Tesfa
الذهاب إلى القناة على Telegram
6 223
المشتركون
-324 ساعات
-47 أيام
-6730 أيام
أرشيف المشاركات
6 223
ከሰው ድካም የእግዚአብሔር ምሕረት እጅግ ያይላል።
አንዳንድ ጊዜ በድካምህ ምክንያት ወድቀህ ልትቀር፣ በኃጢአትም እንደተሸነፍክ እና እጅ እንደሰጠህ ሊሰማህ ይችላል ነገር ግን የእግዚአብሔር ጸጋ ከድካምህ ይበልጣል።
ነገር ግን ኃጢአት ሊያሸንፍህ ቢሞክርም፣ ወደ እግዚአብሔር በንስሐ ብትመጣ እርሱ ይቅር ይልሀል፣ ያነጻሀል፣ እንደገናም በምህረት ያቆምሀል።
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
6 223
እግዚአብሔር የልብን ጸሎት የሚሰማ የቅርብ አምላክ ነው። በምንም አይነት ሁኔታ ብትሆን እንኳን በቅን ልብ ወደ እርሱ ብትጮህ ይሰማሃል።
ዛሬ ያለብህን ሸክም፣ ጭንቀት እና ሀዘን ሁሉ ለእግዚአብሔር ንገረው: እርሱ ጩኸትን የሚሰማ፣ ጸሎትንም የሚመልስ ታማኝ አምላክ ነው።
አቤቱ፥ ጽድቄን ስማ ጩኸቴንም አድምጥ፤ በተንኰለኛም ከንፈር ያልሆነውን ጸሎቴን አድምጥ። - መዝሙረ ዳዊት 17:1
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
6 223
እግዚአብሔር የተስፋ አምላክ ነው። ሁኔታዎች ተስፋ ቢያስቆርጡህ እንኳን፣ እግዚአብሔር ፈጽሞ ተስፋ አያስጥልህም። አቅምህ የተሟጠጠ እና የደከምክ በሚመስልህ ጊዜ ሁሉ ዓይኖችህን ወደ ተስፋህ አምላክ ወደ እግዚአብሔር አንሳ።
በድካምህ ኃይልን፣ ባስጨነቀህ ነገር ፈንታ ሰላምን ይሰጥሃል። በእርሱ ለሚታመኑ ሰዎች ደግሞ ከዚህ ዓለም ያልሆነ እና የማያልቅ ተስፋ አለ፤ ይህም በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ከቀን ወደ ቀን የሚበዛ ተስፋ ነው።
እግዚአብሔር በደስታና በሰላም የሚሞላ አምላክ ነው።
ይህ ደስታና ሰላምበ ሁኔታዎች የሚመጣ ሳይሆን ከእግዚአብሔር የሚመነጭ አዕምሮን ሁሉ የሚያልፍ ነው።
ስለዚህ ዓይኖችህን ከጊዜያዊ ደስታና እርካታ ምንጮች ላይ አንሳ። ሁሉን ቻዩ አምላክ የዘላለም ተስፋህና ደስታህ እንደሆነ እመን። በእርሱ ስትታመን ሰላሙና ደስታው በሕይወትህ ይበዛል፤ ተስፋህም ፈጽሞ አይጠፋም።
ሮሜ 15:13 የተስፋ አምላክም በመንፈስ ቅዱስ ኃይል በተስፋ እንድትበዙ በማመናችሁ ደስታንና ሰላምን ሁሉ ይሙላባችሁ።
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
6 223
የክርስቶስ ሰላም ችግር፣ ጭንቀት፣ ፍርሃት ወይም ግራ መጋባት ሲግጥምህ የሚመራህ እና የሚያሳርፍህ ነው።
ዛሬ ልብህን የሚገዛው ፍርሃት ነው ወይስ የክርስቶስ ሰላም?
