Mereb Media መረብ ሚዲያ
Welcome to our Channel, Mereb Media - መረብ ሚዲያ We provide daily reliable and trusted information. መረጃ ለማድረስ፦ @MerebMereb
إظهار المزيد📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Mereb Media መረብ ሚዲያ
تُعد قناة Mereb Media መረብ ሚዲያ (@merebmedia24) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 20 158 مشتركاً، محتلاً المرتبة 11 370 في فئة الأخبار والوسائط والمرتبة 1 672 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 20 158 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 12 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -589، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -25، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 19.37%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 14.98% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 905 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 3 020 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 23.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“Welcome to our Channel, Mereb Media - መረብ ሚዲያ We provide daily reliable and trusted information. መረጃ ለማድረስ፦ @MerebMereb”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 13 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الأخبار والوسائط.
جاري تحميل البيانات...
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 13 يوليو | +1 | |||
| 12 يوليو | 0 | |||
| 11 يوليو | 0 | |||
| 10 يوليو | 0 | |||
| 09 يوليو | 0 | |||
| 08 يوليو | 0 | |||
| 07 يوليو | 0 | |||
| 06 يوليو | 0 | |||
| 05 يوليو | 0 | |||
| 04 يوليو | 0 | |||
| 03 يوليو | 0 | |||
| 02 يوليو | 0 | |||
| 01 يوليو | 0 |
| 2 | لا يوجد نص... | 1 888 |
| 3 | የምስራች!!!
አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ በላይ ዘለቀ ዕዝ።
በላይ ዕዝ ፀረ አንድነት እጆችን በጣጥሶ ዳግም ላይፈታ የአንድነቱን ውል አስሯል።
የመዋቅር ድልድሉን በሚመለከት ሙሉ መግለጫው በዛሬው እለት በአፋብን በኩል ይሰጣል።
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24 | 1 919 |
| 4 | #85 ጦር አለቀ/42 ክላሽ ተያዘ!
#የክ/ጦሩ አዛዥ ተገደለ/ዋናው እጅ ሰጠ!
#ዋና ካምፑ ተመታ/ሰበር ድል!
https://youtu.be/XCFVwYeMSO8?si=swIXiND00Dmoub87 | 2 517 |
| 5 | لا يوجد نص... | 2 483 |
| 6 | የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ዕለታዊ የግንባር ውሎ፦
ሐምሌ 05/2018 ዓ.ም።
የተከበራችሁ የሚዲያ አካላት እና መላው የአማራ ህዝብ፤ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ስር የሚገኙ ጀግና ፋኖዎቻችን በተለያዩ ግንባሮች በአገዛዙ ወራሪ ኃይል ላይ የወሰዱትን እርምጃ እና ጠላት በንፁሃን ላይ እያደረሰ ያለውን ጥቃት በሚመለከት የዕለቱን መረጃ እንደሚከተለው አቀርባለሁ።
