ሀገረ ማርያም መሰረተ ተዋሕዶ ሰ/ት/ቤት
前往频道在 Telegram
ይህ የሀገረ ማርያም ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን መሠረተ ተዋሕዶ ሰንበት ት/ት ቤት አባላት መማሪያና መልእክት መጋሪያ ብቻ ይሆን ዘንድ የተዘጋጀ አውታር ነው።
显示更多943
订阅者
-124 小时
无数据7 天
+230 天
数据加载中...
吸引订阅者
六月 '26
六月 '26
+12
在0个频道中
五月 '26
+31
在2个频道中
Get PRO
四月 '26
+14
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+10
在1个频道中
Get PRO
二月 '26
+9
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+9
在1个频道中
Get PRO
十二月 '25
+19
在1个频道中
Get PRO
十一月 '25
+12
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+21
在2个频道中
Get PRO
九月 '25
+26
在2个频道中
Get PRO
八月 '25
+14
在1个频道中
Get PRO
七月 '25
+13
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+20
在1个频道中
Get PRO
五月 '25
+12
在0个频道中
Get PRO
四月 '25
+15
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+13
在2个频道中
Get PRO
二月 '25
+16
在0个频道中
Get PRO
一月 '25
+29
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+41
在0个频道中
Get PRO
十一月 '24
+45
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+39
在1个频道中
Get PRO
九月 '24
+49
在1个频道中
Get PRO
八月 '24
+68
在1个频道中
Get PRO
七月 '24
+85
在2个频道中
Get PRO
六月 '24
+111
在3个频道中
Get PRO
五月 '24
+146
在3个频道中
Get PRO
四月 '24
+168
在1个频道中
Get PRO
三月 '24
+199
在1个频道中
Get PRO
二月 '24
+106
在0个频道中
Get PRO
一月 '24
+97
在1个频道中
Get PRO
十二月 '23
+76
在3个频道中
Get PRO
十一月 '23
+292
在3个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 14 六月 | 0 | |||
| 13 六月 | 0 | |||
| 12 六月 | 0 | |||
| 11 六月 | 0 | |||
| 10 六月 | +2 | |||
| 09 六月 | +3 | |||
| 08 六月 | 0 | |||
| 07 六月 | +2 | |||
| 06 六月 | +1 | |||
| 05 六月 | 0 | |||
| 04 六月 | +1 | |||
| 03 六月 | +2 | |||
| 02 六月 | 0 | |||
| 01 六月 | +1 |
频道帖子
Repost from ዲ/ን ወ/አረጋዊ
የሳምራዊቷ ሴት ታርክ እና ትምህርት
በደንብ አንብቡት በቀን 5/10/2018 በአርብ ጸሎት ላይ እንማማራለን ብየ አስበው የነበረው ትምህርት ነው ከተመቻችሁ በክፍል ክፍል እለቃለሁ ጽሑፉን
። ውኃ አጠጪኝ ፤ዮሐንስ 4:7
ቃሉን የተናገረው በቃሉ .....ጌታችን መድሃንታች ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
ቃሉ የተነገረላት በሰማርያ በምትባል መንደር ላይ ትኖር ለነበረችው ለአንድት ሳምራዊት ሴት ነው።
ዮሐንስ 4:7 ከሰማርያ አንዲት ሴት ውኃ ልትቀዳ መጣች። ኢየሱስም። ውኃ አጠጪኝ አላት፤
የክርስቶስ አምላካችን ደቀመዛሙርት መብዛት በጀመሩ ጊዜ ከይሁዳ ምድር ወደ ገሊላ .......በሰማርያ ምትባል መንደር ልያልፍ ግድ ሆነበት ...... ዮሐንስ 4 ተመልከቱ
***አራት ቁልፍ ሀሳቦችን እንመልከት ።
==1ለምን ውኃ አጠጪኝ ብሎ ለመናት? 2 ክርስቶስ የተጠማው ምንድነው ? 3 የሕይወት ውኃ የተባሉት ምንድናቸው ? 4 ዛሬ ላይ ክርስቶስ አምላካችን ከእኛ የሚፈልገው ውሃ ምንድነው ?
❤1 ለምን ውኃ አጠጪኝ ብሎ ለመናት?
