ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
الذهاب إلى القناة على Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
إظهار المزيد2 924
المشتركون
+10524 ساعات
+3357 أيام
+33630 أيام
جاري تحميل البيانات...
القنوات المماثلة
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
سبتمبر '26
سبتمبر '26
+381
في 0 قنوات
أغسطس '26
+133
في 1 قنوات
Get PRO
يوليو '26
+112
في 3 قنوات
Get PRO
يونيو '26
+101
في 3 قنوات
Get PRO
مايو '26
+195
في 4 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+193
في 6 قنوات
Get PRO
مارس '26
+278
في 7 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+590
في 7 قنوات
Get PRO
يناير '26
+363
في 5 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+129
في 2 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+394
في 8 قنوات
Get PRO
أكتوبر '25
+570
في 9 قنوات
Get PRO
سبتمبر '25
+710
في 8 قنوات
Get PRO
أغسطس '250
في 4 قنوات
Get PRO
يوليو '25
+48
في 2 قنوات
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 11 سبتمبر | +24 | |||
| 10 سبتمبر | +105 | |||
| 09 سبتمبر | +181 | |||
| 08 سبتمبر | +35 | |||
| 07 سبتمبر | +19 | |||
| 06 سبتمبر | +5 | |||
| 05 سبتمبر | +4 | |||
| 04 سبتمبر | +1 | |||
| 03 سبتمبر | +1 | |||
| 02 سبتمبر | +1 | |||
| 01 سبتمبر | +5 |
منشورات القناة
እንኳን ለ2019 ዓ.ም. በጽናት አደረሳችሁ፣ አደረሰን!
የአማራ ሕዝብ መዋቅራዊ ጭቆና በርትቶበት፣ ሁለገብ የዘር ፍጅት ታውጆበትና ይህን ሰቆቃ የሚከስበት የፍትሕ ተቋም ተነፍጎት፤ ለሀገር አንድነትና ለአብሮነት ሲል ብቻ መከራውን ለዘመናት በዝምታ ተሸክሞ ቆይቷል።
በየአደባባዩም «አትግደሉን፤ እንደ ሰው እንኑር!» እያለ የሰላም ጥሪ ሲያሰማ ኖሯል። ነገር ግን የሕዝባችንን ታሪክና ትርክት በማዛባት በአማራ ሞት ላይ የፖለቲካ ቁማር የቆመሩ፣ ሀገር የማስተዳደር አደራ ተሰጥቷቸው ሀገርን በማፍረስ የመንደር ምስለኔ መሆንን የመረጡ የጎጥ አለቆች ያደረሱብንን ግፍ መሸከም አብቅቷል።
የሕዝባችንን ክብር ለመመለስ፣ የትውልዳችንን የመከራ ዶሴ ለመቀደድ እንዲሁም ከሕዝባችን ጋር በመቆም ስቃዩን ለመካፈል የመከራውን ቀንበር ተሸክማችሁ በዱር በገደሉ የምትገኙ ውድ የትግል ጓዶቼ፣ የዳግማዊ አድዋ አርበኞችና የአባቶቻችንን ጀግንነት የወረሳችሁ የትውልዳችን ፋኖዎች፤ እንኳን ለ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት በድል እና በጽናት አደረሳችሁ!
የዘንድሮውን አዲስ ዓመት ለየት የሚያደርገው፣ የህልውና ትግላችን ወደላቀ ምዕራፍ የተሸጋገረበት፣ ተቋማዊ አንድነታችን የጸናበትና ወታደራዊ እንዲሁም ፖለቲካዊ መዋቅራችን ይበልጥ የጠነከረበት ሆኖ መምጣቱ ነው። ከዚህም ባለፈ ለሕዝባችን የተስፋ ብርሃን የሆኑ አማራዊ መሪዎች የተፈጠሩበትና ወታደራዊ አቅማችን በገቢር የታየበት ታሪካዊ ዘመን ላይ እንገኛለን። ከቅርብ ጊዜ አጋጣሚዎች ብንነሳ እንኳ፣ በ'ዘመቻ አባ ናደው' የተጎናጸፍናቸው ወታደራዊና ፖለቲካዊ ድሎች የጠላትን ቅስም የሰበሩ፣ የሕዝባችንን ልብ ያሞቁና ጠላትን የሚያንበረክክ ጀግና ሠራዊት መገንባቱን በተግባር ያረጋገጡ ናቸው።
በተለይም ጳጉሜን 3 ቀን 2018 ዓ.ም. በደላንታ ግንባር በተደረገው አውደ ውጊያ የተገኘው አንጸባራቂ ድል፣ ትግላችን የቀጠናው የኃይል ስበት ማዕከል መሆኑን ከማረጋገጡም ባሻገር፤ በምሥራቅ አፍሪካ ተገዳዳሪ የሆነ ፖለቲካዊና ማርሽ ቀያሪ ወታደራዊ ኃይል መገንባታችንን በግልጽ ያስመሰከረ ነው።
በዚህ ወሳኝ ምዕራፍ፣ ድርጅታችን አፋብን እና ዕዛችን (ሚኒልክ 1ኛ ዕዝ) የትግላችን የጀርባ አጥንት በመሆናቸው ከፊታችን ሰፋፊና ታሪካዊ ግዳጆች ይጠብቁናል። ይህንን በአጭር ጊዜ ለማሳካት እያንዳንዱ አመራር በዕቅድ የተለካ ተልዕኮ በመያዝ፤ ጠንካራ መሪ፣ ራሱን ለትግሉ የሰጠ አታጋይ እና ለሕዝቡ ቤዛ የሚሆን የነጻነት ችቦ ለኳሽ ፋኖን ማፍራት ይኖርበታል። ግባችን አማራዊ ክብርን የተላበሰና ድል አድራጊ ሠራዊት መገንባት፣ የዕዙን የትእዛዝ ሰንሰለት አጥብቆ መጠበቅ፣ ሕዝብን ማስቀደም እንዲሁም ፍትሕና ዴሞክራሲን የሚያሰፍን ፖለቲካዊና አስተዳደራዊ መዋቅር ዘርግቶ የሕዝባችንን ህልውና የሚያስጠብቅ ጠንካራ ተቋም መፍጠር ነው።
በአዲሱ ዓመት በአይነቱ የተለየ የትግል ሜዳ የምንከፍትበትና ተከታታይነት ያላቸውን ወታደራዊ ግዳጆች በድል የምንወጣበት ይሆናል። በዚህም ሂደት ለአማራውም ሆነ ለሀገራችን ብቁ የሆኑ፣ ለአላማቸው እስከመጨረሻው የጸኑና እንደ ወርቅ በእሳት የተፈተኑ ድል አብሳሪ ወታደራዊ መኮንኖችን እናበቃለን። ከዚህም ጋር ተያይዞ በአዲሱ ዓመት በአባቶቻችን ጥንታዊ የአርበኝነት አጠራርና በዘመናዊ ወታደራዊ የማዕረግ ስያሜዎች ደምቀው የሚወጡ በርካታ መሪዎችን እንደምናፈራ ሙሉ እምነት አለኝ።
ይህን ታሪካዊ የሕይወታችን ዑደትና የትግል ምዕራፍ እውን ለማድረግ፣ እኔን ጨምሮ ሁላችንም የማይተካ ታሪካዊ ሚናችንን በከፍተኛ ኃላፊነት እንድንወጣ አደራ እያልኩ፤ ትግላዊ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ!
