cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

Ethiopian Press Agency/አማርኛ /

Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
23 673
المشتركون
+1424 ساعات
+727 أيام
+34030 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

በኮሪደር ልማቱ በአራት ኪሎና ፒያሳ የተጠናቀቁና ለህዝብ ክፍት የሆኑ መንገዶች‼️ 👉 ከአራት ኪሎ ራስ መኮንን ድልድይ፣ 👉 ከደጎ አደባባይ በቀይባህር አብርሆት ቤተ መፃህፍት፣ 👉 ከማህሙድ- በቴድሮስ አደባባይ ወዳጅንት አደባባይ፣ ሰኔ 3 ቀን 2016 ዓም
إظهار الكل...
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሐመድ በክልሉ የተከናወኑ የመሠረተ ልማት ስራዎችን አሰመልክተው ለኢፕድ በሰጡት ማብራሪያ ካነሷቸው ዋና ዋና ሀሳቦች‼️ 👉ከ2ሺ ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ከ17 በላይ የአስፋልት መንገዶችን መገንባት ተችሏል፣ 👉 በጂግጂጋ፣ በደጋሃቡር፣ በቀብሪደሃርና በጎዴ የውስጥ ለውስጥ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ተከናውኗል፣ 👉በጂግጂጋ የነበረው መንገድ ዘጠኝ ኪሎ ሜትር ያልበለጠ ነበር፣ በአሁኑ ጊዜ ወደ 40 ኪሎ ሜትር ተሠርቷል፣ 👉 ጎዴ እስከ 16 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ተሠርቶ ግማሹ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል፤ 👉 በቀብሪደሃርና ደጋሃቡርም ከ5 እስከ 6 ኪሎ ሜትር በላይ መንገድ ተሠርቷል፣ 👉 እስከ 2ሺ 200 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ ተሠርቷል፤ 👉 ከ70 እስከ 80 በመቶ የጠጠር መንገዶች አልቀው አገልግሎት እየሠጡ ይገኛሉ፣ 👉 የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ሽፋን የገጠሩም የከተማውም በአማካይ 47 በመቶ ማሳደግ ተችሏል፣ 👉 ከ309 በላይ የጥልቅና መካከለኛ ጉድጓዶች ቁፋሮ ተከናውኗል፤ 15 መለስተኛ የውሃ ጋኖች ተሠርተዋል፤ 👉 አሁን በጎዴና በጂግጂጋ እየተጠናቀቁ ያሉ የእናቶችና ሕጻናት ሆስፒታሎችን ጨምሮ 12 ተጠናቀው ወደ ሥራ ገብተዋል፣ 👉 ከ576 በላይ የ1ኛ ደረጃ፣ ከ90 በላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፤ 12 የአዳሪ ትምህርት ቤቶች ተሠርተዋል፣ 👉 የአዳሪ ትምህርት ቤቶቹ ገና ወደ አገልግሎት አልገቡም፤ አምስቱ በዘንድሮው ዓመት ሥራቸውን ይጀምራሉ፣ 👉 በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በአንድ ክፍል እስከ 107 ተማሪዎች ይማሩ ነበር፣ 👉 በተሠሩት አዳዲስ የመማሪያ ክፍሎች በአንድ ክፍል ውሰጥ የተማሪዎች ምጣኔ ወደ 70 ማውረድ ተችሏል፣ 👉 በክልሉ ወደ 20 የሚሆኑ ወረዳዎች የ24 ሰዓት መብራት አግኝተዋል፣ 👉 ከለውጡ በፊት ክልላችን ወደ 85 የሚደርሱ አነስተኛ፣ መካከለኛ እና ከፍተኛ ፋብሪካዎች ብቻ ነበሩ፣ 👉 በአሁኑ ሰዓት በአጠቃላይ ከ318 በላይ ፋብሪካዎች በሥራ ላይ ይገኛሉ፣ ርዕሰ መስተዳድሩ ከኢፕድ ጋር ያደረጉትን ቆይታ ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129495
إظهار الكل...