እግዚአብሔር ወደ ሰላም፣ ወደ አንድነት እና ወደ ምስጋና ህይወት ጠርቶሀል። ሁኔታዎችህ ምንም ቢሆኑ፣ የክርስቶስ ሰላም ሁሉን አልፎ ልብህን በሰላሙ ይገዛዋል።
ቆላስይስ 3:15 በአንድ አካልም የተጠራችሁለት ደግሞ የክርስቶስ ሰላም በልባችሁ ይግዛ። የምታመሰግኑም ሁኑ።
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
6 223
አንዳንድ ጊዜ ሕዝብ በችግር፣ በጦርነት፣ በማጣት ውስጥ ሊያልፍ ይችላል። በእንደዚህ ያለ ጊዜ ለምድር የሚያስፈልገው ደግሞ እውነተኛ መፍትሔ እና ተስፋ የእግዚአብሔር ጉብኝት ብቻ ነው።
ዛሬ ለምድራችንም ይሄ ነው ሚያስፈልጋት። እግዚአብሔር ሕዝባችንን እንዲያድስ፣ የተሰበሩ ልቦችን እንዲፈውስ፣ ሰላምን እዲሰጠን እና ሕዝቡ እንደገና በእርሱ ደስ እንዲለው በፊቱ መሆን ነው። እግዚአብሔር ሕዝቡን ሲጎበኝ፣ ይሄ ይሆናል! ተስፋ ይታደሳል፤ የተሰበሩ ልቦች ይፈወሳሉ፤ ሰላምም ይሆንልናል።
መዝሙር 85:6 አቤቱ፥ ትመለሳለህ ታድነንማለህ፤ ሕዝቡም በአንተ ደስ ይላቸዋል።
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
6 223
በእግዚአብሔር ፊት ትክክል የሆነ ሕይወት መኖር፣ ፍትሕን መውደድ፣ እውነትን መከተል እና እግዚአብሔርን መፍራት ከፍ ያደርጋል።
ሕዝብ ጽድቅን ሲከተል ሰላም፣ ፍትሕ፣ አንድነት እና በረከት ለምድር ይሆናል። ነገር ግን ኃጢአት፣ ጥላቻ፣ ዓመፅ እና ኢፍትሐዊነት ሲበዙ ግን ሕዝብን ወደ ጥፋት ይመራል።
ለምድራችን ሰላም፣ ፈውስ እና መታደስ የምንፈልግ ከሆነ፣ እንደ ሕዝብ ወደ ጽድቅ ህይወት መመለስ አለብን።
ምሳሌ 14:34 ጽድቅ ሕዝብን ከፍ ከፍ ታደርጋለች፤ ኃጢአት ግን ሕዝብን ታስነውራለች።
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
6 223
ሀገር የምትባረከው ባላት የጠፈጥሮ ሀብት ብዛት ወይም በኃይሏ ሳይሆን፣ እግዚአብሔርን በማወቅና በእርሱ በመታመን ነው።
ሕዝብ እውነተኛ መባረክን የሚያገኘው ከእግዚአብሔር ጋር በመጣበቅ እንጂ በምድራዊ ኃይል ወይም በሀብት አይደልም።
እግዚአብሔርን የሚፈልግ፣ ቃሉን የሚታዘዝ፣ በእርሱ የሚታመን እና ለእርሱ ክብር የሚኖር ሕዝብ ለምድር በረከት ነው። እንዲህ ያለ ሕዝብ የእግዚአብሔርን መሪነት፣ ጥበቃ እና በረከት ያገኛል።
ስለዚህ እንደ ሕዝብ ወደ እግዚአብሔር መመለስ ይኖርብናል። ሕዝብ እግዚአብሔርን ሲፈልግ፣ ስለ ሀገሩ ሲጸልይ እና በእግዚአብሔር መንገድ ሲመላለስ፣ የእግዚአብሔር በረከት በምድሪቱ ላይ ይሆኖልና።
መዝሙር 33:12 እግዚአብሔር አምላኩ የሚሆንለት ሕዝብ ምስጉን ነው፥ እርሱ ለርስቱ የመረጠው ሕዝብ።
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
6 223
መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ነገሥታትና ስለ ባለሥልጣናት ሁሉ እንድንጸልይ ያስተምረናል። መሪዎች በጥበብ እንዲመሩ፣ በፍትሕ እንዲወስኑ እና ለሕዝብ በቅንነት እንዲያገለግሉ እንድንጸልይ ይመክረናል።
