2 507
Obunachilar
+424 soatlar
+237 kunlar
+430 kunlar
Postlar arxiv
2 508
ሸይኻችን አንድ ኪታብ ስንጨርስ የኪታቡ መኽጡጥ ያመጡና ይህ በእጃቸው የፃፉት ነው። አይናችሁ ኳሉበት ይሉን ነበር። ደጋጎቹ አይደለም ዛታቸው አይደለም ሙኣለፋታቸው የኖሩባት ሀገር እንኳ ሷሊሕ ሀገር ትባላለች። በሐዲሱ እንደመጣው መቶ ሰው ገሎ ተውበት ሲጠይቅ ወደ ደጋጎች ሀገር ሂድ ተባለ።
ያ ረቢ ቢሂም...🤲
2 508
ዓቂዳ ማስቀራት ማለት ሌላውን መሳደብ ማዋረድ የሚመስለው ጅላጅል ኡስታዝ ሆኖ ተቸገርን። ዓቂዳ ማለት እራስም ማወቅ ነው። እራሱን ታወቀ ጌታውን ያውቃል። የዓቂዳ ኡስታዝ ሌሎችን የሚወድ የሚያከብር የሚያተልቅ ለሁሉም ዝቅ የሚል የሚተናነስ በራሱ የሚጠመድ ካልሆነ ዓቂዳ ስላልገባው ከሱ አንቀራም። ዓቂዳ ዒልም ነው። ዒልም ደግሞ ከንግግር ዝምታን ከፍ ከፍ ከማለት ዝቅ ማለትን ከጥላቻ ፍቅርን የሚያስተምር ነው።
