EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)
- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
جاري تحميل البيانات...
አፍሪካ እና አውሮፓ በባቡር ትራንስፖርት ሊገናኙ ነው *********************** ለ2030ው የዓለም ዋንጫ አፍሪካ እና አውሮፓ በባቡር ትራንስፖርት ሊገናኙ መሆኑ ተገለጸ። በስፔን ፖርቹጋል እና ሞሮኮ አስተናጋጅነት እንደሚካሄድ በሚጠበቀው የ2030ው ዓለም ዋንጫ አፍሪካ እና አውሮፓ በባቡር ትራንስፖርት...
የትግራይ ክልል ክለቦች ከ2017 ጀምሮ ከጦርነቱ በፊት ወደነበሩበት ሊግ ተመልሰው እንዲወዳደሩ ውሳኔ ተላለፈ ******************** የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ባደረገው መደበኛ ስብሰባ፥ የትግራይ ክልል ክለቦች ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ ለሙሉ ከጦርነቱ በፊት ሲወዳደሩበት...
በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት መጋቢት 24 ቀን የጸደቀው የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥርና አስተዳደር አዋጅ መጽደቁን ተከትሎ ለተግባራዊነቱ እየተሰራ መሆኑን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ገለጸ። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ከኢቲቪ 57 ጋር በነበራቸው ቆይታ፥ የዜጎችን መሰረታዊ የመኖሪያ ቤት ችግር ዘላቂ በሆነ መልኩ ለመፍታት በተጠናከረ መልኩ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። ነገር ግን ዜጎች ከገጠር ወደ ከተማ የሚያደርጉት ፍልሰት ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ የመኖሪያ ቤት ፍላጎትም ጨምሯል ብለዋል። የመኖሪያ ቤት አቅርቦት ችግርን በዘላቂነት ለመፍታት 80 በመቶውን የግሉ ዘርፍ፣ 20 በመቶውን ደግሞ መንግሥት እንዲያለማ ስትራቴጂ ተቀምጦ እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት። የመኖሪያ ቤት ግንባታ ክፍተቱን ለመድፈን በመንግሥትና በግል አጋርነት በቅንጅት እየተከናወነ ያለው ስራም ውጤታማ እየሆነ ነው ብለዋል። በየትኛውም ሃብታም አገር ሁሉንም ሰው የመኖሪያ ቤት ባለቤት ማድረግ አይቻልም የሚሉት ሚኒስትሯ፤ ዜጎች በአቅማቸው የተረጋጋ ኑሮ እንዲኖሩ ለማስቻል የኪራይ ቤቶችን በአማራጭነት ለማቅረብ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል። በአደጉ አገራት ሰራተኞች ከደመወዛቸው ከ20 እስካ 30 በመቶ ለቤት ኪራይ ወጪ የሚያደርጉበት ልምድ ተወስዷል ያሉት ወ/ሮ ጫልቱ፤ እንደኛ ባሉ አገራት ደግሞ ሰራተኛው ሙሉ ደመወዙን ለቤት ኪራይ ወጪ ሊያደርግ እንደሚችል አንስተዋል። ይህ ችግር በሰራተኛው ህይወት ላይ ማህበራዊ ቀውስ እየፈጠረ በመሆኑ የመንግስት ጣልቃ ገብነት አስፈላጊ ሆኗል ነው ያሉት ሚኒስትሯ። የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥርና አስተዳደር አዋጁ በአከራይም ሆነ በተከራይ ላይ ጫና አይፈጥርም ያሉት ሚኒስትሯ፤ ትክክለኛና ሚዛናዊ በሆነ መልኩ ወደ መሬት…
በኢትዮጵያ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የገቢ ምርትን 85 በመቶ በአገር ውስጥ ምርት ለመተካት ጥረት በመደረግ ላይ መሆኑ ይታወቀል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥትም በክልሉ ፈጣን ዕድገት በማስመዘገብ ህዝቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ትኩረት ከሰጣቸው የልማት ዘርፎች አንዱ የኢንዱስትሪው ዘርፍ ነው። ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ክልሉ ለአምራች ኢንዱስትሪ ልማት እምቅ አቅም ያለው መሆኑን ጠቅሰው፤ በክልሉ ያለውን የመልማት ፀጋ በመለየትና አሟጦ በመጠቀም ከዘርፉ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል። ለዚህም ክልሉ ያለውን አቅም በመጠቀም እና የግል ዘርፉን በስፋት በማሳተፍ የአምራች ኢንዱስትሪ ልማትን ለማሳደግ እና ለማስፋፋት ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይ የኢንዱስትሪ ተቋማትን በክላስተር በማቋቋም ሰፊ የስራ ዕድል መፍጠር የሚችሉ እና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ማጠናከርና ማስፋፋት የክልሉ ዋነኛ ትኩረት መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ ሀብት ያፈሩ አርሶና አርብቶ አደሮችን በኢንዱስትሪው ዘርፍ በማሳተፍ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማስቻልም ትኩረት የተሰጠው መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል። የክልሉ መንግሥት በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ የሚያበረታታ መሆኑን ጠቁመው ባለሀብቶች በክልሉ ኢንቨስት በማድረግ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ ማቅረባቸውን ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።