1. በአምባሰል ግንባር አንፀባራቂ ድል ተመዝግቧል!!
በመጀመሪያው ዜናችን የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ጥምር ኃይሎች በጠላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ አድርሰዋል።
ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ከ104ኛ ኮር 24ኛ ክፍለጦር እና ከ101ኛ ኮር 35ኛ ክፍለጦር በጋራ በመሆን ደቡብ ወሎ ዞን፣ አምባሰል ወረዳ ቀበሌ 015 ልዩ ስሙ ወፉጮና ቋሆ ( በርመጠበቂያ) ላይ ዛሬ ሐምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በተጠና የደፈጣ ጥቃት ከአገዛዙ ጦር በኩል ከ75 በላይ ሲደመሰስ፤ ከ30 በላይ ደግሞ ቁስለኛ ሆኗል።
ከጥቃቱ የተረፈው የጠላት ኃይል የተበታተነ ሲሆን፤ ሙትና ቁስለኛውን ለማውጣት ከመርሳ እና ጀነቶ አካባቢ ሆኖ እስከ ቀኑ 9፡30 ድረስ ወደ ህዝብ መኖሪያ ቤት በዘፈቀደ ከባድ መሳሪያ ሲተኩስ ውሏል። ጠላት በአራት የኦራል መኪኖች ሬሳ እና ቁስለኛ ጭኖ ወደ መርጦ እና ወልዲያ አጓጉዟል።
2. በአምሓራ ሳይንት ግንባር የተፈፀመ ስኬታማ የደፈጣ ጥቃትን ስንመለከት፦
በሁለተኛው ዜናችን፤ ጀግኖቹ የፋኖ ኃይሎቻችን በስርዓቱ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች ላይ የማያዳግም እርምጃ ወስደዋል።
ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ፣ 105ኛ ኮር 47ኛ ክፍለጦር አትሮንስ ሻለቃ፣ አምሓራ ሳይንት፣ ከደንሳ ወደ በለጩማ መስመር ልዩ ቦታቸው ወጀድ መገንጠያ እና ጎዴል ላይ ትናንት ሐምሌ 04 ቀን 2018 ዓ.ም በ7 መኪኖች ሲጓጓዝ በነበረው የኦህዴድ/ብልፅግና ወራሪ ኃይል ላይ ድንገተኛ የደፈጣ ጥቃት ተፈፅሟል።
በውጊያው የክፍለጦሩ ዘመቻ ኃላፊ ሻለቃ ወልደ ጊዮርጊስ እና ሻምበል አስራት የሚባሉ የአገዛዙ ወታደሮች በከባድ የቆሰሉ ሲሆን፤ አንድ ስሙን ለጊዜው ያላወቅነው መስመራዊ መኮንን ከአጃቢው ጋር ተደምስሷል። በፓትሮል እና በካሶኒ ተጭኖ የነበረ በርካታ የጠላት ኃይልም ሙትና ቁስለኛ ሆኗል።
3. በመካነሰላም እና አካባቢው በንፁሃን ላይ የደረሰ የከባድ መሳሪያ ጥቃትን ስንመለከት፦
በመጨረሻም፤ በጦር ሜዳ አቅም ያጣው የፋሺስቱ አብይ አህመድ ሰራዊት በንፁሃን አርሶ አደሮች እና ንብረታቸው ላይ እርምጃ መውሰዱን ቀጥሏል።
የጠላት ኃይል ከመካነሰላም ከተማ ሆኖ ወደ ገጠር የአርሶ አደሮች መንደር መድፍ እና ሞርተር ያለማቋረጥ ሲተኩስ ውሏል።
በዚህም በዛሬው ጥቃት በርካታ የአርሶ አደር ንብረት የወደመ ሲሆን፤ የቤት እንስሳት ላይም ጭምር ጉዳት ደርሷል፤ ለአብነት አንዲት እርጉዝ ፍየል በመድፍ ተመትታ ሽሏ ወጥቶ ወድቋል። ከዚህ ቀደም በመቅደላ ወረዳ አሶል ቀበሌም ተመሳሳይ የከባድ መሳሪያ ጥቃት መፈፀሙ ይታወሳል።
መልዕክት፦ የአፋብን ም/ወታደራዊ አዛዥ ዋርካው ምሬ ወዳጆ "ሰው ቢያጣ ንብረትና ቤት አያጣም" ብሎ እንዳስገነዘበው፤ እንዲሁም የአፋብን ሊቀመንበር አርበኛ ዘመነ ካሴ እንዳሳሰበው፤ ጠላት በአማራ ህዝብ ላይ ልዩነት ሳያደርግ ሁለንተናዊ የጥፋት ዘመቻ እያካሄደ ነው። በመሆኑም ዳር ቆሞ ከመመልከት ወጥተን ሁላችንም ህልውናችንን ለማስጠበቅ ልንረባረብ ይገባል። የህልውና ተጋድሎው ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ክብርና ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት!!
ድል ለአፋብን!!
ድል ለአማራ ህዝብ!!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወታደራዊ ቃል አቀባይ
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24 | 2 205 |
| 7 | አንድ የብልፅግና መከላከያ ሰራዊት አባል አንድ ጥቁር ስናይፐርን ከአንድ ጥቁር ክላሽንኮቭ መሣሪያ ጋር ደርቦ እንደያዘ ፋኖን ተቀላቀለ!
