የቀጠናው ተመልካች
Open in Telegram
በአለማችን ቀጠናዎች የሚከሰቱ ክስተቶችን ይዘግባል፣ ሳይቀዘቅዝ በትኩሱ። ለጥያቄና ለአስተያየቶች በኢሜል asuleyma246@Gmail.com ብላችሁ ፃፉልኝ።
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
4 330
Subscribers
-924 hours
-407 days
-8130 days
Posts Archive
4 332
🇮🇷🇺🇸⚡️የCENTCOM ኃላፊ፣ 'በኢራን ላይ በአሜሪካ ወታደራዊ ጥቃት የባሕረ ሰላጤዌውን ሀገራት እና ዮርዳኖስን ተሳትፎ በግልፅ ይገልጻል። አብረዋቸው ኢራንን በማጥቃት ተሳታፊ ናቸው፣ ነው የሚለው' — የኢራን ውጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ።
'እነዚህ አርቴፊሻል የአረብ ግዛቶች፣ የአሜሪካን ጥቃት ለማመቻቸት ግዛቶቻቸውን እንደ ማስጀመሪያና እና ማስወንጨፊያ ቦታዎች በማቅረብ፣ በዚህ ጦርነት ተባባሪ ናቸው። ዒላማዎቻችን ናቸው።'
4 332
🇧🇫- Ibrahim Traore፣ የቡርኪና ፋሶ ፕሬዝዳንት፦
“ጠዋት ከእንቅልፍህ ስትነሳ፣ ፎጣ ታነሳለህ፣ ከውጭ የመጣ ነው። ራስህን ካጠብቅ በኋላ ልብስ ትለብሳለህ፣ ከውጭ የመጣ ነው።
ሞተር ብስክሌትህ፣ መኪናህ - ከውጭ የመጣ ነው። በአፍሪካ፣ ምንም ነገር አልፈጠርንም።
ሁሉም ነገር የተፈጠረው በነጭ ሰዎች ነው፦ ሞተር ብስክሌቶች፣ መኪኖች፣ አውሮፕላኖች፣ መርከቦች። ቅድመ አያቶቻችን ያንን አልፈጠሩትም።
የእኛ ሚና ምንድን ነው?
ነጭ ሰው ወደ አፍሪካ መጣ፣ የባቡር ሐዲድ አነጠፈ። እኛስ?
ነጭ ሰው ኢንተርኔትን እና ስልክን ፈጠረ።
እኛ እንጠቀምበታለን፣ ነገር ግን ምንም ነገር አልፈጠርንም።
እነዚህ ነገሮች እንዴት እንደሚሰሩ እንኳን አናውቅም።”
*-*-*-
ለዚህም ነው "ሦስተኛው ዓለም፣ ኋላ ቀር፣ መሃይማኖች፣ ጨለማው አሕጉር" እያሉ የሚጠሩን። ደንቆሮዎች ስለሆንን ነው።
በዚህ ሁሉ ደግሞ፣ ኢትዮጵያችን የደሃ ደሃዋ እና ኋላ ቀሯ ጭራ ናት፣ ከአፍሪካም ስታንደርድ። ለዚህ በዋነኝነት ተጠያቂዎች አስተዳደሮቻችን ናቸው።
አስቡት፣ ባለፉት ሃምሳ ዓመታት ብቻ ኢትዮጵያን ያስተዳደሩ መንግሥታት ሀገራችንን እንዴት አስገድደው እንደደፈሯት እና እንደጣሏት። አዎ፣ ደፍረው ጥለዋታል።
የቻይና የመንገድ መብራት መትከል፣ ሣር ውሃ ማጠጣት ወንዝ ማቆር፣ የፕላስቲክ መጫወቻ ፈረስ አደባባይ ላይ መትከል፣ የስልጣኔ ማሳያ አይደለም፣ እንዲያውም ካለንበት ተጨባጭ ሁኔታ፣ እነዚህ ነገሮች የድንቁርና እና የድድብና ጥግ ማሳያ ናቸው።
ደንቆሮዎች ናችሁ ካሉን በላይ ደንቆሮ መሆናችንን የሚያሳዩ ሥራዎች ናቸው።
ለዚህ ሁሉ ምስቅልቅል በእርግጥ እኛ የሀገሩ ሕዝብ በዋነኝነት ሃላፊነቱን እንወስዳለን። ከዚህም በላይ ይበለን?
