ch
Feedback
Tesfa

Tesfa

前往频道在 Telegram

አሁንስ ተስፋዬ ማን ነው? እግዚአብሔር አይደለምን?

显示更多
6 177
订阅者
-124 小时
+127
-2630
帖子存档
Tesfa
6 177
በሕይወትህ ውስጥ ጭንቅና መከራ የሚያጋጥም ቢሆንም፣ ከእነዚህ ሁሉ የሚበልጥ ግን የማይናወጥ ተስፋ አለ። ይህ ተስፋ በሁኔታዎች ወይም በሰዎች ላይ የተመሠረተ ሳይሆን፣ በመልካሙና በታማኙ አምላክ ላይ
በሕይወትህ ውስጥ ጭንቅና መከራ የሚያጋጥም ቢሆንም፣ ከእነዚህ ሁሉ የሚበልጥ ግን የማይናወጥ ተስፋ አለ። ይህ ተስፋ በሁኔታዎች ወይም በሰዎች ላይ የተመሠረተ ሳይሆን፣ በመልካሙና በታማኙ አምላክ ላይ የተመሠረተ ነው። እግዚአብሔር በመከራ ወቅት የምትሸሽበት መሸሸጊያ፣ የምትደገፍበት አለት እና የማይፈርስ ምሽግ ነው። “በእርሱ የሚታመኑትን ያውቃል” የሚለው የእግዚአብሔር ቃል ታላቅ ማጽናኛ ነው። እርሱ የልብህን ህመም፣ የምታልፍበትን ፈተና እና የምትፈራውን ሁሉ ያውቃል። ስለዚህ ዛሬ በማንኛውም ጭንቀት ውስጥ ብትሆን፣ ወደ እርሱ ቅረብ። እርሱ የማይሰበር መሸሸጊያህ፣ የማይናወጥ ተስፋህ እና የማይጥልህ አምላክ ነው። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 177
እግዚአብሔር የምሕረት ምንጭ ነው። እርሱ መሓሪ፣ ይቅር ባይ እና በፍቅር የተሞላ አባት ነው። በቅን ልብ የሚጠሩትን ፈጽሞ አይጥላቸውም፤ በፍቅር ይቀበላቸዋል፣ በምሕረቱም ይቅር ይላቸዋል። የእግዚአብሔ
እግዚአብሔር የምሕረት ምንጭ ነው። እርሱ መሓሪ፣ ይቅር ባይ እና በፍቅር የተሞላ አባት ነው። በቅን ልብ የሚጠሩትን ፈጽሞ አይጥላቸውም፤ በፍቅር ይቀበላቸዋል፣ በምሕረቱም ይቅር ይላቸዋል። የእግዚአብሔር ይቅርታ በኃጢአትህ ብዛት አይለካም፤ በማይለወጥ ቸርነቱና በታላቅ ምህረቱ እንጂ። እግዚአብሔር ወደ እርሱ የሚመለስን ልብ ሁልጊዜ ይቅር ይላል። በንስሐና በቅን ልብ ወደ እርሱ ስትመጣ አይጥልህም፤ ይቀበልሃል፣ ያነጻሃል፣ አዲስ ተስፋም ይሰጥሃል። ወደ እግዚአብሔር ለመቅረብ፤ ምሕረቱን ፈልገህ ወደ እርሱ መሮጥ ያስፈልግሃል። እርሱ የተሰበረን ልብ አይንቅም፤ የሚጠሩትንም በምሕረቱ ይመልሳል።
መዝሙር 86:5 አቤቱ፥ አንተ መሓሪና ይቅር ባይ ነህና፥ ምሕረትህም ለሚጠሩህ ሁሉ ብዙ ነውና።
#tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 177
የእግዚአብሔር ምሕረት በሕይወት የምትቆምበት መሠረት ነው። ዛሬ በህይወት ያለኸው፣ አዲስ ቀን ማየትህ በእርሱ የማያልቅ ርኅራኄ እንጂ በራስህ ብቃት አይደለም። በኢየሱስ ክርስቶስ የተገለጠው የእግዚአብ
የእግዚአብሔር ምሕረት በሕይወት የምትቆምበት መሠረት ነው። ዛሬ በህይወት ያለኸው፣ አዲስ ቀን ማየትህ በእርሱ የማያልቅ ርኅራኄ እንጂ በራስህ ብቃት አይደለም። በኢየሱስ ክርስቶስ የተገለጠው የእግዚአብሔር ፍቅርና ምሕረት አዲስ ሕይወት እና ዘላለማዊ ተስፋ ይሰጥሃል። ሰቆ ኤርምያስ 3:22 ሔት። ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው፤ ርኅራኄው አያልቅምና። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 177