መነሻውን ላሊበላ ከተማ ከሚገኘው የአገዛዙ ካምፕ ያደረገ አንድ የብልፅግና መከላከያ ሰራዊት አባል፡ አንድ ጥቁር ስናይፐር ከአንድ ጥቁር ክላሽንኮቭ መሣሪያ ጋር ደርቦ በመያዝ በአፋብን ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር 16ኛ ነብሮ ተወርዋሪ ኮማንዶ ክፍለ ጦርን ተቀላቅሏል።
መረበኞች ነን መረጃ አጥማጆች!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24 | 2 326 |
| 8 | https://youtu.be/6idWA0-VEJ0?si=rVXpQXLvVcv8KQOz | 2 282 |
| 9 | በአምሓራ ሳይንት ግንባር ወጀድ መገንጠያና ጎዴል በተባሉ ስትራቴጅክ ቦታዎች ላይ ፋኖ በፈፀመው የሽምቅ ጥቃት በጠላት የክ/ጦርና የሻለቃ አመራሮችን ጨምሮ በርካታ ወታደሮችን ሙትና ቁስለኛ በማድረግ አኩሪ ድል ተቀዳጅቷል።
የጠላት ኃይል ከደንሳ ከተማ ወደ በለጩማ በ 7 ተሽከርካሪ ተጭኖ እየተጓጓዘ እንዳለ ነው ከፊት ለፊት ያለው ለኋለኛው፡ ከኋላ ያለው ለፊተኛው እንዳያግዝ ከሁለት ቦታዎች ላይ ተቆርጦ ከባድ የቦምብ ጥቃት የተፈፀመበት።
በዚህም፡ የጠላት ክ/ጦር ዘመቻ መምሪያ ኃላፊና የሻንበል ማዕረግተኛ የሆኑ የውጊያ መሃንዲሶችና ሌሎች አመራሮችን ጨምሮ በርካታ የሠራዊቱ አባላት ልክ እንደ ጨው ሟሙተው ቀርተዋል።
ሙሉ መረጃውን ተመልከቱ👉https://youtu.be/XCFVwYeMSO8?si=swIXiND00Dmoub87 | 2 505 |
| 10 | لا يوجد نص... | 2 417 |
| 11 | በሸዋ ጠቅላይ ግዛት እና በወሎ ቤተ-አማራ የተመዘገቡ ወታደራዊ ድሎች
1. የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ግንባሮች
ሀ. በመርሐቤቴ አውራጃ፦
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሥር የሚገኘው አፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር በናደው ክፍለ ጦር ጠላት ተደመሰሰ።
ኮላሽ ተራራማ ስፍራ እና አለም ከተማ ዙሪያ (በልዩ ስሙ ዘይታና አከያ መስክ) በተባለ ቦታ ላይ ከሌሊቱ 10:00 ጀምሮ በተወሰደ መብረቃዊ ጥቃት የጠላት ምሽግ ሙሉ በሙሉ ተሰብሯል። አንድ የጠላት ኃይል የጫነ 'ኦራል' ተሽከርካሪ በቦንብ ተመቶ ወድሟል። የኮላሹን ኃይል ለመታደግ ከፌጥራ እስከ አለም ከተማ የተንቀሳቀሰው ኃይል በደፈጣ ተመቷል።
በጠላት ላይ የደረሰ ኪሳራ፦
3 የኮማንዶ አመራሮች ተማርከዋል።
1 ብሬን፣ 7 ክላሽንኮቭ፣ 3 መውዜር፣ 2 ሬዲዮ መገናኛ፣ 2 ኤፍ-1 ቦንብ እና 360 ጥይቶችን ጨምሮ በርካታ ትጥቆች ተማርከዋል።
በሽንፈቱ የተበሳጨው የአገዛዙ ኃይል በዙ-23 እና ሞርተር በንፁሃን አርሶ አደሮች ላይ የበቀል ጥቃት እየሰነዘረ ይገኛል።
ለ. በደገም ወረዳ ግንባር፦ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሥር የሚገኘው አፄ አምደጽዮን ኮር በራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር - 2ኛ አሊ ሻለቃ
ልዩ ቦታው ሀሮ እና አቦ ለሊሳ (ግራሪያ/ፍቸ ሰላሌ) ላይ ከንጋቱ 12:00 እስከ ቀኑ 5:00 ድረስ በተወሰደ እርምጃ ህዝብን፣ ብሔርና ሃይማኖት ሳይለይ ሲዘርፍ በነበረው የሸኔ ቡድን ላይ የማያዳግም እርምጃ ተወስዷል።
በዚህም የጠላት ካምፕ ተሰብሮ በርካታ የቡድኑ አባላት ተደምስሰዋል። 7 የጦር መሣሪያዎች ሲማረኩ፣ ከተዘረፉት ውስጥ 9 የቀንድ ከብቶች እና 15 በግና ፍየሎች ተመልሰው ለአርሶ አደሩ ተሰጥተዋል።