4 332
🇮🇱🇮🇷 - የምዕራባውያን የስለላ ኤጀንሲዎች ኢራን በእስራኤል ላይ የመጀመሪያውን እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል ገምግመዋል። - የእስራኤል ቻናል 13
4 332
🇮🇱⚡️🇮🇷 የእስራኤል የመከላከያ ሚኒስትር ካትዝ፡-
እስራኤል ለማንኛውም አጋጣሚ ዝግጁ ነች። ለማንኛውም ሁኔታ ዝግጁ ነን። ኢራን እስራኤልን ካጠቃች፣ መጥፊያዋ እንደሆነ ትወቀው።
4 332
🇮🇷🇺🇸⚡️የውጊያ ጉዳት ግምገማ፣ (#BDA) የኢራን ሚዲያ በኩዌት በሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር፣ በ“አሊ አል ሰሊም” AB, የወደሙ የመኖሪያ ክፍሎችን እና የወታደሮችን መኖሪያ ቦታ የሚያሳዩ የሳተላይት ምስሎችን አሳትሟል።
4 332
🇺🇸ፕሬዝዳንት ትራምፕ፦ "በኢራን ላይ ከፍተኛ ጥቃት ለመሰንዘር እያሰብኩ ነው... ከዚህ በፊት ከተደረጉት ሁሉ የሚበልጥ። ውሳኔ ለመወሰን ተቃርቤያለሁ።"
4 332
🇺🇸USAF በዚህ ሰዓት፣ ከEUCOM ወደ CENTCOM እጅግ በጣም ግዙፍ የአየር መመላለሶች እያካሄደ ነው። ሁሉም ነገር ተነቅሎ ወደ መካከለኛው ምሥራቅ እየተጓጓዘ ነው
📌 የሕክምና ሠራተኞች፣ የውጊያ አስኪያጆች፣ መሳሪያዎች፣ ጥይቶች፣ ሁሉም ወደ CENTCOM ግንባር በጉዞ ላይ ናቸው።
*-*-*-
ምሽቱን እጅግ በጣም ከባድ ነገር ይኖራል።
4 332
🇮🇱🇸🇦 — የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ፦
"በቴህራን የሚገኘውን ዘር ጨፍጫፊ አገዛዝን የሚቃወም የአሜሪካ እና የእስራኤል የጋራ ወታደራዊ እርምጃ እና እስራኤል የኢራንን የሽብር ዘንግ መደምሰሷ፣ የሠላምን ተደራሽነት የማስፋት ዕድልን ፈጥሯል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ እንደተናገሩት፣ ሳዑዲ አረቢያ የአብርሃም ስምምነቶችን መቀላቀሏ በመካከለኛው ምስራቅ ለሠላም ታሪካዊ እርምጃ ይሆናል።
ሰላም በጥንካሬ"።
4 332
🇺🇸🇸🇦⚡️🇮🇷 ፕሬዚዳንት ትራምፕ፡ ሁዚዎችን እስካሁን ድረስ በጣም ወድጃቸው ነበር፣ ፕሮፌሽናል እና ስማርት ነበሩ። አሁን ግን፣ ኢራን ምን እንዳስነካቻቸው ባላውቅም፣ የሳዑዲ አረቢያን መርከቦች አጥቅተዋል። መስመሩን አውከዋል። በጣም እወዳቸዋለሁ አሁንም ሁዚዎችን፣ እራሳቸውን ሳዑዲን ከማጥቃት ቢያቅቡ። ካሁን በኋላ ሁዚዎች በቀይ ባሕር ላይ ምንም ጥቃት የሚፈጽሙ ወይም መስመሩን የሚያስተጓጉሉ ከሆነ፣ ኃላፊነቱን ሙሉ በሙሉ ኢራን ትወስዳለች። ኢራንን ነው የምንመታው። ይሄ ይታወቅ። አመሰግናለሁ።
*-*-*-*-
በሆርሙዝም ተዘግቶባት፣ በቀይ ባሕርም ተዘግቶባት፣ ሳዑዲ በየት ሠርታ ትብላ?