የእግዚአብሔር ቸርነት ለሰው ሁሉ የተዘረጋ ነው። እግዚአብሔር ቸር ነው፤ ምሕረቱም በፍጥረቱ ሁሉ ላይ ነው። ፀሐይን በጻድቃንና በኃጢአተኞች ላይ እንደሚያበራ፣ ዝናቡንም በሁሉ ላይ እንደሚያዘንብ፣ ቸር
የእግዚአብሔር ቸርነት ለሰው ሁሉ የተዘረጋ ነው። እግዚአብሔር ቸር ነው፤ ምሕረቱም በፍጥረቱ ሁሉ ላይ ነው። ፀሐይን በጻድቃንና በኃጢአተኞች ላይ እንደሚያበራ፣ ዝናቡንም በሁሉ ላይ እንደሚያዘንብ፣ ቸርነቱም በየቀኑ በሕይወትህ ይገለጣል። ከሁሉ የሚበልጠው የእግዚአብሔር ቸርነት ደግሞ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጧል። በእርሱ ኃጢአትህን ይቅር አለህ፣ አዲስ ሕይወትንም ሰጠህ፣ ከእርሱ ጋርም ዘላለማዊ ተስፋ ሰጥቶሀል። ዛሬም የእግዚአብሔር ቸርነት ከአንተ አልራቀም። በእርሱ ታመን፣ እርሱ ቸር ነው፤ ምሕረቱም በሥራው ሁሉ ላይ ነው። መዝሙር 145:9 እግዚአብሔር ለሚታገሡት ቸር ነው። ምሕረቱም በሥራው ሁሉ ላይ ነው። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 177
የምስጋና ትልቁ ምክንያት እግዚአብሔር ማን እንደሆነ ማወቅ ላይ ነው። እርሱ ቸር ነውና! እግዚአብሔር ዛሬም ቸር ነው:ነገም ቸር ነው: ለዘላለምም ቸር ነው። ምሕረቱ በውድቀትህ አያበቃም፣ ፍቅሩም በድ
የምስጋና ትልቁ ምክንያት እግዚአብሔር ማን እንደሆነ ማወቅ ላይ ነው። እርሱ ቸር ነውና! እግዚአብሔር ዛሬም ቸር ነው:ነገም ቸር ነው: ለዘላለምም ቸር ነው። ምሕረቱ በውድቀትህ አያበቃም፣ ፍቅሩም በድካምህ ወቅት አይቀንስም። በየቀኑ በጸጋው ይደግፍሀል፣ በታማኝነቱም ይመራሀል። የእግዚአብሔር ቸርነት ከሁኔታዎችህ በላይ ነው። ቸርነቱ አያልቅም፣ ምሕረቱም ለዘላለም ይኖራል። ቸር ነውና፥ ምህረቱም ለዘላለም ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ። መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ 16 : 34 #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 177
የእግዚአብሔር ቸርነት ጊዜያዊ አይደለም፤ በሕይወትህ ዘመን ሁሉ ከአንተ ጋር የሚዘልቅ የማይቋረጥ በረከት ነው። ዳዊት “ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል” ሲል የተናገረው፣ በሁሉም
የእግዚአብሔር ቸርነት ጊዜያዊ አይደለም፤ በሕይወትህ ዘመን ሁሉ ከአንተ ጋር የሚዘልቅ የማይቋረጥ በረከት ነው። ዳዊት “ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል” ሲል የተናገረው፣ በሁሉም ወቅት: በደስታም ሆነ በመከራ እግዚአብሔር ታማኝ ሆኖ እንደሚጠብቀው በመተማመን ነው። የዚህ ተስፋ ፍጻሜም ከእግዚአብሔር ጋር ያለው ዘላለማዊ ኅብረት ነው። “በእግዚአብሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ” የሚለው ቃል፣ የእርሱ ቸርነት እስከ ዘላለም የሚዘልቅ መሆኑን ያስረዳሀል። ይህ ተስፋ እና ይህ ሕይወት የሚገኘው በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው። እርሱን የሕይወትህ ጌታና አዳኝ አድርገህ ስትቀበለው፣ የአሁኑንም ሆነ የዘላለም ሕይወትህን ይለውጣል። ዛሬ ይህን ውሳኔ ብትወስን፣ በእግዚአብሔር ቤት ለዘላለም ትኖራለህ። መዝሙር 23:6 ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል፥ በእግዚአብሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 177
