ምግባቸውን አዘጋጅ፣ ቁስለኞችን አክም እንዲሁም ህመምተኞችን እንከባከብ ነበር።" [ሙስሊም፡ 1812] የቡኻሪን باب هل يداوي الرجل المرأة، والمرأة الرجل እንዲሁም ዘርዘር ያለ ነገር የፈለገ ፈትሑል ባሪን መመልከትም ይቻላል።
3ኛ፦ ችሎት ላይ፦ በፍርድ ችሎት ላይ ፍርድ ለመስጠት ዳኛው አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው ፊቷን ይመለከታል። ካልሆነ ሐቅን ማስከበር አስቸጋሪ ሊሆንበት ይችላል። ምስክር ሆና ስትቀርብ ወይም በሷ ላይ ምስክርነት ለመስጠትም እንዲሁ መገለጥ ግዴታ ሊሆን ይቻላል። ኢብኑ ቁዳማ እንዲህ ይላሉ፦
وللشاهد النظر إلى وجه المشهود عليها لتكون الشهادة واقعة على عينها، قال أحمد: لا يشهد على امرأة إلا أن يكون قد عرفها بعينها
"መስካሪ ሰው ምስክርነቱ ቦታው ላይ ያረፈ ይሆን ዘንድ የሚመሰከርባትን ሴት ሊመለከት ይችላል። (ኢማሙ) አሕመድ 'በትክክል ለይቶ እስካላወቃት ድረስ አንዲት ሴት ላይ አይመሰክርም' ብለዋል።" [አልሙግኒ፡ 7/459]
ይሄ የሳቸው ሃሳብ ብቻ አይደለም። ሌሎችም "ኒቃብ በለበሰች ሴት ላይ ፊቷን ሳትገለጥ መመስከር አይቻልም" ይላሉ። [አሸርሑል ከቢር፣ ደርዲር፡ 4194]
4ኛ፦ በግብይት ላይም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ሻጭ ወንድ ገዢዋን ሴት ሊመለከት እንደሚችል ዑለማኦች ይገልፃሉ። [አልሙግኒ፡ 7/459] ያለበለዚያ በግብይቱ ላይ ለተፈጠረ ክፍተት ማስተካከያ ለማድረግ ሊቸገር ይችላል። ለምሳሌ እቃ ሽጦላት ፊቷን ካላየ ኋላ ላይ እቃው ችግር ኖሮበት መመለስ ቢያስፈልግ በትክክል እሷ መሆኗን መለየት አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል።
5ኛ፦ አስገዳጅ ህግ ባለበት ሁኔታ፦ በአንዳንድ ሃገራት ህግ ወይም ኤርፖርት አካባቢ ወይም ሌላ አስገዳጅ ሁኔታ ከገጠመም ፊቷን መግለጥ ትችላለች። ለምሳሌ በመጥፎ ሰዎች እጅ ላይ ወድቃ ራሷን አደጋ ላይ ከምትጥል ፊቷን በመግለጥ ራሷን ማትረፍ ትችላለች። "አስገዳጅ ሁኔታዎች የተከለከለን ነገር ያስፈቅዳሉ።" ስለዚህ ማንነቷን ለመለየት የሚጠይቅ አስገዳጅ ሁኔታ ቢገጥም ወይም ሌላ ተጨባጭ ምክንያት ከኖረ ፊቷን መግለጥ ትችላለች ማለት ነው።
ይሄ እንግዲህ ከዑለማኦች አቋም ውስጥ ለደረሰች ሴት ልጅ ፊትን መሸፈን ግዴታ ነው የሚለውን ስንወስድ ነው። የሆነ ሆኖ ጫን ያለ ሁኔታ ካልገጠማት በስተቀር ለትንሽ ለትልቁ እጅ ልትሰጥ አይገባም። ፍተሻና መሰል ቦታዎች ላይ ሴቶችን መጠቀም የሚቻልበት ሁኔታ ካለ ወይም ደግሞ ጉዳዩ አንገብጋቢ ካልሆነ ባዳ ለሆኑ ወንዶች ፊትን መግለጥ አይገባም። አስገዳጅ ችግር ሲገጥም ደግሞ ጉዳዩን በችግሩ መጠን ብቻ ማስተናገድ ይገባል። "አስገዳጅ ሁኔታዎች በልካቸው ነው የሚስተናገዱት።" እንጂ ችግሩን ማመሀኛ አድርጎ አጉል መዘናጋት ውስጥ መግባት አይገባም። ወላሁ አዕለም! በነጥቡ ላይ ሃሳብ ያለው ሰው ማካፈል ይችላል።
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ መስከረም 01/2017)
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
1 201
Repost from SadatKemal Abu Meryem
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
መውሊድን በተመለከተ በኡስታዝ ኢብኑ ሙነውር የተዘጋጁ ከፊል ፅሁፎችን በቀላሉ እንዚህን ሊንኮች በመጫን ማንበብ ትችላላችሁ።
1, ነብዩ ﷺ መቼ ተወለዱ?