አርበኛ ወንድሙ ማሩ
የአፋብን ሚኒልክ 1ኛ ዕዝ ወታደራዊ አዛዥ
| 2 | لا يوجد نص... | 1 |
| 3 | የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ቃኝዎች በሬማ ከተማ በወሰዱት የሌሊት ኦፕሬሽን፣ ድል ማስመዝገባቸው ተገለፀ!!
መስከረም 01/2019ዓ.ም
መስከረም 01 ቀን 2019 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው 5ኛ ዕዝ አፄ ዓምደ ጽዮን ኮር አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር "የክፍለ ጦሩ ቃኝዎች" በመርሀቤቴ አውራጃ ሬማ ከተማ የተሳካ ሰርጂካል ኦፕሬሽን አከናውነው ድል ማስመዝገባቸውን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን አስታወቀ።
ቃኝዎቹ ከሌሊቱ 10:00 ሰዓት ላይ በወሰዱት እርምጃ አቶ ዲቡ አያሌው የተባለ ቀንደኛ የሚሊሻ አመራር ሲገደል፣ ስማቸው በውል ያልታወቁ ተጨማሪ ሁለት የሚሊሻ አባላትም መገደላቸውን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ገልጿል።
በአዲሱ ዓመት መባቻ ላይ ስኬታማ ኦፕሬሽን ፈፅመው በድል የተመለሱት የክፍለ ጦሩ ቃኝዎች፡ ሁለት(2) የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችንና ሁለት(2) ቦንቦችን በመማረክ ያለምንም ኪሳራ ወደ አሃዳቸው በሠላም መመለሳቸውን አክሏል።
በኦፕሬሽኑ ከፍተኛ ጉዳት ያስተናገደው የጠላት ኃይል፣ ብዙ የተጎዱ የሚሊሻ አባላት እዳሉትና የተጎዱት በሙሉ ሬማ ከተማ ጤና ጣቢያ ድንገተኛ ክፍል ውስጥ እየታከሙ እንደሚገኙ ሲገልፅ ሊድኑ የማይችሉ ከባድ ቁስለኞች እዳሉ በውስጥ መረጃዬ አረጋግጫለሁ ሲል አጠቃሎ አሳውቋል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ | 346 |
| 4 | لا يوجد نص... | 302 |
| 5 | ጠላት ይተማመንባት የነበረችውን በ12ኛ ዕዝ 71ኛ ክፍለጦር በዚህ መልኩ ድርምስምሷ ወጥቷል።
ይህ የምትመለከቱት በለስ ቀንቶት ከተማረከው የጠላት ሠራዊት መካከል ጥቂቱ ነው። | 633 |
| 6 | ለነፃነቱ በቆራጥነት እየታገለ ላለው ኩሩው የአማራ ህዝብ እና ለመላው የትግል አጋሮች፤እንኳን ለአዲሱ አመት በሰላም አደረሳችሁ!!
አሁንም ከገሃነም እሳት፣ ከደም ማዕበልና ከጠላት ከበባ ሳንንበረከክ በጽናት እየታገልን እንኳን ለ2019 አዲስ ዓመት በሙሉ ብርታት በሰላምና በጤና በደህና አደረሳችሁ!
ያለፈው ስምንት ዓመታት በአብይ አህመድ የሚመራው የብልፅግና ስርዓትና ለስርዓቱ ወንበር አስጠባቂ ሆኖ የሚያገለግለው ባንዳው ብአዴን በህዝባችን ላይ የደገሱትን የዘር ማጥፋት፣ የጭካኔና የግፍ ደመና እያሸነፍን የተሻገርንበት የትግል ዘመን እጅጉን ይደንቃል። ዛሬም በዚያ ሁሉ መከራ ውስጥ አልፈን በትግል ላይ እንገኛለን፤ የአማራ ህዝብ አሁንም አንገቱን አልደፋም፣ ጉልበቱም አልተንበረከከም! በየበረሃውና በየተራራው እያካሄድነው ያለነው የፋኖዎቻችን የብረት እምቢተኝነትና የሞት ሽረት ተጋድሎ፣ ነፃነትን በፍቅርና በደም እንጂ በጉልበት ማንበርከክ እንደማይቻል ለመላው ዓለም በወርቃማ ቀለም እያስመሰከረ ይገኛል።
ውድ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የትግል አጋሮቼ እና መላው የአማራ ህዘብ ይህ አዲሱ 2019 ዓመት ትግላችንን አፋጥነን የክብራችንን ትንሳኤ የምናረጋግጥበት፦ የብልፅግናው አረመኔያዊ ስርዓትና የጥፋት አገልጋዩ ብአዴን በህዝባችን ላይ የጫኑትን የወረራ፣ የግፍና የጭቆና ሰንሰለት በቆራጥ ተጋድሎ በጣጥሰን፣ የተደፈረውን ክብራችንንና ህልውናችንን በሙሉ ግርማ የምንመልስበት፤ የተጋድሏችንን መቋጫ ድል የምንጨብጥበት በየቀኑ በበረሃና በሸንተረሩ የጀግኖቻችን መስዋዕትነት አብቦና ፍሬ አፍርቶ፣ የህዝብን ደም የሚነግዱትን ገዢዎች እስከወዲያኛው በመሸኘት የህዝባችንን ፍፁም ነፃነትና ድል የምናበስርበት፤ፍትህና እፎይታን የምናጎናፅፍበት በብልፅግናና በብአዴን ሴራ ከቀያቸው የተፈናቀሉ ወገኖቻችንን በክብርና በደስታ ወደ አባቶቻቸው ርስት የምንመልስበት፣ በግፍ የታሰሩ ንጹሃን ወገኖቻችንን ሰብረን በማስፈታት የነፃነት አየር እንዲተነፍሱ የምናደርግበት የእውነትና የብርሃን ዘመንን የምንገነባበት ወርቃማው አመት እንደሚሆን አልጠራጠርም።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) በሜዳው እያካሄደ ባለው ውጊያና የፖለቲካ ትግል የፋሺስታዊውን ስርዓትና ወንበር አስጠባቂዎቹን ጭካኔ ለዓለም በማጋለጥ፣ የህዝባችንን እውነተኛ ድምፅ እያስተጋባ የድሉን ታሪክ በኩራት የሚፅፍበት እንዲሆንልን አሁንም በግንባር ላይ ከሚፋለመው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ከታችኛው ሰራዊት እስከ ላኛው አመራሮቻችንን ከልብ የመነጨ የትግል ጥሪያችንንና መልካም ምኞታችንን እናስተላልፋለን!
በመጨረሻም ትግላችን እስከ ነፃነታችን ይቀጥላል!ለህዝባቸው ህልውናና ክብር ሲሉ ህይወታቸውን የገበሩ የትግላችን ሰማዕታት ክብርና ሞገስ አግኝተው ለዘላለም በልባችን ይኖራሉ!ጨለማው ተገፎ ብርሃኑ ይወጣል! የጭቆናውና የባንዳዎች ዘመን ያብቃል እየታገለ ያለው ህዝባችን በነፃነት ያሸንፋል!
የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው 5ኛ ዕዝ የህዝብ አስተዳደር መምሪ አርበኛ ኤፍሬም ባዬ | 623 |
| 7 | لا يوجد نص... | 522 |
| 8 | በዚህ አዲስ ዓመት መባቻ ላይ፣ በትግላችን ማዕከል የምናስባቸው እና የደማቸው ጥሪ የሚያስቆጣን ወገኖቻችን መኖራቸውን አንዘነጋም።
በሃይማኖታቸው ምክንያት መከራና ሰቆቃ እየደረሰባቸው ያሉ የክርስትና እና የእስልምና እምነት ተከታዮች፣ ቤተ-እምነቶቻቸው ሲደፈሩ እና ሲቃጠሉ የታገሱት የመከራ ፅዋ ሞልቶ እየፈሰሰ ነዉ።
በየማጎሪያው ያለ ፍርድ በበቀል እና በተረኝነት ስሜት የታጎሩ የፖለቲካ እና የማንነት እስረኞች፣ በማሰቃያ ክፍሎች ውስጥ አካላቸው የጎደለ እና ህይወታቸው ያለፈ ወገኖቻችን ፍትህ የማግኘት መብታቸውን ማስከበር የትግላችን አንዱ ግብ ነው።
በልማት ስም ከቀያቸው የተፈናቀሉ፣ ንብረታቸው የወደመባቸው፣ የአገዛዙን ጥቃት በመሸሽ ስደት ሀገር የሚሰቃዩ ወገኖቻችን ወደ ቀደመ ቀያቸው ተመልሰው በክብር እና በነፃነት የሚኖሩበት ሁኔታ እንዲፈጠር እንታገላለን።
በመጨረሻም
ትግላችን የህልውናችንን ዋስትና በብረት ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን፣ የሁሉም ብሔሮችና ብሔረሰቦች እኩልነት፣ ህግ የበላይነት እና ፍትህ የሰፈነባትን፣ የትኛውም ዜጋ በቋንቋው እና በማንነቱ የማይገፋባትን ከነባር ስልጣኔዋ፣ ታሪካ እና ባህሏ ያልተቃረነች ፍትሃዊ ኢትዮጵያን የመገንባት ስልታዊ ግብ አለው።
ያለፈው አመት ለአማራም ሆነ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝቦች ወሳኝ የሆነ ዕድል ተፈጥሯል፤ የያዝነው አመት ደግሞ ይህን የትብብር ዕድል ተጠቅመን ህልውናችንን የምናረጋግጥበት፣ የጠላት የማጥፊያ አቅሞቹን ሰብረን በአሸናፊነት በአዲስ ፖለቲካዊ መድረክ ሀገርን ወደ ተሟላ እና ዘላቂ ሰላም ለማሸጋገር የምንሰራበት ይሆናል።
በድጋሚ መልካም አዲስ ዓመት
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ | 489 |
| 9 | በሀገራችን በከፍተኛ የእርስ በእርስ መጠራጠር ብሎም መገፋፋት ውስጥ እንዲኖሩ ከፍተኛ ሴራ የተሰራባቸው ህዝቦች የጠላትን እንዲሁም የውጭ ሀይሎችን ጸረ ትብብር ጫና ተቋቁመው በአብሮነት ለመቆም መነሳት የአመቱ ብሎም የክፍለ ዘመኑ ትልቅ ድል ነው። በዚህም የህዝቦችን የተሳሰረ ዕጣ ፈንታ ከጋራ የህልውና ስጋት ባሻገር ለሀገር ግንባታ በጋራ መስራት የሚቻልበትን ፖለቲካዊ መደላድል ለመፍጠር ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል።
በመሆኑም እንደ አማራ ሕዝብ ሁሉ ለሕልውናቸው፣ ለባህላቸው፣ ለማንነታቸውና ለፍትሕ የሚታገሉ ሌሎች የኢትዮጵያ ወንድምና እህት ሕዝቦች በጋራ መቆማቸውንና መተሳሰራቸውን የሚያውጁበት ታሪካዊ ወቅት ላይ እንገኛለን።
፬. በህዝባችን እና በሰራዊታችን ተጋድሎ የከሸፉት የአገዛዙ የስልጣን ማራዘሚያ ፕሮጀክቶች
ያለፈው 2018 ዓ. ም ፖለቲካዊ መዋቅሩን በወታደራዊ አገዛዝ እየለወጠ ያለዉ ዘረ-ፈጁ አገዛዝ በምርጫ ስም ህጋዊ የጭፍጨፋ እውቅና እና ካርድ ለማግኘት እንዲሁም በብሔራዊ ምክክር ስም ግለሰባዊ ቅዠቶችን የብሔራዊ ምክክር ውጤት ለማድረግ በቢሊዬኖች የሚቆጠር ገንዘብን በማባከን በሰፊው የደከመበት ዓመት ነበር።
ይሁን እንጅ የአማራ ህዝብን ጨምሮ መላው ኢትዮጵያዊ ባደረገው ተጋድሎ እና የነቃ እንቅስቃሴ ምክንያት አገዛዙ በምርጫ ስም ዓለምን ማታለል የማይችልበትን ይልቁንም ምርጫን ስልጣን ላይ ለመቆዬት የሚጠቀምበት የማጭበርበሪያ ስልት መሆኑን ማሳዬት ተችሏል። በምርጫም ሆነ በምክክር ስም የህልውና አደጋ የተደቀነበትን ህዝብ የህልዉና ጥያቄ ማዳፈን እንደማይቻል ተረጋግጧል። በመሆኑም ያለፈው ዓመት አገዛዙ ብሔራዊ አጀንዳወችን ለይስሙላ በማጉላት፣ ያልተደረገ ምርጫን እንደተደረገ በማስመሰል እንዲሁም በተጧጧፈ ጦርነት ውስጥ ሆኖ ብሔራዊ ምክክር በሚል ስም ስልጣንን ህጋዊ ቅቡልነት ያለው ለማድረግ ያደረጋቸው ሙከራወች ሙሉ በሙሉ የከሸፉበት መሆኑ በታሪክ የሚታወስ ነው።
ይህ አዲስ ዓመት ተራ የዘመን መለወጫ ብቻ ሳይሆን የአማራን ህዝብ ከምድር ገጽ ለማጥፋት፣ ታሪኩን ለመደምሰስ፣ ሀብቱን ለመዝረፍ እና ስነ-ህዝባዊ አወቃቀሩን ለመቀየር በአገዛዙ የታወጀውን የዘር ማጥፋት ጦርነት በመመከት፣ የህዝባችንን ፍጹም አሸናፊነት የምናበስርበት ታሪካዊ ምዕራፍ እንዲሆን እየተመኘን ተከታዮችን ጥሪወች እናቀርባለን!