ክርስቶስ አምላካችን ሁሉን ማድረግ የሚችል አምላክ ነው በምድር ላይ ሁሉን ያከናወነ መጽሐፍ እንዳለ ሁሉ በእርሱ የሆነ ነው ።. ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም።ዮሐንስ 1:3 ስለዚህ ሁሉን ማድርግ እየቻለ ለምን ውኋ አጠጭኝ አላት ? የሚከተለሉትን ነጥቦች ልያስተምረን ነው
1:::እውነተኛ ሰው መሆኑን ለማሳየት
ክርስቶስ ፍጹም አምላክ እንደሆነ ሁሉ ፍጹም ሰውም ነው።ድካም፣ ረሃብ እና ጥማት እንደ ሰው ተቀብሎ ነበር።
“ውኃ አጠጪኝ” ማለቱ ጥማቱን ያሳያል።6. በዚያም የያዕቆብ ጕድጓድ ነበረ። ኢየሱስም መንገድ ከመሄድ ደክሞ በጕድጓድ አጠገብ እንዲህ ተቀመጠ፤ ጊዜውም ስድስት ሰዓት ያህል ነበረ።ዮሐንስ 4:6 በእግሩ ብዙ ምዕራፍ በመጓዙ ለስም አጠራሩ አምልኮትና ሰግደት ይሁንና በለበሰው ስጋ ተጠማ ተራበ በዚህም ሁሉ ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ መሆኑን ገለጠልን ።ቅዱስ ቀርሎስ ዘእስክንድርያ እንደተናገሩት ፣ ጌታ የሰውን ባሕርይ በእውነት ስለ ተዋሐደ ጥማትን፣ ድካምንና ረሃብን በሰውነቱ ተቀብሏል፤ ነገር ግን እነዚህ መለኮቱን አይቀንሱም።
2 ሳምራዊቷን ሴት ወደ እምነት ለማቅረብ
ውይይቱን የጀመረው በውኃ ጥያቄ ነበር።
ከዚያም ሴቲቱን ወደ “ሕይወት ውኃ” ማለትም ወደ መንፈሳዊ ጸጋ አመራት።
3 ትሕትናውን ለማሳየት
የዓለም ፈጣሪ ሆኖ ሳለ ከአንዲት ሴት ውኃ ጠየቀ።
ይህ የታላቅ ትሕትና ምሳሌ ነው።
2 ክርስቶስ የተጠማው ምንድነው part Two
| 2 | ቅዱስ አምብሮስ፦ "የሃይማኖት ትምህርትን መማር ማለት የሕይወትን መሪ ማግኘት ማለት ነው። ማዕበል በበዛበት የዚህ ዓለም ባሕር ላይ መጻሕፍትና የአባቶች ትምህርት እንደ ኮምፓስ (አቅጣጫ ጠቋሚ) ሆነው ይመሩሃል።"
ተመዝግቦ በመማርና Share በማድረግ ሃይማኖታዊ ግዴታዎን ይወጡ !!! | 10 |
| 3 | ቅዱስ አምብሮስ፦ "የሃይማኖት ትምህርትን መማር ማለት የሕይወትን መሪ ማግኘት ማለት ነው። ማዕበል በበዛበት የዚህ ዓለም ባሕር ላይ መጻሕፍትና የአባቶች ትምህርት እንደ ኮምፓስ (አቅጣጫ ጠቋሚ) ሆነው ይመሩሃል።" | 24 |
| 4 | 没有文字... | 48 |
| 5 | 没有文字... | 70 |
| 6 | አስራት ምንድን ነው?