https://t.me/IbnuMunewor/893
2, መውሊድን ማን ጀመረው? በመረጃ ለሚያምኑ ብቻ
https://t.me/IbnuMunewor/869
3, መውሊድ ለምን አላማ እንደተጀመረ ያውቃሉ?
https://t.me/IbnuMunewor/876
4, መውሊድና ነባሩ እስልምና አይተዋወቁም! {ምስክር እራሳቸው!}
https://t.me/IbnuMunewor/884
5, “በአላህ እዝነት ይደሰቱ...” - ትልቁ የመውሊድ አጋፋሪዎች ምርኩዝ
https://t.me/IbnuMunewor/2227
6, የሰኞ ፆም እና መውሊድ
https://t.me/IbnuMunewor/2214
7, ዐቂቃ ሌላ መውሊድ ሌላ!
https://t.me/IbnuMunewor/2261
8, ዓሹራን ለመውሊድ?
https://t.me/IbnuMunewor/2269
9, መውሊድ ውስጥ እነዚህ አደጋዎች አሉ!
https://t.me/IbnuMunewor/2294
10, በመውሊድ ላይ ስለሚፈፀመው ጭፈራ ዑለማዎች ምን እንዳሉ ታውቃለህ?
https://t.me/IbnuMunewor/882
11, መውሊድን የሚፈቅዱትም አይፈቅዱትም!
https://t.me/IbnuMunewor/2298
12, መውሊድ የማያከብር ሰው የሙሐመድ ﷺ ጠላት ከሆነ፣ ገና የማያከብር ሰው የዒሳ ጠላት ነው!
https://t.me/IbnuMunewor/886
13, እውን የሡወይባ ታሪክ ለመውሊድ ማስረጃ ይሆናል?
https://t.me/IbnuMunewor/2234
14, ሸውካኒ እና መውሊድ (ወሳኝ ነጥቦች የተዳሰሱበት)
https://t.me/IbnuMunewor/898
15, ሲዩጢ፣ የመውሊድ ደጋፊዎች ሌላኛው ምርኩዝ
https://t.me/IbnuMunewor/2277
16, እውን ኢብኑ ተይሚያ መውሊድን ፈቅደዋል?
https://t.me/IbnuMunewor/878
17, በሸይኹል አልባኒ እና “መውሊድ ይፈቀዳል” በሚል ሰው መካከል የተደረገ ድንቅ ቃለ-ምልልስ
https://t.me/IbnuMunewor/34
18, ከ“ወሃብዮች” በፊት የነበሩ የመውሊድ ተቃዋሚዎች
https://t.me/IbnuMunewor/1624
19, መውሊድ ተከሽኖ
https://t.me/IbnuMunewor/2309
20, ለምንድን ነው የመውሊድ ተቃውሞ ኢኽዋኖችን ምቾት የሚነሳቸው?
https://t.me/IbnuMunewor/918
21, መሷሊሐል ሙርሰላ፣ የመውሊድ አክባሪዎች የመጨረሻው ምሽግ
https://t.me/IbnuMunewor/2302
1 201
መውሊድና ተያያዢ ነጥቦች
መውሊድ በማን ተጀመረ?
――――――――
በአማርኛም ይሁን በአረብኛ የሚገጠሙ የሸርክ ስንኞች።
((በድጋሜ የተለጠፈ ወሳኝ ሙሓደራ))
🎤በሸይኽ አወል ቢን አሕመድ አል_ኬሚሴ
t.me/AbuOubeida
1 201
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ብልትን መንካት ውዱእ ያፈርሳልን?
