ar
Feedback
Tesfa

Tesfa

الذهاب إلى القناة على Telegram

አሁንስ ተስፋዬ ማን ነው? እግዚአብሔር አይደለምን?

إظهار المزيد
6 202
المشتركون
+2324 ساعات
+337 أيام
+1430 أيام
أرشيف المشاركات
Tesfa
6 202
DAY 2 የተስፋ አምላክ ተስፋህ ምን ላይ ነው የተመሠረተው? ተስፋ ምንጩን ይመስላል? ምንጩ አስተማማኝ ከሆነ፣ ከዚያ የሚፈስሰው ተስፋም ፈጽሞ አስተማማኝ ነው። የአማኝ ተስፋ ከአምላክ ይጀምራል። የ
DAY 2 የተስፋ አምላክ ተስፋህ ምን ላይ ነው የተመሠረተው? ተስፋ ምንጩን ይመስላል? ምንጩ አስተማማኝ ከሆነ፣ ከዚያ የሚፈስሰው ተስፋም ፈጽሞ አስተማማኝ ነው። የአማኝ ተስፋ ከአምላክ ይጀምራል። የተስፋው ምንጭ እግዚአብሔር ራሱ ነው። ሮሜ 15:13 የተስፋ አምላክም በመንፈስ ቅዱስ ኃይል በተስፋ እንድትበዙ በማመናችሁ ደስታንና ሰላምን ሁሉ ይሙላባችሁ። ይህ ተስፋ ባዶ ተስፋ አይደለም። ምክንያቱም የተስፋ ሰጪው አምላክ ታማኝ ነው። ስለዚህ በዚህ ተስፋ መታመን ማለት የማይታየውን ነገር ለመፍጠር መታገል አይደለም፤ ታማኝ በሆነው አምላክ ላይ መታመን ነው። ምናልባት ዛሬ ደክመህ ይሆናል። ምናልባት እረፍት የሚነሳህ ነገር እየከበበህ ይሆናል። ምናልባት ተስፋ ማድረግ እንኳን ከብዶህ ይሆናል። ዛሬ ዓይኖችህን ከሚያልፉ ነገሮች ላይ አንሳ። ወደ ተስፋህ አምላክ ተመልከት። በድካምህ ላይ ኃይል፣ በጭንቀትህ ፋንታ ሰላም፣ በተስፋ መቁረጥህ ፋንታ ደግሞ የማይጠፋ ተስፋን ይሰጥሃል። ምክንያቱም የተስፋህ ምንጭ እግዚአብሔር ነው። እናም ከምንጩ ጋር እስካለህ ድረስ፣ ተስፋውም አይጠፋም። የማይጠፋ ተስፋ! የማይለወጥ አምላክ! ኢየሱስ ክርስቶስ! #የማይጠፋ_ተስፋ #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 202
ተስፋ ዛሬ ላይ ቆመን ነገን በእምነት መጠበቅ ነው። ምሳሌ 23:18 በእውነት ፍጻሜ አለህና፥ ተስፋህም አይጠፋምና። #የማይጠፋ_ተስፋ #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 202
Day 1 ነገህን ስታስብ ምን ይሰማሃል? የምትጠብቀው መልስ? አካል እንዲለብስ የምትመኘው ሕልም? ወይስ እስካሁን ያልተለወጠ ሁኔታ? አንዳንድ ጊዜ ዛሬ ያለህበት ሁኔታ ነገን እንድትፈራ ያደርግሃል።
Day 1 ነገህን ስታስብ ምን ይሰማሃል? የምትጠብቀው መልስ? አካል እንዲለብስ የምትመኘው ሕልም? ወይስ እስካሁን ያልተለወጠ ሁኔታ? አንዳንድ ጊዜ ዛሬ ያለህበት ሁኔታ ነገን እንድትፈራ ያደርግሃል። የጠበቅከው ሲዘገይ፣ የፈለከው ሳይሆን ሲቀር፣ ተስፋ ማድረግ እንኳን ይከብድሃል። ግን ዛሬ ባለህበት ሁኔታ ብቻ ቆመህ ነገህን አትወስን። ምሳሌ 23:18 በእውነት ፍጻሜ አለህና፥ ተስፋህም አይጠፋምና። የምታየው ሁኔታ የታሪክህ መጨረሻ አይደለም፤ ምክንያቱም ተስፋህ በሁኔታህ ላይ አይመሠረትም። የማይጠፋው ተስፋ የምታየው ነገር አይደለም፤ የምትይዘው አካል ነው። እርሱም ኢየሱስ ነው! #የማይጠፋ_ተስፋ #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 202
https://t.me/YemaytefaTesfaFrameBot ይሄ ትክክለኛው ጊዜ ነው! የማይጠፋውን ተስፋ የምናወራበት፣ ተስፋውን በማን ላይ እንደሚያደርግ፣ እና ተስፋውን ከየት እንደሚጠብቅ ግራ ለተጋባ
+2
https://t.me/YemaytefaTesfaFrameBot ይሄ ትክክለኛው ጊዜ ነው! የማይጠፋውን ተስፋ የምናወራበት፣ ተስፋውን በማን ላይ እንደሚያደርግ፣ እና ተስፋውን ከየት እንደሚጠብቅ ግራ ለተጋባው ሰው የምንነግርበት! ተስፋህ በሁኔታህ ላይ አይደለም። ተስፋህ በሰዎች ላይ አይደለም። ተስፋህ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ነው!
ምሳሌ 23:18 በእውነት ፍጻሜ አለህና፥ ተስፋህም አይጠፋምና።
አንተም የዚህ ተስፋ መልዕክተኛ ሁን! ይህንን የማይጠፋ ተስፋ የሚለውን ፎቶ ፕሮፋይል ፒክቸር በማድረግ አልያም ደግሞ ልክ እንደዚህ አይነት በእርሶ ፎቶ ፍሬም ለመቀየር ሊንኩን በመጫን እና ወደ ቦት በመግባት በመቀየር ለሌሎችም በማጋራት፣ ተስፋቸውን የት ማድረግ እንዳለባቸው እንዲያውቁ እንርዳቸው። 👉 https://t.me/YemaytefaTesfaFrameBot አንድ ፕሮፋይል፣ አንድ መልዕክት፣ ለብዙዎች ተስፋ! #የማይጠፋ_ተስፋ #tesfa #hope

Tesfa
6 202
https://t.me/YemaytefaTesfaFrameBot ይሄ ትክክለኛው ጊዜ ነው! የማይጠፋውን ተስፋ የምናወራበት፣ ተስፋውን በማን ላይ እንደሚያደርግ፣ እና ተስፋውን ከየት እንደሚጠብቅ ግራ ለተጋባ
https://t.me/YemaytefaTesfaFrameBot ይሄ ትክክለኛው ጊዜ ነው! የማይጠፋውን ተስፋ የምናወራበት፣ ተስፋውን በማን ላይ እንደሚያደርግ፣ እና ተስፋውን ከየት እንደሚጠብቅ ግራ ለተጋባው ሰው የምንነግርበት! ተስፋህ በሁኔታህ ላይ አይደለም። ተስፋህ በሰዎች ላይ አይደለም። ተስፋህ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ነው! ምሳሌ 23:18 በእውነት ፍጻሜ አለህና፥ ተስፋህም አይጠፋምና። አንተም የዚህ ተስፋ መልዕክተኛ ሁን! ይህንን የማይጠፋ ተስፋ የሚለውን ፎቶ ፕሮፋይል ፒክቸር በማድረግ አልያም ደግሞ ልክ እንደዚህ አይነት በእርሶ ፎቶ ፍሬም ለመቀየር ሊንኩን በመጫን እና ወደ ቦት በመግባት በመቀየር ለሌሎችም በማጋራት፣ ተስፋቸውን የት ማድረግ እንዳለባቸው እንዲያውቁ እንርዳቸው። 👉 https://t.me/YemaytefaTesfaFrameBot አንድ ፕሮፋይል፣ አንድ መልዕክት፣ ለብዙዎች ተስፋ! #የማይጠፋ_ተስፋ #tesfa #hope

Tesfa
6 202
ተስፋ ማድረግ ሁሉም ነገር ወዲያውኑ እንዲሆን መጠበቅ ማለት አይደለም፤ እግዚአብሔር ታማኝ እንደሆነ አምኖ፣ በትዕግሥት መጠበቅ ነው። ምናልባት ዛሬ የምትጠብቀው መልስ አልመጣም፣ ጸሎትህም ቶሎ አልተመ
ተስፋ ማድረግ ሁሉም ነገር ወዲያውኑ እንዲሆን መጠበቅ ማለት አይደለም፤ እግዚአብሔር ታማኝ እንደሆነ አምኖ፣ በትዕግሥት መጠበቅ ነው። ምናልባት ዛሬ የምትጠብቀው መልስ አልመጣም፣ ጸሎትህም ቶሎ አልተመለሰ ይሆናል። ነገር ግን ዝምታው እግዚአብሔር ትቶሀል ማለት አይደለም። እርሱ በራሱ ጊዜ እየሠራ ነው። ስለዚህ ዛሬ ተስፋህን በሁኔታዎች ላይ ሳይሆን፣ በታማኙ እግዚአብሔር ስምና በቃሉ ላይ ብቻ አድርግ። እርሱን በትዕግሥት የሚጠብቁትን አያሳፍርም። መዝሙር 130:5 አቤቱ፥ ስለ ስምህ ተስፋ አደረግሁህ፤ ነፍሴ በሕግህ ታገሠች። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 202
አንዳንድ ጊዜ መጠበቅ፣ ተስፋ ማድረግ ልብህን ሊያደክም ይችላል። ነገር ግን ዛሬ ይህን እልሀለሁ፦ በርታ! ልብህንም አጽና። ዛሬ ሁኔታዎች ቢከብዱም፣ እርሱ ከአንተ ጋር ነው፤ የምትጠብቀውንም በጊዜው
አንዳንድ ጊዜ መጠበቅ፣ ተስፋ ማድረግ ልብህን ሊያደክም ይችላል። ነገር ግን ዛሬ ይህን እልሀለሁ፦ በርታ! ልብህንም አጽና። ዛሬ ሁኔታዎች ቢከብዱም፣ እርሱ ከአንተ ጋር ነው፤ የምትጠብቀውንም በጊዜው ያደርጋል። ስለዚህ አትፍራ፣ አትደክም፣ ተስፋህንም አትተው። በእግዚአብሔር ተስፋ አድርግ፤ ልብህንም አጽና። መዝሙር 31:24 በእግዚአብሔር የምታምኑ ሁላችሁ፥ በርቱ ልባችሁም ይጥና። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 202
ተስፋ ምኞት አይደለም፤ ከሰማይ የተሰጠ ቃል ኪዳን ነው! የተስፋህ መሠረት ሁኔታዎች ሳይሆን፣ ቃሉን የሰጠህ ታማኝ አምላክ ነው፤ ፍጻሜህም በእርሱ እጅ ነው። ምናልባት ዛሬ የተስፋህ መልስ ዘግይቶ ይሆ
ተስፋ ምኞት አይደለም፤ ከሰማይ የተሰጠ ቃል ኪዳን ነው! የተስፋህ መሠረት ሁኔታዎች ሳይሆን፣ ቃሉን የሰጠህ ታማኝ አምላክ ነው፤ ፍጻሜህም በእርሱ እጅ ነው። ምናልባት ዛሬ የተስፋህ መልስ ዘግይቶ ይሆናል፤ ሁኔታዎችም እንዳትታመን ሊያደርጉህ ይችላሉ። ግን ተስፋህን ከእግዚአብሔር ላይ አታሳ። የተናገረው እግዚአብሔር ታማኝ ነውና፤ የሰጠህን ተስፋ በጊዜው ይፈጽመዋል። ዛሬ ዓይንህን ከሁኔታው አንሳና በታማኙ እግዚአብሔር ላይ አድርግ። ተስፋህን ጠብቅ የተስፋው ሰጪ ታማኝ ነውና! ዕብራውያን 10:23 የተስፋን ቃል የሰጠው የታመነ ነውና እንዳይነቃነቅ የተስፋችንን ምስክርነት እንጠብቅ፤ #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 202
አንዳንድ ጊዜ ልብህ በምታልፍበት ሁኔታ ምክንያት ይደክማል፤ ተስፋም ማድረግ ያቅትሀል። በዚህ አይነት ወቅት በምታልፍበት ጊዜ ግን ነፍስህን በእግዚአብሔር መታመን አስታወሰሳት። ምናልባት ዛሬ ልብህ በ
አንዳንድ ጊዜ ልብህ በምታልፍበት ሁኔታ ምክንያት ይደክማል፤ ተስፋም ማድረግ ያቅትሀል። በዚህ አይነት ወቅት በምታልፍበት ጊዜ ግን ነፍስህን በእግዚአብሔር መታመን አስታወሰሳት። ምናልባት ዛሬ ልብህ በጭንቀት፣ በሀዘን እያለፈ ይሆናል። ነገር ግን ዛሬ ሁኔታህ ላይ ሳይሆን በማይለወጠው አምላክህ ላይ አይንህን አድርግ። ዛሬም ተስፋህን በእርሱ ላይ አድርግ፤ እርሱ የፊትህ መድኃኒት ነው። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 202
እግዚአብሔር የሥጋ ለባሽ ሁሉ አምላክ ነው። የሚያሳስብህን ነገር፣ የሚያስፈራህን ሁኔታ እና የማትችለውን የሚመስልህን ነገር እርሱ ይችላል። ለእግዚአብሔር የማይቻል ነገር የለም! ስለዚህ ይህን ሳምንት
እግዚአብሔር የሥጋ ለባሽ ሁሉ አምላክ ነው። የሚያሳስብህን ነገር፣ የሚያስፈራህን ሁኔታ እና የማትችለውን የሚመስልህን ነገር እርሱ ይችላል። ለእግዚአብሔር የማይቻል ነገር የለም! ስለዚህ ይህን ሳምንት በፍርሃት ሳይሆን በእምነት ጀምር። አንተ የማትችለውን እርሱ ይችላል፤ አንተ የማታየውንም እርሱ ያያል። እነሆ፥ እኔ የሥጋ ለባሽ ሁሉ አምላክ እግዚአብሔር ነኝ፤ ትንቢተ ኤርምያስ 32: 27 #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 202
አንዳንድ ጊዜ መጠበቅ ያዝላል: እንደ ዘገየ እንዲሰማህ ያደርጋል፤ ነገር ግን እግዚአብሔርን በመተማመን መጠበቅ ባዶ ሆኖ መቀመጥ አይደለም። እርሱ እየሠራ እንዳለ በማመን በትዕግሥት መቆየት ነው። ዛሬ
አንዳንድ ጊዜ መጠበቅ ያዝላል: እንደ ዘገየ እንዲሰማህ ያደርጋል፤ ነገር ግን እግዚአብሔርን በመተማመን መጠበቅ ባዶ ሆኖ መቀመጥ አይደለም። እርሱ እየሠራ እንዳለ በማመን በትዕግሥት መቆየት ነው። ዛሬ ደክመህ ከሆነ፣ ኃይልህ ከተዳከመ፣ ተስፋ አትቁረጥ: በእግዚአብሔር ተማመንና ጠብቀው፤ እርሱ ኃይልህን ያድሳል። ምናልባት ሁኔታው እንዳለ ሆኖም፤ ነገር ግን እንድትቀጥል የሚያደርግህ ኃይል እግዚአብሔር ይሰጥሀል። ኢሳይያስ 40:31 እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ፤ እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ፤ ይሮጣሉ፥ አይታክቱም፤ ይሄዳሉ፥ አይደክሙም። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 202
በሕይወት ጉዞህ ላይ አንዳንድ ጊዜ ሁሉንም ነገር ማስተዋልና መቆጣጠር ትፈልጋለህ። ነገር ግን የራስህ ማስተዋል የማያደርስህ ቦታ አለ። በዚያ ቦታ ግን እግዚአብሔርን መታመን ቀናውን መንገድ ይመራሀል።
በሕይወት ጉዞህ ላይ አንዳንድ ጊዜ ሁሉንም ነገር ማስተዋልና መቆጣጠር ትፈልጋለህ። ነገር ግን የራስህ ማስተዋል የማያደርስህ ቦታ አለ። በዚያ ቦታ ግን እግዚአብሔርን መታመን ቀናውን መንገድ ይመራሀል። እግዚአብሔርን መታመን ማለት ሁሉንም ነገር አውቀህ መጓዝ ሳይሆን፣ እርሱ የሚያውቀው እና የሚመራው መንገድ ከአንተ የተሻለ እንደሆነ በሁለንተናህ እርሱን ብቻ ማመን ነው። ዛሬ በራስህ ውስን ማስተዋል ላይ ከመደገፍ ይልቅ ሙሉ ልብህን በእርሱ ላይ ጣል። እርሱ መንገድህን ያስተካክላል፣ ያሳርፍሃል። ምሳሌ 3:5 በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤ #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 202
እግዚአብሔር የሚያስፈልግህን ሁሉ የሚያሟላል እያለፍክበት ካለው ችግር የተነሣ ሳይሆን እንደ ባለጠግነቱ መጠን ነው። እግዚአብሔር የሚያስፈልግህን ሁሉ የሚያውቅ እና በእርሱ ጊዜ እና መንገድ ደግሞ የሚ
እግዚአብሔር የሚያስፈልግህን ሁሉ የሚያሟላል እያለፍክበት ካለው ችግር የተነሣ ሳይሆን እንደ ባለጠግነቱ መጠን ነው። እግዚአብሔር የሚያስፈልግህን ሁሉ የሚያውቅ እና በእርሱ ጊዜ እና መንገድ ደግሞ የሚሰጥህ አምላክ ነው። የሚያስፈልግህን እንደሚያሟላልህ እግዚአብሔርን ታምነዋለህ? ና ወደዚህ አምላክ: የእርሱ አቅርቦት፣ የእርሱ መግቦት ገደብ የለሽ ነው። ዛሬ መሻትህን ሁሉ በጸሎት ወደ እርሱ በማቅረብ የእምነት እርምጃ ብትወስድ ጸጋው የሚያስፈልግህን ሁሉ ያሟላልሀል። የእግዚአብሔር ባለጠግነት በክርስቶስ ከበቂ በላይ እና የተትረፈረፈ ነው። መልካም ሳምንት ይሁንላችሁ! #tesfa #hope #brightmonday Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 202
ዛሬ ቀንህን ስትጀምር ምን እንደሚያመጣ ላታውቅ ትችላለህ፤ ነገር ግን የምትታመነው አምላክ ይታወቃል። እርሱ መጠጊያህ፣ ኃይልህና በመከራ ጊዜ ረዳትህ ነው። ሁኔታዎች ቢለዋወጡ፣ ነገሮች ቢከብዱ እና ኃ
ዛሬ ቀንህን ስትጀምር ምን እንደሚያመጣ ላታውቅ ትችላለህ፤ ነገር ግን የምትታመነው አምላክ ይታወቃል። እርሱ መጠጊያህ፣ ኃይልህና በመከራ ጊዜ ረዳትህ ነው። ሁኔታዎች ቢለዋወጡ፣ ነገሮች ቢከብዱ እና ኃይልህ ቢያንስም፣ ወደ እርሱ መሸሸግ ትችላለህ። የምትጀምረውን ይህን ሳምንት በራስህ ኃይል ሳይሆን በእግዚአብሔር ኃይል ጀምር። እርሱ በየቀኑ ከአንተ ጋር የሚጓዝ ታማኝ አምላክ ነው። ዛሬ በሁኔታህ ላይ ሳይሆን በእግዚአብሔር ላይ ታመን። ይህን ሳምንት ከእርሱ ጋር ጀምር፤ እርሱ ኃይልህና መጠጊያህ ነው። መዝሙር 46:1 አምላካችን መጠጊያችንና ኃይላችን፥ ባገኘን በታላቅ መከራም ረዳታችን ነው። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 202
የእግዚአብሔር ምሕረት ዛሬ ብቻ የሚያኖርህ አይደለም፤ ለዘላለም የሚፀና ምሕረት ነው። እስቲ ወደ ኋላ ተመልከት፤ ከየት እንዳወጣህ፣ ከስንት ነገር እንደጠበቀህና ዛሬ እዚህ እንዳደረሰህ አስብ። የትናን
የእግዚአብሔር ምሕረት ዛሬ ብቻ የሚያኖርህ አይደለም፤ ለዘላለም የሚፀና ምሕረት ነው። እስቲ ወደ ኋላ ተመልከት፤ ከየት እንዳወጣህ፣ ከስንት ነገር እንደጠበቀህና ዛሬ እዚህ እንዳደረሰህ አስብ። የትናንቱ ምሕረት ዛሬም አለ፤ ነገም ምህረቱ አያልቅም። ስለዚህ ዛሬ በምህረቱ ሀሴት አድርግ፤ በምስጋና የእግዚአብሔርን ታማኝነት ለትውልድ ንገር! መዝሙር 89:1 አቤቱ፥ ምሕረትህን ለዘላለም እዘምራለሁ፥ እውነትህንም በአፌ ለልጅ ልጅ እናገራለሁ። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 202
የእግዚአብሔር ምሕረት ወሰን የለውም። ሰው ሊለካው የማይችለው ያህል ሰፊ፣ የማያልቅ ነው። ምሕረቱ በሰማይ ነው፣ የእግዚአብሔር ቸርነት ከምትገምተው በላይ ሰፊ ነው። ዛሬ ያለህበት ሁኔታ ምንም ይሁን፣
የእግዚአብሔር ምሕረት ወሰን የለውም። ሰው ሊለካው የማይችለው ያህል ሰፊ፣ የማያልቅ ነው። ምሕረቱ በሰማይ ነው፣ የእግዚአብሔር ቸርነት ከምትገምተው በላይ ሰፊ ነው። ዛሬ ያለህበት ሁኔታ ምንም ይሁን፣ የእግዚአብሔር ምሕረት አይቀንስም። በድካምህ ይደግፍሃል፣ በውድቀትህ ያነሳሃል፣ በመከራህም ያጽናናሃል። ሁኔታዎች ቢለዋወጡም እርሱ ግን ታማኝ ነው። ምሕረቱ ከአንተ ጋር ነው። ስለዚህ በሁኔታህ ሳይሆን በእርሱ ታማኝነት ታመን። ዛሬም በእግዚአብሔር ምሕረት እረፍ፤ እርሱ አይተውህም። አቤቱ፥ ምሕረትህ በሰማይ ነው፥ እውነትህም ወደ ደመናት ትደርሳለች። መዝሙረ ዳዊት 36:5 #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 202
እግዚአብሔር የማይለወጥ ህያው አምላክ ነው። እርሱ ቃሉን የሚጠብቅ፣ ቃል ኪዳኑን የማይረሳ እና ምሕረቱን የማያቋርጥ ታማኝ አምላክ ነው። ቃል ኪዳኑንና ምሕረቱን እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ ነው። ሰው ቃ
እግዚአብሔር የማይለወጥ ህያው አምላክ ነው። እርሱ ቃሉን የሚጠብቅ፣ ቃል ኪዳኑን የማይረሳ እና ምሕረቱን የማያቋርጥ ታማኝ አምላክ ነው። ቃል ኪዳኑንና ምሕረቱን እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ ነው። ሰው ቃሉን ሊረሳ ይችላል፤ እግዚአብሔር ግን የተናገረውን አይረሳም። ሰው ቃል ኪዳኑን ሊያፈርስ ይችላል፤ እርሱ ግን በቃሉ የፀና አምላክ። ምናልባት ዛሬ እግዚአብሔር የገባልህን ቃል እየጠበቅህ ይሆናል። ጸሎትህ መልስ ያላገኘ ሊመስልህ ይችላል፤ የምትጠብቀውም ነገር የዘገየ ሊመስልህ ይችላል። እግዚአብሔር የሚሰራበት ጊዜ አለው፤ ቃሉንም ደግሞ በጊዜው ይፈጽማል። እርሱ ትናንት ታማኝ እንደነበረ ዛሬም ታማኝ ነው፤ ነገም በታማኝነቱ ፀንቶ ይኖራል። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 202
ይህ ቃል ለዛሬም ታላቅ ተስፋ ነው። እግዚአብሔር የሚናገረውን አይረሳም፤ የሚሰጠውን ተስፋም አይተወውም። ሁኔታዎች ሊቀየሩ፣ መንገዱም ከጠበቅከው በላይ ሊረዝም ይችላል፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ቃል
ይህ ቃል ለዛሬም ታላቅ ተስፋ ነው። እግዚአብሔር የሚናገረውን አይረሳም፤ የሚሰጠውን ተስፋም አይተወውም። ሁኔታዎች ሊቀየሩ፣ መንገዱም ከጠበቅከው በላይ ሊረዝም ይችላል፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ቃል አይለወጥም። ምናልባት ዛሬ እየጠበቅከው ያለ መልስ፣ እየጸለይክለት ያለ ጉዳይ ወይም እግዚአብሔር የሰጠህ ተስፋ ሊኖር ይችላል። እርሱ በጊዜው የሚያደርገውን ያውቃል። የጀመረውንም መልካም ሥራ እስከፍጻሜው ያደርሳል። እርሱ የተናገረው መልካም ነገር አንድም ሳይቀር ይፈጽማል። ኢያሱ 21:45 እግዚአብሔር ለእስራኤል ቤት ከተናገረው መልካም ነገር ሁሉ ተፈጸመ እንጂ ምንም አልቀረም። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 202
እግዚአብሔር እንደ ሰው አይደለም። እርሱ ታማኝ ነው፤ ባሕርዩም አይለወጥም። ይህ ቃል በድካምህ መካከል ታላቅ መጽናናት ይሰጥሀል። እምነትህ ሊደክም ይችላል፤ ነገር ግን የአንተ ድካም የእግዚአብሔርን
እግዚአብሔር እንደ ሰው አይደለም። እርሱ ታማኝ ነው፤ ባሕርዩም አይለወጥም። ይህ ቃል በድካምህ መካከል ታላቅ መጽናናት ይሰጥሀል። እምነትህ ሊደክም ይችላል፤ ነገር ግን የአንተ ድካም የእግዚአብሔርን ታማኝነት አይለውጠውም። አንተ በእርሱ ላይ ልትደገፍ በማትችልበት ጊዜ እንኳን፣ እርሱ አንተን ለመደገፍ ታማኝ ነው። ምናልባት ዛሬ የምትጠብቀው መልስ ዘግይቶ ይሆናል፤ ወይም የምትጸልይለት ነገር እንደምትፈልገው መልስ እያገኘህበት አይደለም ይሆናል: እግዚአብሔር ግን አልተለወጠም። እርሱ በጊዜው የሚሠራ ታማኝ አምላክ ነው። ስለዚህ ዛሬ እምነትህ ቢደክምም፣ በእግዚአብሔር ታማኝነት ላይ ተደገፍ። ሁኔታውን ሳይሆን እርሱን ተመልከት። የተናገረውን አይረሳም፤ የጀመረውን አይተወውም፤ ራሱንም ሊክድ አይችልም። ዛሬ በዚህ እውነት እረፍ፣ እርሱ አይለወጥም። እርሱ ታማኝ ሆኖ ይኖራል። 2 ጢሞቴዎስ 2:13 ባናምነው፥ እርሱ የታመነ ሆኖ ይኖራል፤ ራሱን ሊክድ አይችልምና።” #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads

Tesfa
6 202
እግዚአብሔር በአንተ የጀመረውን ሥራ ይፈጽመዋል! መንፈሳዊ ጉዞህ የሚጀመረው በራስ ጥረት አይደለም። በአንተ ውስጥ መልካምን ሥራ የሚጀምረው እግዚአብሔር ነው። በእርሱ ስታምን፣ በየቀኑ ክርስቶስን እን
እግዚአብሔር በአንተ የጀመረውን ሥራ ይፈጽመዋል! መንፈሳዊ ጉዞህ የሚጀመረው በራስ ጥረት አይደለም። በአንተ ውስጥ መልካምን ሥራ የሚጀምረው እግዚአብሔር ነው። በእርሱ ስታምን፣ በየቀኑ ክርስቶስን እንድትመስል እየቀረጸህና እያሳደገህ ይመራሃል። ምናልባት ዛሬ በሕይወትህ እግዚአብሔር ሚሰራውን ሙሉ በሙሉ ማየት አትችል ይሆናል። እምነትህ ሊፈተን ይችላል: ነገር ግን ተስፋ አትቁረጥ፤ በአንቱ ስራን የጀመረው እግዚአብሔር እስከ ፍጻሜው ድረስ ታማኝ ነው።እግዚአብሔር በቃሉና በመንፈሱ እየመራህ፣ እያስተማረህ፣ እያሳደገህ እና ወደ እርሱ እያቀረበ ይመራሃል። በአንተ የጀመረውን መልካም ሥራ በታማኝነት ይፈጽመዋል። #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads