3 576
المشتركون
+124 ساعات
+37 أيام
+4430 أيام
أرشيف المشاركات
3 576
፨፨፨፨፨
እሞታለሁኝ አይቀራትም
ደርቄ አልቀርም እንደ በጋ፤
ግና ሳላሽት ፈቀቅ የለም
ጓጉተው ሳይወስዱኝ ከማድጋ።
..
ስማር ኖሪያለው ስንት አመታት
ከሞት ተናንቆ ድል ማድረግን፡
እንኳን ለአንዱ ለሺህ አልሳሳም
እያነባሁኝ አልምትም ግን!።
#mikiyas_feyisa
@topazionnn
3 576
ምንድነው ፍላጎትህ/ሽ ? ለነገሩ ምንም ቢሆን Don't worry ....
ግጥም ......
ድርሰት ........
አዝናኝ ወግ......
አጫጭር የፍቅር ታሪክ......
ወይስ ገራሚ ጥቅስ....
የፈለጋችሁበትን አማርጣችሁ ምታገኙበት ድንቅ Channel ጀባ ልበላችሁ.....
በደራሲ @sirius_black1212 የተፃፉ ውብ የ ብዕር አርማዎች እለት በእለት እሚታተምበት ምርጥ Channel
ተቀላቀሉ አትፀፀቱም!
Join us
https://t.me/yebier_arbegna
3 576
ደብረ ታቦር
.
.
ብርሃነ መለኮት ከተገለፀበት፤
መልኩ ተለዉጦ ፀዳል በሆነበት፤
አብም ስለ ልጁ እርሱን ስሙት ብሎ ከመሰከረበት፤
የጌታ አምላክነት የሥላሴ ምስጢር ከተሰበከበት፤
ልብን ከሚመስጥ ከዚህ ድንቅ ስፍራ፤
መንፈስ ከሚያድስ ከታቦር ተራራ፤
በዚህ መኖር ለእኛ .......
እጅጉን መልካም ነዉ ከጌታችን ጋራ።
እንኳን ለደብረታቦር በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ።
........................................................
በዔደን ታደሰ
@ediwub
@topazionnn
@topazionnn
3 576
🗒
.
.
ላይድን ቁስል፤
ጨዉ መነስነስ፤
ከድንጋይ ላይ፤
ዉሃ ማፍሰስ ፤
ለሟች ዘመድ ፤
ዳግም ማልቀስ፤
መኖር ካሉት፤
እንደዚህ ነው፤
ሳቅን ትቶ፤
መንሰቅሰቅ ነው።
🖊ዔደን ታደሰ
@ediwub
@topazionnn
@topazionnn
3 576
መውደዴን ለንፋስ ነግሬው - ይዞብኝ ሄደ
መልክሽን በብራና ስዬው - ተቀደደ
ስስቴን ባሰፍረለት ለባህር
ሳቀብኝ እንደክፉ መምህር
ስላንቺ ሚሰማኝን ለሰማይ ብነግረው
አመቱን በሙሉ - ክረምት አደረገው
በነፍሴ ያመላለስኩት
በአጥንቴ የታመምኩት
ለሳር ለቅጠሉ ብለፍፍ
ተቆጠረ እንደሴተኛ አዳሪ እድፍ!
አየሽ !
ለዚህ ነው የምጎዳው - ለዚ ነው ምትጎጂው
ለማይሰማኝ ነውና የማወራው
ለማይሰማሽ ነውና የምታስረጂው!
እወቁልን አያሻንም ይቅር አንታይ ከጫፍ ጫፍ
ብንታመም ዝም እንበል እንደሚጠረብ ዛፍ
አንዳንድ ልክ አለ
ቢነገረም የማይጠቅም - ቃልን ዝምታ ያሳከለ
አንዳንድ እውነት አለ
አንዳንድ ህመም አለ - ብንለፋ ብንጥር
እያነሰ ሚሄድ ባስረዳነው ቁጥር!
ኤልያስ ሽታኹን
@topazionnn
3 576
+2
የምትመለከቱዋት ወጣት ታዳጊ ኤልሮኢ ቅዱስ ትባላለች በአጥንት ካንሰርን ህክምና ላይ ትገኛለች በሽታው ከታወቀ አንድ አመት ሆኗታል በበሽታው ምክንያትም አንድ እጇ ሙሉ በሙሉ እንዲወገድ ተደርጓል
ሆኖም ግን ኤልሮኢ ተስፋ ሳትቆርጥ ህክምናዋን እየተከታተለች ነው
አሁን ግን በሽታው ወደ ሳንባዋ በመሠራጨቱ የመተንፈስ ችግር ስላጋጠማት በአሁን ሰአት በአዲስ አበባ Heal Venture Medical and Surgical Center በ ICU ትገኛለች ሆኖም ግን በአሁን ሰአት ላይ የሆስፒታሉ ወጪ በቀን ከ50.000ብር ነው ከቤተሰብ አቅም በላይ ስለሆነ የኛን እርዳታ ትሻለች
CBE - 1000487578828
TeleBirr - 0911179293
Awash Bank - 013471629151800
ሁሉም አካውንት ስም - Rahel Aregay
እህታችን ትፈልገናለች እንድረስላት 🙏
3 576
ትንሣኤሽን ልየዉ
ውዳሴሽን አንብቤ ቅዳሴሽን ሰምቼ፣
በዝግ ባዕት በሱባኤ ሰንብቼ።
ትንሳኤሽን ልየዉ ከመቅደሱ ቆሜ፣
ከመሳጭ አንድምታ እዉቀትን ቀስሜ።
ስብሐተ ነግህ ን አድርሼ፣
ድርሳን ስንክሳሩን ከልሼ።
ቅዳሴን ላስቀድስ ከበራፉ ታዛ፣
አለሙን አስትቶ ለነፍስ የሚያስገዛ።
ትንሣኤሽን ልየዉ ከመቅደሱ ቆሜ፣
ከመሳጭ አንድምታ እዉቀትን ቀስሜ።
እንደ ሐዋርያዉ ትንሣኤሽ ይታየኝ፣
ከነጩ ሰበናት በረከቱ ይድረሰኝ።
ዕርገትሽን እንዳይ ፍቀጂ እናቴ፣
በጸሎት በምልጃሽ ይሞላልኝ ቤቴ።
እንኳን አደረሳችሁ🙏
✍ዔደን ታደሰ
@ediwub
@topazionnn
@topazionnn