አስራት ማለት ከሰው ገቢ፣ ምርት ወይም ንብረት አስረኛውን (10%) ለእግዚአብሔር መለየት ማለት ነው። "አስራት" የሚለውም ቃል ከ"አስር" የተገኘ ነው።
የአስራት ታሪክ
1. ከሕግ በፊት በአብርሃም ዘመን
አስራት የጀመረው በሙሴ ሕግ አይደለም። ከሙሴ በፊት በብሉይ ኪዳን አባቶች ዘመን ይታያል።
አብርሃም ነገሥታትን ድል ካደረገ በኋላ ከያዘው ምርኮ አስረኛውን ለመልከ ጼዴቅ ሰጠ (ዘፍጥረት 14፥20)።
ይህ የሚያሳየው አስራት ከሕግ በፊትም እንደ ምስጋናና እንደ አምልኮ መቅረቡን ነው።
2. በያዕቆብ ዘመን
ያዕቆብ በቤቴል እግዚአብሔርን ሲማጸን፦
"ከምትሰጠኝ ሁሉ አስረኛውን ለአንተ እሰጣለሁ"
ብሎ ተሳለ (ዘፍጥረት 28፥22)።
ይህም አስራት ከእግዚአብሔር በረከት ጋር የተያያዘ መሆኑን ያሳያል።
3. በሙሴ ሕግ
እግዚአብሔር ለእስራኤል ሕዝብ አስራትን እንዲያቀርቡ አዘዘ።
የአስራት ዓላማዎች፦
ሀ. ለሌዋውያን
ሌዊ ወገን ለቤተ መቅደስ አገልግሎት ተለይቶ ነበር፤ የራሱ የመሬት ርስት ስላልነበረው ሕዝቡ ከአስራታቸው ይደግፉት ነበር። (ዘኍልቍ 18፥21)
ለ. ለቤተ መቅደስ አገልግሎት
የመቅደስ አገልግሎት፣ መሥዋዕት እና ሌሎች ቅዱሳን ሥራዎች በአስራት ይደገፉ ነበር።
ሐ. ለድሆች
በየሦስት ዓመቱ የሚሰበሰብ አስራት ለመጻተኞች፣ ለድሆች፣ ለድሀ አደጎችና ለመበለቶች ይውል ነበር (ዘዳግም 14፥28-29)።
4. በነቢያት ዘመን
ሕዝቡ አስራት መስጠት ሲተው እግዚአብሔር በነቢዩ ሚልክያስ አማካኝነት እንዲህ አለ፦
"ሙሉ አስራቱን ወደ ጎተራ አምጡ" (ሚልክያስ 3፥10)
ይህ የተነገረው ሕዝቡ የቤተ መቅደስን አገልግሎት ችላ ስላለ ነበር።
5. በአዲስ ኪዳን
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስራትን በቀጥታ አልሻረውም፤ ነገር ግን ከአስራት ይልቅ ፍትሕ፣ ምሕረትና እምነት እንዳይረሱ አስተማረ።
"እነዚህን ማድረግ ሳይተዉ ያንንም ማድረግ ይገባችኋል" (ማቴ 23፥23)
በሐዋርያት ዘመን ምዕመናን ከአስረኛ በላይ እንኳ ንብረታቸውን ለችግረኞችና ለቤተ ክርስቲያን ያካፍሉ ነበር (ሐዋ. 4፥32-35)።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ቤተ ክርስቲያኒቱ አስራትን እንደ ቅዱስ ልማድ ትቀበላለች። ምዕመናን ከገቢያቸው አስረኛውን ለቤተ ክርስቲያን፣ ለካህናት አገልግሎት፣ ለድሆች እና ለወንጌል ሥራ እንዲያወጡ ትመክራለች።
ነገር ግን አስራት በፍርሃት ወይም በግዴታ ሳይሆን፣ በፍቅርና በምስጋና መሰጠት አለበት። ቅዱስ ጳውሎስም፦
"እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፤ በኀዘን ወይም በግድ አይደለም፤ እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጥን ይወዳል" (2ኛ ቆሮ. 9፥7)።
የአባቶች ማብራሪያ
የኦርቶዶክስ አባቶች አስራትን እንደ "የምስጋና መጀመሪያ ፍሬ" ይመለከቱታል። ሰው 100% ያለው ሁሉ የእግዚአብሔር ስጦታ መሆኑን በመቀበል 10% በመለየት ለፈጣሪው ምስጋና ያቀርባል።