ደግሞም እንደ ክርስቲያን ለራሳችን ብቻ ሳይሆን ለሀገራችን፣ ለሕዝባችን እና ለመሪዎቻችንም ጭምር እንድንጸልይ ተጠርተናል።
የሀገር ሰላም በብዙ መንገዶች ይገነባል፣ በዚህ ውስጥ የእኛ ድርሻ ደግሞ ለሀገር እና ለመሪዎቹ በታማኝነት መጸለይ ነው።
ዛሬ ለሀገራችን እንጸልይ፤ ለመሪዎች፣ ለሕዝብ፣
ፊቱ በመቅረብ ሰላምና ፈውስ እንለምን።
1 ጢሞቴዎስ 2:1-2 እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ።
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
6 223
እግዚአብሔር ለእኛ ለሕዝቡ የሰጠን ትእዛዝ የምንኖርባትን ምድር ሰላም እንድንፈልግ እና ስለ ምድራችንም እንድንጸልይ ነው። ለሀገራችን፣ ለሕዝባችን እና ለመሪዎቻችን መጸለይ አለብን።
መሪዎች በጥበብ እንዲመሩ፣ ፍትሕ እንዲሰፍን፣ ሕዝብም በአንድነት እንዲኖር መጸለይ። ለሀገራችን የሚያስፈልጋት የእግዚአብሔር ሰላም ነውና።
ኤርምያስ 29:7 በእርስዋ ሰላም ሰላም ይሆንላችኋልና ወደ እርስዋ ላስማርክኋችሁ ከተማ ሰላምን ፈልጉ፥ ስለ እርስዋም ወደ እግዚአብሔር ጸልዩ።
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
6 223
ሀገር ሰላምን፣ ሕዝብም ፈውስን ይሻል።
ይህ የሚሆነው ደግሞ በጸሎት፣ በትሕትና እና ወደ እግዚአብሔር በመመለስ ነው።
በዚህ ዘመን ሀገራችን ሰላምን፣ ፈውስን እና የእግዚአብሔርን ምሕረት እጅግ ትሻለች። እንደ ሀገር ለምናቅደው ነገሮች ሁሉ፣ ተስፋችን እግዚአብሔር ብቻ ነው።
ወደ እግዚአብሔር በጸሎት ብንጮህ፣ እርሱ ይሰማናል። የተሰበረ ልባችንንም ይፈውሳል፣ ለሀገራችንም ሰላሙን ያመጣልናል።
2 ዜና 7:14 በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢልፈጉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
6 223
እግዚአብሔር የልጆቹን ጩኸት ይሰማል። አንዳንድ ጊዜ በችግር፣ በሀዘን ወይም በጭንቀት ውስጥ ልታልፍ ትችላለህ፤ ነገር ግን እግዚአብሔር ጸሎትህን ይሰማል፣ የምታልፍበትንም ያውቃል፤ ደርሶም በጊዜው ይረዳሀል።
እግዚአብሔር ቅርብ ነው፣ የሚሰማ እና የሚያድንም አምላክ ነው።
ዛሬ በጭንቀት ውስጥ ከሆንክ ተስፋ አትቁረጥ። እግዚአብሔር ጩኸትህን ይሰማል፤ በጊዜውም ይደርስልሀል።
“ጻድቃን ጮኹ፥ እግዚአብሔርም ሰማቸው ከመከራቸውም ሁሉ አዳናቸው።”— መዝሙር 34፥17
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
6 223
እውነተኛ እረፍትና እፎይታ የሚገኘው በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው።
በሀጢያት ወይም በመንፈሳዊ ሕይወትህ ደክመሀል? ኢየሱስ ወደ እኔ ና፤ እረፍት እሰጥሃለሁ ብሎ ይጠራሀል።
እርሱ የሚሰጠው እረፍት: ከሀጢዓተኝነት እና ከበድለኝነት ነፃ የሚያወጣ እረፍት፣ ከጭንቀትና ከፍርሃት ነፃ የሚያወጣ እረፍት፣ በልብ ውስጥ የተረጋጋ ሰላምና እፎይታ የሚሰጥ እረፍት፣ የዘላለም ሕይወት የሚገኝበት እውነተኛ እረፍት ነው።
ዛሬ ወደዚህ እረፍት ተጠርተሀል!
ማቴዎስ 11:28 እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
6 223
እግዚአብሔር በማንኛውም የሕይወት ሁኔታ ውስጥ ለልጆቹ ቅርብ ነው። ከአደጋ ምትሸበት እና የምትጠለልበት መጠጊያ ቦታ ነው። እግዚአብሔር በድካምህ ጊዜ የሚያበረታህ ኃይልህ ነው። አንዳንድ ጊዜ በሕይወትህ የምታልፍበት ነገር ከአቅምህ በላይ ሊሆን ይችላል፤ ነገር ግን እግዚአብሔር በዚያ ጊዜ ውስጥ እንኳ የሚያጸናህ እና እንድትቀጥል የሚያደርግ ኃይል ይሰጥሀል። እግዚአብሔር አምላክ በችግርህ ጊዜ ከአንተ ጋር ያለ፣ የሚረዳ፣ የሚያጽናና እና ተስፋ የሚሰጥ አባት ነው።
ዛሬ በሕይወትህ ውስጥ ድካም፣ ፍርሃት ወይም ጭንቀት ካለ፣ ብቻህን አይደለህም። እግዚአብሔር መጠጊያህ፣ ኃይልህ እና ረዳትህ ነው። ወደ እርሱ በጸሎት ብትቀርብ ሰላሙን ይሰጥሃል፣ ልብህንም ያበረታል።
መዝሙር 46:1 አምላካችን መጠጊያችንና ኃይላችን፥ ባገኘን በታላቅ መከራም ረዳታችን ነው።
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
6 223
በዚህ ቃል መሰረት ፈተና ወይም ፍርሃት ቢኖር እግዚአብሔር ከአንተ ጋር መሆኑን ይነግርሀል። ብቻህን አይደለህም፤ እርሱ ይመራህል፣ ያጽናናሀል፣ ኃይልም ይሰጥሀል።
በምታልፍበት ሁኔታ ሳይሆን በእግዚአብሔር ህልውና ታመን። እርሱ በምትሄድበት ሁሉ ከአንተ ይሆናል። ፍርሃትህን አስወግደህ፤ በእግዚአብሔር ብቻ ታምነህ ምትኖርበትን ህይወት ዛሬ ወስን!
"በምትሄድበት ሁሉ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነውና ጽና፥ አይዞህ አትፍራ፥ አትደንግጥ ብዬ አላዘዝሁህምን?” ኢያሱ 1፥9
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
6 223
እግዚአብሔር በሰው ህይወት ውስጥ የሚፈቅደውን ሁሉ ነገር ለበጎ ይለውጠዋል። ዛሬ የምታልፍበትን ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ይቀይረዋል።
አንዳንድ ጊዜ የምታልፍበት ነገር ለምን እንደሚሆን ላይገባህ ይችላል፤ ህመም፣ መዘግየት፣ ችግር ወይም ውድቀት ቢኖርም በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን እግዚአብሔር እየሠራ ነው።
እርሱ ከባድ ነገሮችን እንኳ ለመልካም ያደርጋቸዋል።
ዛሬ ያልገባህ ሁኔታ ቢኖርም ተስፋ አትቁረጥ። እግዚአብሔር ከህይወትህ አንድም ክፍል አይለይም። እርሱ እያንዳንዱን ነገር ለመልካም ፍጻሜ እያዘጋጀህ ነው።
ሮሜ 8:28 እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን።
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
6 223
በጣም ከባድ ጊዜያቶችን በምታሳልፍበት ጊዜ እንኳን እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው። ዳዊት ብዙ ጦርነት፣ ፍርሃት እና አደጋ አጋጥሞት ነበር፤ ነገር ግን በእግዚአብሔር አብሮነት ላይ ሙሉ በሙሉ ይተማመን ነበር። ምክንያቱም እግዚአብሔር እንዲህ ባለ ጊዜ እንኳ እንደማይተወው ስለሚያውቅ ነው።
ዛሬ ምንም አይነት ጭንቀት ቢገጥምህ፣ ብቻህን አይደለህም! እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው፣ እርሱም ሰላምን ይሰጥሃል።
መዝሙር 23:4 በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ፡ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኵዝህ እነርሱ ያጸናኑኛል።
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
6 223
የእስራኤል ሕዝብ በመከራና በስደት ውስጥ ባሉበት ጊዜ እግዚአብሔር ግን ለእነርሱ ያለውን ፍቅር እና መልካም ዕቅድ ነግሯቸዋል።
እነርሱ ተስፋ ቢቆርጡም እግዚአብሔር ግን እኔ ስለእናንተ መልካም አሳብ አለኝ ብሎ ተስፋን እንደሰጣቸው፤ ይህ ቃል ዛሬም ለአንተ ህይወት ይሰራል፡፡ ለህይወትህም ትልቅ መጽናናት ነው።
አንዳንድ ጊዜ ሕይወት ግራ ሊያጋባህ ይችላል፤ ፈተና፣ መዘግየት ወይም ያልተጠበቀ ነገር ሲመጣ እግዚአብሔር እንደረሳህ እና እንደተወህ ሊሰማን ይችላል።
ነገር ግን እግዚአብሔር ስለ አንተ ያለው አሳብ የሰላም፣ የተስፋ እና የመልካም ፍጻሜ ነው።
እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው የመጨረሻው ታሪክህም በእርሱ በእጁ ነው።
ዛሬ በምንም ዓይነት ግራ መጋባት እና በጭንቀት ብታልፍ፣ እግዚአብሔር ስለ አንተ ያለው ዕቅድ መልካም መሆኑን አስታውስ። እርሱ ተስፋ የሚሰጥ አምላክ ነው፤ ወደፊትህም በእጁ ውስጥ ነው።
ኤርምያስ 29:11 ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
6 223
ሕይወት ብዙውን ጊዜ የፍርሃት፣ የጥርጣሬ እና የድክመት ጊዜያትን እንድታልፍ ታስገድድሀለች። ነገር ግን ብቻህን አይደለህም! እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው።
የእግዚአብሔር መገኘት ከሚገጥምህ ከማንኛውም ችግር ይበልጣል።
እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ፤ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ፥ በጽድቄም ቀኝ ደግፌ እይዝሃለሁ። ትንቢተ ኢሳይያስ 41:10
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
6 223
በህይወት ምልልስ ውስጥ ብዙ ኃላፊነቶች፣ ፈተናዎች ሊገጥምህ ይችላል።
እግዚአብሔር ግን በራስህ ብቻ እንድንተማመን አይፈልግም።
ክርስቶስ ለሚገጥም ማንኛውም ነገር ሁሉ ኃይልን ይሰጥሀል።
ሁሉን መቻል ማለት የፈለከውን ሁሉ በራስህ ኃይል ታደርጋለህ ማለት አይደለም። ይልቁንም በክርስቶስ ኃይል ፈተናን ማለፍ፣ ታማኝ ሆኖ መኖር ማለት ነው።
ዛሬ የሳምንቱን ስትጀም በፍርሃት ወይም በጭንቀት ሳይሆን ክርስቶስ ከአንተ ጋር እንዳለ በመታመን ጀምር። ምንም ዓይነት ሸክም ወይም ፈተና ቢመጣ ብቻህን አይደለህም።
ፊልጵስዩስ 4:13 ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ።
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
6 223
እረፍት ሚታረፈው በሕይወት እያለህ ነው ዛሬ! ህያው ሆንህ ያልጀመርከውን እረፍት እንዴት ትቀጥለዋለህ? ማረፍ ያለብህ በሞትህ ሳይሆን ዛሬ ህያው ሆንህ ነው። ለዛም ነው ጌታችን እና መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።” ብሎ የተናገርው::
ና! ወደዚህ ጌታ መምጣትና ማረፍ ትወዳለህ? በህይወት እያለህ ወደ ሚያሳርፍህ ጌታ መቅረብ ትወዳለህ?
ልንረዳህ በዚህ አለን::
ኢየሱስ የህይወት እረፍት ነው!
እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።
የማቴዎስ ወንጌል 11:28
#tesfa #hope
Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
