3 531
订阅者
+224 小时
+37 天
+5830 天
帖子存档
3 530
ፈረሰኛው
ሰባት አክሊል ተጎናፅፎ
አተረፈኝ
ከ ዓለም ዘንዶ እኔን አቅፎ
የተፈጨው
በ ጣኦታት መንኮራኩር
ደረሰልኝ
በቀማኛ ስመዘበር
ገበዝዋ ነው
ለ ኢትዮጵያ ለሀገሬ
በፈረስህ
ጊዮርጊስ ደርሰህ ቁም ከበሬ
23 🔥 ሰማዕቱ አባቴ🙏🏻!
እንደ ተፃፈ...
✍ @Seb_at7
✍ @truthwater
3 530
ሊጤን....
ባልተቤትሽ ገባ ቤቱን አሟሟቅሽው
ቡናውን አቡነሽ ወጡን ወጠወጥሽው
ራትም ተበላ ሳቅ ደስታው ፈሰሰ
እጣን ጭሳጭሱም ከቤቴ ደረሰ
እቃው ተነሳስቶም አልጋው ተሰናዳ
የውል ደንብ ሊደርስ ተገባ ወደ ሜዳ
.... (ጩኸት ይሰማል! )
እኔ ላጤው እኔ ጅሉ
ቀስሬ አለው!..ከደውሉ
'ወጡን ስትወጠውጥ' የጀመረ ጆሮ
አቦል ቶና እስኪሉ አለ ተገትሮ
ጩኸቱ በርትቶም አቀስሬ ሳለ
የታጠፈ አንጀቴ አላስጨርስ አለ፤
(በሉ እንግዲ!)
የረሀብ አለንጋ ሆዴን ከሚልጠው፣
እኔም....
እጄን ተጣጥቤ 'ሊጤን ልለጥልጠው'!
ያቡ✍️ @Weyblann
3 530
....
አልደውልብሽም
«እናቴ ትሙት»ብየ፣
ይሄው ደወልኩኝ ዛሬ
ቀድሜያት ሞቻለው ብየ፣
ውሸታም እንዳትይኝ!...
አልሆንልህ ቢለኝ ትዝታሽ
ከምሞት ገድያታለው፣
«ከልዤ በፊት» እያለች
ስትፀልይ ሰምቻታለው።
𝑏𝑦 𝑔/𝑚𝑒𝑑ℎ𝑖𝑛 𝑎
@gtmnbegtm3 530
....
አልደውልብሽም
«እናቴ ትሙት»ብየ፣
ይሄው ደወልኩኝ ዛሬ
ቀድሜያት ሞቻለው ብየ፣
ውሸታም እንዳትይኝ!... አልሆንልህ ቢለኝ ትዝታሽ ከምሞት ገድያታለው፣ «ከልዤ በፊት» እያለች ስትፀልይ ሰምቻታለው።𝑏𝑦 𝑔/𝑚𝑒𝑑ℎ𝑖𝑛 𝑎
3 530
በዕለተ እሁድ....በሰንበቱ
ላነግስ ሄድኩኝ... ከታቦቱ
ሰግጄ ልነግረው......
ዓለም የሚባለው
ምን እንዳደረገኝ
ገና ደጁ ስደርስ
ሆድ የባሰው ልቤ
በእምባ ቀደመኝ
👼🏻
ስዕሉ ፊት ቆሜ
ብነግረው ችግሬን
መልአኩ ገብርኤል
ባረከው ዘመኔን
👼🏻
እንደ ተፃፈ...
✍ @Seb_at7
✍ @truthwater
3 530
በዕለተ እሁድ....በሰንበቱ
ላነግስ ሄድኩኝ... ከታቦቱ
ሰግጄ ልነግረው......
ዓለም የሚባለው
ምን እንዳደረገኝ
ገና ደጁ ስደርስ
ሆድ የባሰው ልቤ
በእምባ ቀደመኝ
👼🏻
ስዕሉ ፊት ቆሜ
ብነግረው ችግሬን
መልአኩ ገብርኤል
ባረከው ዘመኔን
👼🏻
እንደ ተፃፈ...
✍ @Seb_at7
✍ @truthwater
3 530
የማር ሰፈፍ
ለመለኮት
ሰባት አክናፍ
ደግፎ አቅፎት
ስጋ በላን
ካንቺ መቅደስ
ተቀደደ
የመርገም ጨርቅ ላይታደስ
እመ አምላክ
ስምሽ ግሩም
የጭንቅ ቀን
ሲያጉረመርም
አለቀስኩኝ ከደጃፍሽ
ልቤን ከፍቶት በሰቀቀን
አልረሳውም....🥹
አልፍያለው የጭንቁን ቀን
እመ አምላክ ኪዳነምህረት 16🔥
እንደ ተፃፈ...
✍@Seb_at7
✍@truthwater
3 530
ተከታይ የሌለው አንድ
(ሳሙኤል አለሙ)
መውደድ....
ባርባ...ባርባው፤
ማፍቀር.....
ባርባ...ባርባው፤
ለታዛዡ ልቤ
ዋሽታ ለማትገባው።
መውደድ....
ባርባ...ባርባው፤
ማፍቀር.....
ባርባ...ባርባው፤
ለተገዢው ልቤ
ክዳው ለማትገባው።
ለታዛዡ ልቤ
ዋሽታ ለማትገባው።
ቀርበው ሲጠይቁኝ...
አንዱን ልቤን
እያስለካው፤
አንዴ ልየው ሲሉኝ...
አንዱን ልቤን
እያስጠጋው፤
ስኖር...አንዴ...አንዴ...አንዴ...አንዴ
ላንዴ...ስኖር...ስኖር...ስኖር...ስኖር
ስኖር..አንዴ...አንዴ...አንዴ...አንዴ
በስንቱ አንዴ-ዎች
አንዱን ልቤን፥ ላንዴ ሳስሞክረው፤
አለሁኝ በተስፋ
ገዢ እንደቸገረው።
ሳሙኤል አለሙ
@topazionnn
3 530
መልከ_ሰይጣን
.
.
እንደዉ በሰዉኛ ሰይጣን የምንለው፤
አስቀያሚ ገፁን በግልጥ ያላወቅነው፣
የከሰለ ምስሉን በምናብ ያየነው፤
በፍጹም መላምት አጽልመን የሳልነዉ።
በማይነጥፍ ንቀት ግብሩ ቢጠለሽም፤
ዳሩ ግን እዉነቱ.....ሰይጣን መልክ የለውም።
መልኩ ምን አይነት ይመስላችኋል ?
✍️ዔደን ታደሰ
@Ediwub
@topazionnn
3 530
በዳንኪራዉ ተመስጭ ጮቤ
እርግጭ እንዳልደንስ
ከቅፅበቶች ደርሶ ያጥራል
ስቅታ ነዉ የአለም ድግስ !
(ካሊድ አቅሉ )
@topazionnn
@topazionnn
3 530
" ሰዎች የሚወዱን "ለራሳቸው" ብለው ነው ~
እግዚአብሔር የሚወደን ግን "ለራሳችን" ብሎ ነው"
(elias shitahun)
@topazionnn
@topazionnn
3 530
ፈገግታየዬ ነው የቀረው እሱን አልነጠቁኝም፤
ላንቺ ደግሞ የእለት ሳቅ አልመኝም ፤
መኖር አባ አለቃ ፤
ከስንቄ ቆንጥሮ መጉረሱን ሲያበቃ ፤
ያልወሰደብኝን ፈገግታዬን እንቺ ፤
ለልብሽም ቢሆን መጨከን አንግቺ ፤
እንጂ እድል አትሰጥም ዓለም ፊቱን ላጨፈገገ፤
ቅድሚያ ይሰጣሉ………
የሰማዩም ለአመስጋኝ የምድሩም ፊት ለፈገገ ፤
አደራሽን እቱ …. https://t.me/meron_Mera
#ሜሮን ዮሐንስ #ሜራ
