ar
Feedback
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/

Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/

الذهاب إلى القناة على Telegram

Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/

تُعد قناة Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ (@ethpress) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 24 811 مشتركاً، محتلاً المرتبة 9 779 في فئة الأخبار والوسائط والمرتبة 1 352 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 24 811 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 26 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -101، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -3، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: موثّقة (مؤكدة رسمياً من تيليجرام)
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 11.34‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 5.56‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 2 814 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 380 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 4.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 27 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الأخبار والوسائط.

24 811
المشتركون
-324 ساعات
-157 أيام
-10130 أيام
أرشيف المشاركات

photo content

የአፍሪካ ተወካዮች ስለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ... ++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - በይፋ የተጀመረው ታሪካዊው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በርካታ አህጉራዊና ዓለም አቀፋ እንግዶች የተገኙበት የአፍሪካ ተወካዮች ስለሀገራዊ ምክክሩ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመልዕክቶቻቸውም ሀገራዊ ምክክሩ "በኢትዮጵያውያን የተመራና የኢትዮጵያውያን የሆነ"፣ የአፍሪካ ኅብረትን "አጀንዳ 2063" ራዕይ የሚያሳካና የአፍሪካውያንን ችግር በአፍሪካውያን የመፍታት መርህን በተግባር ያሳየ መሆኑን ተናግረዋል። ✅ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንትና የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልክተኛ ቺፍ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ የኢትዮጵያን ታሪክ፣ የህዝቦቿን ብዝሃነትና ታታሪነት በመጥቀስ ይህ ህዝብ የሰነቀውን ብሩህ ተስፋ ለማሳካት ደግሞ አሁን የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር ስኬት ቁልፍ መሆኑን ተናግረዋል። ✅ የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ በሀገራዊ ምክክር መክፈቻ ሥነ ስርዓት ላይ ባስተላለፉት መልዕክት በዓለም ታሪክ ውስጥ በግጭት የተገነባ ወይም ያተረፈ ሀገር የለም። በፖለቲካ ባህል ውስጥ ልዩነቶች መኖራቸው ተፈጥሮአዊ ቢሆንም፤ ትልቁና መሰረታዊው ስህተት ግን እነዚህን ልዩነቶች በኃይል ለመፍታት መሞከር ነው። ከሁሉ በላይ ልዩነቶችን መፍታት የሚቻለው በሰላማዊ መንገድ፣ በመነጋገርና በተለያዩ ሰላማዊ መድረኮች መሆኑን ይገባል። ኢትዮጵያም ለዚህ የሚሆኑ በርካታ ባህላዊ የምክክር መንገዶች ያሏት ሀገር መሆኗን ጠቅሰዋል። ✅ የአፍሪካ ህብረት የፖለቲካ፣ የሰላም እና የደህንነት ጉዳዮች ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ በዚህ ታሪካዊ ስፍራ ተገኝተው የዚህ ታላቅ የታሪክ ምዕራፍ አካል መሆን ለአፍሪካ ህብረት ትልቅ ኩራት መሆኑን የገለጹ ሲሆን፣ የሂደቱንም ታላቅነት፣ ስፋትና ጥንካሬ በከፍተኛ ሁኔታ አድንቀዋል። የአፍሪካ ህብረት ይህንን ታሪካዊ ክስተት በሙሉ አቅሙ እንደሚደግፍ በማረጋገጥ፣ ይህ የጋራ ጉዞ ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን፣ ልማትንና አዎንታዊ ለውጥን ማምጣት እንደምትችል የሚያሳይ ህያው ምስክር መሆኑን አመላክተዋል። ኢትዮጵያ የገጠማትን ውስብስብ የፖለቲካ ችግር መፍታት የምትችለው የራሷን ጥንታዊ የዕርቅ እሴቶች በመጠቀምና ሁሉንም አሳታፊ ያደረገ ፖለቲካዊ መፍትሄ በማምጣት ብቻ መሆኑን ነው። ለዚህ ታሪካዊ ሽግግር ዋነኛው መሻጋሪያ ድልድይ መሆኑና ለአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ እንደሚሆን በመልዕክታቸው ገልጸዋል። #Ethiopia #AfricanUnion #IGAD #PeaceBuilding #Agenda2063 #AfricanSolutions

photo content
+1

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለኳታር መንግሥትና ሕዝብ የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹ ++++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቀድሞው የኳታር
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለኳታር መንግሥትና ሕዝብ የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹ ++++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቀድሞው የኳታር አሚር ሼክ ሐማድ ቢን ኸሊፋ አል ታኒ በማረፋቸው የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት ፤ በራሳቸው፣ በመንግሥትና በኢትዮጵያ ሕዝብ ስም ለኳታሩ አሚር ሼክ ታሚም ቢን ሐማድ አል ታኒ፣ ለሀገሪቱ መንግሥትና ለወንድም የኳታር ሕዝብ ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል። የሁለቱ ሀገራት ወዳጅነት ከመጀመሪያው ሒጅራ ጀምሮ የቆየ ታሪካዊ መሠረት እንዳለው ይገልጹ እንደነበር ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውሰው የሁለቱ ሀገራት ታሪካዊ ግንኙነት በአሁኑ አሚር ሼክ ታሚም ቢን ሐማድ አል ታኒ መሪነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። በሞት ለተለዩት መሪ ዕረፍትን፣ ለቤተሰቦቻቸውና ሕዝብ መጽናናትን ተመኝተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የደብረ ማርቆስ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያን ስራ አሰጀመሩ ++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ የደብረ ማርቆስና የአካባቢው ሕዝብ ለዓመታት በ
+7
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የደብረ ማርቆስ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያን ስራ አሰጀመሩ ++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ የደብረ ማርቆስና የአካባቢው ሕዝብ ለዓመታት በጉጉት ሲጠብቀው የነበረውና ለ30 ዓመታት ያህል ተቋርጦ የነበረው ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት የአውሮፕላን ማረፊያ፤ በዘመናዊ መልክ ተሻሽሎና ደረጃው ከፍ ብሎ ተገንብቶ ዛሬ መመረቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታወቁ። በ2,400 ሜትር ርዝመትና 30 ሜትር ስፋት ላይ የተገነባው እንደ Q400 እና B737 ያሉ ግዙፍ የሕዝብና የጭነት አውሮፕላኖችን ማሳረፍ የሚያስችል ከፍተኛ ዐቅምም ፈጥሯል። ይህ አውሮፕላን ማረፊያ ሥራ መጀመሩ የአካባቢውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማነቃቃት ለአካባቢው እና ለመላው ሀገራችን የኢኮኖሚ ዕድገት አዲስ ምዕራፍ ይከፍታል። ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር፤ የሕዝባችንን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመመለስና የጀመርናቸውን ሜጋ ፕሮጀክቶች በጥራትና በፍጥነት አጠናቆ ለምርቃት ለማብቃት ያለንን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየን እንቀጥላለን ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል። #NationalDialogue #ሀገራዊምክክር #ኤርፖርት #airport Ethiopian Airlines

በመደመር መንግሥት የኢኮኖሚ ስትራቴጂ የታገዘው የግብርናው ዘርፍ፣ ፈጣን ዕድገትን በማረጋገጥ የሀገራችንን ራስን የመቻል ርዕይ እውን እያደረገ ይገኛል። ‎ ‎የውጭ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት እ
በመደመር መንግሥት የኢኮኖሚ ስትራቴጂ የታገዘው የግብርናው ዘርፍ፣ ፈጣን ዕድገትን በማረጋገጥ የሀገራችንን ራስን የመቻል ርዕይ እውን እያደረገ ይገኛል። ‎ ‎የውጭ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት እና የሥራ ዕድልን በመፍጠር፣ ዘርፉ ለሌሎች ኢንዱስትሪዎችም የማይናወጥ መሠረት ሆኗል። ይኸው ወሳኝ እመርታ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር አማካኝነት በሀገር በቀል መፍትሔዎች የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወት መለወጥና የሀገርን ኢኮኖሚ ማሳደግ እንደሚቻል በተግባር እያሳየን ነው። ‎ ‎በጋራ እናልማ፣ እናምርት፣ እንበልጽግ! #EthiopiaDelivers #PMOEthiopia

በመደመር መንግሥት የኢኮኖሚ ስትራቴጂ የታገዘው የግብርናው ዘርፍ፣ ፈጣን ዕድገትን በማረጋገጥ የሀገራችንን ራስን የመቻል ርዕይ እውን እያደረገ ይገኛል። ‎ ‎የውጭ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት እና የሥራ ዕድልን በመፍጠር፣ ዘርፉ ለሌሎች ኢንዱስትሪዎችም የማይናወጥ መሠረት ሆኗል። ይኸው ወሳኝ እመርታ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር አማካኝነት በሀገር በቀል መፍትሔዎች የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወት መለወጥና የሀገርን ኢኮኖሚ ማሳደግ እንደሚቻል በተግባር እያሳየን ነው። ‎ ‎በጋራ እናልማ፣ እናምርት፣ እንበልጽግ! #EthiopiaDelivers #PMOEthiopia

"ኢትዮጵያ እየመከረች ነው" – 5ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ++++++++++++++ "ኢትዮጵያ እየመከረች ነው" በሚል ሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓም የሚካሄድ አምስት ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አዘጋጅቷል። በዚህ ታሪካዊ ስፖርታዊ መርሐግብር ላይ ከ20 ሺህ በላይ ዜጎች ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል። በሩጫው ላይ ለመሳተፍ ፍላጎት ያላችሁ ዜጎች ሁሉ እንድትሳተፉ ኮሚሽኑ ጥሪውን አቅርቧል። #ሀገራዊ_ምክክር #ኢትዮጵያ_እየመከረች_ነው #የጎዳና_ላይ_ሩጫ #ሐምሌ_5 #ሀገራዊ_ምክክር_ኮሚሽን #የምክክር_ሩጫ #EthiopianNationalDialogue #Ethiopia

photo content
+3

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና የኮፕ 32 ፕሬዝዳንት ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከኮፕ 30 ፕሬዚዳንት ጋር ያደረጉት ውይይት‼️ #COP32 #COP32Ethiopia #PMOEthiopia #gazette_plus #Ethiopiadelivers

ኢትዮጵያ 33 ሚሊየን ቶን ስንዴ በዓመት እያመረተች ትገኛለች +++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - "በአፍሪካ ትልቋ የስንዴ አምራች ሀገር ግብጽ ነበረች፤ በአመት 9.7 ሚሊዮን ቶን ታመርት ነበር።
ኢትዮጵያ 33 ሚሊየን ቶን ስንዴ በዓመት እያመረተች ትገኛለች +++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - "በአፍሪካ ትልቋ የስንዴ አምራች ሀገር ግብጽ ነበረች፤ በአመት 9.7 ሚሊዮን ቶን ታመርት ነበር። ኢትዮጵያ ከዚህ በጣም ያነሰ ነበር የምታመርተው። ዛሬ ላይ ኢትዮጵያ ከ33 ሚሊዮን ቶን በላይ ስንዴ ማምረት ችላለች። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ቀዳሚ የሆነውን የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያ ምርቃት ሥነ-ሥርዓት ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለፁት ዛሬ ላይ ኢትዮጵያ ከ33 ሚሊዮን ቶን በላይ ስንዴ ማምረት ችላለች። ይህም ቀዳሚ አምራች የነበረችውን ግብጽን በ3 እጥፍ መብለጥ ያስቻለን ትልቅ ድል ነው ብለዋል። በስንዴ ዕርዳታ ጥገኝነት ስትታወቅ የነበረችው ሀገር፣ ባለፉት አምስት የለውጥ ዓመታት የምግብ ሉዓላዊነቷን አረጋግጣ ወደ ስንዴ ላኪነት መሸጋገሯ የኢኮኖሚ "ሉዓላዊነት ማሳያ ነው። #Ethiopia #Wheat #AfricaNo1 #WheatProduction #AgriculturalTransformation #Rising

በአዲስ አበባ 543 ትምህርት ቤቶች የ6ኛ ክፍል ፈተና ሙሉ በሙሉ ማሳለፍ ችለዋል- የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ ⵏበከተማው የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ካ
በአዲስ አበባ 543 ትምህርት ቤቶች የ6ኛ ክፍል ፈተና ሙሉ በሙሉ ማሳለፍ ችለዋል- የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ ⵏበከተማው የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ካስፈተኑ 768 ትምህርት ቤቶች መካከል 543 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ማሳለፍ መቻላቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ማለፊያ ውጤት 50 በመቶ እንዲሆን ወስኗል። የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ፤ ፈተናውን ከወሰዱት ከ97 በመቶ በላይ የሚሆኑት ወደ ቀጣይ ክፍል ተዘዋውረዋል። 543 ትምህርት ቤቶችም የ6ኛ ክፍል ፈተና ሙሉ በሙሉ ማሳለፍ ችለዋል። የማለፊያ ነጥብ ለመደበኛ ተማሪዎች 50 በመቶ እንዲሁም 45 በመቶ ለአካል ጉዳተኞች መወሰኑን ተናግረዋል። በመንግስትና በግል ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በቀንና በማታ መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ከ85 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናውን መውሰዳቸውን ገልጸው፤ በዘንድሮው ፈተና ሁለት ተማሪዎች 98 አማካይ ውጤት ማስመዝገባቸውን ጠቁመዋል። 459 ተማሪዎች 95 እና ከዚያ በላይ አማካይ ማስመዝገባቸውን ጠቅሰው፤አምስት ሺህ 559 የሚሆኑት ከ90 በላይ አማካይ ያስመዘገቡ ናቸው ብለዋል። አጠቃላይ ውጤቱ ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በሁለት ነጥብ አራት በመቶ እድገት ማሳየቱንም ገልጸው፣ ከዛሬ ጀምሮ ተማሪዎች ውጤታቸውን በኦላይን መመልከት የሚችሉ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል። በልጅዓለም ፍቅሬ +++++++++++++++++ #Gazetteplus #ጋዜጣፕላስ #AddisAbaba #AddisAbabaEducation #Grade6Exam

ከወጪ ንግድ ከ10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኘ +++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ│በ2018 በጀት ዓመት ከወጪ ንግድ ከ10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የንግድና ቀጠ
ከወጪ ንግድ ከ10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኘ +++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ│በ2018 በጀት ዓመት ከወጪ ንግድ ከ10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ እያካሄደ ይገኛል። በግምገማ መድረኩላይ የተገኙት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በሀገሪቱ የውጭ ንግድ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ ስኬት ተመዝግቧል። በበጀት ዓመቱ ከወጪ ንግድ 10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት በተሰራው ስራ ዕቅዱን መቶ በመቶ ማሳካት ተችሏል። ይህ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ዋና መሥሪያ ቤትና በተጠሪ ተቋማት አማካኝነት በተከናወኑ የተቀናጁ የሪፎርም ሥራዎች፣ የወጪ ምርቶች ጥራትን በማረጋገጥና በተዘረጉ ዘመናዊ አሠራሮች መሆኑን ተናግረዋል። በበጀት ዓመቱ 3 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዜጎች የንግድ ፈቃድ፣ ምዝገባና ዕድሳት አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ፣ ከ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑት አገልግሎት መስጠት መቻሉን ገልጸዋል። በታደሠ ብናልፈው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት #ጋዜጣ_ፕላስ #የወጪ #ገቢ #ንግድ #ንግድናቀጠናዊትስስር #ኢትዮጵያ

የዲጅታል ዘመኑ አናሎግ ፎቶግራፈር https://youtu.be/MJjd0zAhEnY

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ‎በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ የጎበኙት የኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓ በፎቶ‼️ #EthiopiaDelivers #InvestInEthiopia
+7
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ‎በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ የጎበኙት የኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓ በፎቶ‼️ #EthiopiaDelivers #InvestInEthiopia

ኢትዮጵያ የኃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች ++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ | ኢትዮጵያ እኤአ በ2035 መቶ በመቶ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን
+7
ኢትዮጵያ የኃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች ++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ | ኢትዮጵያ እኤአ በ2035 መቶ በመቶ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች። በውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ዳቢ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ ሀገሪቱ በ2035 መቶ በመቶ የኃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች። የኤሌክትሪክ ኃይልን ተደራሽነትን ለማሳካት ሁለት ዋና ዋና ስትራቴጂዎች ይተገበራሉ ያሉት መሪ ሥራ አስፈፃሚው፤ አንደኛው ከዋናው የኃይል ማሰራጫ መስመር ኤሌክትሪክን ማዳረስ ሲሆን፣ ሁለተኛው ከዋናው መስመር ርቀው የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን የሶላር (የፀሐይ) ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ተጠቃሚ ማድረግ ነው ብለዋል። የሶላር ኃይል ተጠቃሚ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች፣ በየአካባቢያቸው የመሰረተ ልማት ዕድገት እየተስፋፋ ሲመጣ ዘላቂና አስተማማኝ ወደ ሆነው ዋናው መስመር የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንደሚሸጋገሩም ተናግረዋል። በሚቀጥሉት 10 ዓመታት የኃይ አቅርቦት ተደራሽነት ለማረጋገጥ 18 ቢሊዮን ዶላር ፋይናንስ እንደሚያስፈልግ የገለጹት አቶ መስፍን፤ አስፈላጊውን በጀት ከመንግሥት፣ ከግሉ ዘርፍና ከአለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት የማሰባሰብ ሥራውን ለማከናወን አቅጣጫ መቀመጡን ጠቁመዋል። ባለፉት ዓመታት የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማስፋፋት በተከናወኑ ተግባራት የሀገሪቱን አጠቃላይ የኤሌክትሪክ ሽፋን 65 በመቶ ማድረስ መቻሉንም መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ዳቢ ገልጸዋል። በክብረአብ በላቸው #ጋዜጣ_ፕላስ #ኢትዮጵያ #የኤሌክትሪክ_ሽፋን #መሰረተ_ልማት #ታዳሽ_ኃይል

ኢትዮጵያ የኃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች ++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ | ኢትዮጵያ እኤአ በ2035 መቶ በመቶ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን
ኢትዮጵያ የኃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች ++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ | ኢትዮጵያ እኤአ በ2035 መቶ በመቶ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች። በውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ዳቢ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ ሀገሪቱ በ2035 መቶ በመቶ የኃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች። የኤሌክትሪክ ኃይልን ተደራሽነትን ለማሳካት ሁለት ዋና ዋና ስትራቴጂዎች ይተገበራሉ ያሉት መሪ ሥራ አስፈፃሚው፤ አንደኛው ከዋናው የኃይል ማሰራጫ መስመር ኤሌክትሪክን ማዳረስ ሲሆን፣ ሁለተኛው ከዋናው መስመር ርቀው የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን የሶላር (የፀሐይ) ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ተጠቃሚ ማድረግ ነው ብለዋል። የሶላር ኃይል ተጠቃሚ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች፣ በየአካባቢያቸው የመሰረተ ልማት ዕድገት እየተስፋፋ ሲመጣ ዘላቂና አስተማማኝ ወደ ሆነው ዋናው መስመር የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንደሚሸጋገሩም ተናግረዋል። በሚቀጥሉት 10 ዓመታት የኃይ አቅርቦት ተደራሽነት ለማረጋገጥ 18 ቢሊዮን ዶላር ፋይናንስ እንደሚያስፈልግ የገለጹት አቶ መስፍን፤ አስፈላጊውን በጀት ከመንግሥት፣ ከግሉ ዘርፍና ከአለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት የማሰባሰብ ሥራውን ለማከናወን አቅጣጫ መቀመጡን ጠቁመዋል። ባለፉት ዓመታት የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማስፋፋት በተከናወኑ ተግባራት የሀገሪቱን አጠቃላይ የኤሌክትሪክ ሽፋን 65 በመቶ ማድረስ መቻሉንም መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ዳቢ ገልጸዋል። በክብረአብ በላቸው #ጋዜጣ_ፕላስ #ኢትዮጵያ #የኤሌክትሪክ_ሽፋን #መሰረተ_ልማት #ታዳሽ_ኃይል

"ኩሪፍቱ የግሉ ዘርፍ ማበርከት የሚችለውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ በግልጽ የሚያሳይ ነው" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ++++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ የመደመር መንግሥት የገነ
+4
"ኩሪፍቱ የግሉ ዘርፍ ማበርከት የሚችለውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ በግልጽ የሚያሳይ ነው" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ++++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ የመደመር መንግሥት የገነባቸውን መሠረተ-ልማቶች ተከትሎ የግሉ ዘርፍ ማበርከት የሚችለውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ በግልጽ የሚያሳይ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ። ‎በአርባ ምንጭ ከተማ በ52,000 ካሬ ሜትር ስፋት ላይ ያረፈውን የኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓ ዛሬ ጎብኝተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት አርባ ምንጭ፤ የልማት ምንጭነቷ እየጎመራ ቀጥሏል! ብለዋል። ‎ ‎ይህ ታላቅ ፕሮጀክት 53 ቅንጡ ቪላዎችን ያካተተ ሲሆን፣ ከ300 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ መሰል ኢንቨስትመንቶች የመደመር መንግሥት የገነባቸውን መሠረተ-ልማቶች ተከትሎ የግሉ ዘርፍ ማበርከት የሚችለውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ በግልጽ የሚያሳይ ነው ብለዋል። ‎ ‎የሀገራችንን የቱሪዝም አቅም ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ መሰል ታላላቅ ፕሮጀክቶች ላይ፣ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሀብቶች በስፋት እንዲሰማሩና መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል። #EthiopiaDelivers #InvestInEthiopia