ሐ. በመንዝ አውራጃ ግንባር፦ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሥር የሚገኘው አፄ አምደ ፅዮን ኮር በአፄ ምኒልክ ክፍለ ጦር ሞላሌ ከተማ (መንዝ ማማ ክላስተር) ላይ በሌሊት በተደረገ ሰርጎ የመግባት ኦፕሬሽን እና በአባት አርበኞች በተወሰደ አጸፋዊ እርምጃ የብልጽግና አገዛዝ ታጣቂዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።
በዚህም የወረዳው የሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ (አቶ ችላባለው) እና የሚሊሻ መቶ መሪው (ኃይሉ ከፈለውን) ጨምሮ ሌሎች አባላት ተደምስሰዋል። በርካታ የቆሰሉ የጠላት ኃይሎች በሞላሌ ሆስፒታል ይገኛሉ።
2. የወሎ ቤተ-አማራ ግንባር
ሀ. በላሊበላና አካባቢው ግንባር፦ የአፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሥር የሚገኘው 303ኛ አሳምነው ኮር (በ21ኛ ተከዜ ክፍለ ጦር እና 16ኛ ነብሮ ተወርዋሪ ኮማንዶ ክፍለ ጦር) አማካኝነት መነሻውን ኩልመስክና ላሊበላ አድርጎ ወደ ገነተማርያም በተንቀሳቀሰው ኃይል ላይ በተወሰደ እርምጃ በዙ-23 እና በ107 የተደገፈውን የጁላ ሰራዊት ስቦ በማስገባት እና በመቁረጥ ከፍተኛ ኪሳራ ማድረስ ተችሏል።
በዚህም ከ55 በላይ ጠላት ሲደመሰስ፣ ከ30 በላይ ቆስሏል። 42 ጥቁር ክላሽንኮቭ፣ 1 ሬዲዮ መገናኛ፣ 27 የደረትና የወገብ ትጥቆች እንዲሁም 36 ሻንጣዎች ተማርከዋል።
ልዩ መረጃ፦ አንድ የአገዛዙ ሰራዊት አባል 1 ጥቁር ስናይፐር እና 1 ጥቁር ክላሽ ይዞ 16ኛ ነብሮ ተወርዋሪ ኮማንዶ ክፍለ ጦርን በራሱ ፍቃድ ተቀላቅሏል። ይቀጥላል.....
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አበበ ሙላት
የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24 | 2 368 |
| 12 | በወሎ ቤተ አማራ አምባሰል ግንባር የተደረገ ተጋድሎ!
በአፋብን ምኒልክ ዕዝ ከ104ኛ ኮር 24 ክፍለጦር እና ከ101ኛ ኮር 35 ከወልዲያ ፣ ከመርሳ : ከሳንቃ እንዲሁም ከዕዜት ስርዐቱ በብዛት አግተልትሎ ወደ ደቡብ ወሎ ዞን አምባሰል ወረዳ 015 ቀበሌ ልዩ ቦታው ወፉጮና ቋሆ ወደ ተባለ ቦታ ዛሬ ሀምሌ 05/2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 2:30 አካባቢ ሲንቀሳቀስ የነበረው ይህ የስርዐቱ ወንበር ጠባቂ ጦር በተጠና እና ውጤታማ በሆነ ደፈጣ በ35ኛ ክፍለጦር እና በ24 ክፍለጦር በርመጠበቂያ እየተባለ በሚጠራ ቦታ ላይ በመደምሠስ ድል ተጎናፀፉ።
ዛሬ ሀምሌ 05/2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 2:30 ጀምሮ በተደረገ ተጋድሎ የስርዐቱን ጦር በተጠና ደፈጣ ጥቃት ከ75 በላይ መደምሰስ ሲቻል ከ30 በላይ በማቁሰል ድል መጎናፀፍ ሲቻል ፣ይህ ከተለያየ ቦታ በገፍ ተሰባስቦ የመጣ ሀይል ነፍስ አውጭኝ በማለት ወደ መጣበት እየተበታተነ ተመልሷል።
በዚህ የተበሳጨው የጥላት ኃይል ከመርሳ እና ከጀነቶ ጀኔራል መድፎችን ከጥዋቱ 4:00 ጀምሮ በዘፈቀደ ወደ ህዝባችን ያለ ማቋረጥ እሰከ ቀኑ 9:30 ድረስ ሙትና ቁስለኛውን ለማውጣት እየወረወረ ወይም እያስወነጨፈ ውሏል።
በመጨረሻም በአራት ኦራል ሙትና ቁስለኛውን ወደ መርጦና ወልዲያ እያጓጓዘ አመሸቶ ፣ በከባድ መሳሪያ ሽፉን እየሰጠ እያግተለተለ ያመጣውን ቅጥረኛ ሰራዊት ወደ ዕዜት ና መርጦ ጀግኖቹና ነበልባሎቹ 24ኛ እና 35ኛ ክፍለጦሮች መልሰውታል።
ምንጭ፦ በአፋብን ምኒልክ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24 | 2 191 |
| 13 | ➞ ወሎቤተ አማራ ከኩልመስክ እስከ ገነተማሪያም- ከላሊበላ ዙሪያ እስከ ገነተ ማርያም ስለተደረገው ተጋድሎ!