የእግዚአብሔርን ቸርነት መረዳት የምትችለው እርሱን በማወቅ፣ ወደ እርሱ በመቅረብ እና ፍቅሩን በሕይወትህ በመለማመድ ነው። ይሄን የእግዚአብሔርን ቸርነት በሕይወትህ ልትቀምሰው ይገባል። ለዚህም ህይወት
የእግዚአብሔርን ቸርነት መረዳት የምትችለው እርሱን በማወቅ፣ ወደ እርሱ በመቅረብ እና ፍቅሩን በሕይወትህ በመለማመድ ነው። ይሄን የእግዚአብሔርን ቸርነት በሕይወትህ ልትቀምሰው ይገባል። ለዚህም ህይወት ደግሞ እግዚአብሔር እንድትቀርበው፣ በእርሱ ብቻ እንድትታመን እና ቸርነቱን በየቀኑ እንድትለማመድ ይፈልጋል። እግዚአብሔርን የሚታመኑ ሰዎች ቸርነቱን በየቀኑ ያያሉ፣ በድካማቸው ኃይልን፣ በጭንቀታቸው ሰላምን፣ በችግራቸው መፍትሔን ያገኛሉ። አንተም በሁሉም ሁኔታ ታማኝ በሆነው እግዚአብሔር መታመን ዛሬ ጀምር፤ ቸርነቱን በሕይወትህ ትቀምሰዋለህ፣ ከእርሱ ጋር ያለውንም ድንቅ ሕይወት ትለማመዳልህ። መዝሙር 34:8 እግዚአብሔር ቸር እንደ ሆነ ቅመሱ እዩም፤ በእርሱ የሚታመን ሰው ምስጉን ነው። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 177
የእግዚአብሔር ላንተ ያለው ፍቅር ቅድመ ሁኔታ የሌለው፣ ዘላለማዊ እና ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን እስከ መስጠት የደረሰ ፍቅር ነው። ይህን ፍቅር በመልካምነትህ ወይም በሥራህ አላገኘኸውም፤ በእግዚአብሔር
የእግዚአብሔር ላንተ ያለው ፍቅር ቅድመ ሁኔታ የሌለው፣ ዘላለማዊ እና ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን እስከ መስጠት የደረሰ ፍቅር ነው። ይህን ፍቅር በመልካምነትህ ወይም በሥራህ አላገኘኸውም፤ በእግዚአብሔር ጸጋ በነፃ የተሰጠህ ስጦታ ነው። ፍቅር አንተ እርሱን እንደወደድከው አይደለም፤ እርሱ አስቀድሞ እንደወደድህ ነው። አንተ ገና ኃጢአተኛ ሳለህ፣ ክርስቶስ ስለ አንተ ሞቶ የእግዚአብሔርን ፍቅር ገልጦልሀል። እግዚአብሔር አስቀድሞ ወዶሃል። ፍቅሩ አይለወጥም፣ አያልቅም፣ ዘላለማዊ ነው። ይህን ያለ ምክንያት የተሰጠህን ፍቅር ስትረዳ፤ ሰዎችንም በዚያው ፍቅር መውደድ ትችላለህ። ዛሬ ለዚህ ድንቅ ፍቅር ምላሽ ትሰጣለህ? እርሱ አስቀድሞ ወዶናልና እኛ እንወደዋለን። 1ኛ የዮሐንስ መልእክት 4:19 #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 177
የሰው ልጅ እውቀት እና ግንዛቤው ውስን በመሆኑን በራስህ መደገፍ የለብህም:: ለዚህም ነው እግዚአብሔርን መታመን እርሱ ፍጹም በሆነ እቅድ እንደሚመራህ በማወቅ እርግጠኛ መሆን የምትችለው። በዚህ አድካ
የሰው ልጅ እውቀት እና ግንዛቤው ውስን በመሆኑን በራስህ መደገፍ የለብህም:: ለዚህም ነው እግዚአብሔርን መታመን እርሱ ፍጹም በሆነ እቅድ እንደሚመራህ በማወቅ እርግጠኛ መሆን የምትችለው። በዚህ አድካሚ የህይወት ጉዞ ዝለሃል? እንግድያውስ ለዚህ ሁሉ መፍትሄ የሚሆነውን ልንገርህ፤ የራስህን ውስን የሆነ ማስተዋል መተው!በእግዚአብሔር መታመን፤ ጥቂት በሆነው በገዛ ማስተዋል መባዘኑን ትተህ፤ ፍጹም በሆነው በእግዚአብሔር ማስተዋል ላይ ተደገፍ። እርሱ ያሳርፍሀል:: በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤” — ምሳሌ 3፥5 #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 177
እግዚአብሔር እርሱ መሐሪ፣ ሞገስ ያለው፣ ታጋሽ፣ በቸርነትና በእውነት የተሞላ አምላክ ነው። ዛሬ በድክመት ምክንያት እግዚአብሔር ርቀህ ይሆን? እርሱ ለንስሐ የሚጠራ፣ የሚቀበል፣ የሚምር እና በፍቅሩ
እግዚአብሔር እርሱ መሐሪ፣ ሞገስ ያለው፣ ታጋሽ፣ በቸርነትና በእውነት የተሞላ አምላክ ነው። ዛሬ በድክመት ምክንያት እግዚአብሔር ርቀህ ይሆን? እርሱ ለንስሐ የሚጠራ፣ የሚቀበል፣ የሚምር እና በፍቅሩ የሚያቆም አባት ነው። የእግዚአብሔር ቸርነት ከውድቀትህ ይበልጣል፣ ምሕረቱም ከኃጢአትህ ይበልጣል። ወደ እርሱ ስትቀርብ በምህረት ይቀበልሃል። ዘጸአት 34:6 እግዚአብሔርም በፊቱ አልፎ፡— “እግዚአብሔር፥ እግዚአብሔር መሐሪ፥ ሞገስ ያለው፥ ታጋሽም፥ ባለ ብዙ ቸርነትና እውነት፥ #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 177
የእግዚአብሔር ባሕርይ ፈጽሞ አይለወጥም። እርሱ ሁልጊዜ ቸር፣ ምሕረቱ የማያልቅ፣ በቃሉም የታመነ አምላክ ነው። ሰዎች ሊለወጡ ይችላሉ፤ ሁኔታዎችም ሊቀየሩ ይችላሉ፤ እግዚአብሔር ግን በቸርነቱና በታማኝ
የእግዚአብሔር ባሕርይ ፈጽሞ አይለወጥም። እርሱ ሁልጊዜ ቸር፣ ምሕረቱ የማያልቅ፣ በቃሉም የታመነ አምላክ ነው። ሰዎች ሊለወጡ ይችላሉ፤ ሁኔታዎችም ሊቀየሩ ይችላሉ፤ እግዚአብሔር ግን በቸርነቱና በታማኝነቱ ፈጽሞ አይለወጥም። ምሕረቱ ለዘላለም ይኖራል። እውነቱና ታማኝነቱም ከትውልድ እስከ ትውልድ ይቀጥላል። ከጥንት ጀምሮ ታማኝ የነበረው አምላክ ዛሬም በአንተ በሕይወትህ ታማኝ ነው። እግዚአብሔር ቸር፥ ምሕረቱም ለዘላለም፥ እውነቱም ለልጅ ልጅ ነውና። - መዝሙረ ዳዊት 100:5 #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 177
የእግዚአብሔር ጸጋ ያለፈውን ሕይወትህን ይቅር ብሎ ብቻ አይተውህም፤ አዲስ ማንነትንም ይሰጥሃል። በክርስቶስ ኢየሱስ ከእርሱ ጋር አስነስቶ፣ በሰማያዊ ስፍራም ከእርሱ ጋር ያስቅምጥሀል። ይህ የሚሆነው
የእግዚአብሔር ጸጋ ያለፈውን ሕይወትህን ይቅር ብሎ ብቻ አይተውህም፤ አዲስ ማንነትንም ይሰጥሃል። በክርስቶስ ኢየሱስ ከእርሱ ጋር አስነስቶ፣ በሰማያዊ ስፍራም ከእርሱ ጋር ያስቅምጥሀል። ይህ የሚሆነው በአንተ በጎ ሥራ ወይም ብቃት ሳይሆን፣ በእርሱ ታላቅ ጸጋና ቸርነት ነው። እግዚአብሔር ይህን ያደረገው በሚመጡ ዘመናት የጸጋውን ከሁሉ የመብለጥ ባለጠግነት እንዲያሳይ ነው። የእርሱ ጸጋ የማያልቅ ነው፤ ቸርነቱም በየዕለቱ በሕይወትህ ይገለጣል። ስለዚህ ያለፈው ውድቀትህ የአንተን ማንነት አይወስንም፤ በክርስቶስ ኢየሱስ የምታገኘው አዲስ ማንነት ነው እንጂ። ዛሬም በእርሱ ታመን፤ እርሱ በሕይወትህ የጀመረውን መልካም ሥራ እስከ ፍጻሜ ያደርሳል። ኤፌሶን 2:6-7 በሚመጡ ዘመናትም በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለ ጠግነት ያሳይ ዘንድ፥ ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 177
በእግዚአብሔር ለሚታመኑት የተዘጋጀው ቸርነት የተትረፈረፈ ነው። የጌታ ቸርነት በድንገት የሚያልቅ እና አንድ ቀን የሚቋረጥ አይደለም፤ በእርሱ ለሚታመኑት ሁሉ የማያልቅ ምንጭ ነው። እርሱ መልካም አምላ
በእግዚአብሔር ለሚታመኑት የተዘጋጀው ቸርነት የተትረፈረፈ ነው። የጌታ ቸርነት በድንገት የሚያልቅ እና አንድ ቀን የሚቋረጥ አይደለም፤ በእርሱ ለሚታመኑት ሁሉ የማያልቅ ምንጭ ነው። እርሱ መልካም አምላክ ነው፤ በመከራ ቀንም መጠጊያ፣ በድካም ጊዜ ኃይል፣ በጭንቀት ውስጥ የማይተወ መፅናኛ አባት ነው። ምናልባት ዛሬ በሕይወትህ ውስጥ ጥያቄዎች ይኖሩ ይሆናል፤ አንዳንድ ጸሎቶችህም መልስ የዘገዩ ሊመስሉህ ይችላሉ: ነገር ግን እግዚአብሔር ለሚወዱት እና በእርሱ ለሚታመኑት ያዘጋጀው ቸርነት ሁልጊዜ በትክክለኛው ጊዜ ይገለጣል። በአንተ ለሚያምኑ በሰው ልጆች ፊት ያዘጋጀሃት ለሚፈሩህም የሰወርሃት፥ ቸርነትህ እንደ ምን በዛች! መዝሙረ ዳዊት 31:19 #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 177
መልካም ስጦታና ፍጹም በረከት ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው። ከእርሱ የሆነ ስጦታዎች ቁሳዊ በረከቶችን ብቻ አይደለም። እርሱ የመልካም ነገር ሁሉ ምንጭ ነው። እግዚአብሔር የሚለዋወጥ አምላክ አይደለም። ሁ
መልካም ስጦታና ፍጹም በረከት ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው። ከእርሱ የሆነ ስጦታዎች ቁሳዊ በረከቶችን ብቻ አይደለም። እርሱ የመልካም ነገር ሁሉ ምንጭ ነው። እግዚአብሔር የሚለዋወጥ አምላክ አይደለም። ሁኔታዎች ቢቀየሩ፣ ሰዎች ቢለዋወጡ፣ ዘመናት ቢያልፉም የእርሱ ቸርነት፣ ታማኝነት እና ፍቅር አይለወጡም። ትናንት የረዳህ አምላክ ዛሬም ይረዳሃል፤ ነገም አይተውህም። ስለዚህ ዛሬ በሕይወትህ ላለው መልካም ሁሉ እግዚአብሔርን አመስግን፤ ገና እንዲሆን ተስፋ ለምታደርገውም በእምነት እርሱን ብቻ ጠብቅ። ያዕቆብ 1:17 በጎ ስጦታ ሁሉ ፍጹምም በረከት ሁሉ ከላይ ናቸው፥ መለወጥም በእርሱ ዘንድ ከሌለ በመዞርም የተደረገ ጥላ በእርሱ ዘንድ ከሌለ ከብርሃናት አባት ይወርዳሉ። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 177
ድነት የሚገኘው በሰው ጥረት ወይም በመልካም ሥራ ሳይሆን፣ በእግዚአብሔር ጸጋ ብቻ ነው። የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱም በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ተገልጧል። እርሱ ኃጢአትህን ይቅር ብሎ፣ በመ
ድነት የሚገኘው በሰው ጥረት ወይም በመልካም ሥራ ሳይሆን፣ በእግዚአብሔር ጸጋ ብቻ ነው። የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱም በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ተገልጧል። እርሱ ኃጢአትህን ይቅር ብሎ፣ በመንፈስ ቅዱስ አዲስ ሕይወት ሰጥቶሃል። ስለዚህ ያለፈው ውድቀትህ የወደፊት ተስፋህን አይወስንም፤ የእግዚአብሔር ጸጋ ከውድቀትህ ይበልጣል፣ ፍቅሩም ከኃጢአትህ ይበልጣል። ስለዚህ ዛሬ ክርስቶስ በሰራልህ ስራ ብቻ እመን። ያዳነህ ጌታ ዛሬም ህይወትህን ሙሉ ያድሰዋል። ቲቶ 3:4-5 ነገር ግን የመድኃኒታችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱ በተገለጠ ጊዜ፥ እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም፤ #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 177
አብርሃም ልጁን ይስሐቅን ለመሠዋት በታዘዘ ጊዜ አንድ ልጁን ለእግዚአብሔር ለመሰዋት እላቅማምም ነበር። በእግዚአብሔርም ታምኖ ታዘዘ። እግዚአብሔር ግን በምትኩ የሚሠዋን በግ አዘጋጀለት። አብርሃምም በ
አብርሃም ልጁን ይስሐቅን ለመሠዋት በታዘዘ ጊዜ አንድ ልጁን ለእግዚአብሔር ለመሰዋት እላቅማምም ነበር። በእግዚአብሔርም ታምኖ ታዘዘ። እግዚአብሔር ግን በምትኩ የሚሠዋን በግ አዘጋጀለት። አብርሃምም በልጁም ፋንታ መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር ሠዋው። ከዚያም አብርሃም ያንን ቦታ “ያህዌ ይርኤ” ብሎ ጠራው፤ የእግዚአብሔርንም አቅርቦት መሰከር። ያህዌ ይርኤ ዛሬም ሕያው የእግዚአብሔር ቃል ነው። ስለዚህ ዛሬ በጭንቀት ፈንታ በእግዚአብሔር ታመን። እስካሁን የረዳህ አምላክ ዛሬም ያይሀል፣ ነገም አይተውህም። ያህዌ ይርኤ በእውነት በእግዚአብሔር ተራራ ይታያል። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 177
እስራኤላውያን በምድረ በዳ ሲጓዙ በነበረበት ወቅት ውኃ የለም፣ ምግብ የለም፣ ተስፋ የሚያደርጉት ምንም ነገር አልነበረም። ነገር ግን እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር ነበረ፤ መንገዳቸውን ያውቅ ነበር፣ የእ
እስራኤላውያን በምድረ በዳ ሲጓዙ በነበረበት ወቅት ውኃ የለም፣ ምግብ የለም፣ ተስፋ የሚያደርጉት ምንም ነገር አልነበረም። ነገር ግን እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር ነበረ፤ መንገዳቸውን ያውቅ ነበር፣ የእጃቸውንም ሥራ ባረከ፣ የሚያስፈልጋቸውንም ሁሉ አቀረበላቸው። አንዳችም አላሳጣቸውም። ዛሬም ይህ ቃል ላንተም ተስፋ ነው። ምናልባት አንተም አሁን ምድረ በዳ የሚመስልህ ዘመን ውስጥ ትሆናለህ፤ነገር ግን መንገድህን የሚያውቅ አምላክ አለ። አንተ ያለህበትን ሁኔታ ያያል፣ የሚያስፈልግህንም ሁሉ በጊዜው ያቀርብልሃል፤ አንዳችም አያሳጣህም! #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 177
ቁራዎች አይዘሩም፣ አያጭዱም፣ ጎተራም የላቸውም፤ ነገር ግን እግዚአብሔር በየቀኑ የሚያስፈልጋቸውን ሁሉ ያቀርብላቸዋል። እግዚአብሔር ፍጥረቱን ሁሉ የሚመግብ አምላክ ነው። አንተ ደግሞ በእግዚአብሔር ፊ
ቁራዎች አይዘሩም፣ አያጭዱም፣ ጎተራም የላቸውም፤ ነገር ግን እግዚአብሔር በየቀኑ የሚያስፈልጋቸውን ሁሉ ያቀርብላቸዋል። እግዚአብሔር ፍጥረቱን ሁሉ የሚመግብ አምላክ ነው። አንተ ደግሞ በእግዚአብሔር ፊት ውድ ልጁ ነህ። ወፎችን የሚመግብ አምላክ፣ በአምሳሉ የፈጠረህን አንተን ደግሞ እጅግ ይንከባከብሀል! አንተ መሥራት እና መትጋት እና አለብህ ፤ ነገር ግን የሕይወትህ እውነተኛ መጋቢ እና አቅራቢ እግዚአብሔር መሆኑን ግን በሙሉ ልብህ እመነው። የምትሰራው ስራ እና የምታገኘው ገቢዋስትና አይሆንህም፤ ዋስትናና የማይነጥፍ ምንጭ እግዚአብሔር ብቻ ነው። እግዚአብሔር ብቻ የሕይወትህ አቅራቢ ነው። ምናልባት ዛሬ ምን እበላለሁ?፣ ምን እሰራለሁ?፣ ቤተሰቤን እንዴት እመራለሁ? የሚሉ ሀሳቦች አስጨንቀውህ ሊሆን ይችላል። እግዚአብሔር ግን ከጭንቀት ይልቅ አይኖችህን ወደ እርሱ እንድታነሳ ይነግርሀል። እስከዛሬ ያኖረህ አምላክ፣ ለነገም ያዘጋጅልሀል፤ ርሀብን ያጠግባል፣ የጎደለንን ይሞላል፣ የሚያስፈልግህንንም ሁሉ ያቀርብልሀል። ዛሬ በእግዚአብሔር መጋቢነት እና አቅርቦት ታመን። እርሱ እንዴት እንደሚያኖር የሚያውቅ ታማኝ አባት ነው። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 177
በቅንነት መመላለስ፣ እግዚአብሔርን በሙሉ ልብ መውደድ፣ በቃሉ መመላለስ እና ፈቃዱን ለመፈጸም መኖር ማለት ነው። እንዲህ ያለ ሕይወት በእግዚአብሔር ሞገስና በረከት ውስጥ ያኖራል። በዚህ ዘመን ብልጠት
በቅንነት መመላለስ፣ እግዚአብሔርን በሙሉ ልብ መውደድ፣ በቃሉ መመላለስ እና ፈቃዱን ለመፈጸም መኖር ማለት ነው። እንዲህ ያለ ሕይወት በእግዚአብሔር ሞገስና በረከት ውስጥ ያኖራል። በዚህ ዘመን ብልጠትና ማታለል ስኬት የሚያመጡ የሚመስሉ ቢሆንም፣ እግዚአብሔር ግን የቅን ሰውን መንገድ ይባርካል። የእርሱ በረከት የሚያመጣው እውነተኛ እርካታ ነው። ዛሬ በእግዚአብሔር ላይ ታመን፤ በቅንነትም ተመላለስ። እርሱ ሞገሱን ይሰጥሃል፣ በረከቱንም ያበዛልሃል፤ ከመልካም ነገርም አያሳጣህም። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 177
የእግዚአብሔር ጸጋ ሁሉን የሚያበዛ፤ የሚባርክ ነው። ስለዚህ የህይወትህ መባረክ ምንጩ የራስህ አቅም ወይም ሀብት ሳይሆን የእግዚአብሔር የተትረፈረፈ በረከት ነው። እግዚአብሔር የሚሰጠው ጸጋ አንተ የሚ
የእግዚአብሔር ጸጋ ሁሉን የሚያበዛ፤ የሚባርክ ነው። ስለዚህ የህይወትህ መባረክ ምንጩ የራስህ አቅም ወይም ሀብት ሳይሆን የእግዚአብሔር የተትረፈረፈ በረከት ነው። እግዚአብሔር የሚሰጠው ጸጋ አንተ የሚያስፈልግህን ብቻ ሳይሆን፣ ሌሎችንም ለመባረክ ምክንያት አድርጎህም ጭምር ነው። እርሱ በሕይወትህ ውስጥ ሲሠራ ማጣትህን በመሙላት በማትረፍረፍ እና፤ ለበጎ ሥራ ሁሉ እንድንበዛ በማድረግ ነው። ዛሬ አቅም፣ ገንዘብ፣ ኃይል አጥተሀል? ወደ እግዚአብሔር ቅረብ: እርሱ የጎደለውን የሚሞላ፣ ለተጠራህበት ሥራ የሚያበቃህ አምላክ ነው። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads