በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የኢ-ለርኒንግ አውደ ጥናት ተካሄደ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ስኮላርስ ፕሮግራም አዘጋጅነት «Transforming Teaching and Learning through Digital Technology at the University of Gondar: Experiences, Innovation, Challenges and Opportunities» በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው የኢ-ለርኒንግ አውደ ጥናት ነሀሴ 21/2018 ዓ.ም በዘርዓያቆብ አዳራሽ ተካሂዷል።
በዚህ አውደ ጥናት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር የቻለ ከበደን ጨምሮ፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ ዲኖች፣ ዳይሬክተሮች፣ በአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ በኦንላይን ትምህርታችውን እየተከታትሉ የሚገኙ 36 የጎንደር ዩኒቨርሲቲ መምህራን፣ ተማሪዎችና የቀደሞው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፕ/ር መንገሻ አድማሱ ተገኝተዋል፡፡
አውደ ጥናቱ ቀደም ሲል በዲጂታል ቴክኖሎጂ፣ በአካቶ ትምህርት እና በሰውሰራሽ አስተውሎት ዙሪያ የተሰጡ ስልጠናዎችን እንዲሁም የተዘረጉ መሰረተ ልማቶችን በመጠቀም የመማር ማስተማር ሂደቱን ትራንስፎርም ለማድረግ ያለመ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም በተናጠል ይከናወኑ የነበሩ አሰራሮችን ወደ አንድ በማምጣትና የተቀናጀ ተቋማዊ መልክ በመስጠት፣ በተለያዩ ምክንያቶች በአካል ተገኝተው መማር ለማይችሉ የማህበረሰብ ክፍሎች ትምህርትን አካታች በሆነ መልኩ በኦንላይን ተደራሽ ማድረግ የአውደ ጥናቱ ዋና አላማው መሆኑን በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ስኮላርስ ፕሮግራም ዳይሬክተር ዶ/ር ሞላልኝ በላይ ተናግረዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የዩኒቨርሲቲው አይሲቲ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ተስፋሁን መለሰ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ያሉ የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶችን በተመለከተ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን፤ የኢ-ለርኒንግ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አበበ አለሙ በበኩላቸው በዩኒቨርሲቲው ከኢለርኒግ ጋር በተያያዘ እየተሰሩ ያሉ ሰራዎቸን በተለይ ደግሞ በትምህርት ሚኒስቴር የተዘረጋውን የ eSHE (eLearning to Strengthen Higher Education) ፕሮጀክት አፈጻጸምን በተመለከተ ገለጻ አድርገዋል።
በአውደ ጥናቱ ላይበኢ-ለርኒንግ ዘርፍ የተመዘገቡ አበይት ውጤቶችና የተቀሰሙ ልምዶች፣ መምህራንና ተማሪዎች ከበይነ-መረብና ቅይጥ (Blended) ትምህርት ለመሸሽ የሚያቀርቧቸው ምክንያቶችና የመፍትሔ አቅጣጫዎች፣ የዲጂታል ምዘናንና የአካዳሚክ አስተዳደርን አቅም በሙድል ማጠናከር፣በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ኮርሶችን ቀላቅሎ በመስጠት ሂደት ያጋጠሙ እንቅፋቶችና መፍትሔዎቻቸው ላይ የጥናትና የልምድ ልውውጥ ጽሁፎች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር የቻለ ከበደ ዲጂታል ቴክኖሎጂ ለዩኒቨርሲቲው በሁለት ዋና ዋና መንገዶች ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸዋል። የሀገራችን ሁለንተናዊ እድገት በቴክኖሎጂ የተደገፈ እንዲሆን እየተደረገ ያለውን ጥረት ለመደገፍ እና ዩኒቨርሲቲውን በ የኢ-ለርኒንግ የተሻለ ቦታ ላይ በማድረስ ተደራሽ እና አካታች የመማር ማስተማር ከባቢን ለመፍጠር ዕድል ይሰጣል ብለዋል።
በመጨረሻም አመራርን፣ ፖሊሲን፣ መሰረተ ልማትንና ዲፓርትመንቶችን ያካተተ ጠንካራ ዲጂታላይዜሽን ኢኮ-ሲስተም በመገንባት፣ የትምህርት ጥራቱን የጠበቀ አሰራር በመዘርጋት የዩኒቨርሲቲውን ራእይ ማሳካትና ለሀገሪቱ የዲጂታል 2030 ስኬት የጎላ አስተዋጽኦ ማበርከት እንደሚገባ ተመላክቷል።
ለልህቀት እንተጋለን!
የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ
ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
eLearning Workshop Held at the University of Gondar
The Mastercard Foundation Scholars Program at the University of Gondar hosted an e-learning workshop under the theme “Transforming Teaching and Learning through Digital Technology at the University of Gondar: Experiences, Innovation, Challenges and Opportunities” on August 27, 2026 at the Zerayakob Hall.
The workshop was attended by the President of the University of Gondar, Dr. Yechale Kebede, vice presidents, deans, directors, academic staff members currently pursuing online studies at Arizona State University, students, and former University of Gondar President Professor Mengesha Admasu.
The workshop aimed to transform the teaching and learning process by building on previous trainings provided in digital technology, inclusive education, and artificial intelligence, as well as the digital infrastructure that has been established. It also sought to bring together initiatives that had previously been implemented separately and provide them with an integrated institutional framework. The main objective was to make education more inclusive and accessible for members of the community who are unable to attend in-person classes for various reasons.
In his remarks, Dr. Molalign Belay, Co-Director of the Mastercard Foundation Scholars Program at the University of Gondar, emphasized the importance of creating an integrated approach to e-learning and expanding access to education through digital platforms.
During the program, Dr. Tesfahun Melese, Director of the University’s ICT Directorate, provided an overview of the technological infrastructure available at the University of Gondar. Mr. Abebe Alemu, Director of the E-Learning Directorate, also presented an update on the University’s ongoing e-learning activities, with particular emphasis on the implementation of the eSHE (eLearning to Strengthen Higher Education) project launched by the Ministry of Education.