Photo unavailableShow in Telegram
በበጀት ዓመቱ 11 ወራት ወደ ውጪ ከተላከ የቡና ምርት ከፍተኛ ውጤት ተመዘገበ ****** (ኢ ፕ ድ) በ2016 በጀት ዓመት 11 ወራት ወደ ውጪ ከተላከ የቡና ምርት ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ። በግንቦት ወር በተላከ የቡና ምርት በወራት ሲታይ በመጠንም ሆነ በገቢ ከፍተኛ ውጤት የተገኘበት መሆኑ ተገልጿል። በግንቦት ወር ብቻ 43 ሺህ 481 ቡና በመላክ ከእቅዷ 105 በመቶ ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል። ከገቢም አንጻር በወሩ ብቻ 209 ነጥብ 54 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ማሳካቷን መቻሉንም ባለሥልጣኑ ገልጿል። በበጀት ዓመቱ 11 ወራት 252 ሺህ 466 ነጥብ 98 ቶን የቡና ምርት በመላክ 1 ቢሊዮን 208 ሚሊዮን 73ሺህ የአሜሪካን ዶላር በማግኘት ከፍተኛ ውጤት የማምጣት ግስጋሴው መቀጠሉን የቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል። ሰኔ 03 ቀን 2016 ዓ.ም
إظهار الكل...
01:44
Video unavailableShow in Telegram
#ውብ_አዲስ አራዳ፤ አዲስ ጽጌሬዳ‼️
إظهار الكل...
29.48 MB
በአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት የውበትና አረንጓዴ ልማት ሥራዎች‼️ 👉 በመልሶ ልማት መልክ እየለሙ ያሉ የአረንጓዴ ቦታዎችና የህዝብ መዝናኛ ስፍራዎች በቁጥር 11 👉 20 የህዝብ መፀዳጃ ቤቶች 👉ከራስ መኮንን እስከ ባሻ ወልዴ ኮንዶሚኒየም የሚደርስ ከወዳጅነት ፓርክ ጋር የሚገናኝ የአረንጓዴ ቦታዎች ልማት፤ ✍️ 4 ትላልቅ ፕላዛዎችና የዕይታ ሥፍራዎች፤ 40 የሕዝብ መገልገያ ሱቆች፣ ✍️ 8 የሕዝብ መፀዳጃ ቤቶች፤ 6 ካፌና ሬስቶራንቶች፣ ✍️ የእግር መንገድ፣ 5 ኪሎ ሜትር የሳይክልና 5 ኪሎ ሜትር የመሮጫ መስመሮች 👉ቴዎድሮስ አደባባይ ዋፋ ሲኒማ ፐላዛ፤ ✍️ የህፃናት መጫወቻ ስፍራ፣ የኤሌክተሪክ መኪና ቻርጅ ማድረጊያ፣ለመዝናኛ የሚሆን አኳሪየም፣ ✍️ የሳይክል ኪራይ አገልግሎት መስጫ፣ የመሰብሰቢያና የውጭ ቲያትር መመልከቻ ሥፍራ፣ ✍️ የተለያዩ መቀመጫዎች፣የካፌና ፋስት ፉድ አገልግሎት መስጫ ቦታዎች እንዲኖሩት ታስቦ የተጀመረ 👉 ዕድሳት ስራዎች፤ 102 ህንፃዎች መካከል 92 ዕድሳት የተጠባቀቀ፤ በአርኬድ የታለፈ ህንፃ 25፣ ሰኔ 3 ቀን 2016 ዓም
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
አስተዳደሩ ለአረንጓዴ ዐሻራ ከአምስት ሚሊዮን በላይ ችግኞች አዘጋጀ ****** (ኢ ፕ ድ) ለዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ከ5 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ለመትከል መዘጋጅቱን በኦሮሚያ ክልል የማያ ከተማ አስተዳደር ገለጸ። የማያ ከተማ ከንቲባ ዶክተር ኢፍረሃ ወዘር ለኢትዮጵያ ፕሬስ ኤጀንሲ እንደገለጹት፤ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ለምስራቁ የሀገራችን ክፍል በተለይም ለከተማዋ ያለውን ከፍተኛ ጥቅም በመረዳት በየዓመቱ በሚሊዮች የሚቆጠር ችግኞችን እየተተከሉ፣ ክትትልና እና እንክብካቤ እየተደረገባቸው ይገኛል። ለአብነትም በባለፈው ዓመት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ወቅት የከተማው አስተዳደር እና ማህበረሰብ መንግሥት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ከ4 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ችግኝ መተከሉን አውስተው፤ ከተከላ በኋላ በተሠራው የመንከባከብ እና የመጠበቅ ሥራ ከ82 በመቶ በላይ ችግኞች መጸደቃቸውን....... ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129647
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
76 አዳዲስ የገጠር ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ሆነዋል ****** (ኢ ፕ ድ) ባለፉት 10 ወራት በኢትዮጵያ 76 አዳዲስ የገጠር ከተሞችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ እንደተቻለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ። የተቋሙ የአገልግሎት ታሪፍ ወጪን መሠረት ያደረገ አለመሆኑ አገልግሎቶችን ለማስፋፋት እንቅፋት መፍጠሩ ተጠቁሟል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ መላኩ ታዬ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ ባለፉት አስር ወራት የኤሌክትሪክ አቅርቦት ተደራሽነትን ለማስፋት የተለያዩ ሥራዎች ተሠርተዋል። በዚህም 76 አዳዲስ የገጠር ከተሞችንና መንደሮችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። አቶ መላኩ ባለፉት አስር ወራት ከ328 ሺህ በላይ አዲስ ደንበኞች ኃይል እንዲያገኙ መደረጉን ጠቁመው፤ ከነዚህም ውስጥ 31 ሺዎቹ በሚያዚያ ወር አገልግሎቱን........ ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129645
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
በክልሉ ከበጋ መስኖ ልማት 31 ነጥብ አምስት ሚሊዮን ኩንታል ምርት ተገኘ ****** (ኢ ፕ ድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በበጋ መስኖ ልማት 31 ነጥብ አምስት ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። በበጋ መስኖ ልማት ሥራው ከ33 ሺህ በላይ ዜጎች የሥራ እድል እንደተፈጠረላቸው ተመላክቷል። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የግብርናና ገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር ለኢፕድ እንደገለጹት፤ ገበያው የሚፈልገውን እና ክልሉ ባለው የመሬትና የውሃ አቅም ልክ የበጋ መስኖ ልማት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ሲሠራ ቆይቷል። በበጋ መስኖ ልማት 147 ሺህ ሄክታር መሬት በማልማት 33 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማምረት ታቅዶ፤ 147 ሺህ 500 ሄክታር መሬትን በማልማት 31 ነጥብ አምስት ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን አስታውቀዋል። በበጋ መስኖ ልማት ከለማው 147 ሺህ 500 ሄክታር መሬት ውስጥ ሁለት ሺህ 600 ሄክታር መሬትን በበጋ ስንዴ በማልማት ከ100 ሺህ ኩንታል በላይ የስንዴ ምርት...... ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129651
إظهار الكل...