~
ብልትን መንካት ውዱእ ያፈርሳል ወይስ አያፈርስም የሚለውን በተመለከተ ከዑለማዎች የተለያዩ ሃሳቦች ተሰንዝረዋል። የልዩነቱ መነሻ ሁለት የተለያየ የሚመስል ይዘት ያላቸው ሐዲሦች መኖራቸው ነው። እነሱም፦
▶️ በአንድ በኩል ከቡስራ ቢንት ሶፍዋን ረዲየላሁ ዐንሃ የተላለፈው "ብልቱን የነካ ሰው ውዱእ ያድርግ" የሚለው ሐዲሥ ሲሆን
▶️ ሌላኛው ደግሞ ከጦልቅ ብኑ ዐሊይ ረዲየላሁ ዐንሁ የተላለፈው "በሶላት ውስጥ ብልቱን የነካ ሰው ውዱእ ማድረግ አለበትን?" ተብለው ሲጠየቁ ነብዩ (ﷺ) "የራስህ ቁራጭ አካል ነውኮ" ብለው መመለሳቸው ነው።
* ሁለቱም ሐዲሦች ከሰነድ አንፃር ትክክለኛ (ሶሒሕ) ናቸው። ታዲያ የቱን ይዘን የቱን እንተው? ዑለማዎች በዚህ ጉዳይ ላይ የተለያዩ አቋሞችን አንፀባርቀዋል፦
1⃣ኛ አቋም፡- የቡስራን ሐዲሥ ይዘው "ብልትን መንካት ውዱእ ያፈርሳል" ያሉ አሉ።
2⃣ኛ አቋም፡- የጦልቅን ሐዲሥ ይዘው ''የለም ብልትን መንካት ከነጭራሹ ውዱእ አያበላሽም" ያሉ አሉ።
* "ውዱእ ያፈርሳል" የሚለው የመጀመሪያው አቋም "የራስህ አካል ነውኮ" የሚለውን ሐዲሥ ያለ በቂ ምክንያት ስለሚገፋ ልክ አይደለም።
* "አያፈርስም" የሚለው 2ኛው አቋም "ብልቱን የነካ ሰው ውዱእ ያድርግ" የሚለውን ሐዲሥ በሚገፋ መልኩ ከተተረጎመ ትክክል አይሆንም።
"አንዱ ሐዲሥ ሌላኛውን ሽሮታል" በማለት መግፋት ደግሞ አጥጋቢ መረጃ ያስፈልጋል። መረጃ ደግሞ የለም። "ይሄኛው ሐዲሥ የቀደመ ነው፤ ያኛው የዘገየ ነው" የሚለው ሙግት ብቻውን በቂ አይደለም። ያለ ተጨባጭ መነሻ፣ ያውም ሁለቱ ሐዲሦች የሚጣጣሙበት አቅጣጫ እያለ አንዱን ሐዲሥ ይዘን ሌላኛውን ልንገፋ አይገባም። እና እንዴት ይሁን? ወደ ሌላኛው የዑለማዎች እይታ ይወስደናል፦
3⃣ኛ አቋም፡- "ብልትን በመንካት ውዱእ የሚጠፋው በስሜት ከሆነ ነው። ካልሆነ ግን ውዱእ አይጠፋም'' በሚል ሁለቱን ሐዲሦች ሊያጣጥሙ የሞከሩ አሉ። አንዱን ሐዲሥ ይዘው ሌላኛውን ከሚጥሉት የመጀመሪያዎቹ አቋሞች አንፃር ሲታይ ይሄኛው የተሻለ ነው። ነገር ግን "በስሜት" እና "ያለ ስሜት" ብሎ ለመክፈል ግልፅ መረጃ የለም። በዚህ የተነሳ ይሄኛውም ድምዳሜ አጥጋቢ አይሆንም። ስለዚህ ሁለቱ ሐዲሦች ተጣጥመው የሚሄዱበት ሌላ የዑለማእ ምርጫ ማየት ሊኖርብን ነው። ይሄውና፦
4⃣ኛው አቋም፡- የሁለቱ ሐዲሦች መልእክት የሚጋጭ አይደለም የሚል ነው። "የራስህ ቁራጭ አካል ነውኮ" የሚለው ብልትን መንካት ውዱእ እንደማያጠፋ ሲገልፅ፤ በሌላ በኩል "ብልቱን የነካ ሰው ውዱእ ያድርግ" የሚለው ሐዲሥ ደግሞ ብልቱን ለነካ ሰው ውዱእ ማድረጉ እንደሚወደድ ይጠቁማል። ትእዛዝ አዘሉን መልእክት ከግዴታነት ወደ 'ሙስተሐብነት' ያወረደው "የራስህ አካል ነውኮ" የሚለው ሐዲሥ ነው። በዚህ መልኩ ሁለቱን ሐዲሦች አጣጥሞ መረዳት የተሻለው ምርጫ ነው። ይሄ የኢብኑ ተይሚያ አቋም ነው። ስለዚህ በስሜትም ሆነ ያለ ስሜት፣ የራስንም ሆነ የሌላን፣ የህፃንንም ሆነ የአዋቂን ብልት መንካት ውዱእ አያበላሽም የሚለው ይበልጥ ጠንካራ ምርጫ ነው ማለት ነው። ግዴታ አይሁን እንጂ ታዲያ ውዱእ ማድረጉ ተወዳጅ ነው።
ነገር ግን በስሜት ነክቶ ፈሳሽ (መዝይ) ከወጣ ያኔ ውዱኡ ይፈርሳል። በዚህን ጊዜ ብልትን አጥቦ ውዱእ ማድረግ ግዴታ ይሆናል።
ወላሁ አዕለም።
=
ኢብኑ ሙነወር
(ጥር 04/2014)
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