➞ በጎንደር ጠቅላይ ግዛት በወርጋጃ ግንባር፣ በኒሊ ግንባር፣ በገላ ማጠቢያና ከአቁሃ እስከ አልውሃ ግንባር ስለተደረገው ተጋድሎ!
➞በወሎ ቤተ አማራ ቀጠና አማራ ሣይንት ወረዳ በጠላት የክፍለጦር አመራሮች ጭምእ ያለቁበት የሽምቅ ጥቃት!
እነዚህንና ሌሎች የዛሬ ሃምሌ 05/2018 ዓ/ም እለታዊ የግንባር ተጋድሎዎችን ተከታተሉ👉https://youtu.be/XCFVwYeMSO8?si=swIXiND00Dmoub87 | 2 358 |
| 14 | لا يوجد نص... | 2 347 |
| 15 | ጀግና አይሞትም፤ ታሪክ ሁሌም ያዘክረዋል!
ቀን፦ ሐምሌ 05/2018 ዓ.ም
ክብር እና መፅናናት ለአርበኛ ፀጋው ታፈሰ እና ለቀኝአዝማች አቡ አሳመረው ቤተሰቦች፣ ጓዶችና ለመላው የአማራ ህዝብ!
ታሪክ ራሱን በጀግኖች ደምና አጥንት ይፅፋል። ትናንት በመርሐቤቴ አውራጃ፣ ላይ ቤት ወረዳ በኮላሽ ተራራማ ስፍራ በነበረው ታላቅ ፍልሚያ፤ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርዓያዕቆብ ኮር ናደው ክፍለ ጦር ባደረገው የላቀ ጀግንነት የአገዛዙ ትልቅ የቁም ምሽግ ሲሰባበር፣ የጠላት ዋይታ በየጉድጓዱ አንባርቋል። የአገዛዙን ቅልብ ኮማንዶ በያለበት ክፉኛ በመምታት፣ ለወሬ ነጋሪ እንኳ ሳይተርፉ በርካታ የጠላት ኃይሎችን በመደምሰስ የክብር ሰማዕትነት የተቀበሉት አርበኛ ፀጋው ታፈሰ እና ቀኝአዝማች አቡ አሳመረው ለሕዝባቸው ያላቸውን ፍቅር እና የገቡለትን ቃል በአንድያ ነፍሳቸው በተግባር አስመስክረዋል።
እነዚህ የቁርጥ ቀን ጀግኖች በፋኖ ማዕቀፍ ውስጥ በመሆን ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ለአማራ ሕዝብ ህልውና፣ ክብርና መብት ሲሉ በግንባር ቀደምትነት የተሰለፉ፣ ያዋጉ፣ የተዋጉና ሕዝብን በማደራጀት ረገድ የተዋጣላቸው የትግሉ አብሪ ኮከቦች ነበሩ። ዛሬም እንደ ትናንቱ በኮላሽ ጠንካራ የቁም ምሽግ ላይ ታሪክ ዘላለም ሲዘክረው የሚኖር የጀግንነት ሥራ ሠርተው አልፈዋል።
• አርበኛ ፀጋው ታፈሰ፦ መርሐቤቴ ሰራዊት በማደራጀት እስከ ምስራቅ አማራ ድረስ በግንባር ቀደምትነት የተሰለፈ፣ የታገለና ያታገለ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው።
• ቀኝአዝማች አቡ አሳመረው፦ የመጀመሪያውን የአጣዬና የደራን የጠላት ከበባ ከሰበሩ አብሪ የትግል መሪዎች አንዱ ሲሆን፤ ይመራው የነበረውንም ሰራዊት ለአማራ ሕዝብ ህልውና ሲባል "ምርጫችን ወይ ሞት ወይ ማሸነፍ!" በሚል መርህ ያታገለ ጀግና ነበር።
