Assaye Derbie
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Assaye Derbie 的分析概览
频道 Assaye Derbie (@asayede) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 368 名订阅者,在 博客 类别中位列第 2 646,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 349 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 368 名订阅者。
根据 18 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -169,过去 24 小时变化为 -11,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 37.71%。内容发布后 24 小时内通常能获得 11.37% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 419 次浏览,首日通常累积 1 634 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 38。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 19 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 博客 类别中的关键影响点。
14 368
订阅者
-1124 小时
-237 天
-16930 天
帖子存档
14 368
በቂሊንጦ እስር ቤት ውስጥ ፣ የተደቀነብንን አደጋ መላው ህዝባችን እንዲያውቅልን እንፈልጋለን!
በቂሊንጦ የፌዴራል እስር ቤት የምንገኝ የአማራ የህሊናና የፖለቲካ እስረኞች በከፍተኛ ችግር ውስጥ እንገኛለን። የማረሚያ ቤቱ ከሚፈፅምብን በርካታና የተለመዱ አስተዳደራዊ ፣ አካላዊና ሥነልቦናዊ ጥቃት በተጨማሪ የፌዴራል ፖሊስ የኮማንዶ ፣ የአዲስ አበባ ልዩ ኃይል ፣ የመከላከያ ኮማንዶ ከፌዴራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራና አቃቤ ህግ ጋር በመቀናጀት ተከታታይ የህልውና ስጋት የሚደቅኑ ግፎችና የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እየፈፀሙብን ይገኛሉ።
በትናንትናው እለት የፌዴራልና የመከላከያ ኮማንዶ ወታደሮች ከማረሚያ ቤቱ ፖሊስ ጋር በመቀናጀት ከሌሊቱ 10:00 ሰዓት ላይ ''ዞን አምስት'' ተብሎ በሚጠራውና እነ አቶ ዮሀንስ ቧያለው ፣ ክርስቲያን ታደለ ፣ አብዱራህማን አሊ ፣ ዶ/ር ሲሳይ አውግቸውና ሌሎችም የአማራ የፖለቲካና የህሊና እስረኞች የሚገኙበትን ዞን በመውረር ፣ እስረኞችን በብርድ ከዞን ቅጥር ውጭ በማስወጣት ፣ አካላዊ ጥቃት በማድረስና በማንገላታት ከፍተኛ ግፍ ፈፅመዋል።
ውድ ወገኖቻችን! ''በህዝባችን ላይ የሚፈፀመው ሥርዓታዊ ጥቃትና የህልውና አደጋ መቆም'' አለበት ብለን በመታገላችን ምክንያት እስከ ሁለት ዓመት ድረስ ያለምንም ፍትህ ፥ ከሰመራና አዋሽ አርባ የማሰቃያ ካምፖች ፣ ሜክሲኮ ከሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ፣ በገላንና ማዕከላዊ ማጎሪያዎች ከተፈፀመብን የግፍ መዓት ተርፈን እስከአሁኑ ሰአት ድረስ በፍትህ ማጣት እየተሰቃየን እንደምንገኝ ይታወቃል።
በአሁኑ ሰዓት በብልፅግና ሥርዓት ተስፋ የቆረጠ አካሄድ ምክንያት ፣ በቂሊንጦ የምንገኝ የአማራ የህሊናና የፖለቲካ እስረኞች የህልውና አደጋ እንደተደቀነብንና በማናቸውም ሰዓት ወደከፉ የማሰቃያ ስፍራዎች ድጋሚ ልንጋዝና በህይወታችን ላይ አደጋ የሚጥል ጥቃት ሊፈፀምብን እንደሚችል መላው ህዝባችን እንዲያውቅልን እንሻለን!
የአማራ ህዝብ ያሸንፋል !
14 368
"የመምህራን ደሞዝ ይስተካከል፥ በወቅቱም ይከፈል" የሚሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ሀድያ ዞን ተማሪዎች ቁጣቸውን ሲገልጹ ውለዋል። በመላው ኢትዮጵያ የአመጽ እንቅስቃሴም እየተቀጣጠለ መሆኑ ተሰምቷል።💪
14 368
አፋሕዶች የአንድ ጊዜ ዜና ከመሆን ይልቅ በቻሉት መጠን ትግሉን አዳክመውና የአማራን ሞራል ገድለው በተበጣጠሰ መልኩ መግባት ስለፈለጉ እንጂ የሁሉም እጣ ፈንታ ከወ/ሮ ጸዳለ የሚለይ አይደለም። ሁሉም የአፋሕድ መሪዎች ከብአዴን ጋር ተደራድረው ስለጨረሱ የመከታውም ይሁን የኮሎኔል ፈንታው፣ የደረጄም ይሁን የማስረሻ ፍጻሜ ከጸዳለ ጋር ተመሳሳይ ነው።
14 368
ጥብቅ ማሳሰቢያ፦
የመከላከያ ኮማንዶ አባላትን በተለያየ መንገድ(በመክዳት፣በመማረክ...) ወደ ፋኖ በመቀላቀል የፋኖ አመራሮችን ለመምታት ትዕዛዝ ተላልፎ እንቅስቃሴ ስለተጀመረ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መልዕክቱን አድርሱላቸዉ።
14 368
ውሸትን እና ክሕደትን ባሕላቸው ያደረጉት የአፋሕድ ደጋፊዎች በኢትዮ 360 አስነዋሪ ትንታኔ ዙሪያ የሠራሁትን ቪዲዮ ለእነሱ ፕሮፖጋንዳ በሚመች መልኩ ቆራርጠው እራሳቸውን እያስደሰቱ ስለሆነ እንዳትታለሉ አሳስባለሁ። ሙሉ ሐሳቡም ከስር ያለው መሆኑን እገልጻለሁ።
14 368
ኑሮውን ሰማይ ላይ ሰቅለህ የዜጎችን ገቢ ከመሬት ጠለል በታች ያደረግከው እለት ፥ ከሥራ መባረርም ሆነ ደሞዝ አልባ መሆን የማያስጨንቀው አመጸኛ ትውልድ እንደሚፈጠር ማወቅ ነበረብህ።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