ሳዑዲዎች፣ መውጫቸውም መግቢያቸውም ከእነሱ ቁጥጥር ውጭ መሆኑ የገባቸው በቅርቡ ይመስለኛል፣ በዚህም ተጋላጭ (exposed) ሆነዋል።
ውሃውን የሚያዙበት ኢራንና የመን ናቸው። ሳዑዲ፣ በቀላሉ የምትያዝ ሀገር እንደሆነች በዚህ ሳምንት ታይቷል።
ባለፈው እንዳልኩት፣ ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህና በተለይ የመን ባለፈው ሳምንት ሳዑዲን ማስጠንቀቋን ተከትሎ፣ በዲያስፓራ የሳዑዲ ተቃዋሚ ፖርቲዎች MBS Bunker ውስጥ ተደብቆ ነው ያለው የሚለው ወሬ እውነት ሆኖ ከተገኘ፣ ለሳዑዲ የሁኔታው አንገብጋቢነት ይገለጥላችኋል።
የነ ትራምፕም ለሳዑዲ ያላቸው ስጋት የሚመነጨው ከዚህ ነው።
ጉዳዩ የሁለት መርከብ መቃጠል ብቻ አይደለም። ጉዳዩ፣ ሳዑዲ ላይ ወደፊት ወይም ከአሁን በኋላ እንዴት ነገሮች ሊከወኑ እንደሚችሉ ማሳያ ነው፣ እነሱን እንዴት መቆለፍ እንደሚቻል በዚህ 'ናሙናዊ ሙከራ' ታይቷልና።
4 332
🇺🇸🇷🇺 የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ፣ ማርያ ዛካሮቫ፣ የዛሬውን ስብሰባ ማን እንዳቀደው ለተጠየቀችው፣ "ስብሰባውን ለማድረግ ሐሳቡ የመነጨው ከአሜሪካ ነው" ብላለች።
*-*-*-
አይመስለኝም ፊትሽን ሳየው፣ ማርያ ዛካሮቫ። አሜሪካኖች ጆሮ ስለሰጧችሁ እጅግ የጓጓሽና በደስታ የተርበተበትሽ ይመስላል። የእንገናኝ መማጸኑ የመነጨው ከሩሲያ ይመስለኛል። የሆነው ሆኖ፣ ተገናኝተዋል።
ፑቲን፣ አሁን ላይ በማንኛውም መንገድ ጦርነቱን ማቆም ይፈልጋል፣ ጦርነቱ አፍንጫው ሥር ክሬምሊን ገብቷልና። ግን እንዴት ብሎ ያቁመው? አንድ፡ ሼም ይዞታል፣ ሁለት፣ አውሮፓና ዩክሬን፣ የድሉ ንፋስ ያዘነበለላቸው ስለመሰላቸው፣ በአሁኑ ሰዓት ጦርነቱን ማቆም አልፈለጉም። ስለዚህም እንዳያቆም እንቅፋት ሆነውበታል።
ፑቲን፣ ኮርቶ ገና የመጀመሪያው ዓመት ላይ በድል አድራጊነት ማጠናቀቅ ይችል ነበር ጦርነቱን። ነገር ግን፣ ለማይታወቅ ምክኒያት ሩሲያን ወደ ኋላ ሲጎትታት መቀመቅ አስገብቷታል።
ለማንኛውም፣ ጦርነቱን ማቆም ከዩክሬን በላይ ለሩሲያ አንገብጋቢ ጉዳይ ነው። በዓለም ፊት፣ የሩሲያ ኃይልና ክብር በዩክሬን፣ ተገፏል።
የቀራትን ግርማ ሞገሣዊ ገጽታ ማዳን የምትችለው፣ ከአሁን በኋላ ጦርነቱን ስታቆም ብቻ ነው።
4 332
🇷🇺🇺🇸 በአሁኑ ሰዓት የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ማርኮ ሩቢዮ፣ በማኒላ ፊሊፒንስ፣ ከሩሲያው አቻው ሰርጄ ላቭሮቭ ጋር፣ ከደቡብ ምሥራቅ እስያ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ጎን ለጎን፣ ተገናኝተው በመነጋገር ላይ ናቸው።
ሁለቱ ከዚህ በፊት ለመጨረሻ ጊዜ የተገናኙት ከአንድ ዓመት በፊት ነበር።
4 332
🇸🇦🇾🇪⚡ በቀይ ባሕር ውስጥ፣ በሳዑዲ አረቢያ አል-ሹካይቅ የባህር ዳርቻ፣ አንድ የሳዑዲ አረቢያ ነዳጅ ጫኝ ታንከር በሚሳይል ተመቷል።
ከርቀትም፣ ሲነድ ታይቷል።
እስካሁን ሃላፊነቱን የወሰደ አካል ባይኖርም፣ የመኖች ምናልባት በቅርቡ ለጥቃቱ ሃላፊነቱን ይወስዳሉ።
4 332
🇮🇷🇺🇸⚡️CENTCOM, 'የአሜሪካ ኃይሎች በኢራን ላይ አዳዲስ ጥቃቶችን ጀምረዋል።'
— ይህም በተከታታይ ለ12ኛ ምሽት የቦምብ ጥቃቶች እንደተደረጉ ያመለክታል።
ይህ የተባለው፣ ባለፈው ሰዓት በበርካታ የኢራን ከተሞች ፍንዳታዎች ሪፖርት ከተደረጉ በኋላ ነው።
4 332
🇷🇺🇺🇦⚡️ሩሲያዊያን፣ እሳቱን መሞቅ ጀምረዋል። መጣላቸው ቤታቸው ድረስ፣ እድሜ ለፑቲን ደካማነትና ሴራ ይሁንና። ይህ ስሜት የብዙ ሩሲያዊያን ስሜት ነው ዛሬ።
ፑቲን ለምዕራቡ ዓለም ሩሲያን ሊያስበጣጥስ ይፈልጋል፣ ሩሲያን ሊበታትን ተፈራርሟል፣ ሩሲያን ሊያዳክም እና ሊሰብር ቃል ኪዳን ይዟል፣ ያ ባይሆን በምን ስሌት አንድ መሪ ሀገሩን እና ጦሩን በዚህ መጠን ወደ ኋላ እየጎተተ ጦርነት ያረዝማል? ይላሉ፣ ቁጥራቸው ቀላል ያልሆኑ ሩሲያዊያን።
መዋጋታ ሲችል፣ ጦሩን በማስተባበር ጦርነት ማወጅ ሲችል፣ ሩሲያን አስበላ፣ አንድ ነገር ይደረግ፣ ይላሉም ናሽናሊስቶች።
ፑቲን፣ በዚህ ሁሉ ግድ የሰጠው አይመስል። በዚህ አያያዙ የሚቆይም አይመስልም።
4 332
🇺🇸🇮🇷⚡— ፕሬዝዳንት ትራምፕ በኢራን ላይ የሚደረገውን ወታደራዊ ዘመቻ ለማስፋፋት፣ እያሰበ ነው። አሜሪካም፣ ተጨማሪ ኃይሎችን፣ አውሮፕላኖችን እና የሕክምና ሠራተኞችን ወደ መካከለኛው ምስራቅ እየላከች ነው፣ በWSJ ጋዜጣ ዘገባ መሠረት።
➡️ እንቅስቃሴው፣ በአሜሪካ እና በእንግሊዝ በተጠንቀቅ የተቀመጡ ኃይሎችን፣ ተዋጊ ጀት ስኳድራኖችን፣ ከባባድ ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖችን እና በመካከለኛው ምሥራቅ ለተጎዱ የአሜሪካ ወታደሮች ሕክምና የሚሰጡ ከ150 በላይ ዶክተሮችን፣ ያካትታል።
4 332
🇺🇸🇮🇷⚡— ፕሬዝዳንት ትራምፕ በኢራን ላይ የሚደረገውን ወታደራዊ ዘመቻ ለማስፋፋት እያሰበ ነው፣ ተጨማሪ ኃይሎችን፣ አውሮፕላኖችን እና የሕክምና ሠራተኞችን ወደ መካከለኛው ምስራቅ እየላከች ነው፣ በ WSJ ጋዜጣ ዘገባ መሠረት።
➡️ እንቅስቃሴው፣ በአሜሪካ እና በእንግሊዝ በተጠንቀቅ የተቀመጡ ኃይሎችን፣ ተዋጊ ጀት ስኳድራኖችን፣ ከባባድ ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖችን እና በመካከለኛው ምሥራቅ ለተጎዱ የአሜሪካ ወታደሮች ሕክምና የሚሰጡ ከ150 በላይ ዶክተሮችን ያካትታል።
4 332
🇮🇷 | ከIRGC የአየር ላይ ኃይል አዛዥ Seyed Majid Musawi (H) የተሰጠ ወሳኝ ማስጠንቀቂያ፦
"የእኛ ድልድዮች እና የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ጥቃት ከደረሰባቸው፣ በሕፃናት ገዳይ አጋሮች እና አስተናጋጅ ግዛቶች (አረብ ሀገራት) ውስጥም የኤሌክትሪክ ኃይል እንደሚቋረጥ እርግጠኛ ሊሆኑ ይገባል።
እኛም፣ መሠረተ-ልማቶቻቸውን እናቃጥለዋለን።
4 332
🇺🇸🇮🇷🇷🇺⚡- የአሜሪካ የስለላ ባለሥልጣናት፣ ሩሲያ ለኢራን የስለላ መረጃ፣ የዒላማዎችን መገኛ እና የተሻሻለ የድሮን ቴክኖሎጂ በማቅረብ በባሕር ወሽመጡ እና በባሕረ ሰላጤው ሀገሮች ውስጥ የሚገኙ የCIA ተቋማትን ዒላማ እንድታደርግ መርዳቷን እየመረመሩ ነው፣ ምንም እንኳን እስካሁን ጠንካራ ድምዳሜዎች ላይ ባይደርሱም።
ኢራን፣ ሪያድ ውስጥ የነበረውን ጨምሮ፣ በቀጠናው ባሉ ሀገራት ውስጥ የሚገኙ የCIA ድብቅ ቤቶችን እና ማዘዣ ጣቢያዎችን መምታቷ እና ፔንታገንም ቦታዎቹን ለቅቆ እንዲወጣ ማስገደዷ፣ የወታደራዊ አመራሮችን እስከ አሁን ያስደነገጠ ክስተት ሆኗል -- ሮይተርስ።
*-*-*-
አሜሪካ፣ የደረሰባትን ሕመም ለማስታመምና ለኢራን ሙሉ የጥቃቱን ክሬዲት ላለመስጠት፣ አንዴ ሩሲያ አንዴ ቻይና፣ በማለት እያሳበበች ነው።
በኢራን ነው የተመታነው ላለማለት፣ አቀበት እየቧጠጡ ናቸው። ነገር ግን ጋዜጣው እንዳለው፣ እነዚህን ሀገሮች ለመክሰስ በተጨባጭ ያገኙት መረጃ የለም።
ይህም ማለት፣ ጥቃቱን ሙሉ በሙሉ አቀነባብራ የፈፀመችው ኢራን ናት ማለት ነው። ይሄ የኢራን አቅም ነው ያስደነገጣቸው።
4 332
🇪🇹⚡️በተመሳሳይ፣ በአማራ ግዛት የሚገኙ የፋኖ ታጣቂዎች፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለውን የገዢውን ፓርቲ ብልጽግና ሰራዊት አባላት መማረካቸውን፣ እንዲሁም ብዙውን መግደላቸውን ዛሬ ከወጡ ምስሎች ለማየት ተችሏል።