እነዚህ የሸንቁጥ ልጆች፣ አባቶቻቸው ከፋሺስት ጣሊያን ጦር ጋር ታሪክ በሠሩበት በታሪካዊቷ ላይ ቤት ወረዳ ኮላሽ ሰንሰለታማ ተራራ ላይ የብልፅግናን ሰራዊት ለወሬ ነጋሪ ሳይተርፍ ካረገፉ በኋላ፣ ውድ ሕይወታቸውን በጀግንነት ለአማራ ሕዝብ ህልውና ሲሉ ሰውተዋል።
በዕለቱ የነበረው ተጋድሎ ወደር የሌለው ነበረ፤ ጀግኖቹ ሙሉ አንድ ሻለቃ የጠላት አየር ወለድን ያንበረከኩ፣ በጀግንነት መሃል ገብተው የቦምብ ናዳ በማውረድ ታሪክ የሠሩ ብርቅዬዎች ነበሩ። ምንም እንኳ እነዚህ የቁርጥ ቀን ልጆች ሙሉ ድሉ ከመጠናቀቁ በፊት ቢሰዉም፣ ያፈሯቸው ሺህ ጀግኖች ግን ዓላማቸውን አንግበው ተልዕኮውን ፈጽመዋል። የጀግኖቹ ደም በከንቱ አልቀረም፤ የጀመሩት እና የመሩት ውጊያ በተተኪዎቹ የናደው ክፍለ ጦር አናብስት በተቀጣጠለ ወኔና ልዩ የመዋጋት ጥበብ ቀጥሎ፣ በጠላት ላይ ሙሉ በሙሉ በደረሰ የድምሰሳ ፍጻሜ ተጠናቋል። የጀግኖቹም ደም በድል ተክሷል። በዕለቱም ማትያስ ማድቦ ሲመራው የነበረ ጦር በጀግኖቹ ምት በኮላሽ ተራራ ተቀብሮ የብልፅግና ሹማምንቶችን ሀዘን ያስቀመጠ ክስተት ሆኖ አልፏል።
"ጀግና ቢወድቅም የጀመረው ዓላማና የለኮሰው የነጻነት እሳት መቼም ቢሆን አይጠፋም።"
• ለተከበሩ ቤተሰቦቻቸው፦ በእንዲህ ዓይነት የቁርጥ ቀን የህልውና ዋስትና የሆኑ ጀግኖችን ለአማራ ሕዝብ ያበረከታችሁ የጀግና ወላጆችና ቤተሰቦች፤ ሐዘናችሁ የሁላችንም ሐዘን ቢሆንም ማኅፀናችሁ በኩራትና በክብር ሊመሰገን ይገባዋል። ፈጣሪ ጽናቱንና መጽናናቱን ይስጣችሁ።
• ለትግል ጓዶቻቸው፦ የአብሮነት፣ የደምና የዓላማ ጓዶቻቸው የሆናችሁ የነጻነት ታጋዮች፤ የጀግኖቹ መውደቅ የትግል ወኔያችሁን የሚያጠነክር፣ የተረከባችሁትን አደራ በድል ለማጠናቀቅ ጉልበት የሚሆን ነው። የአማራ ሕዝብ ህልውና የሚረጋገጠው በጀግኖች መስዋዕትነት እና ጠላትን በየቦታው በመቅበር በመሆኑ፣ ከትናንቱ ነገ ይበልጥ እንድትጠነክሩ ያደርጋችኋል። ጀግንነታችሁ ይቀጥል!
• ለመላው የአማራ ሕዝብ፦ ሕዝባችን እንደነዚህ ያሉ ውድ ልጆቹን ለነጻነቱና ለህልውናው ሲል መስዋዕት አድርጓል። ታሪክ የማይረሳቸው እነዚህ ሰማዕታት የቁጭትና የድል አርማዎቻችን ናቸው።
የጀግኖቹ የአርበኛ ፀጋው ታፈሰ እና የቀኝአዝማች አቡ አሳመረው ስምና ታሪክ በትውልድ ልብ ውስጥ ለዘላለም ሕያው ሆኖ ይኖራል!
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! ፈጣሪ ለቤተሰቦቻቸውና ለጓዶቻቸው መፅናናትን ይስጥ!
ምንጭ፦ በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24 | 2 326 |
| 16 | ከጋሸና ወደ ላሊበላ ሲንቀሳቀስ በነበረ የብልፅግና መከላከያ ሠራዊት ላይ ከባድ የቆረጣ እርምጃ ተወሰደ!