፩) ለመላው የአማራ ህዝብ:-
አረመኔያዊውን ግፍና መከራ በትዕግስትና በጀግንነት እያሸነፍክ ላለኸው ኩሩ ሕዝባችን፣ አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የፍትሕ፣ የዕረፍትና የታሪካዊ ክብርህ መመለሻ ዓመት እንዲሆንልህ ንቅናቄያችን ከትላንት በተሻለ መልኩ ደምና አጥንቱን ከስክሶ ህልውና እና ነጻነትን ለማስከበር ከምንጊዜውም በላይ ለመሥራት ቁርጠኛ መሆኑን ዛሬም እንደ ትላንቱ ያረጋግጣል። ስለሆነም የምታደርገውን ሁሉን አቀፍ ድጋፍና ደጀንነት ከምንግዜውም በላይ አጠናክረህ እንድትቀጥል ታሪካዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
የትኛውም ስትራቴጂም ሆነ ታክቲክ አንድነትን አያክለውም፤ አንድነትን የሚያሳጣ አማራጭ በምንም መመዘኛ ተገቢ፣ አስፈላጊ አለያም ጠቃሚ ሊሆን አይችልም። ህዝባዊ አንድነት፣ መዋቅራዊ አንድነት እና የአመራር አንድነት የትግላችን አይተኬ ስትራቴጂካዊ አቅሞቻችን ናቸው።
በየትኛውም ጊዜ በተለይ ደግሞ በዚህ ወቅት አንድነትን የትግሉ ስትራቴጂካዊ አቅም መሆኑን ተረድተን አቅማችንን እንጠብቅ። ከዚህ በተቃራኒ የሆነ አካሄድ እና አሰላለፍ በጋራ እንታገል። አማራን በንዑስ ማንነት እና የጥቅም ትስስር በትኖ፣ የጀመረውን ዘር ማጥፋት በስኬት ለማጠናቀቅ ጠላት ከፋፍሎ ሊያጠፋን እየሰራ እንደሆነ ተረድተን አማራ ከብዙ አመታት በኋላ ያገኘውን ብሔራዊ አንድነት በጥንቃቄ ልንጠብቅ እና ከአቆርቋዥ ከፋፋዮች በጽናት ልንከላከለው ይገባል።
በተጨማሪም አማራው የህዝብ እና የድርጅት አንድነት ባሳካበት አመት ህዝቡን ከከበባ እና ንጥልነት አውጥቶ በሀገር ውስጥ ካሉ ብሔራዊ ሀይሎች ጋር መተባበር መቻሉ ለአማራም፣ ለሌላውም ብሎም ለሀገር ትልቅ ዕድልን አስገኝቷል። ይህን መልካም ዕድል እና ተስፋ መንከባከብ ይገባል።
፪) ለአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አመራርና አባላት፦
አማራ ተገፍቶ እና ተበድሎ የሚጠፋ ህዝብ ሳይሆን፣ በመከራ ውስጥ ታድሶ፣ የብረት ምሽግ ሆኖ የሚነሳ የጽናት አምድ ነው! የታጠቁ ድሮኖች፣ የተደረደሩ ታንክና መድፎች የተበላሹ የፕሮፓጋንዳ ማሽኖች የጊዜያዊ ጉልበት ምልክቶች እንጂ የህዝብን የእውነት እና የፍትህ ፍላጎት አይሰብሩም። የጠላቶቻችን ውድቀት ተቃርቧል፤
የብልፅግናን አገዛዝ አረመኔያዊ ጥቃት መክታችሁ፣ የሕዝባችሁን ሕልውና ለማስከበር በዱር በገደሉ የምታሳዩት የጀግንነት ታሪክ በአሁኑ ትውልድ ብቻ ሳይሆን፣ በመጪውም ትውልድ ዘንድ ታሪክ በወርቅ ቀለም የሚከትበው አኩሪ ገድል መሆኑን ለማሳሰብ እንወዳለን።
አዲሱ 2019 ዓ.ም የሕዝባችንን ከሕልውና አደጋ አውጥተን፣ ነፃነት እና እኩልነትን የምናረጋግጥበት እንዲሁም ወንጀለኞችን ለፍርድ አደባባይ የምናቀርብበት የድል ዓመት እንዲሆን፣ ከምንጊዜውም በላይ ከፍተኛ አደራና ቃል-ኪዳናችንን የምናድስበት ዘመን እንዲሆን እንመኛለን።
፫) ለጸረ አገዛዝ ብሔራዊ ሀይሎች
ካለፉት ስምንት አመታት የተማርነው ወሳኝ እውነት በተራ ለመበላት ወረፋ የምንጠብቅበት ጊዜ እና ሁኔታ ላይ አለመሆናችን ነው።
እናም ሁሉም ህዝባዊ ሀይል ለህልውናው በአንድ የጋራ ጠላት ላይ በሁሉም ግምባር የቆመበት ምዕራፍ ለዚህ ለትውልዶች ለተደገሰው ጦርነት የመጨረሻው ምዕራፍ ነው፤ ለህዝቦች የአሸናፊነት ምዕራፍ።
እናም ቀጣዩ አመት በትብብር አቅም የህልውና አደጋን በመመከት ጠላትን ጨርሶ በማስወገድ እልህ አስጨራሽ ተጋድሎ የምናደርግበት አመት ነው። ለዚህም የተጀመሩ መልካም የትብብር ተግባራትን በማስቀጠል፣ የጠላትን የፕሮፓጋንዳ ጥቃት ለመመከት በህዝባዊነት እንድንሰራ መልዕክታችንን ለማስተላለፍ እንወዳለን። የህዝቦችን እና የብሔራዊ ሀይሎች መልካም ግንኙነት ለጠላት ትልቅ አደጋ በመሆኑ ይህን ለማፍረስ የሚሰራቸውን ተግባራት ለመቀልበስ የህዝብን አቅም በጋራ መጠቀም ይገባል። ለዚህም የትብብሩን ተስፋዎች መንከባከብ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ህዝቡ እና ሁሉም ብሔራዊ ሀይሎች በሁሉም ረገድ የጠላትን መግቢያ በሮች ለመድፈን የጋራ ርብርብ ልናደርግ ይገባል።
፬) ለአፍሪካውያንና ለመላው የዓለም ሕዝብ፦
በኢትዮጵያ ምድር እየተፈጸመ ያለውን አረመኔያዊ የሰብአዊ መብት ረገጣና የዘር ማጥፋት ወንጀል ዓለም በዝምታ ሊመለከተው አይገባም። የጭቁን ሕዝቦችን የነፃነት ድምፅና ትግል በሁሉም መስክ ሊደገፍ የሚገባዉ ነው።
የአማራ ህዝብ የህልውና እና የፍትህ ጥያቄ ከዓለም አቀፍ ህጎች (IHL) እና ከህግ የበላይነት ጋር የተጣጣመ ነው። በምስራቅ አፍሪካ፣ በአፍሪካ ቀንድ እና በቀይ ባህር ቀጠና ዘላቂ መረጋጋት እና የንግድ መስመር ሰላም ሊመጣ የሚችለው የህዝባችን ሰብአዊ፣ ታሪካዊ እና ፖለቲካዊ መብቶች ሲከበሩ ብቻ ነው። ያልተረጋጋች ኢትዮጵያ ለቀጠናው ስጋት ናት፤ የህዝባችንን ትግል መደገፍ ደግሞ በቀጠናው ህጋዊነትን፣ ፍትህን እና ዘላቂ ሰላምን የመትከል ብቸኛው መንገድ ነው።
በመሆኑም የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ሰላም እና መረጋጋትን የሚያውከውን የብልፅግና አገዛዝን ማስወገድ ለሰላማዊ የንግድ እና ፖለቲካ እንቅስቃሴ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን በማመን አገዛዙን ባለመደገፍ እና ለተጋድሏችን ዲፕሎማሲያዊ ድጋፍ በመስጠት የበኩላችሁን ድርሻ እንድትወጡ እንጠይቃለን።
፭) ለአገዛዙ የሰቆቃ ሰላባወች:- | 427 |
| 10 | አዲስ ዓመትን አስመልክቶ ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ
መስከረም 01/ቀን 2019 ዓ.ም
መላው የአማራ ህዝብ እና ኢትዮጵያዊያን፣ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አመራርና አባላት፣ የብልፅግናን አገዛዝ በየግንባሩ የምትታገሉ ፀረ ብልፅግና ኃይሎች፣ አፍሪካውያን ወንድሞቻችንና ለመላው የዓለም ሕዝብ፤ ድርጅታችን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) እንኳን ለ2019 ዓ.ም አደረሳችሁ፣ አደረሰን ይላል!