ስለዚህ በኦርቶዶክስ አስተምህሮ አስራት የገንዘብ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የእምነት፣ የምስጋና እና የታዛዥነት ጉዳይ ነው። | 92 |
| 7 | 没有文字... | 109 |
| 8 | 没有文字... | 104 |
| 9 | 没有文字... | 114 |
| 10 | 没有文字... | 114 |
| 11 | 没有文字... | 91 |
| 12 | 没有文字... | 97 |
| 13 | በንስሐ ውስጥ ያላችሁ ራሳችሁን ዝቅ ዝቅ አድርጉ
ይ.ዲ፦
❝እለ ውስተ ንስሐ ሐሎክሙ አትሕቱ ርዕሰክሙ — በንስሐ ውስጥ ያላችሁ ራሳችሁን ዝቅ ዝቅ አድርጉ❞
ትርጓሜ፦
ዲያቆኑ «ራሳችሁን ዝቅ ዝቅ አድርጉ» ማለቱ ልቡናችሁን ከትዕቢት ለዩ ማለት ነው፡፡ ይኸውም ዮሐንስ መጥምቅ ትዕቢትን በተራራና በኮረብታ መስሎ ሲናገር፦
❝ተራራውም፣ ኮረብታው ሁሉ ዝቅ ይበል፤ ሰንከልካላውም የቀና ጥርጊያ ይሁን ወጣ ገባ መንገድም ይስተካከል❞
— ብሏል (ሉቃ ፫፥፭-፯) ይህም ማለት ተራራ/ኮረብታ የተባለው ትዕቢተኛ ልቡና፤ ሰንከልካላ ወጣ ገባ መንገድ የተባለው ደግሞ የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት የሚጠራጠር ተጠራጣሪ ልብ ነው። ስለዚህ ከጥርጥርና ከትዕቢት፣ ተለይታችሁ በፍጹም ትሕትና ሁናችሁ ካህኑ የሚለውን አድምጡ ለማለት ነው።
ካህኑም አያይዞ ለምዕመናኑ፦
❝አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ በንስሐ ውስጥ ወዳሉት ወገኖችህ ምዕመናን ተመልከት እንደ ይቅርታህም ብዛት ይቅር በላቸው፤ እንደ ቸርነህትህ ብዛት በደላቸውን አጥፋላቸው፤ ከክፉ ነገርም ሁሉ ጠብቃቸው፥ ሰውራቸውም፡፡ የቀደመ ሥራቸውን ይቅር ብለህ በሰላም ነፍሳቸውን አድን❞
— እያለ ሲጸልይላቸው ልቡናቸው ከትዕቢት የለዩ ሰዎች ሁሉ ጸሎቱ ይደርሳቸዋል፡፡ ጸሎቱ እንዲደርሰው የሚፈልግ ሁሉ ልቡናችሁን ሊያዋርድ ይገባዋል ማለት ነው፤ ጸጋ እግዚአብሔር በትዕቢት አትገኝም። ራስን ዝቅ ዝቅ በማድረግ፥ ጌታዬ ሆይ በአንተ ምህረት እንጂ እንደ ስራዬ ቢሆንማ በመቅደስህ መገኘት ቀርቶ ልጅህ ለመባል ስንኳ ባልተገባኝ ነበር እያሉ ከልብ ራስን ዝቅ ዝቅ በማድረግ ሲሆን ግን ያኔ ትገኛለች።
❝ራሱን ከፍ ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳል፤ ራሱንም የሚዋርድ ይከብራል❞
— እንዲል ቅዱስ መጽሐፍ (ሉቃስ ፲፰፥፲፫-፲፰)።
ከዚህ በኋላ ዲያቆኑ፣ ካህኑና ሕዝቡ በንባብ «ተንሥኡ ለጸሎት» ፥ «እግዚኦ ተሣሃለነ» ፤ «ሰላም ለኩልክሙ» ፥ «ምስለ መንፈስከ» ይላሉ፡፡ ይህም በተለየ ሁኔታ በንባብ ብቻ መባሉ መንፈስ ቅዱስ ሕብስቱን ለውጦ ሥጋ ወልደ አምላክ አምላክ፥ ወይኑንም ለውጦ ደመ አምላክ አድርጎ በቅዳሴው ጊዜ ምን ሰዓት እንደሚለውጠው አለመታወቁን ያስገነዝበናል፤ ዜማ እንደሚታወቀው የጩኸት ነው ከሩቅ ይሰማል፤ በትሑት ዜማ ወይም በንባብ ከሆነ ግን ጩኸቱ ብዙ አይደለምና በዜማ ጮክ ብሎ ያለመሰማቱ መንፈስ ቅዱስ ሥጋ ወደሙን ሲለውጥ እዚህ ሰዓት ላይ ነው የሚለውጠው ተብሎ አለመታወቁን ያሳስባል።
ከዚህ ቀጥሎ ኅብስቱ ተለውጦ ሥጋ ወልደ አምላክ፤ ወይኑም ተለውጦ ደመ ወልደ አምላክ መሆኑን ካህኑ ይመሰክራል፤ እምነቱንም ይገልጣል፡፡
ዲ/ን ኃይለራጉኤል | 161 |
| 14 | 没有文字... | 128 |
| 15 | ሁሉም ካህናት የእግዚአብሔር ላይሆኑ ይችላሉ
ሁሉም ካህናት የእግዚአብሔር ላይሆኑ ይችላሉ በሁሉም ካህናት ግን እግዚአብሔር ይሠራል ።
ሳይገባቸው የተቀበሉ እና ተቀብለውም እንደሚገባቸው የማይኖሩ አሉና።
ከዚህም በላይ ክህነቱን እና ክርስትናን ጭምር የሚያስነቅፋ አሉ።
ካህናት በሚቻላቸው መጠን ለተሰጣቸው ክብር በሚገባ መጠን ለመኖር መትጋት ይኖርባቸዋል ።
ክህነቱን አቅልለው በሚያስቅፋ መልኩ የሚኖሩ ከሆነ ከእግዚአብሔር ቅጣት በሥጋም በነብስም አያመልጡም ።
ምዕመናን ግን ካህናት በእግዚአብሔር እንደሚሾሙ ተረድተው የሥነምግባር ጉድለት ቢኖርባቸውም ክህነቱን እስካላቸው ድረስ ለካህን እንደሚገባ የማክበር ግደታ አለባቸው ።
https://t.me/felege_yohanis | 125 |
| 16 | 没有文字... | 302 |
| 17 | ለሃይማኖት ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ!
የቡሌ ሆራ ፈለገ ዮርዳኖስ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወልደታ ለማርያም ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት፤ ልዩ የክረምት መንፈሳዊ ትምህርት (ስልጠና) አዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል።
📌 የሚሰጡ የትምህርት ዓይነቶች፦
ትምህርተ ሃይማኖት
የቤተ ክርስቲያን ታሪክ
ነገረ ድኅነት
📅 የትምህርት ጊዜ ሰሌዳ፦
የትምህርቱ ቆይታ፦ ከሰኔ 15 እስከ ነሐሴ 30 ቀን
የመማሪያ ቀናት፦ ዘወትር ከሰኞ እስከ ረቡዕ
የመማሪያ ሰዓት፦ ከቀኑ 10:30 - 12:00
ትምህርቱ የሚጀመርበት ቀን፦ ሰኔ 15 ቀን
📍 ቦታ፦ በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ
📝 የምዝገባ መረጃ፦
የምዝገባ ቀን፦ ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 14 ቀን
📞 ለበለጠ መረጃ በነዚህ ስልኮች ይደውሉ፦
0979823772
0706874979
📱 የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ፦
https://t.me/felege_yohanis
"የእግዚአብሔር ቃል ይደርሳችሁ ዘንድ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!" | 220 |
| 18 | ስለዚህ ራስሽን ተገቢ ባልሆነ መንገድ ለመሸለምና ለመኳኳል አትጣጣሪ። ጎደሎ የኾነ የእግዚአብሔር ሥራ የለምና፤ ወይም በአንቺ አማካኝነት መስተካከል የሚሻው ግብር የለምና።
በእንተ makeup ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የማቴዎስ ወንጌል ማብራሪያ ክፍል ሁለት ገጽ 123
ከክርስቶስ ጋር አንድ እንደ ሆንሽ አስቢና ከዚህ የማይገባ ነገር ራስሽን አርቂ። ጌታሽ ክርስቶስ በእነዚህ መቀባባቶች ደስ አይሰኝምና፤ ይልቅስ እርሱ የሚፈልገው ሌላ ውበትን ነው - እርሱ እጅግ አብዝቶ የሚሻው የነፍስሽን ውበት ነው። ነቢዩ ደስ ትሰኚበት ዘንድ ያዘዘሽም ይህንን ነው፤ እንዲህ በማለት:- “ንጉሥ ውበትሽን ወዶታልና” (መዝ.44:11)።
ስለዚህ ራስሽን ተገቢ ባልሆነ መንገድ ለመሸለምና ለመኳኳል አትጣጣሪ። ጎደሎ የኾነ የእግዚአብሔር ሥራ የለምና፤ ወይም በአንቺ አማካኝነት መስተካከል የሚሻው ግብር የለምና።
የእግዚአብሔር መልአክ ይቅርና የአንድ ንጉሥ ሐውልትም ተሠርቶ ከቆመ በኋላ ማንም መጥቶ የራሱን ነገር ለመጨመር ቢደፍር ከዚያ በኋላ ከባድ ቅጣት ያገኘዋል እንጂ ደኅና ኾኖ አይኖርም። ሀቅም... ሰው በሠራው ላይ እንዲህ መጨመር አትችዪም። ታዲያ እግዚአብሔር የሠራውን ለማሻሻል ትደፍሪያለሽ? እንዲህ ለማድረግ ስታስቢ አንዳች የእሳት ገሃነም ጥቂትስ እንኳን ትዝ አይልሽም? የነፍስሽን ጥፋት አይታሰብሽምን? በዚህ ምክንያት ቸል ብለሻል፤ ድካምሽን ዅሉ በሥጋሽ ላይ ባክኗል።
ስለ ነፍስ የምንናገረው ለምንድን ነው? ለገዛ ሥጋሽም ቢኾን የሚገኘው አንቺ ካሰብሽው ዅሉ በተቃራኒ ነው። እስኪ ተመልከቺ! መልካ መልካም መኾንን ነው አይደለም የምትፈልጊው? ይህ ግን መልካም መልካም ኾነሽ እንድትታዪ አያደርግሽም። ባልሽን ደስ ማኘት ነው አይደለም የምትፈልጊው? እንደዚህ ማድረግሽ ግን ያሳዝነዋል። ባልሽን ብቻም አይደለም፤ ሌሎች ባዕዳን ሰዎችንም ጭምር አንቺን እንዲንቁሽ ያደርጋቸዋል... | 177 |
| 19 | በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስ ለምን ዓላማ ወረደ?
፩. ኀይልን ለመስጠት
ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ በሰጣቸው ተስፋ መሠረት በበዓለ ሃምሳ ለደቀዛሙርቱ መንፈስ ቅዱስን ስለላከላቸው፣ ደቀ መዛሙርቱ በመንፈስ ቅዱስ ኀይል ድኩማን የነበሩ ኀያላን፤ ፈሪዎች የነበሩ ደፋሮች ሆነው በራቸውን ዘግተውና ተደብቀው ከነበሩበት ቤት በድፍረት ወጥተው በቤተ መቅደሱ አካባቢ በተለያዩ ሥፍራዎች ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ በይፋ ያለ አንዳች ፍርሃት ማስተማር ጀምረዋል። በዚያ የተሰበሰቡት የአይሁድ ሕዝቦች በሁለት ነገር እጅግ ተደነቁ፣ አንደኛ ሐዋርያት ለእነሱ እንግዳ የሆነ ስለ ክርስቶስ አዲስ ትምህርት ማስተማራቸው ሲሆን፣ ሁለተኛ ደቀ መዛሙርቱ በተለያዩ ቋንቋዎች ሲነጋገሩ ማየታቸውና መስማታቸው ነበር። ፈሪ ልብ የነበራቸው ሐዋርያት ይህንን አልጫውን ዓለም በወንጌል ጨውነት ለማጣፈጥ ጨለማውን ዓለም ወደ ብርሃን ለመለወጥ ከአርያም ልዩ ኀይል ያስፈልጋቸው ስለነበር ጎይልን ሊያለብሳቸው ወርዷል። ጌታችን ሊያርግ ሲል እንዲህ ብሎ ተስፋ ሰጥቷቸው ነበር፦
❝እነሆም አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ አልክላችኋለሁ፣ እናንተ ግን ከላይ ኀይል እስክትለብሉ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ❞
— ብሏቸው ስለነበር በዚያ ቃል ኪዳን መሠረት መንፈስ ቅዱስ ኀይል ሰማያዊ ሊያጎናጽፋቸው ወረደላቸው (ሉቃ ፳፬፥፵፱ ፤ የሐዋ ፩፥፰)።
፪. ሐሰተኛውን ዓለም ለመውቀስ
ሽፍታው በርባን እንዲፈታላት ጻድቁ ክርስቶስ እንዲሰቀልላት አብዝታ የጮኸችው ሐሰተኛዋ ዓለም መንፈስ ቅዱስና መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ሰው ካልሆነ በስተቀር ደፍሮ ሊወቅሳት የሚችል ኀይል አልነበረም:: ምክንያቱም በውስጧ የሚኖሩ ሐስተኞች ናቸውና:: ለበርባን ነጻነትን፣ ለክርስቶስ ሞትን የደገሰችውን ዓለም መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት አድሮ ወቅሷታል። ጌታችን በቅዱስ ወንጌሉ፦
❝እርሱም መጥቶ ስለኀጢአት ስለጽድቅም ስለፍርድም ዓለምን ይወቅሳል
❞
— ብሎ በተናገረው መሠረት መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት አንደበት ይህቺን ግፈኛ ዓለም ወቅሷታል - (ዮሐ ፲፮፥፲፪)።
በእውነተኛው ጌታ አለማመን፤ ድል ስለተነሣው ጠላት ስለዲያብሎስ ውድቀት አለማወቅ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቀደመ ክብሩ መመለሱን አለማመን ትልቅ በደል ስለሆነ ይህንኑ በሐዋርያት ላይ አድሮ ግልጥ አድርጎ ለመውቀስ መንፈስ ቅዱስ ወረደ:: ስለዚህ ድንቅ ምሥጢር ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ ሲዘምር፦
❝አውጽኦሙ አፍአ እስከ ቢታንያ እንሥእ አዴሁ ወባረኮሙ ወይቤሎሙ ሰላም ለክሙ አዐርግ ሰማየ ኀበ አቡየ ወእቡክሙ ካዕበ እመጽእ ወእነሥአክሙ እነ እሄሉ ምስሌክሙ እፌኑ ለክሙ ጰራቅሊጦስሃ መንፈስ ጽድቅ — እስክ ቢታንያ አወጣቸው እጁን አንሥቶ ባረካቸው ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው ወደ አባቴ ወደ አባታችሁ ዐርጋለሁ፤ ዳግመኛም እመጣለሁ እወስዳችኋለሁ፤ እኔ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ፤ የእውነት መንፈስ ጰራቅሊጦስንም አልክላችኋለ
ሁ❞
— በማለት ተቀኝቷል፡፡
፫. ሰዎችን ወደ እውነት ለመምራት
ሕይወታችንን ወደ እውነት የሚመራን መንፈስ ቅዱስ ነው፤ ወይም በእውነት ጸንተን ስለእውነት እንድንመስክር የሚያደርገን መንፈስ ቅዱስ ነ
ው።
❝ወይቤሎሙ እፌኑ ለክሙ መንፈሰ ጽድቅ ጸራቅሊጦስሃ ዘይሄሉ ዘልፈ ምስሌክሙ ኢየጎድገክሙ ዕጓለ ማውታ ትኩኑ ዘኢይክል ዓለም ነሢኦቶ — ከእናንተ ጋር የሚኖር የእውነት መንፈስ ጰራቅሊጦስን እልክላችኋለሁ፤ እንደ እጓለ ማውታ አልተዋ
ችሁም❞
ነቢዩ ዳዊት ወደ ጽድቅ ጎዳና ወደ እውነት ቦታ የሚመራ መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ ሲ
ዘምር፦
❝ወመንፈስከ ቅዱስ ይምርሐኒ በምድረ ጽድቅ — ቅዱስ መንፈስህ ወደ ጽድቅ ምድር
ይምራኝ❞
— ብሎ እግረ ነፍሳችንን ወደ መንስተ ሰማያት፣ እግረ ልቡናችንን ወደ ወንጌል የሚያቀናልን መንፈስ ቅዱስ ነው!
አሁን መንፈስ ቅዱስ ወደ እውነት ይመራል ሲባል ያለፈቃዳችን ይወስዳል ማለት አይደለም፤ ልቡናችን በጎ ሐሳብ እንዲያስብ ያደርገዋል፣ ሐሳብ ያሰበ ልቡና ደግሞ ወደ በጎ ስፍራ ይሄዳል ማለት ነው (መዝ ፻፵፩፥፲) ፤ ወደ እውነት የሚመራን መንፈስ ቅዱስ በመሆኑ ሁላችንም በዚህ መንፈስ ምሪት ልንጓዝ ያስፈልጋል። እውነተኞች ክርስቲያኖች ያለመንፈስ ቅዱስ ቅኝት በራሳቸው ምኞት አንዳችም ነገር አያደርጉም፤ የክርስቲያኖች የሕይወት አቅጣጫ ጠቋሚያቸው መንፈስ ቅዱስ ነው። ሐዋርያው ቅዱስ
ጳውሎስ፦
❝እናንተ ግን የእግዚአብሔር መንፈስ በእናንተ ቢኖር በመንፈስ እንጂ በሥጋ አይደላችሁም የክርስቶስ መንፈስ ከሌለው ግን የእርሱ ወገን አይደለም፣ ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ ቢሆን ሰውነታችሁ በኀጢአት ምክንያት የሞተ ነው፤ መንፈሳችሁም በጽድቅ ምክንያት ሕ
ያው ነው❞
— በማለት መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ሰው በምድርም ቢኖር ኑሮው ግን ሰማያዊ ነው፤ በሥጋ ቢታይም ሕይወቱ ግን መንፈሳዊ መሆኑን ነግሮናል። ለኀጢአት ሙ መሆን ማለት ኀጢአት አለመሥራት ማለት ነው፣ ለጽድቅ ሕያው መሆን ማለት ደግሞ ለጽድቅ ሥራ መትጋት ማለት ነው (ሮሜ ፰፥፱)።
ልጅነታችንን ከምናስመስክርበት ወይም ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅር ከምናሳይበት መንገድ አንዱ በምንኖረው ኑሮ ውስጥ በእግዚአብሔር መንፈስ መመራት መቻላችን ነው፤ ሐዋርያው ቅ
ዱስ ጳውሎስ፦
❝በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመራ ሁሉ እነዚህ የእግዚአብሔ
ር ልጆች ናቸው❞
— ሲል ያስረዳናል (ሮሜ ፰፥፲፬)።
አባቶቻችን «ጻድቃንን ወደ ገዳም ሰማዕታትን ወደ ደም የሚወስድ መንፈስ ቅዱስ ነው»፡፡ ይላሉ:: ይህ ማለት ጸድቃን በገዳማት ሰማእታት በምስክርነት ጸንተው እንዲኖሩ ኀይል ብርታት የሚሰጥ መንፈስ ቅዱስ ነው ለማለት ነው (ዮሐ ፲፮፥፲፫ ፤ ዮሐ ፳፩፥፲፰)። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሐዋርያት ከዕርገቱ በፊት እንዲህ ሲል ተስፋውን
ነግሯቸው ነበር፦
❝እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ይመራችኋል የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ ከራሱ አይናገርምና፤ የሚመጣውንም ይነግራችኋል፤ እርሱ ያከብረኛል፤ ለእኔ ካለኝ ወ
ስዶ ይነግራችኋልና❞
— በማለት ሐዋርያት ለእውነትና በእውነት መኖር እንዲችሉ በሥራቸው ሁሉ መንፈስ ቅዱስ እንደማይለያቸው ነግሯቸዋል (ዮሐ ፲፮፥፲፫)።
መንፈስ ቅዱስ ኀጢአተኞችን ወደ ንስሐ ይመራል (መዝ ፲፬፥፰)።
በክርክር ጊዜም እውነቱን ይገልጣል (ማቴ ፲፥፳ ፤ ዮሐ ፲፬፥፮ ፤ ፩ኛ ቆሮ ፲፪፥፫)።
፬. ስለ እግዚአብሔር ወልድ ለመመስከር
ዓለም እግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስን ስላላወቀው ስለ ወልደ እግዚአብሔር በሐዋርያት አድሮ ለመመስከር ተገለጠ:: ስለዚህ አንድ ሰው መንፈስ ቅዱስ ምሥጢሩን ካልገለጠለት በቀር ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ጌትነት ማወቅና መመስከር አይችልም (ዮሐ ፲፭፥፳፮)። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ስለጌታችን ስለኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ ልጅነት፥ ጌትነትና ከሃሊነት መመስከር የሚቻለው በመንፈስ ቅዱስ ኀይል
እንደሆነ ሲናገር፦
❝ስለዚህ ማንም በእግዚአብሔር መንፈስ ሲናገር ኢየሱስ የተረገመ ነው የሚል እንደሌለ፤ በመንፈስ ቅዱስ ካልኾነ በቀር ኢየሱስ ጌታ ነው ሊል አንድ እንኳን እንዳ
ይችል አስታውቃችኋለሁ❞
— በማለት ያለመንፈስ ቅዱስ ገላጭነት የክርስቶስን ጌትነት መመስከር እንደማይቻል ተናግሯል (፩ኛ ቆሮ ፲፪፥፫)። | 129 |
| 20 | 没有文字... | 1 |
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