በአፋብን ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር አካል የሆኑት 19ኛ( እሸት) ክፍለ ጦር እና 16ኛ (ነብሮኮማንዶ) ክፍለ ጦር አርበኞች በጋራ በመቀናጀት ከጋሸና ወደ ላሊበላ ሲንቀሳቀስ የነበረ የብልፅግና መከላከያ ሠራዊት ድብኮ ልዩ ስሙ ቆጋ ወንዝ ላይ ከባድ እርምጃ ወስደው በመደምሰስ አኩሪ ድል ተቀዳጅተዋል።
ኦፕሬሽኑ፡ ዛሬ ሃምሌ 05/2018 ዓ/ም ከማለዳ ጀምሮ እስከ ረፋድ ድረስ የዘለቀ ሲሆን፡
በዚህም የአገዛዙ ጦር ክፉኛ ሲቀጠቀጥ የተዝረከረከው እና የተራረፈው ቀሪው ኃይል ሙትና ቁስለኛውን ይዞ ፈርጥጧል።
በተጋድሎው የፋኖን ክንድ መቋቋም አቅቶት ፈርጥጦ የነበረው የጠላት ኃይል እኩለ ቀን ገደማ ላይ ዳግም ኃይሉን አጠናክሮ ቢንቀሳቀስም፡ አርበኞቹ ከባድ የቆረጣ ጥቃት ፈፅመው ይሄንንም አሽመድምደው ብትንትኑን አውጥተውታል።
በተደረገው የደፈጣ ውጊያ 13 የአገዛዙ ወታደሮች እስከ ሲገደሉ፡ ከ17 በላይ ቁስለኛውን እያዝረከረከ ወደ መጣበት ተመልሷል ሲል የ303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል መረጃውን አድርሷል።
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24 | 2 421 |
| 17 | በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ክር 74ኛ ክ/ጦር የአባይ ሸለቆ ተርቦች ዲቦ ከተማ ሰፍሮ በነበረው የጠላት ኃይል ላይ መብረቃዊ እርምጃ ወስደው ድል ተቀዳጁ።
ትናንት ሃምሌ 04/2018 ዓ/ም አመሻሽ ጀምሮ
በዲቦ ንዑስ ወረዳ ዲቦ ከተማ ከሚገኝ ካምፕ ወጥቶ ወደ እነብሬ ቀበሌ ተንቀሳቅሶ በነበረው የጠላት ኃይል ላይ አርበኞቹ ድንገተኛ ጥቃት በመፈፀም ሙትና ቁስለኛ አድርገውታል።
በዚህም በርካታ የአገዛዙ ወታደሮች ሙትና ቁስለኛ ሲደረጉ፡ ቀሪው ኃይል የዕዝ ሰንሰለቱ ተበጣጥሶ ሕይወቱን ለማትረፍ በየአቅጣጫው ተበታትኟል።
በዚህ ተጋድሎ የተለያዩ ጠመንጃዎች እንዲሁም የብሬንና የክላሽ ተተኳሾች በአርበኞቹ ቡጥጥር ስር ውለዋል።
በአውደ ውጊያው ከተደመሰሱ ባንዳዎች መካከል ተመስገን ይርጋ እና ትልቅ አወቀ የተባሉ የአገዛዙ ሠራዊት መንገድ መሪ ተላላኪዎች ይገኙበትል።
በመጨረሻም፡ አሁንም አልረፈደም ጠብ አጫሪው አብይ አህመድ በሚጠራው የጦርነት ድግስ ውስጥ እየገባችሁ የምትማገዱ የብልፅግና አገልጋዮች ኑ የአማራ ፋኖ ይቅር ባይ ነውና በይቅርታ ወደ ቤተሰባችሁ ተቀላቀሉ በማለት ጥሪያችን እናስተላልፋለን።
ምንጭ፦ በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24 | 2 249 |
| 18 | በመካነሰላም ቀጠና ወደ አርሶ አደሮች መንደር ከባድ መሳሪያ በተደጋጋሚ ተተኩሶ በቤት እንሰሳት እና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል::
የፋሽስቱ አብይ አህመድ ሰራዊት ባገኘው አጋጣሚ በአማራ ህዝብ ላይ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ጉዳት ማድረሱን ስራዬ ብሎ ከያዘው እነሆ 3 ዓመታት አለፉ:: በየእለቱ በህዝባችን እና በንብረቱ ላይ ግፍ እየተፈፀመ ነው:: ዛሬም ከመካነሰላም ከተማ መድፍ ወደ ገጠር ሲተኮስ የዋለ ሲሆን የቤት እንስሳት ላይ ጭምር ጉዳት ደርሷል:: ጠላት መድፍ ብቻ ሳይሆን ሞርተርም ሲተኩስ ውሏል::
ጠላት ማረፊያው የማይታወቅ የመድፍ እና ሞርተር ቅንቡላ ወደ አርሶ አደሮች መንደር እየወረወረ ያለው መቼም ማረፊያው አማራ ወይም ንብረቱ ላይ ነው ብሎ ሲሆን ይህ የሚያመላክተው ደግሞ ታጥቀን ገጠምነውም አልገጠምነውም ጠላት ሊያጠፋን መነሳቱን ነው:: በምናገባኝነት እሳቤ ትግሉን ሳትቀላቀሉ ቀርታችሁ ዳር ለዳር በተመልካች ቦታ የተሰየማችሁ አማሮች ነግበኔ ልትሉ ይገባል:: በቅርቡ መቅደላ ወረዳ አሶል ቀበሌ ውስጥ የቀንድ እና የጋማ ከብት በመድፍ የመታው የፋሽስቱ አብይ አህመድ ሰራዊት ዛሬም መካነሰላም ውስጥ የግፍ ግፍ ፈጽሟል:: በዛሬው የከባድ መሳሪያ ጥቃት በርካታ የአርሶ አደር ንብረት የወደመ ሲሆን አንድት ክበድ ፍየል ጭምር በመድፍ ተመትታ በምታዩት መልኩ ሽሏም ወጥቶ መሬት ላይ ወድቋል::
የነፍሰ ጡር እናት ሆድን ቀደው ሽል ሲያወጡ የነበሩት አሁንም ክበድ ፍየልንም ታርጌት አድርገው ግፍ እየፈፀሙ ነው::
ምንጭ፦በአፋብን ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24 | 2 315 |
| 19 | በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ክር 74ኛ ክ/ጦር የአባይ ሸለቆ ተርቦች ዲቦ ከተማ ሰፍሮ በነበረው የጠላት ኃይል ላይ መብረቃዊ እርምጃ ወስደው ድል ተቀዳጁ።
ትናንት ሃምሌ 04/2018 ዓ/ም አመሻሽ ጀምሮ
በዲቦ ንዑስ ወረዳ ዲቦ ከተማ ከሚገኝ ካምፕ ወጥቶ ወደ እነብሬ ቀበሌ ተንቀሳቅሶ በነበረው የጠላት ኃይል ላይ አርበኞቹ ድንገተኛ ጥቃት በመፈፀም ሙትና ቁስለኛ አድርገውታል።
በዚህም በርካታ የአገዛዙ ወታደሮች ሙትና ቁስለኛ ሲደረጉ፡ ቀሪው ኃይል የዕዝ ሰንሰለቱ ተበጣጥሶ ሕይወቱን ለማትረፍ በየአቅጣጫው ተበታትኟል።
በዚህ ተጋድሎ የተለያዩ ጠመንጃዎች እንዲሁም የብሬንና የክላሽ ተተኳሾች በአርበኞቹ ቡጥጥር ስር ውለዋል።
በአውደ ውጊያው ከተደመሰሱ ባንዳዎች መካከል ተመስገን ይርጋ እና ትልቅ አወቀ የተባሉ የአገዛዙ ሠራዊት መንገድ መሪ ተላላኪዎች ይገኙበትል።
በመጨረሻም፡ አሁንም አልረፈደም ጠብ አጫሪው አብይ አህመድ በሚጠራው የጦርነት ድግስ ውስጥ እየገባችሁ የምትማገዱ የብልፅግና አገልጋዮች ኑ የአማራ ፋኖ ይቅር ባይ ነውና በይቅርታ ወደ ቤተሰባችሁ ተቀላቀሉ በማለት ጥሪያችን እናስተላልፋለን።
ምንጭ፦ በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!
የመረብ ሚዲያ ቴሌግራም ገፅን ይቀላቀሉ👉
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24
https://t.me/MerebMedia24 | 1 |
| 20 | #85 ጦር አለቀ/42 ክላሽ ተያዘ!
#የክ/ጦሩ አዛዥ ተገደለ/ዋናው እጅ ሰጠ!
#ዋና ካምፑ ተመታ/ሰበር ድል!
https://youtu.be/XCFVwYeMSO8?si=swIXiND00Dmoub87 | 2 289 |