ሀገራችን ኢትዮጵያ አዲሱን ዓመት እየተቀበለች ያለችው የቀውስ አገዛዙ በነደፈው የጥፋት ፕሮጀክት ምክንያት ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ምስቅልቅል ውስጥ ሆና ነው። የህዝባቸውን ህልውና ባስቀደሙ ብሔራዊ ኃይሎች እና በኢትዮጵያዊነት ላይ ሁለንተናዊ አደጋ በደቀነው የአገዛዙ ኃይል መካከል በሚደረግ ጦርነት ምክንያት በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የእልቂት እና የቀውስ ምዕራፍ ውስጥ እንገኛለን። ከሀገራዊ ቀውሱ ባሻገር ብልፅግና በጎረቤት ሀገራት የውስጥ ሰላም ላይ ጭምር በደቀነው አደጋ ምክንያት የቀይ ባህር ከባቢን ጨምሮ የቀጣናው መልክዓ ፖለቲካ በዘላቂ አለመረጋጋት ውስጥ እንዲገባ ሆኗል።
እንደ ሀገር ሙሉ ሉዓላዊነታችንን ለታዳጊ ኢምፔሪያሊስቶች በማከራዬት ኢትዮጵያን ተላላኪ መንግስት ያደረገው አረመኔያዊ አገዛዝ የሥልጣን ዕድሜውን ለማራዘም ብቻ የውስጥ ጦርነቶችን ከማፋፋም አልፎ፣ አደገኛ ቀጣናዊ ቀውሶችን እያወለደ አገሪቱን ወደማያባራ ቀጠናዊ ጦርነት በመምራት ወደ ጥልቁ ገደል ለመክተት እየተንደረደረ ይገኛል። ዘመኑ ባፈራቸው የቴክኖሎጂ መሣሪያዎች ሁሉ ንጹኃንን በድሮን መደብደብ፣ በታሪካዊ ከተሞችና በሃይማኖት ቦታዎች ላይ ከባድ መሣሪያ በመተኮስ፣ ኢትዮጵያዊያንን በማንነታቸው ማሳደድ፣ ማሰርና ማፈናቀል የአገዛዙ መገለጫዎች ከሆኑ ውለው አድረዋል።
አገዛዙ የኢትዮጵያንን ማንነት እና ወጥ ስልጣኔ ምልክት የሆነውን ዘመን መለወጫን ጊዜን ለመለወጥ በምክክር ኮሚሽን ስም አጀንዳ በማድረግ ከኢትዮጵያዊ ማንነታችን እና ከታሪካችን ጋር የተጋጨ መሆኑንም አሳይቶናል።
በተለይም በአማራ ህዝብ ላይ የተደቀነው ሁለንተናዊ የህልውና አደጋ ስሁት ትርክትን እና አጥፊ ፖሊሲዎችን እና ስልቶችን መነሻ ያደረገም ጭምር መሆኑ ይታወቃል።
የአማራ ህዝብ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር ያደረገውን ሰላማዊ ትግል እና የለውጥ ተስፋ እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ስልጣን ላይ የወጣው አገዛዝ የአማራን ሕዝብ ከምድረ-ገጽ ለማጥፋት ሁሉን አቀፍ ጦርነት እያደረገ ይገኛል። ለጨቋኞች ተንበርክኮ የማያውቀው የአማራ ሕዝብም የአገዛዙን የህልውና አደጋ ቀንበር ለመስበር በጽናት መራር ትግል እያደረገ ባለበት በዚህ ወቅት ዘርፈ ብዙ ድሎችንም ማስመዝገብ ችሏል።
የጠላትን ወረራ በመመከት የተደረጉት ወታደራዊ ተጋድሎዎች በጦረኝነት ለወረራ የመጣውን ሰራዊት የውጊያ አቅም እና ሞራል በተደጋጋሚ መስበር ችለዋል።
በዚህም የአማራ ህዝብ በመሪ ድርጅቱ አማካኝነት የገጠመውን የዘር ማጥፈት ጦርነት እየመከተ ይገኛል። ባለፈው አመት በተለያየ ቦታ የተገኘቱት የውጊያ ድሎች ባሻገር በተለይ በስልጠና ዘርፍ የታየው ሽህ ክንዶችን በአንዴ አሰልጥኖ ማስመረቅ የተቻለበት በመሆኑ በትግሉ ወቅት ትልቅ አቅም መጨመር ችሏል።
ከእነዚህ እና መሠል ድሎች ባሻገር 2018 አመት ምህረት በአማራ ህዝብ ትግል ወሳኝ ስትራቴጂካዊ ድሎችም ተመዝግበዋል።
፩. የአፋብን ውልደት
ትግሉ ባልተማከሉ አደረጃጀቶች ውስጥ መቆዬቱ የራሱ ታክቲካዊ ፋይዳ የነበረዉ ቢሆንም አቅምን የሚከፋፍል በመሆኑ የአደረጃጀት አንድነትን ማረጋገጥ ግዴታ ነበር።
የአማራ ህዝብም በታሪኩ እና በትግል ሂደቱ መራር በሆነ መንገድ የተረዳው ተጨባጭ እውነት ቢኖር አንድነት መተኪያ የለሽ ስትራቴጂካዊ አቅም መሆኑን ነው።
በአማራነት የመደራጀትና የመታገል ጉዳይ ግለሰባዊ እና ጠባብ ቡድናዊ ፍላጎትን፤ ትናንሽና መለስተኛ ቅራኔና ፀብን፥ ኩርፊያና ልዩነትን መተውና ለወል ፍላጎታችን መሰለፍን ይጠይቃል። ከትናንትም ሆነ ከዛሬ ነገሮቻችን መካከል መርጦ መዘንጋት እና ለይቶ ማንሳትን፣ ስለጋራ አማራዊ ፍላጎታችን በአንድ መስመር መሰለፍን ይጠይቃል።
ይህንን የማይታበል ሀቅ በመቀበል የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ምስረታን ማሳካታችን የአመቱ ዋነኛ ፖለቲካዊ ስኬት ነበር። በዚህ ውስጥ የትግሉ ስትራቴጂካዊ አቅሞችን በማሰባሰብ እና በአንድ ድርጅታዊ ማዕቀፍ ስር ህልውናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ትግል ውስጥ ሁሉም አቅሞች እንዲውሉ ለማድረግ መድላድሉን መፍጠር ተችሏል። ይህም የአመቱ ስኬት ብቻም ሳይሆን በቀጣይ ጊዜያት ለሚያደርጋቸው ትግሎች ወሳኝ ስትራቴጂካዊ አቅም ሆኖ የሚቀጥል ነው።
፪. የዓለምን ትኩረት የሳበው ተጋድሏችን
አፋብን ከምስረታው ማግስት በሁሉም ዕዞቹ ውስጥ ከትግሉ መነሻ ጀምሮ የነበረውን ህዝባዊ ድጋፍ የትግል ግለቱን ለማስቀጠል እንዲያስችል በሁሉም አካባቢዎች የተደረጉት ህዝባዊ መድረኮች ወሳኝ ህዝባዊ ንቅናቄ ፈጥረዋል። በነዚህ መድረኮች ህዝቡ በአጀንዳዎቹ ላይ የበለጠ ግልጸኝነት በመፍጠር፣ የትግሉን አላማ ለማሳካት ያለውን ቁርጠኝነት እና መነሳሳት ያሳየበት ነበር። በዚህም የአደረጃጀት አንድነቱን፣ ህዝባዊ ደጀኑን በአላማ በማስተሳሰር መሬት ላይ ይበልጥ መትከልና ማጽናት ተችሏል።
ከዚህ በተጨማሪ የአማራ ህዝብ የትግልን አላማዎች በሀገር ውስጥ ብሎም በአለምአቀፍ ማህበረሰብ ዘንድ፣ በተመሳሳይ በአንድ ድምጽ በስፋት ማሰማት ተችሏል። ለአማራ ህዝብ ጥሪ ለወትሮው ጆሮ ባለመስጠት የምስክርነት እና የትርጓሜ ግፍ ሲፈጸምበት ቢኖርም ዛሬ ግን በተለያዩ ሀገራት፣ በተለያዩ ቋንቋዎች አማራ ለራሱ እውነት መመስከር ብሎም ማስረዳት ችሏል።
በዚህም በአማራ ህዝብ ትግል ዙሪያ በተዛባ መልክ ተስፋፍተው የኖሩ ትርክቶችን ለማረም ጥቂት ዕድል ተገኝቷል። የአማራ ህዝብ መደመጥ በመቻሉም ህዝቡን ነጥሎ ለማጥቃት እና ለማስጠቃት ከዳግመ ጣሊያን ወረራ ጀምሮ የተተከሉ የጥላቻ ግምብ ለማፍረስ እና ጥርጣሬን አስወግዶ በህዝቦች መካከል መልካም ግንኙነት ለመፍጠር የሚያስችል ድልድይ እየተፈጠረም ይገኛል።
፫) የፖለቲካ ርዕደ መሬት የፈጠረው የትብብር ማዕቀፍ
ዘረ ፈጁን አገዛዝ በማስወገድ በፋሽስታዊ ዕሳቤ ተተክሎ የኖረውን የትውልዶች ጦርነት በህዝባዊ ትግላችን መቀልበስ እና ህልውናን በዘላቂነት ማረጋገጥ አንደኛው ተልዕኳችን ነው። አማራን ለማጥፋት የተነሳው ዘረ ፈጅ አገዛዝ ሌሎች ህዝቦችንም በጉልበት ጨፍልቆ ከመግዛት አልያም ከመጥፋት ውጭ ሌላ አማራጭ አላስቀመጠም። ለዚህም እንዲመቸው የህዝቦች የጎንዮሽ መልካም ግንኙነት እንዲበላሽ እና ቅራኔወች እንዲሰፉ በሙሉ አቅሙ እየሰራ ይገኛል።
ይሁንና እርስ በዕርስ እንዲተላለቁ የተደገሰላቸው ህዝቦች እና ብሔራዊ ሀይሎች የጥፋት ትርክት እና ሴራን አክሽፈው፣ ለህልውናቸው ሲሉ የጋራ ጠላትን በጋራ ለመታግል መግባባታቸዉን የሚያውጁበት የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሰዋል።
በየትኛውም የዓለም ማዕዘን ተከስተው የነበሩ ፀረ-ህዝብ አገዞች የተገረሰሱት የጋራ እጣ ፋንታን በሚጋሩ ፀረ ጭቆና የትግል ኃይሎች ነው። ይህ መሠረታዊ እውነት ህዝባዊ አላማን አንግበው በሚታገሉ ብሔራዊ ሕዝባዊ ኃይሎች መካከል ያሉትን ልዩነቶች ተቀራርበው እንዲሰሩ አስችሏል። በእርግጥም እንኳንስ የሁሉም ህዝቦች ብሎም ሀገር የህልውና አደጋ ውስጥ ወድቀው አይደለም፤ የአንድ ማህበረሰብ የህልውና አደጋ ብቻዉን ህዝባዊ ኃይሎች እንዲተባበሩ የሚያስገድድ በቂ ምክንያት ነው። | 486 |
| 11 | لا يوجد نص... | 491 |
| 12 | በተዋረድ ላለው ለሁሉም የትግሉ አመራሮች ከመሪያችን የተላለፈ መልዕክት ነው።👇
እንኳን አደረሳችሁ ጓዶች!!
መጭው 2019 ዓም እጣፋንታችን የተቋጠረበት ልዩ አመት ነው። እንበርታ። ያልተሞከረ ሞክረናል፥ የማይታሰብ የሚመስል ነገር አስበን፥ የማይታለም አልመን አሳክተናል። በፈጣሪ እገዛና በመስዋእትነታችን "ተአምር" ሰርተናል። አሁን ሁሉም ነገር ወደ መቋጫውና ወደ መለያው ምእራፍ ደርሷል። የበለጠ ጥርሳችን መንከስና ወገባችን ማሰር ነው የሚጠበቅብን።
እኛ የዚህ መከረኛህዝብ ውድ ልጆች ነን። ባለ ውድ አላማ ነን። ለዚህ ውድ አላማ ብዙ ውድ ህይወቶች ተከፍለዋል። በየቀኑ እየተከፈሉም ነው። የአንድ ትግል ብቻ ሳይሆን የአንድ ዘመን እጣፋንታ መዳፋችን ላይ ነው ያለው። ከባድና ጥንቃቄ የሚፈልግ ተልእኮ ነው። ብዙ ቀደምቶቻችን አዳልጦ ከጣለው የተንኮልና የመጠላለፍ መንገድ በብዙ ሽህ ክንድ መራቅ አለብን። ክፋት፥ ቅናትና ጠማማነት ውሎ አድሮ ባለቤቱንም የሚገድሉ አደገኛ "ኡቃቢዎች" ነው።
ሰሞኑን አንድ አሜሪካው የጥቁሮች መብት ተሟጋች እሱ ስለወከለው ማህበረሰብ ሲያወራ እየሰማሁት ነበር። የሰማሁትን በግርድፉ ወደ አማረኛ ብመልሰው "እርስበርስ በምንጠላላው ልክ ጠላቶቻችን አንጠላም፥ ጭቆናን፥በደልን፥ ዘርማጥፋትን ጭምር ከምንጠላው በላይ እርስበርስ እንጠላላለን። የሚያሳዝነው ይህ ራስጠል ቅጥቅጥ ስነልቦና በእራሱ ያለፉት በደሎች ውጤት መሆኑ ነው" ይላል። ይህን እንገንዘብ። እንዋደድ። አሁን የሚታዩትና እያደጉ የመጡት የመቀራረብና ጓዳዊነት መንፈሶች በእንክብካቤ ማደግ አለባቸው። በሞት መካከል በኩራትና በስኬት የሚያራምደን ወንድማማችነትና ፍቅር ነው። እና መጭውን አመት በፍቅር ታጅበን፥ በትግላችን ምኞታችን የምናሳካበት እንዲሆን እመኛለሁ::
በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ፥ መልካም አዲስ አመት! | 470 |
| 13 | لا يوجد نص... | 425 |
| 14 | ለመላው የፋኖ ሰራዊት አባላት፣ ለጀግናው የአማራ ህዝብ እንዲሁም ለመላው ኢትዮጵያውያን በሙሉ፤
እንኳን ለአዲሱ አመት የዘመን መለወጫ በዓል በፅናት አደረሳችሁ! አዲሱ ዓመት የትግላችን ፍሬ የሚታይበት፣ የነፃነት፣ የአንድነትና የሙሉ ድል ዘመን እንዲሆንላችሁ ከልብ እመኛለሁ።
አሮጌውን 2018 ዓ.ም ቆም ብለን ስናስታውስ፣ እጅግ ፈታኝ ውጣ ውረዶችን እና አንፀባራቂ ድሎችን አቅፎ ያለፈ ሆኖ እናገኘዋለን። በተለይም የአማራ ህዝብ የህልውና ትግሉን በተደራጀ መንገድ የሚመራበት ጠንካራ አታጋይ ተቋም እንዳይኖረው፣ እንዲሁም ኃይላችን የተበታተነ ሆኖ እንዲቀር ያልተሸረበብን ሴራ አልነበረም። ትግላችንን ለማኮላሸት ጠላት ብዙ ርቀት ተጉዟል፤ ውስብስብ የሆኑ ተግዳሮቶችንም ደቅኖብናል። ነገር ግን ከነዚህ ሁሉ ፈተናዎች ባሻገር፣ ሴራዎችን ሁሉ በጣጥሰን አፋብን የተሰኘውን ተቋማችንን መመስረታችን እና በአንድ ጠንካራ አታጋይ ተቋም ስር መሰባሰባችን የዓመቱ ትልቁ ታሪካዊ ስኬታችን ነው።
በጀግናው የፋኖ ሰራዊት እና በቆራጡ ህዝባችን ያላሰለሰ ተጋድሎ፣ በህዝባችን ላይ መከራን የጫነው አገዛዝ ዛሬ ላይ የሞት አፋፍ ላይ ይገኛል። አሁን ያለንበት ጊዜ ትግላችን የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ የደረሰበት ወሳኝ ወቅት ነው።
"አገዛዙ የሞት አፋፍ ላይ ባለበት በዚህ የመጨረሻ ምዕራፍ፣ ከምንጊዜውም በላይ ፅናት እና የማይበገር አንድነት ያስፈልገናል።"
ይህን በሞት አፋፍ ያለ አገዛዝ ወደ መቃብር አውርደን የህዝባችንን ነፃነት፣ ክብር እና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ የጀመርነው ትግል ከግብ መድረስ አለበት። ለዚህ ደግሞ አንድነታችንን እንደ ዐይናችን ብሌን ጠብቀን፣ በፅናት ተደጋግፈን እስከ መጨረሻው ጠብታ መታገል ይኖርብናል። አዲሱ ዓመት የፈተና ሳይሆን የሙሉ ድል ዓመት እንደሚሆን ጽኑ እምነቴ ነው!
መልካም አዲስ ዓመት!
ድል ለህዝባችን!
አርበኛ ሀብቴ ወልዴ
የአፋብን ም/ሊቀመንበር ለወታደራዊ ጉዳዮች መምሪያ ሃላፊ | 441 |
| 15 | لا يوجد نص... | 431 |
| 16 | በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ፤ ምድረ በዳውም ስብል ይጠግባል። መዝሙር ፷፬፤ ፲፩
የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው 5ኛ ዕዝ የሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር ለ2018 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓል ያስ አስተላለፈው መልዕክት!!
ውድ የክፍለ ጦራችን አባላት፣ የመላው አማራ ህዝብ እና ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን፦
ተፈጥሮ በክረምቱ ዝናብ ታጥባ፣ ምድር በአደይ አበባ አምቃ፣ ብርሃንና ተስፋን ሰንቃ በምትቀበለው በዚህ የ2019 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓል (እንቁጣጣሽ) እንኳን አደረሳችሁ!
እንቁጣጣሽ የጥንታውያን አባቶቻችንና እናቶቻችን ውብ ባህላዊና ሃይማኖታዊ እሴት፣ የህብረታችንና የመታደሳችን ማሳያ ልዩ መለያችን ነው። “መስከረም ሲጠባ አደይ ሲፈነዳ እንደሚባለው፣ ወንዞች ጎድለው ምድር በሚያብብበት በዚህ ወቅት፣ ህዝባችን ከባዕድ እስከ ዘመድ በፍቅርና በሰላም የሚጠያየቅበት የቃል ኪዳን ጊዜ ነው። ይህ አዲስ ዓመት ለአማራ ህዝብ የጽናት፣ የአንድነትና አዲስ ተስፋ የሚበሰርበት ወቅት ነው፤
አዲስ መንፈስና ራዕይ፦ ሰራዊታችን በተቀደሰ ዓላማ የታጀበ አሸናፊነትን ለመጎናጸፍ በቁርጠኝነት የተነሳበት ነው።
መጪው ዘመን የታቀዱ ህልሞቻችንና የትግል ግቦቻችን በድል አድራጊነት የሚያበቁበት፣የህዝባችን ነፃነትና ደህንነት የሚረጋገጥበት ይሆናል። የሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር ለሁሉም የአመራር አካላት፣ ለውድ ታጋዮቻችን፣ በየደረጃው ለሚገኘው ሰራዊታችን፣ ለመላው የአማራ ህዝብና ደጋፊዎቻችን እንኳን አደረሳችሁ ይላል።አዲሱ ዓመት የድል፣ የአንድነት፣ የሰላምና የተድላ ዘመን ይሁንልን!
በእልህ አስጨራሹ ትግል ለህዝብና ለሀገር ሲሉ ህይወታቸውን የገበሩ ሰማዕታት ጓዶቻችንንና ንጹሃን ዜጎቻችንን ነፍስ ፈጣሪ በደጋግ አባቶቻችን አብርሃም፣ ይስሐቅና ያዕቆብ አቅፍ ያኑርልን።
መልካም አዲስ ዓመት!
ክብር እና ሞገስ ለተሰዉ ሰማዕታት!
ድል ለአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ!
የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው 5ኛ የሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር ቃል አቀባይ ዝናው በቀለ!! | 477 |
| 17 | لا يوجد نص... | 513 |
| 18 | በመረሐቤቴ አውራጃ ሰፊ ሕዝባዊ መድረኮች እና የአደረጃጀት ሥራዎች መካሔዳቸውን ተገለፀ!!
ጳጉሜ 05/2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መረሐቤቴ አውራጃ በሚገኘው ሞረትና ጅሩ ወረዳ ሰፊ ሕዝባዊ መድረኮች እና የአደረጃጀት ሥራዎች በተሳካ ሁኔታ መካሄዳቸውን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ መርሀ-ቤቴ ስምሪት ቡድን አስታወቀ።
በመድረኮቹ ወቅት መሠረቱ ሕዝብ የሆነው የፋኖ ፖለቲካዊ ትጥቅ ትግል ከማህበረሰቡ ጋር በየዕለቱ በመወያየት ላይ ሲገኝ፣ በቀበሌዎች አዳዲስ ድርጅታዊ አሠራሮችንና መዋቅሮችን የማስፋፋት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ገለፁ።
የአገዛዙን ፀረ-አማራነት ጉዞ በመመከት፣ በፋኖ አሠራርና መርህ መሠረት ማህበረሰቡን በክላስተርና በአውራጃ ደረጃ በማደራጀት ወደ አንድ የተቀናጀ አደረጃጀት የማምጣት ሥራ በቋሚነት እየተሠራበት እደሚገኝ አክለው ገልፀዋል።
በሞረትና ጅሩ ወረዳ ከተከናወኑ ሰፊ የሕዝባዊ መድረክ እና የአደረጃጀት ሥራዎች መካከል የ"አብዲናጎ ክላስተር "እና "የውሎ ክላስተር" በርካታ ቀበሌዎችን በማቀናጀት አደረጃጀቶች የተዘረጉ ሲሆን፣ ከሕልውና ትግሉ ጎን ለጎን የሕዝቡን የመልካም አስተዳደር ችግሮች በሲቪል አስተዳደሩ በኩል በተሳካ መልኩ እዲፈቱ የሚያስችል ተሠርቷል ብለዋል።
በተካሄዱት ሕዝባዊ መድረኮች በየደረጃው ያሉ የድርጅቱ አመራሮች፣ በተለይም የዕዝና የኮር አመራሮች የተገኙ ሲሆን፣ አመራሮቹ ከማህበረሰቡ ለተነሱ አስተያየቶችና ጥያቄዎች አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት፤ ከወቅታዊ ሁኔታዎች አኳያ ሰፊ ዝርዝር ጉዳዮች ላይ በመወያየት ቀጣይ የትግል አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።
በዚህም መሠረት አባት አርበኞች በአደረጃጀታቸው፣ ወጣቶች ደግሞ ወደ ስልጠና ማዕከላት እየገቡ በመሰልጠን የብልፅግናን አገዛዝ በጋራ ሊታገሉ እንደሚገባ መግባባት በመድረኩ የተሳተፉት የመላው ማህበረሰብ አባላት በትግሉና በአፋብን ሁሉን አቀፍ ውሳኔዎች መደሰታቸውን ገልጸዋል።
በመጨረሻም የዕዙ የስምሪት ቡድን፣ የአማራ ሕዝብ የትግሉ ዋና ባለቤት በመሆኑ በሚችለው አቅም ሁሉ በቁርጠኝነት አስተማማኝ ደጀን ሆኖ ሊታገል እንደሚገባ በመጠቆም መድረኮቹ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቃቸውን አሳውቋል።
" ክብር ለተሰውት ሰማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!! | 577 |
| 19 | لا يوجد نص... | 556 |
| 20 | እንኳን ለ2019 አዲስ ዓመት በሰላም፣ በጤና እና በህይወት አደረሳችሁ!!
ውድና የተከበራችሁ የፍኖተ አማራ ሚዲያ ቤተሰቦች፣ የጽናት አርማ የሆናችሁ ተከታታዮቻችን እና መላው የአማራ ህዝብ፤
ከፈተናዎች ማዕበል፣ ከመከራው እሳት እና ከጽናቱ መንገድ ተገናኝተን እንኳን ለ2019 አዲስ ዓመት በሰላም፣ በጤና እና በህይወት አደረሳችሁ! ይህ አመት የብርሃን፣ የጽናት እና የድል ዘመን ይሁንላችሁ ይሁንልን!
ያለፈው ስምንት ዓመታት ህዝባችን በአቢይ አሕመድ አረመኔያዊ ሥርዓት የሚፈጸምበትን ግፍ፣ ጭፍጨፋ እና መከራ በጽናት የታገለበት እየታገልንበት ያል የደምና የእንባ ዘመን ሆኖ የተመዘገበ መሆኑ አለም ህዝብ ጥቁሩም ነጩም የሚያዉቀዉ ሃቅ ነዉ። ሆኖም በእዚያ ሁሉ የሥርዓቱ የጨካኝነትና የግፍ ማዕበል ውስጥ የአማራ ህዝብ በግፍ እየተገደለም ቤሆን በአብይ አህመድ ስርዓት አልተንበረከከም! የአማራ ልጅ ፋኖ እምቢተኝነትና የብረት ጽናት፣ የትኛውም አረመኔያዊ ኃይል የህዝባችንን ክብርና ህልውና ማንበርከክ እንደማይችል ለአለም አሳይተዋል እሰከ ነፃነትም ይህ የአባቶቻችን ጀግንነት ተላብሶ ትግላችን ይቀጥላል።
ይህ አዲሱ 2019 ዓመት፦ የህልውና እና የሉዓላዊነት ዘመን የአብይ አህመድ አረመኔያዊ ስርዓት በህዝባችን ላይ የጫነው የወረራና የግፍ ወይን አብቅቶ፣ የወደቀው ክብራችን የሚመለስበትና ህልውናችን የሚረጋገጥበት፤የአማራ ልጅ ፋኖ ፍትሃዊ ትግል ፍፃሜ ለዉዱ ህዝባችን ነፃ የሚያወጣበት ነው።
አረመኔውን የአብይ አህመድ ሥርዓት ለመመከት በየበረሃውና በየተራራው የሚፋለመው የአማራ ልጅ ፋኖ መስዋዕትነት ፍሬ አፍርቶ ታሪካዊውን የድል ማክተሚያ የሚያበስርበት፤የፍትህና የመልሶ ማቋቋም ዘመን፦ በስርዓቱ የግፍ ፖሊሲ ምክንያት በየካምፑ የሚሰቃዩ ወገኖቻችን በክብር ወደ ቀያቸው የሚመለሱበት እና ንጹሃን ከእስር ነፃ የሚወጡበት፤ የብርሃንና የእውነት መድረክ እነደሚሆን አንጠራጠርም ሚዲያችን «ፍኖተ አማራ» የአረመኔውን ስርዓት በደልና ጭካኔ በማጋለጥ፣ የህዝባችንን እውነተኛ ድምፅ በማስተጋባት እና የድሉን የምስራች በኩራት የሚያበስርበት፤እንዲሆንልን በፍኖተ አማራ ሚዲያ ስም ከልብ እንመኛለን!
ጨለማው ይገፈፋል፤ የአረመኔዎች ስርዓት ያበቃል፤ የታገለው ህዝባችን በእርግጥ ያሸንፋል! ፍኖተ አማራ ሚዲያ (Finote Amhara Media) ቴሌግራም / ሶሻል ሚዲያ፦https://t.me/httpsuYkZrGfSZrNjNjFk
ከከበር ሰላምታ ጋር
Finote Amhara Media
መልካም አዲስ ዓመት 2019 | 657 |
