💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀
前往频道在 Telegram
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر» قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ ↓↓↓↓↓↓ @Ass_selefyaa_bot @Ass_selefyaa_bot
显示更多📈 Telegram 频道 💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀 的分析概览
频道 💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀 (@https_asselefya1) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 265 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 6 132,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 370 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 265 名订阅者。
根据 08 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -2,过去 24 小时变化为 -5,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 16.75%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.90% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 2 390 次浏览,首日通常累积 1 269 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر»
قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله
ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ
↓↓↓↓↓↓
@Ass_selefyaa_bot
@Ass_selefyaa_bot”
凭借高频更新(最新数据采集于 09 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
14 265
订阅者
-524 小时
-67 天
-230 天
帖子存档
Repost from 💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
ትዳር ማለት፦
~ሁለት ልቦችን ማስተሳሰር
~ሁለት ነፍሶችን ማያያዝ
~ሁለት ሩሖችን መቀላቀል
~በመጨረሻም ሁለት አካሎችን ማቀራረብ ማለት ነው።
በሺር አል ኢብራሂምይ [አል አሣር 3/297]
ጅዳ የኢቃማን (የባስፖርትን)ቁጥር ለማዉጣት አሻራ (በስማ)የሚሠጥበትን ቦታ የምታቁ ንገሩኝ
👉👉 @Ass_selefyaa_bot
አይ የኛ ሞኝነት! ሰዉ መሳደብ ስንፈልግ በማያቁን አካዉንት
በሚያቁን አካዉንት ደግሞ መልካም መልካም ያጫዉተናል ህእ? ግን ማን እያታለልን ይሆን ? መለይካዎች ስራ መዝገባችን ላይ በራሳችን ስም እንደሚፀፉ የት እየረሳነዉ ነዉ ግን !? አይገርማችሁም ??
#ትገርሚኛለሁ
=➭ያአሏህ!
አልቻልኩም ያ አሏህ አሁንስ ከፍቶኛል፡
መውጫና መግቢያዬ ቀኑ ጨልሞኛል፡
ከላይም ከታችም ወንጀል አስምጦኛል፡
የአርሹ ባለቤት የአለም ፈጣሪ፡
ከእናት በላይ አዛኝ እጂጉን መሀሪ፡
ያ አሏህ እባክህ በል ሀጂን ወፍቀኝ፡
ሀዘን በዝቶብኛል ደስታ ያጥለቅልቀኝ፡
እንደ አድስ ልወለድ መንገደም ይሁን ቀኝ፡
ለበይክ አልኩ አምላኬ__!!
ወዜ ተመጠጠ የልጂነት መልኬ፡
ልብሴም አልሆን አለኝ ገዝቸው በልኬ፡
ስለዚህ ከንግድህ ሀጂ ይሁን ታሪኬ፡
መካና መድናን ከማየው በስልኬ፡
በአካል ውሰደኝ ለበይክ አልኩ አምላኬ፡
✍ከወንድሜ ኑረድን ፅሁፍ የተቆረጠች
http://t.me/https_Asselefya1
Repost from هَذِهِ عَقيدَتُنَا
በቁንጅናሽ ልትወደጂ ትችያለሽ
👉የምትከበሪውና ትዳርሽ ፍሬያማ የሚሆነው
በአስተሳሰብሽ እና በዲንሽ ቀጥ ስትይ ብቻ ነው።
عِنْدَمَا تَقُول: "اَللَّهُ أَكْبَر"
فَعَلَيْكَ أَنْ تَعْرِفَ مَعْنَاهَا حَقِيقَةً!
ابن عثيمين رحمه الله
=
🔖 ሰዉን አዋርዳለሁ ሲሉ ለራስ መዋረድ እንዳለ ስንቶች አስተዉለናል ህእ!? ለምሳሌ ፦
ከአንድ እኛ ካልመለስን ካልፃፍን ሲደወል ካላነሳን በግድ አዉሩኝ ብሎ አያስገድድማ!? So በራስ እጅ ብዙ ቦታ ተደርሶ ያ ሰዉየ ብቻ ጥፋተኛ ማድረግ ይሄ ጅልነት ነዉ።
ለመፍረድ ከሁለቱም ጎን ያለ ነጥብ መታየት ያለበት ከአንድ በኩል ይዞ መሮጥ ይሄ አሽቃባጭነት ይባላል።
=Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የደዕዋው ጉዳይ ለሚያሳስባችሁ ሁሉ!
~
እውቀት ያለው በእውቀቱ፣
ሃብት ያለው በሀብቱ፣
በየትኛውም በምንችለው መንገድ ሁሉ ለደዕዋ አስተዋፅኦ ይኑረን። መስጂዶችን፣ ማህበራዊ መገናኛዎችን፣ ... ለደዕዋ እንደሚገባ እንጠቀማቸው። ካልሆነ የተጋረጡብንን አደጋዎች መቋቋም አንችልም።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
የዙል ሒጃ ስምንቱን ቀናት መፆም
~
ነብያችን ﷺ የዙልሒጃን አስር ቀናት አስመልክቶ እንዲህ ብለዋል፦
مَا مِنْ أَيَّامٍ الْعَمَلُ الصَّالِحُ فِيهِنَّ أَحَبُّ إِلَى اللَّهِ مِنْ هَذِهِ الأَيَّامِ الْعَشْرِ . فَقَالُوا : يَا رَسُولَ اللَّهِ ، وَلا الْجِهَادُ فِي سَبِيلِ اللَّهِ ؟ فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ : وَلا الْجِهَادُ فِي سَبِيلِ اللَّهِ ، إِلا رَجُلٌ خَرَجَ بِنَفْسِهِ وَمَالِهِ فَلَمْ يَرْجِعْ مِنْ ذَلِكَ بِشَيْءٍ
''በውስጣቸው መልካም ስራ ከሚፈፀምባቸው ቀናት ውስጥ ከነዚህ አስር ቀናት በላይ አላህ ዘንድ የተወደደ የለም።" "በአላህ መንገድ መታገልም ቢሆን?" ብለው ሲጠይቋቸው የአላህ መልእክተኛ ﷺ "በአላህ መንገድ መታገልም ቢሆን! በነፍሱም፣ በገንዘቡም ወጥቶ ከዚህ ውስጥ ምንም ያልተመለሰ ሰው ሲቀር" ብለው መለሱ። [አልቡኻሪይ፡ 969]
በዚህ መሰረት በነዚህ የተከበሩ ቀናት የተለያዩ ዒባዳዎችን መፈፀም በጣም ትልቅ ዋጋ ያለው ነው። ፆም ወደ አላህ መቃረቢያ ከሆኑ ዒባዳዎች ውስጥ አንዱ መሆኑ ግልፅ ነው። ከመሆኑም ጋር በያመቱ "የዙል ሒጃን አስር ቀናት መፆም ይቻላል ወይ?" የሚል ጥያቄ ሲነሳ ያጋጥማል። የግርታው መነሻ እናታችን ዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ "በነዚህ አስር ቀናት ውስጥ የአላህ መልእክተኛን ﷺ ፈፅሞ ፆመው አላየሁም" ማለቷ ነው። [ሙስሊም፡ 1179]
ይሄ ግን ግርታ ሊፈጥር የሚገባው አይደለም። እንደሚታወቀው የነብዩ ﷺ ሱና በሶስት መንገድ ይተላለፋል።
1- በቃላቸው
2- በተግባራቸው እና
3- ሌሎች ሲፈፅሙ አይተው የሚሰጡት ይሁንታ (ኢቅራር)።
የዙል ሒጃን ስምንት ቀናት መፆም ከነዚህ ውስጥ በቃላቸው የተላለፈው ሐዲሥ ውስጥ ይካተታል። ሐዲሡ አስተማማኝ፣ መልእክቱም ፆምን አካታች ነው። ከዚህ በኋላ የዓኢሻ ነብዩን ﷺ ሲፆሙ አለማየት የሳቸውን ጥቅል የቃል መልእክት ለመገደብ መነሻ መሆን የለበትም። ለዓኢሻ አለማየት የተለያዩ ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ። ደግሞ የሚገድብ መረጃ እስከሌለ ድረስ በጥቅል ቃላዊ መረጃ የተገኘው በቂ ነው።
ስለዚህ ሌሎች መረጃዎች ደካማዎች (ዶዒፎች) ቢሆኑ እንኳ መግቢያ ላይ የተጠቀሰው ሐዲሥ በቂ ማስረጃ ነው።
ይሄ እንግዲህ ስምንቱን ቀናት በተመለከተ ነው።
* ዘጠነኛው ቀን የሁለት አመት ወንጀል እንደሚያሳብስ አስተማማኝ መረጃ መጥቶበታል። [ሙስሊም፡ 1162] ስለዚህ ብዥታ የሚነሳበት አይደለም።
* አስረኛው ቀን በአል ስለሆነ አይፆምም።
ወሏሁ አዕለም።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor☞የዉሸት እና የሀሜት አደገኚት!!»
«በአል ኢህሳን የሰለፍዮችየየቲሞች ሴንተር ግንባታ ግሩፕ የተደረገ!!»
🎙በአቡ ረይስ ሙሀመድ ኢብኑ ኢማም
⟱⟱⟱⟱⟱⟱⟱⟱⟱⟱⟱⟱⟱⟱⟱⟱⟱
http://t.me/abu_reyyis_arreyyis
t.me/AlihsanCharityAssociation
Repost from قُدوَتي الصَحَابِيَاتْ🎀
ቤተሠቦቻችን ጎራ በሉ ተጋብዛችኋል
11:00 ስአት ላይ ማለትም ከ2 ስአት በኋላ ላይቭ እንገናኝ ተዘገጃጁ ቂርአት ስራ ጨራርሱ 🤏
ወላጆች ልጆቻቸው ይስቁ ዘንድ ያለቅሳሉ፣
ወላጆች ልጆቻቸው ይደሰቱ ዘንድ ያዝናሉ፣
ወላጆች ልጆቻቸው ይጠግቡ ዘንድ ይራባሉ...!
=
-አሰላሙዐለይክ ሰሚራ ነኝ አወከኝ?
-ወአለይኩምሰላም አወቄሻለሁ እንዴት ነሽ?
አልሀምዱሊላህ መንጃፍቃድ አወጣው እኮ ሰማህ?
-ይህን ለኔ መናገር አይጠበቅብሽም የኔና ያንቺ ነገር አብቅቷል
-መንገድ ስትሻገር ግራና ቀኝ እያየህ ለማለት ነው በተረፈ አሏህ ይጠብቅህ ህእ
ለፈገግታ ያክል ነዉ ¡
